Wednesday, December 11, 2013

እዩኝ እዩኝ ደብቁኝ ደብቁኝን ያመጣል :: አቶ ሀብታሙ አያሌው = ከኢህአዴግ ወደ መድረክ የተላከ ሰርጎ - ገብ

December 11/2013
ምኒልክ ሳልሳዊ

እዩኝ እዩኝ ደብቁኝ ደብቁኝን ያመጣልጋሻው መርሻእንዳለመታደል ሆኖ የሀገራችን ፖለቲካ የሚተረማመሰው በአማተሮችና ሆድ - . አደር አሽከሮች ነው ይህ በመሆኑ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ከገዥው ፓርቲ ጋር ከሚደርጉት ትግል የበለጠ የሚያደክማቸው አግድም / ሆርዞንታል / እርስ በርስ የሚያካሂዱት መቦጫጫቅ ነው ለዚህ ደግሞ ምቹ ሁኔታዎችን በማመቻቸት በኩል የራሳቸው አስተዋጽኦ ሚያደርጉ ሰርጎ - . ገቦች በየዘመኑ ይነሳሉ ምንም እንኳን ይህ አላስፈላጊ መሸነቋቆጥና ስድብ / መተቻቸት አላልኩም / የማልወደው ቢሆንም የአውራው ፓርቲ የውስጥ አርበኞች የትግሉን ስሜት ለማቀዝቀዝ የሚያደርጉት እሰጥ አገባና , አጀንዳ መዘዛ , እውነተኛ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና ሀገር ወዳድ ዜጎች ባላወቁት ወጥመድ እየገቡ መሆኑን ስመለከት የሚያውቁትን መረጃ አለማጋለጥ የሚረጩትን መርዝ ሰርጎ እንዲገባ እገዛ ማድረግ መስሎ ስለተሰማኝ ይህንን እውነት ለመከተብ ተነሳሁ .

 ለጽሁፌ መነሻ የሆነኝ ነሀሴ 11 በወጣው ላይፍ መጽሄት ላይ አቶ ሀብታሙ አያሌው ያደረገው ቃለ መጠይቅና ከዚህ በፊት ያደረጋቸው አፍራሽ ንግግሮች ናቸው . እውነቱን ከማሳየት ውጭ ሌላ ምንም አላማ የሌላት ይህች አጭር ጽሁፍ ተናጋሪውና አንባቢዎች በቅን ልቡና ያነቡልኝ ዘንድ በቅድሚያ አሳውቃለሁ . ደራሲ በዓሉ ግርማ የህሊና ደወል በሚለው መጽሀፉ ገጽ 173 ላይ በአንደበቱ እየሸነገለ ከሀዲ የሆነውንና በኢትዮጵያ ስም እየማለ የይሁዳን ገጸ ባህሪ የሚተውነውን ኢትዮጵያዊ ሲገልጸው - ውዲቷ ሀገሬ እናት ኢትዮጵያ ብሎ ባንደበቱ የሚያሞጋግሰኝ ሞልቷል በየ ቤቱ ምላስ አልነበረም እኔን የቸገረኝ ቤዛ የሚሆን እጅ ነው ያጠረኝ ባፉ ተናግሮ በጁ ከሚክደኝ ከወጣቱ ትውልድ ከሸክም አድነኝ . ይላል ባለ ብሩህ አእምሮው ደራሲ በዓሉ ግርማ . ከኢህአዴግ ቤት በመተጣጠፍ ስልት ሰተት ብሎ ወደ አንድነት ም / ቤት የገባው አክሮባቲስቱ ሀብታሙ አያሌው እና ግብረ አበሮቹ በአፋቸው ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ እያሉ በተግባራቸው ግን የታጋዩንና የህዝቡን ስሜት ለማቀዝቀዝ ሲታትሩ እንመለከታቸዋለን . ለመሆኑ ሀብታሙና መሰሎቹ ስለ ኢትዮጵያ የመናገር ሞራል አላቸው ? ራሳቸውን የታጋይ ቁንጮ አድርገው የሚቆጥሩት በምን መስፈርት ነው ? እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን አንባቢ የሚፈርዳቸው ሆኖ አቶ ሀብታሙ በላይፍ መጽሄት ላይ ወደ ቀባጠራቸው ጉዳዮች እንለፍ .

  ከኢህአዴግ ፓርቲ ስለለቀቀበት መንገድ ሀብታሙ ከኢህአዴግ ፓርቲ የለቀቀበትን መንገድ ሲያብራራ « ኢህአዴግ ቤት እያለሁ ወፍራም ደመወዝ ነበረኝ መኪና ተመድቦልኝ የተለያዩ አበሎች ይከፈለኝ ነበር ....... » ነገር ግን ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች ያዘጋጀውን ጽዋ መጠጣት ለእኔ ክብር እንደሆነ በማሰቤ በቃኝ ለማለት አልተቸገርኩም ይለናል . ከኢህአዴግ ጋር ፍች የፈጸመበትን ምክንያት በሀብታሙ አንደበት ሲገልጽ አንባቢን ያማልላል . ይቀጥልና ኢህአዴግ ቤት ሀሳብ መሸጥ ስለማይቻል ወጥቻሁ ይለናል . አባባሉ እውነት ነው ኢህአዴግ ቤት ህሊና እንጅ ሀሳብ አይሸጥም . እውነተኛው የአወጣጡ ምክንያት ይህ ነው ? የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም . ይህ ከነበረስ ኢህአዴግን ከለቀቀበት 2002 ዓም ጀምሮ አንድነት እስከገባበት 2005 ዓም ድረስ የት ነበር ? ስለዚህ ጉዳይ በተለያዩ ቃለ መጠይቆች ሀብታሙ አያነሳልንም . መቸም እንደ እየሡስ ክርስቶስ ገዳም ገብቶ የሚል የዋህ አይኖርም . በቅርብ የሚያውቁት ምክንያቱን ሲገልጹ ከአስካሉካ ትሬዲንግ ጋር በተያያዘ በተፈጠረው ውዝግብ የድርጅቱ ባለቤት በስደት ወደ ጀርመን ሀገር ሲያቀና ሀብታሙ በበኩሉ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሄደ ነው .

  ለመሆኑ የተቃዋሚዎችን ጽዋ ለመጨለጥ የቆረጠ ሰው ደቡብ አፍሪካ ምን ወሰደው ? አንዳንዶች በደቡብ አፍሪካው የአለም ዋንጫ ሰዎችን ወደ ደቡብ አፍሪካ እልካችኋለሁ እያለ በወገኖቻችን ላይ የተለያየ ግፍ ሲፈጽም ከነበረው አቶ ግርማይ ብርሀኔ ጋር ንክኪ የነበረው ሀብታሙ የተነሳው የተቃውሞ ወጀብና የተዘረፍን ለቅሶ ሁለቱንም ለስደት ዳርጓቸዋል በሚል ይስማማሉ . ለዚህም እንደመከራከሪያ የሚያቀርቡት አቶ ግርማይ ብርሀኔ ከጀርመን ተይዞ ሲመጣ ሀብታሙ የመከላከያ ምስክር ሆኖ መቅረቡን ነው . ድንቄም የጠቃዋሚን ጽዋ መጨለጥ ¡ ¡ ¡ ከዚህ ሁሉ በኋላ በሀገር ወዳድ ወጣቶች የተመሰረተውን ባለራዕይ ወጣቶች ማህበርን በአቦሸማኔ ፍጥነት ወደ አንድነት ብሄራዊ ምክር ቤት ለማሳለጥ ተጠቅሞበታል . ወደ አንድነት ም / ቤት ከመግባቱ እና የፈረመበት ብዕር ሳይደርቅ የተለመደውን እንካ ስላንትያ ዲስኩሩን ከፓርቲው እውቅና ውጭ ከመድረክ አመራሮች . ጋር በመሆን ጀመረ ዘመናቸውን በሙሉ ለሀገር ሲታገሉ የኖሩ አዛውንት ምሁራንን በአላዋቂ ብዕሩ ያበሻቅጣቸው ገባ መድረክ መፍረስ አለባት ; . መድረክ የፓርቲዎች ሳይሆን እንደ አፍሪካ ህብረት የመሪዎች ስብስብ ነው , የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ከአንድነት የወጡት አቅም ስላልነበራቸው ነው , ወዘተ የሚሉ አፍራሽ ንግግሮችን ከአንድነት ፓርቲ እውቅናና ፈቃድ ውጭ ሲናገር እውነት ይህ ሰው ከኢህአዴግ ለቆ ወጥቷል ? ያስብላል .

 በዚህ ንግግሩም የመድረክ ከፍተኛ አመራሮች ከኢህአዴግ ወደ መድረክ የተላከ ሰርጎ - . . ገብ መሆኑን ይስማማሉ አንድነት ከመድረክ መውጣት አለበት , መድረክ በአስቸኳይ ይፍረስ , ምናምን የሚሉትን የፓርቲውን ሊቀመንበር ጨምሮ የአንድነት አባላትና አመራሮች አይስማሙበትም ከዚህ በመቀጠል መድረክን የማፍረስ ተልዕኮ አልሳካ ሲል ሰማያዊ አልዋሀድም አለ ሲል ዘለፋ ጀመረ ለመሆኑ ትናንት ስለመፍረስ ባወራበት አንደበት ዛሬ ስለ መዋሀድ የማውራት ሞራል ከየት አገኘ ( ከዚያው ከላኩህ ሰዎች ካልሆነ ) . እንግዲህ ይህ ሰው ነው ኢህአዴዴግ ቤት ሀሳብ መሸጥ አይቻልም የሚለን . ስልብ አሽከር በጌታው እቃ ይኮራል . በጌቶቹ ሀሳብ እንጅ በራሱ ላለመመራቱ አንዱ ማሳያ ይህ እንፍረስ እንዋሀድ ዝባዝንኬው ነው . ሌላው በዚሁ መጽሄት ላይ ሀብሙ እንዳለው " የራስን ገጽታ ለመገንባት የሌሎችን መልክ ማቆሸሽ " የሚለው አባባል በአግባቡ ሊገልጸው የሚችለው ኢንጅነር ይልቃል ጌትነትን ወይስ አቶ ሀብታሙን ? መልሱን አንባቢ ይፍረድ . ለምሳሌ መጋቢት 8/2005 ዓም ግራዚያኒን ለመቃዎም የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ያነሳሱት አቶ ታዲዎስ ታንቱ ናቸው . ለዚህም ተገቢ አክብሮት ሊቸራቸው የሚገባ ቢሆንም ሌሎች መድረኩን በመቆጣጠር የማይገባቸውን ውዳሴ ለመሸመት ተጠቅመውበታል ሲል ሰማያዊ ፓርቲን ይከሳል . ለመሆኑ በዚህ ሰልፍ የማይገባውን ውዳሴ የሸመተው አቶ ሀብታሙ ወይስ ሰማያዊ ፓርቲ ? መቸም ሀብታሙ ሰማያዊ ፓርቲ ያደረገውን አስተዋጽኦ ረስቶት ከሆነ ደግሜ ላስታውሰው እወዳለሁ . የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ሰልፉን ለማሳካት ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ቁርጠኛ ከመሆናቸው በላይ የሚያፈልገውን ሙሉ ወጭ / የቲሸርት , የህትመት ጨምሮ / , መኪና , ጀነሬተርና ሞንታርቦ በመከራየት ያደረጉትን ክብር ያለው ስራ ልንክደው አንችልም . ሌላው ደግሞ በሰልፉ ዋዜማ ለቅስቀሳ የወጡትን የፓርቲውን አባላትና የማህበሩን አመራሮች በቁጥጥር ስር ሲውሉ የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች እኛንም እሰሩን በማለት ፖሊስ ጣቢያ ገብተው አንወጣም በማለታቸው ለእስርና ድብደባ መጋለጣቸውን ሀብታሙ አልሰማም እንዴ ? በጣም የሚያስገርመው በሰልፉ እለትም የፓርቲውን ሊቀመንበር ኢ / ር ይልቃል ጌትነትን ጨምሮ እነ ዶ / ር ያዕቆብ ኃ / ማርያም , አቶ ታዲዎስ ታንቱ ; እንዲሁም ከ 40 በላይ ወጣቶች ሲታፈሱ የጸጥታ ሀይሎች ሀብታሙን እንድንይዝ አልታዘዝንም ብለው በግልጽ መናገረቸው ኢህአዴግ የሀብታሙ መታሰር ከእነዚህ ሰዎች በላይ ኪሳራ ውስጥ የሚጥለው ሆኖ ወይስ የሚሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በሀብታሙ ፊታውራሪነት እንዲመራ ተፈልጎ ? ይህ ሁሉ ሆኖ ታዲያ ዛሬ ሌሎች ተጠቅመውበታልን ምን አመጣው ? ሰው ተጠቀመበት የሚለው ሂሳብ ይወራረድ ቢባል እንኳን የሀብታሙን ያክል ውዳሴ ለመሸመት የተሯሯጠና የደከመ የለም .

  ከ 1997 በኃላ ባለው የተቃውሞ ጎራ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ያክል ሰፊ መሰረት እና አደረጃጀት ያለው ፓርቲ አልተፈጠረም ብየ አምናለሁ . ለአንድነት ፓርቲ ነባር አባሎችና አመራሮች ብሎም አሁን እያደረገ ላለው እንቅስቃሴ ተገቢውን ክብር እሰጣለሁ . ነገር ግን አንድነት ገርበብ አድርጎ የከፈተውን በሩን በደንብ ካልዘጋ ወይም ጠንካራ ጥበቃ ካልቀጠረ ባጭር ጊዜ ውስጥ ወጣ ወጣና እንደ ሸንበቆ .............. ! እንዳይሆን ስጋት አለኝ . እስከ መቼ ድረስስ ነው አንድነት የኢህአዴግ ካድሬዎችን አመራር እያደረገ የሚቀጥለው . ለዚህ መከራከሪያ ደግሞ የፓርቲውን ሊቀመንበር ጨምሮ , ስየ አብርሀ , ሀብታሙና ጓደኞቹ እንዲሁም የአቋም አልባ መገለጫ የኢንጅነር ግዛቸው ሽፈራው መውጣትና መግባት የአንድነትን ነባር አባሎችና አመራሮች ያስኮርፋልና ቢታሰብበት እላለሁ . ባጠቃላይ ቆራትና ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ የሆኑ አባሎች የሞሉበትን አንድነት ከተቀላቀለ አጭር ጊዜ የሆነው / የፈረመበት ቀለም ያልደረቀው / ሀብታሙ ኢህአዴግ ባስታጠቀው የሴራ ፖለቲካ ከኔ በላይ ተቆርቋሪ የለም በሚል አስመሳይነት ከፓርቲው ነባር አባላት በላይ አድራጊ ፈጣሪ ሆኖ ፓርቲውን ወደ አዘቅት ለመክተት ሲጣደፍ ሲታይ , ለፓርቲው የመሪነት መስፈርት ከኢህአዴግ ቤት መምጣት ብቻ ይሆን እንዴ . ወይም የፓርቲው ነባር አባላት ለአመራርነት አይመጥኑም ? ያስብላል .

  ሌላው ሊተኮርበት የሚገባው የሀብታሙ ሴራ በቀጣይ የአንድነት የአመራር ምርጫ ቁልፍ ቁልፍ ቦታዎችን በእርሱና በጓደኞቹ ካልተያዙና ሽማግሌዎች / በእርሱ አገላለጽ / ገለል ካላሉ ፓርቲውን የመሰንጠቅና ሌላ ፓርቲ የማቋቋም አላማው እንዳለው ነው . ለዚህ አላማው ማስፈጸሚያ በዙሪያው የሚሰበስባቸው ጭፍራዎቹ ከፍተኛ ድርሻ ይኖራቸዋል የሚል ግምት አለኝ . እየሱስ ክርስቶስ በምድር ሲመላለስ ሌጊዎን የተባለውን የሰይጣን ጨፍራ ከሰውየው ላይ ወጥቶ ወደ እሪያዎቹ / አሳማዎቹ / እንዲገባ እንደገሰሰው ሁሉ ሀብታሙና መሰሎቹን ሌጊዎን ሆይ ከአንድነት ቤት ውጡና ወደ ዘመዶቻችሁ ግቡ እላለሁ . ይሁንና ግለሰቡ በቅርቡ ማንነቱ ተጋልጦ በአደባባይ እርቃኑን እንደሚቀር አልጠራጠርም . እስከዚያው ድረስ የክቡር ዶ / ር ጥላሁን ገሰሰን እንክርዳድ እንክርዳድ የተንከረደደ ስንዴ መስሎ ገብቶ ስንቱን አሳበደ . የሚለውን ዘፈን ጋብዘነው ብንለያይስ ?

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ! !

No comments: