Friday, May 9, 2014

“የኢትዮጵያ የብሔሮች ጥያቄና መፍትሔዉ” እስክንድር ነጋ(ከቃሊቲ እስር ቤት)

May 9/2014
የዲሞክራሲያዊ መብቶች ጋር ተያይዞ፣ የብሔረሰቦች የእኩልነት መብት በቃልና በፕሮግራም ብቻ ሳይሆን፣ በግብር መታወቅ
አለበት፡፡ የእያንዳንዱም ብሔረሰብ ቋንቋ፣ ባህል፣ ሃይማኖትና ሌሎችም መለያዎች በእኩልነት መታወቅና መከበር አለባቸዉ፡፡
ብሔሮች ሁሉ ትልቅም ሆነ ትንሽ የራሳቸዉን የወደፊት ዕድል የመወሰን መብት መታወቅና በትክክል ከስራ ላይ መዋል አለበት፡፡
ብሔሮች ቋንቋቸዉንና ጠቃሚ የሆኑትን ባህሎቻቸዉን በነፃ እንዲያዳብሩ መደረግ አለበት፡፡ ማንም ሰዉ በዉስጥ አስተዳደራቸዉ
ላይ ጨቋኝ ተፅዕኖ እንዳያደርግ መከላከል አለበት፡፡ ኢትዮጵያን ከብሔሮች እስር ቤትነት ወደ ብሔሮች ማበቢያ ሥፍራ ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡ ይቻላልም፡፡ የሕዝቦች አንድነት፣ በሳንጃና በመድፍ በተቋቋመዉ አንድነት ፋንታ፣ በመግባባትና በመፈቃቀድ ላይ
ሊመሠረትና እንደአለት ጸንቶ ሊኖር የሚችለዉ በዚህ መንገድ ብቻ ነዉ፡፡ በንጉሱ እና በደርግ ጊዜ የብሔርን ጥያቄ አንግበዉ
የተነሱ አካላት ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ(ሻቢያ)፣ ሕወሓት እና ኦነግ ነበሩ፡፡ በአሁን ግዜ ግን ነፃ አዉጭ ብሔር የሌለዉ
የደቡብ ክልል ብቻ ነዉ ይህም ሊሆን የቻለዉ እንደሚመስለኝ የጎሳዎች ብዛት እና የመልክአምድራዊ አቀማመጥ ብሎ ነግሮኛል፡፡
አምባገነን ባለበት አገር ላይ የብሔር ጥያቄ የሚያነሱ አካላት እየበዙ እንጅ እያነሱ አይሄዱም፡፡ እንደ ምሳሌ ታላቋን ሩስያ ማንሳት
በቂ ነዉ፡፡ በእስታሊን አምባገነንነት ምክንያት አብዛኞቹ አገሮች ለመገንጠል ምክንያት ሆናቸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የዩጎዝላቪያ፣ የራሽያ
እና የሶማሊያ እጣ ፋንታ ሳያጋጥማት እኛ ቀድመን ልናድናት ይገባል፡፡ ይሄም ሊሆን የሚችለዉ በአንድ እና አንድ መንገድ ብቻ
ነዉ፡፡ እሱም በሰላማዊ ትግል ወያኔን ስናስወግድ ብቻ፡፡ከዛም ስራዉ የኛ የጋዜጠኞች እና የፖለቲከኞች ይሆናል፡፡ የብሔር
ፖለቲካ የበሰበሰ እና ያለፈበት መሆኑን ምርጫ 1997 አስተምሮን አልፏል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ኤርትራ እንዳትገነጠል የበኩልን
ድርሻ ቢወጣም በወያኔ እንቢተኝነት በ1984 ዓ.ም ምህረት ህዝቡን አሰሩ፣ ገደሉ አቆሰሉ፡፡ ይህም አልበቃ ብሏቸዉ የኤርትራ
ህዝብን በምርጫ በማወናበድ ምርጫቸዉን አሳኩ፡፡ በየት አገር ነዉ ባርነት ወይስ ነፃነት የሚል ምርጫ የተካሄደባት አገር አለች፡፡

የኤርትራ ህዝብ ግን የጣሊያን እና የእንግሊዝ አስተዳደር አሻፈረኝ ብሎ ወደ እናት አገራቸዉ ለመመለስ የበኩላቸዉን ጥረት
ሲያደርጉ እንደነበር የታሪክ ድርሳናቶች ይናገራሉ፡፡ ሁለት ኤርትራዊያን ግለሰቦችን ማንሳት ያዉም በቂ ነዉ ዘርዐይ ደረስ
ጣሊያኖች በኢትዮጵያ ባንዲራ ላይ ሲቀልዱ በመበሳጨት ጣሊያኖች ላይ ጉዳት አድርሷል፤ አብርሃም ደቦጭ በግራዚያኒ ላይ
ቦምብ በመወርወር የመግደል ሙከራ ያደረገ እና ያቆሰለ፡፡ህዝቡም ሲጠይቅ የነበረዉ ኢትዮጵያዊነት ነዉ፡፡ይህንንም አሳክተዉ
ከ60 ዓመታት በኋላ ተመልሰዋል፡፡ ለዚህ ሁሉ መሳካትም የዉጭ ጉዳይ ሚኒስተር የነበሩት የአክሊሉ ሀብተወልድ ድርሻ ላቅ ያለ
ነበር፡፡

“ኢትዮጵያ ወይም ሞት” በማለት በሀገር ፍቅር ማህበር ስር የተሰለፉ ሀገር ወዳድ ኋይሎች ህዝቡን በማስተባበር በነቂስ ወጥቶ
የኤርትራን ግዛቶች ሲያጥለቀልቅ እንደነበርም ይታወሳል፡፡ ከኢትዮጵያ ጋር አብረዉ ለመኖር የሚፈልጉ ህዝቦች ነበሩ፡፡ ሁሉም
የኤርትራ ህዝብ ለመገንጠል ከሻቢያና ከወኔ ጋር አብረዉ ቁመዋል ማለት ከእዉነት የራቀ ነዉ፡፡ የኤርትራ መገንጠል
ለአስገንጣኞች አካላት ብቻ ነዉ የጠቀመዉ፡፡ ኤርትራ በመገንጠሏ የኤርትራ ህዝብ ምን አገኘ? የኢትዮጵያ ህዝብስ ምን አገኘ?
አሁንም የኤርትራ ህዝብ በጭቆና፣ በርሀብ፣ በስደት እና በበሽታ እያለቀ ነዉ፡፡ መገንጠል እንደማያዋጣ የኛዉ ኤርትራ
አስተምራናለች፡፡

እስክንድር ነጋ የሚፈልገዉ እኩልነትና ነፃነት የሠፈነበት፣ የህዝቦቿ አንድነት ከብረት የጠነከረባትና ብሔረሰቦች ሁሉ ያበቡባት፣
የማንም ተመፅዋች ያልሆነ በራሱ የሚተማመን በማንም ፊት የባታችነት ስሜት ሊኖረዉ የሚችል ህዝብ እንዲይፈጠር ነዉ፡፡
የኢትዮጵያ ሕዝቦች ትግል የፈጀዉን ጊዜ ቢፈጅምና የፈለገዉን ያህል መሥዋዕትነት ቢጠይቅም፣ ብዙ ችግሮችና መሰናክሎችን
ከፊታችን ቢደቀኑም፤ የዚች ዓይነት ኢትዮጵያ እንድትመሰረት እስከ መጨረሻዉ ለመታገል ቆርጨ ተነስቻለዉ፡፡ የእናት አገራችን
ህልዉና ላያስጠብቅ የሚችለዉ ለ22 ዓመታት ፈላጭ ቆራጭ ጫማ ስር የተረገጠችበት ብሔራዊ ነፃነቿን ክብሯ ተገፍፎ የቆየችበት
ዓመታት ነዉ፡፡ በሁሉም ወገን የሚደረገዉ መሯሯጥና መሰናዶ ሲታይ አበረታታች ነዉ፡፡ ወሳኝ የሆነዉ ፍልሚያ ገና ከፊታችን
እንደሚጠብቀን ምንም ጥርጥር ሊኖረዉ አይችልም፡፡

የግንቦት 7 መስራች እና መሪ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በሚመለከት ከግብፅ መንግስት እርዳታ ተቀብሏል ተብሎ ወሬ እየተናፈሰ መሆን
ስጠይቀዉ፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ብርሃኑ የሚያደርገዉ አይመስለኝም ካደረገዉ ግን በጣም አዝኘበታለዉ፡፡ ለምንድን ነዉ
አባቶቻችን የሰሩትን ስህተት የምንደግመዉ፡፡ መኢሶን፣ ኢህአፓ፣ ጀብዐ እና ወያኔ በአንድ ይሁን በሌላ መልኩ የዉጭ እርዳታን
እየተቀበለዉ፡፡ አገራችን እና ህዝቧን ጎርቷል፡፡ ኤርትራን እንድናጣ ሁነናል፡፡ አሁንም መናገር የምፈልገዉ ኢህአዴግን እና
ኢትዮጵያን ለይተን ማዬት አለብን፡፡ ኢህአዴግን የጎዱ እየመሰላቸዉ አገራችንን እያደሟት ነዉ፡፡
ለተቃወሚ ፓርቲዎች እችን መልዕክት አስተላልፏል፡፡

1.የዉጭ ኋይሎች ድጋፍ የዚችን ኩሩና ታሪካዊ አገራችንን ብሔራዊ ክብርና ነፃነት የማይነካ፣ ራስን ለመቻል የምታደርገዉን
ጥረት የሚያግዝ እንጅ የማያደናቅፍ እርዳታ መሆን አለበት፡፡

2. ማንኛዉም ህዝብ በዉጭ እርዳታ ላይ በመተማመን አብዮቱን ከግብ ለማደረስ እችላለሁ ብሎ ካሰበ ራሱን ማታለሉ ብቻ
ሳይሆን አብዮቱንም ብሔራዊ ነፃነቱን ያጣል፡፡ ማንም ህዝብ በተለይም ደግሞ እንደኢትዮጵያ ሕዝቡ ኩሩና ባለታሪክ ሕዝብ ከሆነ
ለገዛ ነፃነቱ፣ ለገዛ ለዉጡ ለገዛ ክብሩ ከሁሉም በፊት መተማመን ያለበት በራሱ መሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ ስለሆነም የዉጭ
እርዳታን በሚመለከት በኩል ብሔራዊ ክብርና ነፃነት እንደዚሁም ከሁሉ በፊት በራስ መተማመን የሚለዉ ዋናዉ መመሪያችን
ይሆኑ፡፡

እስክንድር ነጋ

ተቃዋሚ ፓርቲዎች በምርጫ ጊዜያቸዉን ማባከን የለባቸዉም የሰማያዊ ፓርቲ እና አንድነት ፓርቲ የሰላማዊ ትግል መንገድ
መቀላቀል አለባቸዉ፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲ “ሰላማዊ ትግሉን(አብዮቱን) እኛ ካልመራነዉ አብዮት አይሆንም” ከሚል አመለካከት
መጀመሪያ መላቀቅ አለባቸዉ፡፡ትግሉን ማንም ይምራዉ ማን ሕዝቡ ለትክክለኛዉ የስልጣን ባለቤት መሆን አለበት፡፡ ዛሬ
የሚወነጃጀሉት ኢህአፓ፣ መኢሶን፣ ማሌሪድ፣ ሰደድ፣ ወዝ ሊግ፣ ሻዕቢያ፣ ህወሓት ይህን የህዝብ መብት ረግጠዉ እና አፍነዉ
በህዝቡ ቦታና ጥያቄ እራሳቸዉን መተካታቸዉ ሲሆን ዋና የህዝቡን የበመደል መነሻ ምክንያት ይህ ነዉ፡፡ በመሆኑም በአንዳንድ
ታዳጊ አገሮች ዉስጥ ሕዝቡን በዙሪያቸዉ አጠቃለዉ ለማሰለፍ አይነት ተግባራዊነት ታላላቅ ሰዎችን የመሰሉ እንኳን ለማፍራት
አልቻለችም፡፡ ከዚህ አኳያ ጋንዲን ያፈራች ህንድ፣ ማኦን ያፈራች ቻይና፣ ማንዴላን ያፈራች ደቡብ አፍሪካ እና ፓትርስ ሉሙባን
ያፈራች ኮንጎ ጋር ሀገራችን በአቻ አትታይም፡፡ እነዚህ ታላላቅ ሰዎች ከሀገራቸዉ አልፈዉ የአለም ሰዎች ሁነዉ ኑረዋል፡፡እየኖሩም
ነዉ፡፡ እንዲያዉም ኢትዮጵያ ዛሬ የጎደላት ነገር ቢኖር እኒእኒህን የመሰሉ ቅን ሰዎችን ማግኘት ነዉ፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንኳን
የብሔረሰቦችን የአመለካከት ድንበር አቋርጦ በማለፍ የህዝቦቷን አመኔታ ሊያገኝ የቻለ የፖለቲካ ሰዉ መፍጠር ቀርቶ ለተወለደበት
ብሔረሰብ ለመቆም የቻለ ሀቀኛ የህዝብ ሰዉ መፍጠር አልተቻለም፡፡

በመጨረሻም እስክንድር ልብን በሚማርክ ሁኔታ ስለ ኢትዮጵያ እናት እና አባቶቻችን ለብዙ ዓመታት ታግለዉና ተዋግተዉ
ነፃነታቸዉን ያወጁት፡፡ ስለዚህ ይህ ትዉልድ ጭቆናና ግፍ በቃኝ ብሎ የራሱን መሪዎች ገርስሶ መጣል አለበት፡፡
“እኔ ለዲሞክራሲ ስል ታሰርኩ እንጅ ሌላ ምን ሆንኩኝ ለነፃነት የምከፍለዉ መስዋዕትነት እስከ ሞት ድረስ ነዉ”

እስክንድር ነጋ

“እኔ ከኢትዮጵያ የተሻለ አገር የለኝም የምታሰርባት፣ የምገረፍላት፣ የማለቅስላት፣………. በቃ በአጭሩ እኔ የምሞተዉ በአገሬ
በኢትዮጵያ መሬት ነዉ፡፡ ነፍሴም የምታልፈዉ ሥጋዬም የሚፈርሰዉ በምወዳት አገሬ ኢትዮጵያ ነዉ”

እስክንድር ነጋ

No comments: