Saturday, March 22, 2014

ግብፅ አፄ ምኒልክ በተፈራረሙት ውል እየተከራከረች ነው

March 22/2014

ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ እየገነባች ያለችው የታላቁ የህዳሴ ግድብ አፄ ምኒልክ በ1902 ከእንግሊዝ ጋር የተፈራረሙትን ውል የሚጥስ ነው ሲል የግብፅ መንግስት ቃል አቀባይ ቢሮ መግለጫ ያወጣ ሲሆን አፄ ምኒልክ ውሉን ሲፈራረሙ የውሀውን ፍሰት አናቆምም እንጂ አንጠቀምበትም በሚል እንዳልተስማሙ ሰነዶች ያመለክታሉ፡፡

 የቃል አቀባይ ቢሮው ባለፈው ረቡዕ ባወጣው መግለጫ፤ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በአባይ ላይ እየገነባች ያለችው ግድብ በ1902 በእንግሊዝ እና በአፄ ምኒልክ የተፈረመውን የሚጥስ ነው፣ አፄ ምኒልክ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት ተብለው ስልጣን ላይ ከወጡ በኋላ ከእንግሊዝ ጋር በተፈራረሙት ውል መሰረት ከእንግሊዝ እና ሱዳን ፈቃድ ውጪ  ኢትዮጵያ በአባይ፣ በጣና ሀይቅ እና በሶባት ላይ ምንም አይነት ግንባታ እንደማታደርግ እና ለመንባት የሚሞክሩ ወገኖችንም እንደምትከለክል ተስማምታለች፤

ስለዚህ የአሁኑ ግንባታ ስምምነቱን ይጥሳል ብሏል፡፡ በአለም አቀፍ ህግ የውሀ ባለሙያ የሆኑት አቶ እምሩ ታምራት ጉዳዩን አስመልክተው ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ በመጀመሪያ ደረጃ ግብፅ የ1902 ስምምነት አካል ስላልሆነች፤ ይህን ስምምነት በመከራከሪያ ማንሳት አትትችልም፤ ሌላው የስምምነቱ  የአማርኛ ትርጓሜ  “ኢትዮጵያ ውሃውን ሙሉ በሙሉ የሚደፍን ስራ አትሰራም ይላል እንጂ ጥቅም ላይ አታውል” ብላ አልተስማማችም፡፡

አዲስ አድማስ


No comments: