Monday, March 10, 2014

ዛሬ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ ሁለት ከፍተኛ አመራሮችና አባሎች ለመጋቢት 5 ተቀጠሩ

march 10/2014
ዛሬ ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ ሁለት ከፍተኛ
እሁድ ለት በተካሄደው የሴቶች 5000 ሜትር ሩጫ ላይ ለነፃነት እንሩጥ በሚል መርህ በሩጫው ላይ በመሳተፍ በርካታ ፖለቲካዊና መሀበራዊ ጥያቄዎችን ያነሱ የሰማያዊ ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ ሀላፊዎችና አባላት እንዲሁም ሰፍራው ንበረቶ ነን ቻቸውን ይዘው የነበሩ ሁለት የፓረቲው ከፍተኛ አመራሮች እና አንድ አባል ታፍሰው ወደ ሾላ የካ ፖሊሰ መምሪያ መወሰዳቸው ይታወቃል ፡፡
በዛሬው እለትም ፍርድቤት ቀርበው የተከሰሱበትን ምክንያት መርማሪ ፖሊሱ /ኮማንደር የማታ/አብራርቷል፡፡ የተከሰሱበት ምክንያት እሁድ በተካሄደው የሴቶች ሩጫ ላይ ተመሳስሎ በመግባት የጣይቱ ልጆች ነን ፣ የምኒልክ ልጆች ነን ፣ ኑሮ መረረን ፣ የህሊና እስረኞች ይፈቱ በሚል ሁከትን ለማነሳሳት ቀስቅሳችኋል የሚልኘ ሲሆን መርማሪው መረጃ አሰባስቤ ስላልጨረስኩና መረጃዎቼን ያጠፋሉ ሰዎችንም እንዳይመሰክሩ ያስፈራሩብኛል በተጨማሪም ብዙዎቹ ቋሚ አድራሻ የሌላቸው ስለሆነ መረጃ እስካሰባስብ የ15 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ ብሏል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮችም እድል እየጠየቁ ለማስረዳት ጥረት ያደረጉ ሲሆን የተከሰሱበት ምክንያት ሀሳባቸውን በአጋጣሚው በነፃነት በመግለፃቸውና በተባለው መልኩ ሳይሆን አስበው እና ሩጫውንም እንደማንኛውም ሴት ኢትዮጵያዊ ቲሸርት ገዝተውና ተመዝግበው ሲሆን አሉ የተባለውን እንዳሉ አስረግጠው ነገር ግን ሁከት አለማስነሳታቸውንም እንዲሁም ሩጫው ሲጠናቀቅ አፍሰው እስርቤት እንደወሰዷቸው ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ አብረው የታሰሩት ወንዶችም በወቅቱ በቦታው የጓደኞቻቸውን እቃዎች ተሸክመው ሩጫውን እስኪፈፅሙ እየጠበቁ በነበረበት ሰዓት ሴቶቹን እየለቀሙ ሲወስዱ ለምንድነው የምትወስዷቸው በማለታቸው ብቻ አብረው እንደታሰሩ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡ አክለውም እኛ ህጋዊ ሰውነት ያለን የፓርቲ አመራሮችና አባላት ነን ስራችንም በዚሁ በአዲስ አበባ ሆኖ ሳለና በተፈለግን ጊዜ የምንገኝበት ግልፅ አድራሻ በምርመራ ወቅት ተመዝግቦ እያለ ዋስትና አይሰጣቸው የተባለው ተቀባይነት የለውም እንዲሁም መረጃ ላሰባስብ የሚለውም ምክንያት ሁሉም ንብረቶቻችን በወቅቱ ተወስደው በፖሊሶች እጅ የሚገኝ ስለሆነ ተገቢ አይደለም በሚል ፍርድ ቤቱን ሞግተዋል፡፡
ክሱን የሚመራው ኮማንደር ይህን በማስተባበል የዋስትና መብታችን ይከበር ማለታቸውን “ፍርድ ቤቱ እንደሚያውቀው በሀገሪቱ ያለው ነገር የታወቀ ነው የአሸባሪዎች ስጋት አለ እና ከዛ ጋር የሚተባበሩ ተልዕኮ ያላቸው ስለሆኑ ለማጣራት ጊዜ ያስፈልገኛል” በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲነሳ ጠይቋል፡፡
በመጨረሻ ዳኛው ኮማንደሩ ይህን ለማጣራት የጠየቀው ጊዜ የተንዛዛ ስለሆነ በአምስት ቀን ውስጥ አጣርቶ ለአርድ መጋቢት 5 እነዲቀረቡ አዞአል ለታሰሪዎቹም ፓርቲው አሰፈለጊውን ሁሉ ድጋፍ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
በሀገር ወሰጥ ሆነ ከሀገር ውጭ ሆናችሁ ደጋፍ ላደረጋችሁልን ሁሉ ከልብ እናመሰግናለን፡፡

No comments: