Sunday, March 30, 2014

መጋቢት 28 2006 ደረሰ !!! አዲስ አበባ‹‹ለእሪታ ቀን!››ትዘጋጅ ዘንድ ጥሪ ተደርጓል። የሰማህ ላልሰሙት ንገራቸው !!!

March 30/2014

ምንሊክ ሳልሳዊ

1234
መብራት ውሃ የስልክና የኢንተርኔት ኔትወርክ አገልግሎቶች መብቶች የህዝብ ናቸው!!!!!
አቤቱታችን ከፖለቲካ ነጻነት እና ዲሞክራሲያዊነት ጎን ለጎን የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥያቄ ነው …ይህ ደሞ ለየት ባለ መልኩ አብዮታዊ ነው::እኛ በሰው አገር የምንኖር ዲያስፖራዎች በወገናችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ከማውራት እና መኖሪያ ፍቃዳችን ሲታደስ ከመቀዝቀዝ ዉጪ በወያኔ ላይ የምናሳድረው ጫና እምብዛም ጉልፍ ስፍራ የለውም:: እርስ በርሳቸው የሚላተሙ የጆተኒ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች በላም አለኝ ተስፋ ህዝባችንን አረንቋ ውስጥ እየጨመሩት ነው::
ለጋች አገራት የሚያወጧቸው ሃሰተኛ ጸረ አፍሪካ ሪፖርቶች በተለይ የምስራቅ አፍሪካን ተገን አድርጎ የተመቻቸው የብሄራዊ ጥቅማቸው ፎርሙላ ስኬት የአምባገነኖችን እድሜ በማስረዘም ህዝብ እንዲጭበረበር የህዝብ ጥያቄዎች እንዲደናቀፉ ለገዢዎቻችን የልብ ልብ ሰቷቸዋል:: ለብሄራዊ ጥቅም አስጊ ይሆናሉ የተባሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን እስከማጨማደድ እየዘለቀ በኢጅ አዙህ ህዝባዊ ጥያቄዎች እንዲታፈኑ እየተደረገ አምባገነናዊ አገዛዝን አፍልተውብናል እንሱ ለጋሽ አገራት::
መሰረታዊ ፍላጎቶች እና የአገልግሎት ፍጆታችን በበቂ ሁኔታ ባልተሟላበት አገር መንግስት ፕሮጀክት ለመጨረስ የገንዘብ እጥረት ገጠመኝ በሚልበት አገር ብሄራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሬ የለኝም በሚልበት እና የመንግስት ካዝና ባዶ ሆኖ በዕቃ ግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታ ከቱጃሮች መንግስት በሚበደርባት አገር ጥቂት ፖለቲካው የወለዳቸው ሃብታሞች እጅግ ብዙ የኢኮኖሚ ድቀት ያፈራቸው ደሃዎች በፈሉበት አገር ምን አይነት የኢኮኖሚ እድገት እንደተመዘገበ አነጋጋሪ ነው:; እስከመቼ የአምባገነኖችን ደጋፊዎች ዉሸት ተሸክመን እንዘልቃለን::
መብራት ውሃ ስልክ ሀገሪቷ ተሰርቶ እና ተበድራ ሳይሆን በተፈጥሮ የታደለችው ጸጋዋ እንደሆነም ያለን ሃብት ይመሰክራል ህዝቡ ያለውን ቴክኖሎጂ ከተፈጥሮ ሃብቱ ጋር አደባልቆ እንዳይጠቀም እኛ እናውቅላቹዋለን የሚሉ የወያኔ አውሬዎች ቀፍድደው ይዘውታል::
በቀላል ሊፈታ የሚችል ችግርን በፖለቲካዋ ሳንካ መተብተብ ምንም የሚጠቅም ስላልሆነ ህዝቡ አስፈላጊውን የአገልግሎቶች አቅርቦት እንዲያገኝ መደረግ አለበት ብለን ካሁን በፊት ብንጮህም ከቀድሞ በባሰ መልኩ ብሶበት ይገኛል::
በአለማችን በረሃ በተባሉት አገሮች የውሃ አቅርቦት በሰፊው ለህዝባቸው እየሰጡ ሲሆን የተጣሩ ውሃዎች ሳይቀር በርካሽ ዋጋ እየተሸጡ ነው::በኢትዮጵያችን ግን በተፈጥሮ የታደልነውን ውሃ በፖለቲካ ሹማምንት ልፍስፍስነት ልንጠቀምበት አልቻልንም ትልልቅ እና ገባር እንዲሁም ትንንሽ ወንዞች እና የተፈጥሮ ውሃ ምንጮች በሞሉባት ሃገራችን ህዝብ ውሃ ተጠማሁ ሲል መመልከት አስደንጋጭ ነው::ሃገሪቱ በውሃ ችግር ተውጣልች::የውሃ እጥረት ኖሮን ሳይሆን በአግባቡ አለመጠቀም እና ችግሩን የመፍታት ባህል ስላሌለን ነው::ለጎረቤት አገሮች ውሃ እንሰጣለን እየተባለ ባለበት የፕሮፓጋንዳ ጡዘት ውስጥ እኛ በጥማት ማለቃችን አሳፋሪ ነው::
ወድ መብራት ስንመጣ ደሞ መንግስት ያለ እንኳን ተደርጎ ማሰብ ይከብዳል:: የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ መብራት ጠፍቶ ሲመጣ መብራት መጣ ብሎ መጮህ ነው ተብሎ በሰው ሃገር ጋዜጦች እስኪቀለድብን ድረስ ወያኔ በህዝብ ጭንቅላት ጢባጢቦ እየተጫወተች ነው::ይህ እንደገጠመኝ እና እድል የሚታየው የመብራት እቃቃ ጨዋታ በአግባቡ መፍታት እየተቻለ ችግሩንም ማድረቅ እየተቻለ ለምን መዘናጋት እንደሚፈጠር ማስረዳት የሚችል ባለስልጣን አልተገኘም::በኤሌክትሪክ መጥፋትና ሥርዓት አልበኝነት ምክንያት በርካታ ኢንዱስትሪዎች ሥራቸውን እያቆሙ ናቸው፡፡ በርካታ ማሽኖች ከጥቅም ውጭ እየሆኑ ናቸው፡፡ በመኖሪያ ቤቶች ቴሌቪዥኖች፣ ፍሪጆችና ሌሎች የኤሌክትሪክ ዕቃዎች እየፈነዱና እየተቃጠሉ ነው፡፡ በመብራት መጥፋት ምክንያትም የየዕለቱ ኑሮ ይዘቱም ገጽታውም እየተበላሸ ነው፡፡ ከመኖሪያ ቤቶች አልፎ ካፌዎችም በመብራት መጥፋት ምክንያት ‹‹ተረኛ መድኃኒት ቤት›› እየመሰሉ ነው፡፡ ሻይ ታዞ ‹‹ይቅርታ መብራት የለም›› የሚል መልስ መስማት የተለመደ እየሆነ ነው፡፡ እውነት ኢትዮጵያ ለዜጎቿ፣ ለኢንዱስትሪዎቿም ሆነ ለሁሉም ዓይነት እንቅስቃሴዎቿ የሚሆን በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል የላትም? አይኖራትም? አላትም ይኖራታልም፡፡ በቂ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች የንፋስ የኃይል ማመንጫዎች የፀሐይ የኃይል ማመንጫ አቅም የጂኦ ተርማል የኃይል ማመንጫ አቅምም አለ፡፡ እንኳን ለራስዋ ለሌሎች አገሮችም የሚሆን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ዕምቅ ሀብት አላት፡፡ ኦኖም ግን በአግባቡ የሚያዳርስ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች አጣብቂኝ ውስጥ ስለከተቷት ህዝቧ አስፈላጊውን የአገልግሎት መብቶች እና አቅርቦቶች ሊያገኝ አልቻለም::በሃይል ግንባታ ሰበብ በህዝብ ላይ መንግስታዊ አሻጥር እየተፈፀመ ነው::
ወደ ስልክ እና ኢንተርኔት ኔትወርክ ስንመጣ በጸሎች የሚገኝ ያውም ተለቅሶ መፍትሄም የጠፋለት ጉዳይ ከሆነ ቆይቷል:: በአለማችን በስፋት ይህን የኔትዎርክ ችግር ተቀርፎ ባለበት ሰአት የወያኔ ባለስልጣናት ግን በአደናባሪዎቻቸው በኩል በፋይበር ቅንጠሳ እና በህንጻ መብዛት ቢያሳስቡም ከነሱ ቀድሞ ንቃተ ህሊናው ያደገውን ህዝብ ግን ሊሸውዱት አልቻሉም:: ያው እንደለመዱት በጠበንጃ እና ሽብር በመንዛት ዝም አሰኝተውታል:: የወያኔ መንግስት የህዝብን የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች መፍታት እየቻለ እንዳይፈቱ በማድረግ በሚፈጸም አሻጥር እራሱ አጣብቂኝ ውስጥ እንደገባ ሊገነዘበው አልደፈረም:: የመልካም አስተዳደር ብልሃት የሞላበት አመራር ህግ አክባሪ እና አስከባሪ ባለስልጣንትን ለማግኘት ሁላችንም በትግሉ ላይ እንረባረብ። ምንሊክ ሳልሳዊ

No comments: