Tuesday, April 2, 2013

ሰበር ዜና ማንም የወያኔ ካድሬም ሆነ የመንግሥት ሠራተኛ ከፌደራል ጀምሮ እንዲገመገም፣ ልዩና ጥብቅ ትዕዛዝ ተላልፏል።

የፋሽስት ጣሊያን አሽከሮች የሹምባሽ አስረስ ተሰማ የልጅ ልጅን እና የሹምባሽ ዜናዊ አስረስ ልጅን የመለስ ዜናዊ አስረስን ፀረ-ኢትዮጵያዊነትና በተለይም የፀረ-አማራነት ራዕይ ጅምር ለማስፈፀም፤ ዘረኛ ትግሬዎች በተለይም ወጣቶቹ የተጀመረውን ኢትዮጵያን የማፈራረስ እና አማራውን የማጥፋት ዘመቻ እስከመጨረሻው እንዲያስፈጽሙ በመለስ ዜናዊ ስም የፋሽስቶች ፋውንዴሽን ሊመሠረት ነው። ሙዚዬምም ይሠራለታል በመማለት ወያኔ በትናንትናው ምሽት ዜና ቢያስታውቅም፤
በአሸባሪው ወያኔ መንደር ግን ከፍተኛ ሽብርና ጭንቀት ገብቷል፣ ማንም የወያኔ ካድሬም ሆነ የመንግሥት ሠራተኛ ከፌደራል ጀምሮ እስከ ቀበሌ ድረስ እንዲገመገም፣ ዕረፍት እንዳይኖረውና ሌላ ነገር እንዳያስብ ልዩና ጥብቅ ትዕዛዝ ተላልፏል።
የራሱን ሕዝብ በማሸበር በሚታወቀው በወያኔ መንደር ከፍተኛ ሽብርና ጭንቀት ገብቷል። የኢትዮጵያ ግብርና ምርት ዕድገት በተከታታይ ዓመታት ከ10 በመቶ በላይ አደገ እያለ በሀሰት ሲመፃደቅ የከረመው የወያኔ መንግሥት፤ የውሸቱ ክምር በአገሪቱ የሚያስፈልገውን የምርት መጠን ሊያስገኝ ባለመቻሉ፣ የግብርና ግብዓት ዋጋ በየዓመቱ እየናረ ባለበትና የአርሶ አደሩ የግብዓት አጠቃቀም እየቀነሰ በሄደበት ሁኔታ፣ የግብርና ባለሙያዎች ሙሉ ጊዜያቸውን የኢህአዴግን ፖለቲካ ብቻ እያስፈፀሙ በመገደዳቸውና አርሶ አደሩ ከግብርና ባለሙያዎች ምንም ዓይነት የሙያ ድጋፍና የምርት ዕድገት ማግኜት ስላልቻሉ ተስፋ በመቁረጣቸው፣ በተለይ ባለፉት ሁለት ዓመታት አርሶ አደሮች ተገድደው ከሚሠሩት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ በስተቀር፤ ከ1989 ዓ.ም. በኋላ በግብርናው ዘርፍ ተመዘገበ የሚባለው የምርት ዕድገት የሀሰት ቁጥር ክምር መሆኑን፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢህአዴግ ባለፈው 9ኛ ጉባኤው ላይ በይፋ አምኗል።
ከዚህም በተጨማሪ በተለይ በአማራው፣ በኦሮሞው ፣ በጉራጌው፣ በአኝዋኩ፣ በአፋሩና በኢሳው ወዘተ ሕዝብ መካከል በህወሃት አቀነባበሪነት የሚደርሰውን በደል እና ሕዝብን እርስ በእርስ ለማጋጨት የሚደርገውን ሴራ ሕዝቡ እየተረዳ በመሄዱ፣ በትግራይ ሕዝብ ስም ህወሃቶች በተለይም ጥቂት የአድዋ የባንዳ ርዝራዦች እየነገዱበት እና የትግራይን ሕዝብ ከቀሪ የኢትዮጵያ ወገኑ ጋር ለማቆራረጥ እየጣሩ መሆኑን በመረዳቱ የትግራይ ሕዝብም ፊቱን ወደ አረና ትግራይ እያዞረ በመሄዱ፣ እንዲሁም የሙስሊሙ እና የክርስቲያኑ አንድነት ህወሃት እንዳሰበው ወደ ግጭት ሊያመራለት ባለመቻሉ፣ እንዲያውም አንድነቱን እያጠናከረ በመሄዱ፣ ወዘተ ወያኔ ተጨንቋል፣ ተሸብሯል።
ይህ ሁሉ ሽብር የመጣው የኢትዮጵያ ሕዝብ በውስጡ ማንም ሊፍቀው የማይችለው የአንድነት፣ አብሮ የመኖርና የመቻቻል ባህሉ በወያኔ ሴራ ሊናጋ ባለመቻሉ፣ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ወደ ትጥቅ ትግሉ የሚቀላቀሉ ወጣቶች ቁጥር እየተበራከተ በመምጣቱ፣ የሕዝቡን አንድነትና ዝምታ ክፉኛ በመፍራት ነው።
ስለዚህ የተጀመረው የተቀናጀ ሁለገብ ትግል በተጠናከረ መልኩ መቀጠል አለበት። አንድነት ሃይል ነው። በተባበረ የሕዝቦች ትግል ወያኔ ይወገዳል። ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ።

No comments: