Monday, October 20, 2014

የአዲሱ ወጣት የአንድነት መሪ፣ በላይ ፍቃዱ ቃለ ምልልስ

October 20,2014
Belay Fekadu
አቶ በላይ ፍቃዱ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዘዳንት
“ማር እንኳን 23 አመትት ቢላስ ይመራል ። 23 አመት እንደ ኢሕአዴግ ላለ ፓርቲ እጅግ በጣም ረጅም አመት ነው”
“ሕዝቡ ለዉጥ ይፈልጋል። በዚህ ላይ ምንም አነት ጥርጣሬ የለም፡፡በመላው ኢትዮጵያ ሲኬድ ይሄን አይነትት ስሜት አለ”
“ትልቁ ነገር አማራጭ ሆኖ ሕብረተ ሰቡ ተስፋ ሊይደርገው የሚችል ፓርቲ ሆኖ መዉጣት የውወቅቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ይመስልኛል”
“አንድነት የሁሉም ኢትዮጵያዊያኖች ቤትና ፓርቲ እንዲሆን ለመስራት ከፍተኛ ትጋት እናደርጋለን። በፕሮግራም በደንብ ደረጃያአንድነት ከሁሉም ፓርቲ በሚለይ መንግድ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያኖች በሚያቅፍ ሁኔታ የተዋቀረ ነው። በአሰራርና ቶበአካሄድ አንዳንድ ክፍተቶች አሉብን ፣ ስለዚህ እነዚህ ክፍተቶችን የመሙላትና፣ በቀን ተቀን ስራዉ ሁሉም ኢትዮጵያዉያኖችን ማቅቀፍ የሚችል መሆኑን ማሳየት አለብን።”
ከላይ የተጠቀሱት ፣ አቶ በላይ ፍቃደ፣ አዲሱ ወጣት የአንድነት ፓርቲ ፕሬዘዳንት፣ ዛሬ ጥቅምት 9 ቀን ለአንድነት ራዲዮ ከተናገሩት የተወስደ ነው።
አቶ በላይ ለመረጧቸዉና ለደገፏቸው ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ከርሳቸው የተሻለ ሌሎች አሉ ብለው ሌሎችን ለደገፉ ከፍተኛ ክብርርና አድናቆት እንዳላቸው የገለጹት ሲሆን፣ አሁን ግን የመሰባሰብና የስራ ጊዜ እንደሆነም አስረድተዋል።
የተቃዋሚዎች መዳከምና አማራጭ ሆኖ አለመገኘት ለኢሕአዴግ መቆየት ምክንያት እንደሆነ የሚናገሩት አቶ በላይከሌሎች ድርጅቶች ጋር አብረዉ እንደሚሰሩ፣ ከወዲሁ ንግግሮች እንደትጀመረና ሁኔታው በሂደት እንደሚገለጽ ሳይጠቁሙ አላለፉም።
“ኑና አብረን እንስራ” ሲሉ፣ በአገር ውስጥና ከአገር ዉጭ ላሉ ኢትዮጵያዉያን መልእክታቸውን ያጠናቀቁት አቶ በላይ፣ ትግሉ የጥቁቶች ሳይሆን የሚሊዮኖች እንደመሆኑ፣ ሁሉም ዜጋ ትግሉን እንንዲሳተፍና እንዲተባበር ተማጽኖ አቅርበዋል።

No comments: