Thursday, April 18, 2013

ነጻነትን ከነጻ አውጭዎች የምንጠብቅበት ጊዜ ላይ አይደለንም!


ነጻነት እኛ ሰዎች በልደት ወደዚህ አለም ስንመጣ አብሮን የሚመጣ የተፈጥሮ ፀጋ ነዉ። ነጻነት ከሌሎች የምንጠብቀዉ ወይም ማንንም ስጠን ብለን የማንጠይቀዉ ፈጣሪ ለእያንዳንዳችን ያደለንን፤ በዚህ አለም ቆይታችን ለደቂቃም ቢሆን እንዲለየን መፍቀድ የሌለብን ኃብት ነዉ። ነጻነታችን እጃችን ላይ ሲኖር በግለሰብ ደረጃ የምንደሰትበት፤ እንዳንቀማ በጋራ የምንጠብቀዉና እንደወያኔ አይነቱ ፀረ ህዝብ ኃይል ሲቀማን ደግሞ በጋራ ታግለን ማስመለስ የሚገባን የግልና የጋራ ኃብት ነዉ። ዛሬ ከ21 የወያኔ አመታት በኋላ እኛ ኢትዮጵያዉያን በድህነትና በረሀብ የምንጠቃዉ፤ በዘረኝነት አለንጋ የምንገረፈዉ፤ የምንሰደደዉ፤ የምንታሰረዉና የምንገደለዉ ይህንን ፈጣሪ ያደለንን ነጻነት የሚባል ኃብት ወያኔ አንድ፤ ሁለትና ሦስት እያለ ሲቀማን አፋችንን ዘግተንና እጃችንን አጥፈን ስለተመለከትን ነዉ። መፈናቀላችን፤ ስደታችን፤ ዉርደታችንና በገዛ አገራችን ሁለተኛ ዜጋ ሆኖ መኖራችን እንዲያበቃ ለማድረግ ያለን ብቸኛ አማራጭ ሌሎች መጥተዉ ነጻ ያወጡናል ከሚለዉ አመለካከት ተላቅቀን ነጻነታችንን ለማስመለስ ህዝባዊ ትግሉን መቀላቀል ብቻ ነዉ።
 
ነጻነታችንን የቀሙን የወያኔ ዘረኞች ነጻነታችንን እንደቀሙን ለረጂም አመታት ለመግዛት እንዲመቻቸዉ በዘር፤ በቋንቋ፤ በክልልና በሐይማኖት ከፋፍለዉን ከሃያ አንድ በፊት በኢትዮጵያ ሀዝብ ላይ ጀመሩትን እስራት፤ ስደት፤ ግድያና ዝርፍያ አሁንም እንደቀጠሉ ነዉ። የወያኔ ዘረኞች ነጻነታችንን ቀምተዉ እየገዙን ቢሆንምገዛናቸዉ ብለዉ እጃቸዉን አጣጥፈዉ አልተቀመጡም። ዜጎች ነጻነታቸዉንና መብታቸዉን እንዳይጠይቁ አፋቸዉን ያዘጋሉ፤ አንዱ ለሌላዉ አንዳይቆም አገር፤ ባንዲራና ኢትዮጵያዊነት የሚባሉ ትላልቁቹን የጋራ እሴቶቻችንን በየቀኑ ያፈርሳሉ። ይህ የሚያሳየን ዜጎች ትልቅተስፋይዘዉ፤ ቤተሰብ መስርተዉ ለራሳቸዉና ለአገራቸዉ የሚኖሩበት ግዜ እየጠፋ ተስፋ መቁረጥ፤ ስደትና የመከራ ኑሮ ዘመን እየከበበን መምጣቱን ነዉ። ይህ ከሆነ የነገዋንየነጻነት፣ የፍትህ፣ የዴሞክራሲባለጸጋ ኢትዮጵያንለማየትእያንዳንዱዜጋበቻለው አቅሙሁሉጠንክሮበመታገል እና ከራሱባለፈሌላውዜጋ የነጻነት ትግሉንጎራእንዲቀላቀል ብሎም የዚህትግልባለቤት እንዲሆን እንጠይቃለን፡፡የሀገራችን ህዝብ የነጻነት ችቦ አቀጣጣይ የትግሉአካልበመሆንመስራት እንጅ፣ ከቶ ሌላ አካል፣ ሌላ ሃይል መጦ ነጻ ያወጣኛል በሚል በባርነት እየተገዛ መጠበቅ የለበትም። ነጻነትናዴሞክራሲ በችሮታ አሊያም ከሰማይ እንደሚወርድ መና የሚጠበቅ ስጦታ አይደለም። ነጻነት የራስን መሰዋእትነት ይጠይቃል። አለበለዚያላምአለኝበሰማይወተትዋንምአላይእንዳይሆን ያስፈልጋል።
 
የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔ የዘር በትር አለንጋ የሚደርስበት ግርፋት፣ ስቃይ፣ ርሃብ፣ ስደት፣ እንግልት በራሱ በህዝቡ ላይ ነው። ስለዚህ ህዝቡ ራሱ ለራሱ ነጻነት፣ በእምቢ አልገዛም ባይነት የሚነሳበት ጊዜው አሁን ነው። ነጻነትን ከነጻ አውጭዎች በመጠበቅ እስከመቼ የወያኔ የጥይት ሰለባዎች እንሆናለን?
ወገንሁሉለራሱ ነጻነት፣ ህልውና ሲል የለውጡ እንቅስቃሴ ታጋይ የመሆን ኢትዮጵያዊግዴታውንእንዲፈጽምጥሪ እናደርጋለን፡፡ለአገሩ፣ ለማንነነቱ መሰዋእትነት ለመሆንእንደሚኮራሁሉአገሩም በሱ ትኮራለች ፡፡
 
በርግጥ ነው በህወሃት/ኢህአዴግ የአሰቃቂ ዘመናት ስለአገራችንየፖለቲካጉዳይማሰብና መናገር ወንጀልና ሽብርተኛ አስደርጎበጠራራፀሐይ የሚታሰሩበትናበግፍየሚገደሉበትጊዜነው።ይህንን አድርገሃል ተብሎ ሳይሆን ይህንን ሳታስብ አትቀርም ተብሎ ያለምንም ህጋዊና በቂ ምክንያት ወጣቶች፣ አረጋውያንያለጊዜያቸው፣ያለዕድሜያቸውበከንቱአልቀዋል።በቅርቡም ደግሞ በአማራው ተናጋሪ የተጀመረው ዘርን የማጥፋት ዘመቻ አንዱ ነው። ስለዚህ እስከ መቼ ነው ለራሳችን ነጻነት ሌላ አካል ነጻ እስኪያወጣን የምንጠብቀው? ከዚህ በላይ ምን ስቃይ አለ? ሀገር የጠፋች እለት ምን ሊውጠን ይችላል።
 
እማማ ኢትዮጵያ ለልጆቿ ህልውናዋን ከመፍረስ አደጋ እንዲጠብቋት፣ ከወያኔ የዘርና ዘረኝነት አደጋ እንዲታደጓት ስትማጸን፤ ልጆቿ ደግሞ አንዳች ሃይል መጥቶ ነጻነታቸውን ያጎናጽፋቸው ዘንድ የኢትዮጵያ አምላክ እያሉ ሲጠባበቁ እስከ መቼ? ስለዚህ ወጣት ጎልማሳ አዛውንት ሽማግሌ ዘር ጾታ ሳይለይ የዛሬ የነጻነትህ ትግል ጅማሮ እጅህ ላይ ነው። ሀገራችንየዛሬውንየወያኔን ጨለማሸኝታ የነገውንየነጻነት ብርሃንእየጠበቀችብቻሳይሆንእየናፈቀችአለች።ያንንድቅድቅጨለማሰንጥቆየሚወጣ የወጣት ጀግኖች ልጆቿንብርኃንትናፍቃለች።እናም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የብርሃኑመታያችቦ ሆኖ ታሪክ ይሰራ ዘንድ ለነጻነቱ የሚታገልበትና ትግሉን የሚቀላቀልበት ሰአት እየፈጠነ፣ እየቆጠረ፣ እየቀረበ ነውና ተነስ ባለህበት ያለህን አንሳና ወርውር፣ አቀብል። 
 
ቋንቋችን አንድ ነው ለነጻነትህ ታገል! በማንነትህ በብሄር ምክንያት በተወለድክበት ሀገር፣ ቀዪ አትሰደድ! በሀገርህ ምድር እንደ ሁለተኛ ዜጋ የመኖሪያ ፈቃድ ጠያቂ አትሁን! ወንድምህ፣ እህትህ፣ አባትህ እናትህ ባልሰሩት ወንጀል ወደ እስር ቤት ሲታጎሩ፣ ሲገደሉ ዝም ብለህ አትይ! በሀገርህ ስብእና ክብርህ ተዋርዶ አትመልከት! ተነስና መብራቱን አብራ! ጀግኖች መከታ ሊሆኑህ ከጎንህ ተሰልፈዋል።
 
በአሁኑ ወቅት አያሌ ኢትዮጵያዉያን ወያኔን ለመታገል መሳሪያ ካነሱ ከነጻነት ታጋዮች ጋር በየቀኑ እየተቀላቀሉ ቢሆንም፤ ሀገር ውስጥ ያላችሁ እለታዊ ኑሮን ለማሸነፍ ስትሉ በየፋብሪካው በመንግስት ሴክተሩ እና ሌሎች ተቋማት የምትገኙ ሁሉ በድጋሜ ግንቦት 7 እንደሁሌው ሁሉ የውስጥ አርበኛ ሆናችሁ የነጻነት ትግሉን መቀላቀል፣ ራሳችሁንና ሀገራችሁ ከወያኔ የዘረኛ ማዳፍ እጅ ነጻ ትወጣ ዘንድ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ ትግሉን ቀጥሉበት። ፍርሃታችሁን በጥሳችሁ በመደራጀትና መረጃ በማስተላለፍ ግዴታችሁን ተወጡ ለሀገራችው ቅርብ ሁኑ ለነጻነት ትግሉ የትግል ስልትና የተለየ የትግል ቦታ ሳትመርጡ ወያኔን  ያስወግዳል በምትሉት ስልትና ይመቸናል በሚሉት ቦታ ሁሉ እስከመጨረሻው ትታገሉ ዘንድ አደራችን ነው።
 
ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ዛሬም ቢሆን የህዝባችን ሰበአዊ መብትና ነጻነትንገፈውሕግንያፈረሱ ህገ አራዊት የሆኑትን ወያኔዎች ከሀገራችን ምድር ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ በማስወገድ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በእኩልነትና በነጻነት የሚኖርባትን ሀገር ለመመስረት የሚያደርገውን የትግል ጉዞ ይቀጥላል።
 
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

No comments: