Saturday, May 31, 2014

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 1ኛ ዓመት ተማሪ ከዩኒቨርስቲ ግቢ ባልታወቁ ኃይሎች ታፈነ

May30/2014
10426
በጎንደር ምዕራብ አርማጨሆ ነዋሪ የሆነውና በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 6ኪሎ የአካውንቲግ 1ኛ ዓመት ተማሪ የሆነው እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የአንድነት መዋቅር ስራ አስፈጻሚ አባል ወጣት መልካሙ አምባቸው ሰኞ ግንቦት 18 ቀን 2006 ዓ.ም ማታ ራት ከበላ በኋላ ከዩኒቨርስቲ ግቢ ባልታወቁ ኃይሎች ታፍኖ ተወስዷል፡፡ ወጣት መልካሙ በጎንደር የሚደረገውን የድንበር ማካለል የአካባቢው ነዋሪ እንደመሆኑ መጠን የሚያውቀውን መረጃ በመስጠቱ ክትትል አንዳንዴም ማስፈራሪያ ይደረግበት እንደነበር ለፍኖተ ነፃነት ዘጋቢ ይገልጽ ነበር፣ አሁንም የተያዘው ከድንበር ማካለሉ ጋር በሰጠው መረጃ እንደሆነ በቦታው የነበሩ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ፓርቲው ወጣት መልካሙ ያለበትን ሁኔታ ለማጣራት በዩኒቨርስቲው አካባቢ ያሉ ፖሊስ ጣቢያዎች ቢሞከርም እስካሁን ድረስ ያለበት አልታወቀም፡፡  

No comments: