Sunday, May 18, 2014

አዜብ አከርካሪዋ በስብሃት ነጋ ተሰባብሮዋል። /እየሩሳሌም አርአያ/

May 18,2014
የአዜብ ነገር


ከሰሞኑ ኢህአዴግ ባካሄደው ጉባኤ ላይ አዜብ መስፍን ነበሩ። ከኋላ ፈንጠር ብለው ተቀምጠው ነበር። በሽተኛ ይመስላሉ። “እንኳንስ ዘንቦብሽ..” እንደሚባለው ያ ፊታቸው ገርጥቶ፣ የፉጨት አስተማሪ መስለው፣ ያ ሁሉ መኮፈስና ትእቢት ተንፍሶ ታይተዋል። አንዲት የአባይ ፀሐዬ ስጋ ዘመድ በቅርቡ ልጅ ለመውለድ ዲሲ መጥታ ስትናገር፥ « አዜብ አከርካሪዋ በስብሃት ነጋ ተሰባብሮዋል። ስብሃት አዜብን እንዳንታንሰራራ አድርጐ ከነተከታዮችዋ ከጨዋታ ውጭ አድርጓታል። የአዜብ ነገር አክትሞዋል፤ መልቀቂያ ብትጠይቅም ተቀባይነት አላገኘም። ስብሃት እያሳቀቀ በቁም እያሰቃያት ነው» ብላለች። ስብሃት ነጋ ይህን ማድረጋቸው እርግጥ ቢሆንም ነገር ግን ሁሉም አገሪቱን ቁልቁል የሚሰዱና በተለይ ስብሃት የዘርና ጐሳ መሐንዲስ እንደሆኑ ይታወቃል።….አዜብ “እበላዋለሁ” ብለው ከህዝብ ዘርፈው ያከማቹትን በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ- እያስጐመዠ በሰቀቀን የጨረሳቸው ይመስላል። ነፃ ፍ/ቤት ቢኖር ኖሮ አዜብ፣ አባይ ፀሐዬ፣ ስብሃት፣ በረከት…ወዘተ በሙስና ወንጀል መጠየቅ ነበረባቸው። ግን የለም!!… ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በ1995ዓ.. በኢትኦጵ ጋዜጣ ላሰፈረው ርእሰ አንቀጽ የሰጠው ርእስ ሁሌም ያስገርመኛል፤ « የሙስና ኮሚሽን!» ነበር ያለው። በወቅቱ በዩኒቨርሲቲ ምሁራን፣ በገዢው ባለስልጣናትና መሰል አካላት ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። እንዳውም የኮሚሽኑ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጠርተው እንዳነጋገሩት አስታውሳለሁ። ..ለማንኛውም “የአዜብ ጥጋብ ሲተነፍስ ላሳየኸን ፈጣሪ ምስጋና ይድረስህ!!” ቀጣዩ ደግሞ….

No comments: