Monday, April 8, 2013

አንዱዓለም አራጌ እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሰኞ በዳግም ቀጠሮ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር  አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ አቶ ናትናኤል መኮንን እና እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ፣ አቶ አንዱዓለም አያሌው፣አቶ ዮሐንስ ተረፈ፣ ሻምበል የሺዋስ ይሁንዓለም፣ አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ እና አቶ ምትኩ ዳምጤን ጨምሮ 24 ሰዎች በተከሰሱበት ክስ ከላይ ስማቸው የተጠቀሱ 8ቱ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት የወሰነውን የጥፋተኝነት ውሳኔ በመቃወም ለፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቢጠይቁም እስካሁን ውሳኔ ሳይሰጥ ለ
አራተኛ ጊዜ ተቀጥሮ ነበር፡፡

 ይሁን እንጂ ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2005ዓ.ም. 6 ኪሎ በሚገኘው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተቀጠረው መሰረት ከጠዋቱ 3ሰዓት ውሳኔ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

 ይህ በእንዲህ እንዳለ ከላይ በተጠቀሰው ክስ ተፈርዶበት አቃቂ ቃሊቲ በሚገኘው ቂሊንጦ ወህኒ ቤት በልዩ ጥበቃ ያለው አቶ ናትናኤል መኮንን የጥበቃ ኃላፊዎች ለአንድ ወር ከቤተሰብ እንዳይገናኝ የወሰኑበትን ቅጣት በመቃወም ለአንድ ሳምንት ምግብ ሳይበላ የርሃብ አድማ ማድረጉን ተከትሎ በእስር ቤት ያሉ ጓደኞቹና ከተከላካይ ጠበቆቹ አቶ አበበ ጉታ እና አቶ ደርበው ተመስገን ጋር ባደረጉት ውይይት አሁን ምግብ መብላት መጀመሩን ጠበቃው አቶ አበበ ጉታ በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡
አቶ አበበ ጉታ አያይዘውም “አቶ ናትናኤልን ካነጋገርን በኋላ ከጥበቃ ክፍል ኃላፊ ከሆኑት ሐጎስ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ብንነጋገርም በቀጥታ የሚመለከተው ኃላፊ ልናገኛቸው ባለመቻላችን የተጣለበት ቅጣት አግባብ እንዳልሆነ እና ቅጣቱም በአስቸኳይ እንዲነሳ በወቅቱ ላገኘናቸው መልዕክት አስተላልፈናል፤ እነሱም ለሚመለከተው የበላይ ኃላፊ መልዕክቱን እንደሚያደርሱ አረጋግጠውልናል” ሲሉ ገልፀውልናል፡:

የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አቶ አንዱዓለም አራጌ፣ አቶ ናትናኤል መኮንን እና እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ፣ አቶ አንዱዓለም አያሌው፣አቶ ዮሐንስ ተረፈ፣ ሻምበል የሺዋስ ይሁንዓለም፣ አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ እና አቶ ምትኩ ዳምጤን ጨምሮ 24 ሰዎች በተከሰሱበት ክስ ከላይ ስማቸው የተጠቀሱ 8ቱ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት የወሰነውን የጥፋተኝነት ውሳኔ በመቃወም ለፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቢጠይቁም እስካሁን ውሳኔ ሳይሰጥ ለ 4 ጊዜ ተቀጥሮ ነበር፡፡

ይሁን እንጂ ሰኞ መጋቢት 30 ቀን 2005ዓ.ም. 6 ኪሎ በሚገኘው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተቀጠረው መሰረት ከጠዋቱ 3ሰዓት ውሳኔ እንደሚሰጥ ይጠበቃል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከላይ በተጠቀሰው ክስ ተፈርዶበት አቃቂ ቃሊቲ በሚገኘው ቂሊንጦ ወህኒ ቤት በልዩ ጥበቃ ያለው አቶ ናትናኤል መኮንን የጥበቃ ኃላፊዎች ለአንድ ወር ከቤተሰብ እንዳይገናኝ የወሰኑበትን ቅጣት በመቃወም ለአንድ ሳምንት ምግብ ሳይበላ የርሃብ አድማ ማድረጉን ተከትሎ በእስር ቤት ያሉ ጓደኞቹና ከተከላካይ ጠበቆቹ አቶ አበበ ጉታ እና አቶ ደርበው ተመስገን ጋር ባደረጉት ውይይት አሁን ምግብ መብላት መጀመሩን ጠበቃው አቶ አበበ ጉታ በተለይ ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡

አቶ አበበ ጉታ አያይዘውም “አቶ ናትናኤልን ካነጋገርን በኋላ ከጥበቃ ክፍል ኃላፊ ከሆኑት ሐጎስ ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ብንነጋገርም በቀጥታ የሚመለከተው ኃላፊ ልናገኛቸው ባለመቻላችን የተጣለበት ቅጣት አግባብ እንዳልሆነ እና ቅጣቱም በአስቸኳይ እንዲነሳ በወቅቱ ላገኘናቸው መልዕክት አስተላልፈናል፤ እነሱም ለሚመለከተው የበላይ ኃላፊ መልዕክቱን እንደሚያደርሱ አረጋግጠውልናል” ሲሉ ገልፀውልናል፡፡

ምንጭ  ፍኖተ ነፃነት http://www.fnotenetsanet.com/wp-content/uploads/2013/04/Finote-Netsanet-News-PaperNo-71.pdf





 








         

No comments: