Wednesday, May 21, 2014

የስደተኞች ዋይታ በሱዳን

May20/2014
አንድ የሱዳን ፍርድ ቤት፣ በአንዲት የ 27 ዓመት ሴት፣ ከልጅነቷ አንስቶ የ ወላጅ እናቷን ሃይማኖት ስተከተል መኖሯን በይፋ ብትገልጸም ፣ ያላሳደጋትን ሙስሊም አባቷን ሃይማኖት እንደለወጠች በመቁጠር ሙት-በቃ በመፍረዱ፣ በዛ ያሉ ምዕራባውያን መንግሥታትና የሰብአዊ መብት ድርጅቶች፣
Konflikt im Südsudan Flüchtlinge 16.01.2014
ሱዳን የሃይማኖት ነጸነትን እንድታከብር መጠየቃቸው ይታወሳል። በዚያ የሚኖሩ ስደተኞች ደረሰብን ስለሚሉት ወከባ፤ እንግልት ፣ እሥራት፤ የንብረት መቀማትና የመሳሰለው ግን ያን ያህል ትኩረት ያገኘ አይመስልም። ከተለያዩ ምንጮች እንደምንሰማውና በቀጥታም ዶቸ ቨለም ከሚደርሰው መልእክት መረዳት እንደቻልነው ፤ ባለፉት 3 ወራት በተለይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ወከባው ያየለባቸው ሲሆን ፤ እየታደኑ እንደሚያዙ፣ እንደሚታሠሩ ንብረታቸው እንደሚዘረፍ በምሬት ይገልጻሉ ተክሌ የኋላ ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል።
ተክሌ የኋላ
አርያም ተክሌ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC


No comments: