Saturday, December 21, 2013

በ ‹‹በመለስ ራዕይ ተቃዋሚን ዜሮ እናስገባለን›› የሚል ዘመቻ ተጀምሯል

December 21/2013

 የአቶ መለስ ዜናዊን ራዕይ ለማስቀጠል ተቃዋሚዎችን ዜሮ እናስገባለን የሚል ቅስቀሳ በጎንደር የኢህአዴግ ካድሬዎች መጀመራቸውን ተከትሎ ተቃዋሚዎችን እንደሚደግፉ በሚገመቱና በጎንደር የአንድነት አባላት ላይ ማስፈራሪያ፣ውክቢያና ዛቻ እየተፈጸመ ነው፡፡ በመለስ ራዕይ ሰበብ ከገዢው ፓርቲ የተለየ አመለካከት በሚያራምዱ ዜጎች ላይ ቅስቀሳ መጀመሩና ይህንኑ ተከትሎም አደጋ እያንዣበባቸው እንደሚገኝ በጎንደር የሚገኙ የአንድነት አባላቶች አስታውቀዋል፡፡ ተቃዋሚዎችን ዜሮ ማስገባት የሚለው ዘመቻው ከተቻለ በፈቃደኝነት ተቃዋሚዎቹ ኢህአዴግን መቃወም እንዲያቆሙ ካልሆነ ግን ጫና በመፍጠር እንቅስቃሴያቸውን ማኮላሸት ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ ታውቋል፡፡በ2002 ምርጫ 545 ወንበር ማግኘቱን ያወጀው ኢህአዴግ አውራ ፓርቲ ነኝ ማለቱን ተከትሎ ዳዴ ማለት የተሳነው የመድብለ ፓርቲ የፖለቲካ ስርዓት በከፋ ሁኔታ ውስጥ ይገኛል፡፡



በምኒልክ ሳልሳዊ

No comments: