Thursday, May 29, 2014

በደብረማርቆስ ከተማ ከ400 በላይ ቤቶች በዶዘር እየፈረሱ ነው

May 29/2014

በዛሬው ዕለት ደብረ ማርቆስ ከተማ ውስጥ ህገ ወጥ ናቸው የተባሉ ቤቶች በዶዘር እየፈረሱ እንደሚገኙ ከቦታው የደረሰን መረጃይጠቁማል፡፡ በተለይ ቦሌ እየተባለ የሚጠራው ሰፈር የሚገኙ ቤቶች በዛሬው ዕለት እየፈረሰ እንደሚገኝና ህዝብ ይቃወማልበሚል ቡችሌ፣ ሚሊሻ፣ ህዝባዊና ልዩ ፖሊስ ከፍተኛ ጥበቃ እያደረገ እንደሚገኝ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ተናግረዋል፡፡(ደብረማርቆስ ከተማ)ይህ ቦሌ ተብሎ የሚጠራው ሰፈር ትናንት ሊፈርስ የነበረ ቢሆንም በግንቦት 20 ምክንያት እንደታለፈ ተገልጾአል፡፡

ደብረ ማርቆስ ውስጥ ቤቶችን ማፍረስ የተጀመረው ግንቦት 18ና 19/2006 ዓ.ም ሲሆን ቀበሌ አራት (4) በተለይም ሞንቃተብሎ በሚጠራው ሰፈር 400 ያህል ቤቶች እንደፈረሱ ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ቦሌ የተባለው ሰፈር እንዳይፈርስ በተደረገበትበትናንትናው ቀን ከ23 አመት በላይ ግብር ሲከፈልበት የኖረ የአንድ ግለሰብ ቤት መፍረሱም ታውቋል፡፡

 አፍራሽ ግብረሃይሉየቤቱን ጣራ ካፈረሰ በኋላ ግለሰቡ ለ23 ዓመት ግብር ሲከፍልበት የነበረ መሆኑንበመገለጹግድግዳው ብቻ እንደቆመ ወደአቤቱታ መመራቱን ምንጮች ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ደብረ ማርቆስ ውስጥ አብዛኛዎቹ ቤቶች ከ1997 ጀምሮ የተሰሩ ሲሆኑ አብዛኛዎቹ ቤቶች አርሶ አደሮች በአሁኑ ወቅት ወደከተማ በተከለለው መሬታቸው ላይ የሰሯቸው እንደሆኑ ታውቋል፡፡ ‹‹የአርሶ አደሮቹ መሬቶች ወደ ከተማ ሲከለሉ መንግስትተለዋጭ ወይንም ካሳ የመስጠት ግዴት የነበረበት ቢሆንም በአሁኑ ወቅት በህገ ወጥነት እያፈረሰ እያፈረሰ ይገኛል›› ያሉት አንድየከተማዋ ነዋሪ እርምጃው ህገ ወጥ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

No comments: