Saturday, October 4, 2014

በወያኔ አገዛዝ ባለስልጣናት ላይ በኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የሚወሰደው እርምጃ አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።

Oktober3,2014
በመተማ ወረዳ ገንዳ ውሃ ከተማ አንድ የአገዛዙ ባለሥልጣን የተገደለ ሲሆን አንዱ ደግሞ ክፉኛ ቆስሏል።

የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ መዋቅር አካል በመሆን ሕዝብን ኢ-ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ሲያስሩ፣ ሲደበድቡና ሲገድሉ የኖሩትን ሹማምንቶች ከዚህ እኩይ ተግባራቸው ለማስቆም በተጀመረው እንቅስቃሴ፣ በምክር አልመለስ ያሉት ላይ እርምጃ የመውሰድ ሰፊ ዘመቻ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል። የዚህ ዘመቻ ዋና አስፈፃሚ የሆኑት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የውስጥ አርበኞች /ህቡዕ አባላት/ ሰሞኑን በወያኔ ቅጥረኞች ላይ ያነጣጠረ ተከታታይ ጥቃቶችን በመሰንዘር አስተማሪ እርምጃዎች መወሰዳቸው ይታወሳል።

ይህ በውስጥ አርበኞች የተጀመረው ዘመቻ ተጠናክሮ በመቀጠል ማክሰኞ መስከረም 22 ቀን 2007 ዓ/ም በመተማ ወረዳ ገንዳ-ውሃ ከተማ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ላይ በተወሰደው እርምጃ ሁለት የወያኔ አገዛዝ ባለሥልጣናት የጥቃቱ ሰለባ የሆኑ ሲሆን፤ በጥቃቱም የወረዳው ፖሊስ ኢንስፔክተር ዮሃንስ ይግዛው ሲገደል፣ ኮንስታብል ሻንበል አበበ በጥይት ተመቶ ክፉኛ ቆስሏል።

በዚህ የማጥቃት እርምጃ መደሰታቸውን የገለጹት የገንዳ-ውሃ ከተማ ነዋሪዎች እነዚህ እርምጃ የተወሰደባቸው ባለሥልጣናት፣ ሥልጣናቸውን ተገን በማድረግ ሕዝቡ ላይ ሲያደርሱ የነበረውን በደልና ግፍ በምሬት የገለጹ ሲሆን ሕዝብን በሚበድሉ የወያኔ ባለሥልጣናት ላይ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ እንደሚደግፉና በማንኛውም መልኩ ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ጎን እንደሚቆሙ ተናግረዋል።
ሀገርንና ወገንን እያጠፋ ካለ አምባገነን አገዛዝ ጋር ማበር ውጤቱ ሰሞኑን እየተወሰደ ያለው እርምጃ መሆኑን በመረዳት የወያኔ ሆድ አደር ባለሥልጣናት ከእኩይ ተግባራቸው ካልተቆጠቡ የተጀመረው የማጥቃት ዘመቻ ሰለባ እንደሚሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በጥብቅ ያሳስባል።
http://www.arbegnochginbar.org/index.php?option=com_content&view=article&id=806%3A2014-10-03-22-12-14&catid=41%3Anews&Itemid=50

No comments: