Thursday, October 2, 2014

በጋምቤላ ክልል የተፈናቀሉ እና ከዘር ማጥፋቱ የተረፉ አማሮች ወደ መኢአድ ቢሮ መጡ!

Oktober2,2014
በፋሽሽቱ ወያኔ ከጋምቤላ ክልል በግፍ የተፈናቀሉ እና ከዘር ማጥፋት ወንጀል የተረፉት አማሮች ወደ መኢአድ ጽ/ቤት መጥተዋል፡፡
በጋምቤላ ክልል ሜጢ ከተማ ጎሽኔ ቀበሌ አቶ በለጠ ጌታቸው ጎጃም ቢቸና አካባቢ የመጡ የግራ እጃቸውን በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ 

በዚሁ ቀበሌ ከወሎ መካነሰላም ቦረና አካባቢ የመጡ አቶ ገበየሁ ኮስትር በጀርባቸው በኩል በከፍተኛ ሁኔታ በጥይት ከተመቱ በኋላ ጥይቱ በሰውነታቸው ውስጥ ይገኛል፡፡ በአካባቢው በተደረገላቸው ህክምና ጥይቱን ማውጣት ስላልተቻለ በከፋ ስቃይ ውስጥ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ቤተሰቦቻቸው ይሙቱ ይዳኑ ምንም አይነት መረጃ ባለማግኘታቸው በጭንቀት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ ወ/ሮ ጀምበሬ ኮስትር፣ወ/ሮ ሳዓዳ ተፈራ፣ ወ/ሮ ኮከቤ ኮስትር ከእነ ህፃን ልጆቻቸው በባሰ ችግር ውስጥ ሆነው ወደ መኢአድ ጽ/ቤት በመምጣት በሰቀቀን ችግራቸውን ተናግረዋል፡፡

ተፈናቃዮችና ከዘር ማጥፋት የተረፉት፤ እኛስ ከእነ ችግሩም ቢሆን የተወሰነ ድጋፍ አግኝተናል፡፡ ከዚያው የቀሩት ወንድሞቻችን ጉዳይ በእጅጉ ያሳስበናል ካሉ በኋላ ለእኛም ሆነ ለወንድሞቻችን የኢትዮጵያ ህዝብ በአሰቸኳይ እንዲደርስልን ሲሉ ተማጽነዋል፡፡
ተስፋሁን አለምነህ
LikeLike ·  · 

No comments: