Friday, March 14, 2014

ግብጽ ጦሯን በደቡብ ሱዳን ልታሰፍር ነው::

march13/2014
ለሰላም ማስከበር ይሁን በቅርብ ርቀት ኢትዮጵያን ለመውጋት ውሉ አለየለትም::



 የግብጽ እና የደቡብ ሱዳን ውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተገናኝተው ግብጽ በአየር እና በምድር የታጠቀ ጦሯን በደቡብ ሱዳን እንድታሰፍር መስማማታቸው የተሰማ ሲሆን ይህ ጉዳይ ኢትዮጵያን የሚያሳስባት ሲሆን ኢትዮጵያን እና የህዝቧን ሉዋላዊነት እና ደህንነት ደቡብ ሱዳን አደጋ ላይ ለመጣል ያሴረችው ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል::

በማርች 2014 መጨረሻ ድረስ ግብጽ በጦር ልምምድ ስም የኢትዮጵያን የግድብ ስራዎች ሂደት ለመቃኘት እና አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ታስቦ ሊሆን ይችላል ሲሉ ፍራቻቸውን የገለጹት አስተያየት ሰጪዎች ግብጽ ኢትዮጵያን ለመውረር ውይንም ለማስፈራራት ያደረገችው አዲስ እቅድ መሆኑን ሲገልጹ ደቡብ ሱዳን የኢሕኣዴግ መንግስት የሳልቫ ኬርን ተቃዋሚዎች ይረዳል በሚል ስለምታስብ ግብጽን ኢትዮጵያን ለማስደንገጥ ልትጠቀምባት ሊሆን ይችላል ሲሉ ገምተዋል::

እስካሁን በዚህ ጉዳይ አስተያየት ያልሰጠው የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት ምን አይነት እርምጃ ሊወስድ ይችላል የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ነው:: የኢሕኣዴግ መንግስት በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የውጪ መንግስታት የሚያራምዱትን ፖሊሲ በቸልተኝነት የሚመለከት ሲሆን አሁን ግብጽ በደቡብ ሱዳን ልታደርግ ያቀደችውን የጦር ሰፈራ ግን እንዴት ሊመለከተው ይችል ይሆናል የሚሉ ወገኖች በርክተዋል::ምንሊክ ሳልሳዊ

የግብጽ መንግስት በሶስት ቡድን ከፍሎ የሚያሰፍራቸው የጦር ሰራዊቱ አብዛኛውን በምስራቅ የደቡብ ሱዳን አማካጭ የስትራቴጂ አከባቢዎች ለ አማራው ክልል ይቀርባልኡ ተብለው በሚገመቱ ቦታዎች ሲሆን በዚህ በሚሰፍረው ጦር ውስጥ ከጦር አይሮፕላኖሽ ጀምሮ ሚሳኤሎች እና ታንኮች በተጨማሪም ወታደራዊ ኮማንዶዎች እንዲሁም ከፍተኛ ወታደራዊ ደህንነቶንች እና እግረኛ ወታደሮች ይጠቃለላሉ::ምንሊክ ሳልሳዊ

በዚህ ጉዳይ ላይ እስካሁን የኢሕኣዴግ መራሹ መንግስት የተናገረው ነገር የለም::


No comments: