Tuesday, April 30, 2013

የኢትዮጵያ ፊዴራላዊ ዲሞክራሳዊ አንድነት መድረክ አባል ድርጅቶች በአስቸኳይ እንዲዋሃዱ ጠየቀ

ሚያዚያ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ላለፉት አምስት ወራቶች የመድረክን የሥራ አፈፃፀም ሁኔታ በቅርብ ሲገመግም የነበረው የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ቅዳሜ ሚያዝያ 19 ቀን 2005 ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የአራት ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው መድረክ እንዲዋሃድ ብሏል ሲል ፍኖተ ነፃነት ዘግቧል።

... ድርጅቱ ላለፉት አራት ዓመታት አሳሳቢ በሆኑና በበርካታ ችግሮች ተተብትቦ የቆየ ቢሆንም ሀገራችን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማሸጋገር በተደረገው ትግል ውስጥ የተጫወተው ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አረጋግጧል።

እንደዘገባው ከሆነ ብሔራዊ ምክር ቤቱ በሰየመው ገምጋሚ ኮሚቴ አማካኝነት የመድረክ አጠቃላይ ሁኔታ በስድስት ዋና ዋና ክፍሎች ተገምግሞ የቀረበ ሲሆን በምክር ቤቱ ውይይት ተደርጎበታል። በዚህ የግምገማ ሪፖርት ላይ ብቻ በመወያየት የመድረክ ጉዞ በውህደት እንዲጠናቀቅ የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ወስኗል።

የሀገሪቱ አጠቃላይ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የጠቀሰው የምክር ቤቱ መግለጫ እራሱን የኢትዮጵያ ሕዝብ በሚፈልገው የለውጥ ደረጃ በማጠናከርና አማራጭ የመፍትሔ አቅጣጫ በማስቀመጥ ሕዝቡን በዙሪያው የማሰባሰብ ሥራ እንዲሰራ ብሄራዊ ምክር ቤቱ ጥሪ አስተላልፏል።

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ አባል ድርጅቶች በአስቸኳይ እንዲዋሃዱ ተጠየቀ
ሚያዚያ ፳፪ (ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ላለፉት አምስት ወራቶች የመድረክን የሥራ አፈፃፀም ሁኔታ በቅርብ ሲገመግም የነበረው የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ቅዳሜ ሚያዝያ 19 ቀን 2005 ባስተላለፈው ውሳኔ መሰረት የአራት ፓርቲዎች ስብስብ የሆነው መድረክ እንዲዋሃድ ብሏል ሲል ፍኖተ ነፃነት ዘግቧል።

ድርጅቱ ላለፉት አራት ዓመታት አሳሳቢ በሆኑና በበርካታ ችግሮች ተተብትቦ የቆየ ቢሆንም ሀገራችን ወደ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማሸጋገር በተደረገው ትግል ውስጥ የተጫወተው ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አረጋግጧል።

እንደዘገባው ከሆነ ብሔራዊ ምክር ቤቱ በሰየመው ገምጋሚ ኮሚቴ አማካኝነት የመድረክ አጠቃላይ ሁኔታ በስድስት ዋና ዋና ክፍሎች ተገምግሞ የቀረበ ሲሆን በምክር ቤቱ ውይይት ተደርጎበታል። በዚህ የግምገማ ሪፖርት ላይ ብቻ በመወያየት የመድረክ ጉዞ በውህደት እንዲጠናቀቅ የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ወስኗል።

የሀገሪቱ አጠቃላይ ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የጠቀሰው የምክር ቤቱ መግለጫ እራሱን የኢትዮጵያ ሕዝብ በሚፈልገው የለውጥ ደረጃ በማጠናከርና አማራጭ የመፍትሔ አቅጣጫ በማስቀመጥ ሕዝቡን በዙሪያው የማሰባሰብ ሥራ  እንዲሰራ ብሄራዊ ምክር ቤቱ ጥሪ አስተላልፏል።

No comments: