Saturday, April 20, 2013

የወያኔ ባለስልጣናት የፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊቱን ለተጠንቀቅ የሚዘጋጅበትን ሁኔታ መከሩ::



ባለፈው የአከባቢ ምርጫ ህዝቡ ለወያኔ የሰጠውን የድምጽ ስውር መልእክት የስርኣቱን ተባዎች ያስደነገጣቸው ስለሆነ ዋና መወያያ ርእስ ከመሆኑም በተጨማሪ በካድሬው አከባቢ በስፋት እያነጋገረ ሲሆን አስደንጋጭ ድንገተኛ የራስ ውዝግብ የፈጠረባቸው የወያኔ ባለስልጣናት እና ጀነራሎችን ስለ ተከታዩ ትላንት ለሊቱን ሲወያዩ አድረዋል::

የዚህን ምርጫ ዉጤት ተከትለው ተቃዋሚ ሃይሎች ለፖለቲካ ፍጆታቸው ብሶት ያለበትን ህዝብ ሊጠቀሙ ይችላሉ:: በሚል ፍራቻ እንዲሁም መንግስታዊ መዋቅሮች ተዛንፈው ለወያኔ አደጋ እንደፈጠሩበት አድርገዋል:: የክልል ባለስልጣናት ስልጣናቸውን ያለኣግባብ በመጠቀም በማናለብኝነት የሚፈጽሙት ድርጊት ለኢሕኣዴግ ውድቀቱን እያፋጠነ ነው::አይን ያወጣ በልቼ ልሙት የሚል የቶሎ ቶሎ ኪራይ ሰብሳቢነት/ሙስና/ መንሰራፋቱ ኑሮ ዉድነት እንዲከሰት ምክንያት ሆኗአል በሚል ዙሪያ እና በሙስሊሙ ጉዳይ ዙሪያም እንዲሁ ተመክሯል:;

የአከባቢ ምርጫ የህዝቡ ብሶት ተንጸባርቆበታል ስለዚህ ተቃዋሚ ሃይሎች ይህ ነገር የልብ ልብ ስለሰጣቸው ህዝቡን ቀስቅሰው የራሳቸውን አብዮት ሊሰሩ ስለሚችሉ የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊቱ በተጠንቀቅ እንዲቆም አስፈላጊው ዝግጅት እንዲደረግ ለጄኔራሎቹ እና ለፖሊስ ባለስልጣናት የተነገራቸው ሲሆን ተቃዋሚዎች በሰላማዊ ተቃውሞ ስም የሚያደርጉት ማንኛውንም እንቅስቃሴ ወደ ግርግር ለመለወጥ እና ህዝቡን ዝም ለማሰኘት እንዲሁም ተቃዋሚዎችን ወደ ውህኒ ለማውረድ አስፈላጊው ሁሉ እንዲሰራ ለደህንነት ባለስልጣናትም መመሪያ ተሰቷል::

የክልል ባለስልጣናትን በተመለከተ በትእግት ድንገተኛ እርምጃ በመውሰድ ከስልጣን ማባረር እና ተጠያቂ የሚሆኑበትን ሰበብ ፈልጎ ህዝቡን ለማረጋጋት ወደ እስር ቤት መወርወር...እንዲሁን በምትካቸው ከፌዴራል መንግስት የተደራጀ እንቅስቃሴያቸውን የሚቆጣጠር ኮሚቴ ተዋቅሮ በየክልሉ እንዲመደብ ሲሉ የትግራይ እና የኣማራ ክልልን ይህ የኮሚቴ ምደባ አይመለከተውም በሚል ተስማምተዋል::

ሙስናን በተመለከተ ሁሉም የያዘውን ይዞ ለጊዜው ረገብ እንዲል እና በኢንቨስተሮች በሃገር ዉስጥ ነጋዴዎች ላይ እየተደረገ ያለው ማነቆን ረገብ ለማድረግ ሲወያዩ... በሃገር ውስጥ ያለው የወያኔ የንግድ ተቋማት ገንዘቦች ወድ ተለያዩ የአፍሪካ ባንኮች ውስጥ በዶላር እንዲቀመጡ ሃሳብ ቀርቦም ነበር:;ባሃሳቡ መሰረት ሁኔታዎች ታይተው አስቸኳይ ውሳኔ ይሰጥበታል ተብሎ ታልፏል::የሙስሊሙም ጉዳይ ከተለያዩ አካላት ጋር እየተነጋገርን እና እየተደራደርን ስለሆነ የፍርዱ ሁኔታ እንዲዘገይ አድርገናል መፍትሄው እየተጠና ነው ቢባልም ብዙ ትኩረት ተሰቶት እንዳልተወያዩበት የብኣዴን ነባር ታጋይ የሆኑ የውስጥ አዋቂ ምንጫችን
ያደረሱን መረጃ ይገልጣል::

ምንጭ ምንሊክ ሳልሳዊ

No comments: