Friday, April 12, 2013

ወደ ቤንቺ ማጅ ዞን የተመለሱ የአማራ ተወላጆች ጫካ ውስጥ ወድቀናል ይላሉ

ሚያዚያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ወደ ቤንቺ ማጅ ዞን የተመለሱ የአማራ ተወላጆች ጫካ ውስጥ ወድቀናል ይላሉ
ሚያዚያ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ከቤንሻነጉል ጉሙዝ ከከማሺ ዞን ከያሶ ወረዳ ተፈናቅለው ፍኖተሰላም ከተማ ሰፍረው የነበሩት የአማራ ተወላጆች ወደ መጡበት ቦታ እንዲመለሱ ቢደረጉም፣ መጠለያ እና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ነገሮች ባልተሟሉበት ጫካ ውስጥ እንዲሰፍሩ መደረጋቸውን በቦታው ደርሰው ያነጋገርናቸው ተፈናቃዮች ገልጸዋል።
ተፈናቃዮቹ ህጻናቱም ሆኑ አዋቂዎች ምግብ ሳይመገቡ መዋላቸውን፣ ከአንድ ቀን በሁዋላ ዱቄት ተሰፍሮ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል። የቀይ መስቀል ሰራተኞች አብረዋቸው እንደመጡ የሚገልጹት ተፈናቃዮች ፣ የተቅማጥ በሽታ በመከሰቱም ሀኪሞቹ ከአቅማችን በላይ ነው እያሉ መሆኑን ገልጸዋል።
ተፋናቃዮች አንድም ባለስልጣን መጥቶ እንዳልጎበኛቸው ተናግረው የአማራ ክልል ባለስልጣናት መልሰው እንዲወስዷቸው ጥያቄ ማቅረባቸውንም ገልጸዋል። vvvv አሁንም የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው የተናገሩ ሲሆን፣ የወረዳው ባለስልጣናት በቦታው ተገኝተው ሊቀበሏቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ስጋታቸውን እንደጨመረው ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ክልል በመተከል ዞን በቡለን ወረዳ ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ የሚገኙ ከ2 ሺ በላይ አርሶአደሮች አንድም ባለስልጣን እንዳላናገራቸው ገልጸዋል። ተፈናቃዮቹ ከሶስት ቀናት በፊት ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ 7 አመራሮቻቸው ተይዘው ለ24 ሰአታት ከታሰሩ በሁዋላ በይቅርታ እንዲፈቱ መደረጋቸውን ታስረው የተፈቱ አንድ ተፈናቃይ ገልጸዋል።
ተፈናቃዩ ” የተዘረፍነው ንብረት ይመለስልን፣ ወደ ቀያችንም እንመለስ” በማለት በሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ የወረዳው ባለስልጣናትም የቻግኒን ከተማ ህዝብ ጸጥታ ታደፈርሳላችሁ በሚል ሰልፉን እንዲበተን እንዳደረጉና መሪ ናቸው የተባሉትን ሰዎች አስረው እንደለቀቁዋቸው ገልጸዋል። ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ ከ500 በላይ ሰዎች እንታሰራለን በሚል ከከተማዋ መውጣታቸውን የገለጡት ተፈናቃዮ፣ በአሁኑ ጊዜ ከ1600 በላይ ሰዎች መፍትሄ አጥተው መቀመጣቸውን ገልጸዋል።
ከከማሺ ዞን የተፈናቀሉት እንደተመለሱ ብንሰማም ከመተከል ዞን ለተፈናቀሉት ግን አሁንም መልስ አልተሰጠንም በማለት ተፈናቃዩ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በመተከል ዞን እንዲፈናቀሉ ሲደረጉ ድብደባ የተፈጸመባቸው አንድ የአማራ ተወላጅ፣ የደረሰባቸውን ጉዳት ዘርዝረው አቅርበዋል። ተፈናቃዩ እንዳሉት ድብደባው የደረሰባቸው አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ተጠይቀው ፣ አልወጣም የሚል መልስ ከሰጡ በሁዋላ ነው ።
የክልሉ ፕሬዚዳንት ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ተገቢውን ካሳ እንደሚያገኙ ለኢሳት መግለጻቸው ይታወሳል።

ኢሳት ዜና:-ከቤንሻነጉል ጉሙዝ ከከማሺ ዞን ከያሶ ወረዳ ተፈናቅለው ፍኖተሰላም ከተማ ሰፍረው የነበሩት የአማራ ተወላጆች ወደ መጡበት ቦታ እንዲመለሱ ቢደረጉም፣ መጠለያ እና ሌሎች አገልግሎት መስጫ ነገሮች ባልተሟሉበት ጫካ ውስጥ እንዲሰፍሩ መደረጋቸውን በቦታው ደርሰው ያነጋገርናቸው ተፈናቃዮች ገልጸዋል።

 ተፈናቃዮቹ ህጻናቱም ሆኑ አዋቂዎች ምግብ ሳይመገቡ መዋላቸውን፣ ከአንድ ቀን በሁዋላ ዱቄት ተሰፍሮ እንደተሰጣቸው ገልጸዋል። የቀይ መስቀል ሰራተኞች አብረዋቸው እንደመጡ የሚገልጹት ተፈናቃዮች ፣ የተቅማጥ በሽታ በመከሰቱም ሀኪሞቹ ከአቅማችን በላይ ነው እያሉ መሆኑን ገልጸዋል።

 ተፋናቃዮች አንድም ባለስልጣን መጥቶ እንዳልጎበኛቸው ተናግረው የአማራ ክልል ባለስልጣናት መልሰው እንዲወስዷቸው ጥያቄ ማቅረባቸውንም ገልጸዋል። vvvv አሁንም የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው የተናገሩ ሲሆን፣ የወረዳው ባለስልጣናት በቦታው ተገኝተው ሊቀበሏቸው ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ስጋታቸውን እንደጨመረው ገልጸዋል።

... ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ክልል በመተከል ዞን በቡለን ወረዳ ተፈናቅለው በቻግኒ ከተማ የሚገኙ ከ2 ሺ በላይ አርሶአደሮች አንድም ባለስልጣን እንዳላናገራቸው ገልጸዋል። ተፈናቃዮቹ ከሶስት ቀናት በፊት ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ 7 አመራሮቻቸው ተይዘው ለ24 ሰአታት ከታሰሩ በሁዋላ በይቅርታ እንዲፈቱ መደረጋቸውን ታስረው የተፈቱ አንድ ተፈናቃይ ገልጸዋል።

 ተፈናቃዩ ” የተዘረፍነው ንብረት ይመለስልን፣ ወደ ቀያችንም እንመለስ” በማለት በሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸው፣ የወረዳው ባለስልጣናትም የቻግኒን ከተማ ህዝብ ጸጥታ ታደፈርሳላችሁ በሚል ሰልፉን እንዲበተን እንዳደረጉና መሪ ናቸው የተባሉትን ሰዎች አስረው እንደለቀቁዋቸው ገልጸዋል። ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ ከ500 በላይ ሰዎች እንታሰራለን በሚል ከከተማዋ መውጣታቸውን የገለጡት ተፈናቃዮ፣ በአሁኑ ጊዜ ከ1600 በላይ ሰዎች መፍትሄ አጥተው መቀመጣቸውን ገልጸዋል።

 ከከማሺ ዞን የተፈናቀሉት እንደተመለሱ ብንሰማም ከመተከል ዞን ለተፈናቀሉት ግን አሁንም መልስ አልተሰጠንም በማለት ተፈናቃዩ ገልጸዋል።

 በሌላ በኩል ደግሞ በመተከል ዞን እንዲፈናቀሉ ሲደረጉ ድብደባ የተፈጸመባቸው አንድ የአማራ ተወላጅ፣ የደረሰባቸውን ጉዳት ዘርዝረው አቅርበዋል። ተፈናቃዩ እንዳሉት ድብደባው የደረሰባቸው አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ተጠይቀው ፣ አልወጣም የሚል መልስ ከሰጡ በሁዋላ ነው ።

 የክልሉ ፕሬዚዳንት ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ተገቢውን ካሳ እንደሚያገኙ ለኢሳት መግለጻቸው ይታወሳል።

No comments: