Thursday, May 22, 2014

ፍትህ በምዕራብ ወለጋ እንጨት ለቀማ ወጥቶ በወታደሮች ጥይት ሕይወቱ ላለፈው ገመቺስ

May 22/2014
ከዳዊት ሰለሞን
ፍትህ ለገመቺስና ለመሰሎቹ
በምዕራብ ወለጋ የጊምቢ አጎራባች በሆነችው ዋሎ የሱስ መንደር ነዋሪ የነበረው ገመቺስ ደበላ ከእንጨት ከሰል እያመረተ
ቤተሰቦቹን በመደጎም ህይወትን ሲጋፈጥ ቆይቷል፡፡የ16ዓመቱ ገመቺስ በ02/09/2006 እንደተለመደው ማለዳ ተነስቶ
ለከሰል የሚሆነውን እንጨት ፍለጋ ወደ ጊምቢ እያቀና ነበር በወታደሮች በተተኮሰበት ጥይት እግሩ ላይ የተመታው፡፡የዘጠነኝክፍል ተማሪ የነበረውን ገመቺስን በጊምቢ የሚገኘው የአድቪንቲስት ሆስፒታል ህክምና ሲሰጠው ቢቆይም በ12/09/2006ይህችን አለም በግፍ ተሰናብቷል፡፡

No comments: