Tuesday, December 31, 2013

አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ታሰረ

December 31/2013

(ዘ-ሐበሻ) በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይተላለፍ በነበረው ገመና ድራማ የዶ/ር ምስክርን ገፀ ባህርይ ወክሎ የተወነውና በተለያዩ ፊልሞች ላይ የተወነው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ መታሰሩን የዘሐበሻ ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ ገለጹ። አርቲስቱ የታሰረው በካራማራ ፖሊስ ጣቢያ ሲሆን ዛሬ ፍ/ቤት ይቀርባል፡፡ የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበት ለቀጣዮቹ 14 ቀናት እስር ቤት እንደሚቆይም ይጠበቃል፡፡

የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች የአርቲስቱን የክስ መዝገብ በመጥቀስ እንደዘገቡት ዳንኤል የታሰረበት ምክንያት አንዲት ባለትዳር ሴትን ከሌላ ወንድ ጋር ስትሳሳሚ ፎቶ አንስቼሻለሁ ይህንንም ፎቶ በፌስ ቡክ አለቀዋለሁ ብሎ በስልክና በአካል በማስፈራራቱ ነው፡፡ አርቲስቱ ከዚህችው ወ/ሮ ፊልም እሰራለሁ ብሎ 500 ሺ ብር እንደተቀበለና በማጭበርበር ክስ እንደቀረበበት በተለያዩ ሚዲያዎች በዘገቡ ይታወቃል፡፡( ስለዚሁ ጉዳይ ባለፈው ቅዳሜ ለንባብ የበቃው ቁም ነገር መፅሄት ሁለቱንም ወገኖች ማነጋገሩ ይታወቃል) ሰለጉዳዩ ተከታትለን እናቀርባለን።


No comments: