Wednesday, April 10, 2013

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ለካድሬዎች የግል መረጃቸውን እንዲሰጡ እየተገደዱ ነው


images.jpgDSvgsgwg
 
የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች፣የፖሊስ አባላትና ደንብ አስከባሪዎች ቤት ለቤት በመዘዋወር የአዲስ አበባ ነዋሪዎች የግል መረጃቸውን እንዲሰጡ በማስገደድ ላይ መሆናቸው ታወቀ፡፡

የቤት ለቤት ምዝገባው ወቅት የሚሰበሰበው መረጃ የነዋሪው የትምህትር ደረጃ፣ ሃይማኖትና የስራ አይነት የሚያጠቃልል ነው፡፡

የፍኖተ ነፃነት የመረጃ ምንጮች እንዳስታወቁት የመረጃ ስብሰባው በምርጫ የሚሳተፈውንና የማይሳተፈውን ለመለየትና መንግስት በቅርቡ የቤቱ ሊጀምረው ላሰበው የአንድ ለአምስት ፖለቲካዊ አደረጃጀት የሚረዳውን መረጃ ለማሰባሰብ ነው፡፡

በአንዳንድ የአዲስ አበባ አካባቢዎች የሚገኙ ነዋሪዎች “ያከራያችኋቸውን ግለሰቦች ስም፣የትምህርት ደረጃና ሃይማኖት ማረጋገጥ አለባችሁ” የሚል ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ለምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጨምረው እንደገለፁት ሙስሊም ነዋሪዎች በብዛት በሚገኙባቸው አካባቢዎች የተጠናከረ የመረጃ ስብሰባ እየተደረገነው፡፡

ፍኖተ ነፃነት

No comments: