Monday, May 5, 2014

የአራቱ ሃዋርያት በትግራይ ጉብኝት አነጋጋሪ ሆኗል

May5/2014
ከአስገደ ገ/ስላሴ፣ መቐለ

ሰሞኑን ባልተለመደ መንገድ ከትግራይ ክልል የሰልጣን መዋቅር እርከን ወጣ ያለ የክልሉን ስልጣን የተጋፋ (የነጠቀ) የስለላ ስራ የሚመስል እንቅስቃሴ ከ23 አመት የህ.ወ.ሃ.ት አገዛዝ በኃላ አራት አዛውንት የለውጥ ሃዋርያት መስለዉ በመላው ትግራይ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ ከዛም አልፎ በቀበሌ ከተሞች ሳይቀር በልዩ ሃይል ታጅበዉ እየዞሩ ሰንብተዋል።

የነዚህ ሃይል ሃዋርያት ጉብኝት አላማዉ ለህዝቡና የክልል መዋቅር ሰራተኞች ለህ.ወ.ሃ.ት ታጋዎች ግልፅ አልነበረም። ነገር ግን እንቅስቃሴአቸዉ በ3ትመንገድ ይፈፅሙት ጀመሩ። ከነዚህም አንደኛ በየከተማዉ ያለዉ ከንቲባ ስብሰባ አስጠርተዉ ከተሰብሳቢዉ ህዝቡ ላይ ችግር ምን አለ፤ ነፃ ሁናችሁ ንገሩንና ችግሩን አብረን እንፈታዋለን። ሁለተኛ ከነዋሪዎች ቤት ለቤት እየዞሩ የስለላና የመረጃ አሰባሰብ ግለሰቦች ን በማነጋገር ያለዉን ችግር ይጠይቃሉ። ሶስተኛ በ17ትአመቱ የትጥቅ ትግል ጊዜ ልጆቻቸዉ የሞቱባቸዉ አዛውንት ወላጆች ነባር ሚሊሻዎችና ነባር የፓርቲ አባላት ለነበሩና ነባር ታጋዮች የነበሩ የጦር አካል ጉዳተቾች በተናጠል አነጋግረዋል፤ ይህ ተግባር በሁሉም ከተሞችና ገጠሮች ይሰሩት ነበር።

  Read more http://www.ethiomedia.com/16file/aratu_hawaryat.pdf

No comments: