Thursday, April 25, 2013

የተመሰገን ደሳለኝ ጉዳይ ለግንቦት 22 ተቀጠረ

በፌደራል አቃቢ ሕግ ተቃውሞ የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የተመስገን ደሣለኝ ምክሥሮች ቃል ሳይሰማ ቀረ፡፡
ተመስገን ደሣለኝ - የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ
ተመስገን ደሣለኝ – የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ
የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤቱ 6ኛ ወንጀል ችሎት ተከሣሽ ያቀረባቸውን ምሥክሮች ቃል ለመስማት ለግንቦት 22/2005 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡
ፍርድ ቤቱ ቀደ
ም ሲል ባዘዘው መሠረት ምሥክሮቹ የቀረቡ ቢሆንም አቃቢ ሕግ የታዘዙለት የድምፅና የምሥል ማስረጃዎች በእጁ የገቡት “ዛሬ ስለሆነ የምሥክሮቹ ቃል መሰማት የለበትም” ሲል አቤቱታ አቅርቧል፡፡

የተከሣሽ ጠበቆች የተባለውን የድምፅና የምሥል ማስረጃ ቀደም ብለው በታዘዘው መሠረት እንዳስገቡ ገልፀው “ዘግይቷል ቢባል እንኳ የምሥክሮችን ቃል ከመስማት ሊያግድ የሚችልበት ምክንያት የለም” ሲሉ ተከራክረዋል፡፡

ምሥክሮቹ ተቃውሞ ባለማቅረባቸው ምክንያት ፍርድ ቤቱ ቃላቸውን ለመስማት ቀጠሮውን መስጠቱ ታውቋል፡፡

No comments: