Tuesday, February 4, 2014

ህግ እና ስርኣት ለባለስልጣናት የሚገዛበት አገር ..

Feb.4/2014
በሃገሪቱ የተፈጠሩ ስብርባሪ ህወሓት መራሽ መንግስታት የህዝቦችን የመኖር መብት ደፍጥጠዋል::
 ባለስልጣናት ለህግ እና ለስርኣት ተገዢ አለመሆናቸው ህግና ስርኣት ለእነሱ ተገዢ እንዲሆን ማድረጋቸው ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ነው;: የህግን የበላይነት ማረጋገጥ የተሳነው ስርኣት የወለዳቸው ስብርባሪ ህወሓት መራሽ መንግስታት የህዝቦችን የመኖር መብት ደፍጥጠዋል::በሃገራችን ውስጥ ላለፉት 22 አመታት ተንሰራፍቶ ያለው የአንድ ፓርቲ ህገወጥ አገዛዝ ለህዝቦች ነጻነት የሚከፈለውን መስእዋትነት እንደ መንግስት ሳይከፍል ህዝብን በማሸበር እና በማወናበድ የህግ የበላይነትን ደፍጥጦ ለስልጣኑ ብቻ እየተራወጠ ይገኛል::በሃገሪቱ የህግ የበላይነት የተከበረ ጊዜ ስልታንህ ያበቃል የተባለ ይመስል ከበላይ ባለስልጣናት ጀምሮ እስከ በታች ካድሬዎች ድረስ የህግን የበላይነት ክደዋል:: ማንም ማንንም ማዘዝ በማይችልበት እና የተሰባበሩ ትንንሽ በንግስታት በራሳቸው ሂደት የተፈጠሩባት ኢትዮጵያ ባለስልጣናቱ መናበብ አለመቻላቸው ህዝቡ በፍትህ ላይ ተስፋ ከቆረጠ ውሎ አደረ አድሮም ኖረ::
የአንድ ሃገር ህግ የህዝብን ትኩሳት እና ጥያቄዎች ይዞ መጓዝ ሲኖርበት በሃገራችን ግን የህግ የበላይነትን የፖለቲካ ትኩሳቶች እያሽመደመዱት እንዳይከበር እና እንዲደፈጠጥ እያደረጉት ይገኛሉ:; አንድ ህዝብ ባላረቀቀው እና ባላጸደቀው ህግ ሲገዛ የህግን ትርጉም እንደማያውቅ ታሳቢ አድርጎ በህዝብ ነጻነት ላይ የሚደረጉ የፖለቲካ ጨዋታዎች እንኳን በበሰለው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ይቅር እና በሌላውም ባልሰለጠነ ህዝብ ላይ ሊተገበር መድፈር ራስን እንደመናቅ ይቆጠራል:: ወያኔ ራሱ አርቅቆ እና አጽድቆ ህጎችን በማውጣት ከፈለገም በመሻር በመቀየር በመገለባበጥ በመተርጎም ህዝቦች የራሳቸውን መብት እና ነጻነት እንዳያገኙ በከፍተኛ ደረጃ መሸራረፎችን እየፈጠረ ነው::ምንሊክ ሳልሳዊ
ባለስልጣናት የወንበር ግዝፈታቸውን ተጠቅመው የተለያዩ ውሳኔዎችን ትእዛዞችን ተግባራትን በስልክ በደብዳቤ በቀላጤ ወዘተ የህግን ስርኣት ባልተከተለ መልኩ እያሽከረከሩት ከህግ የበላይነት ላይ በድንፋታና በትእቢት በመጓዝ ላይ ሲሆኑ ይህንን ያየ የበታች ካድሬ እንዲሁ ህግን እና ስራትን ባልትየከተለ መንግድ የህዝቦችን ህልውና ገደል ከቶታል:: ከበላይ ባለስልጣናት ባልተናነሰ እንዲሁም በበለጠ ማለት ይቻላል የወያኔ ካድሬዎች እና ተባባሪዎቻቸው በአገሪቱ ላይ ስርኣት አልበኝነት እና ህገወጥነት እንዲሰፍን እየሰሩ ነው::ይህ ደግሞ ህዝብ በስርኣቱ ላይ ተስፋ እንዲቆርጥ አድርጎታል::
በከፍተኛ ደረጃ ህግን እየበረዙ አድርገው በሙስና የተዘፈቁ የወያኔ ባለስልጣናት እና ደጋፊ ታዛዥ ካድሬዎቻቸው በሃገሪቱ ራሳቸው ያወጡትን ህግ ራሳቸው እየጣሱ የሚገኙ ሲሆን በራሳቸው ህግ ራሳቸው እንደሚጠየቁበት እየዘነጉ መሆኑን አለማወቃቸው ለህዝብ ያላቸውን ንቀት ያመለክታል::የምናነበው ሕጉና የምንመለከተው ተግባሩ የተለያየ ነው፡፡በሙስና ከተዘፈቁበት አንዱ የመሬት እደላ እና አሰጣጥ ነው መሬትን በተመለከተ ህጉ የሚለውን የሚከተል ባለስልጣን ማግኘት አስቸጋሪ ነው ህጉን የሚያስፈጽም ካድሬ ሹመኛም ማግኘት አይታሰብም::ይህ ማለት ደሞ ሁሉም ከመሬት እደላ ጋር በተያያዘ ህጉን ተከትለው የሚሰሩት ሳይሆን የግለሰቡ ብሄር እና የፋይናንስ አቅም ተመልክተው ይፈጽሙለታል:; ለእውነት እና ለሃገር የሚሰራ ኢንቨስተር ከአከባቢው ይነቀላል ሌባው እና ሙሰኛው ኢንቨስተር በአደባባይ በመንግስት ባለስልጣናት እንክብካቤ ይደረግለታል አፋሽ አጎንባሽ ካድሬዎችን ይበዙለታል::
የህግ የበላይነት በሃገሪቱ አለመስፈኑ ኢኮኖሚውን ከማንኮታኮቱም በላይ ባለስልታናት በዝርፊያ እና በሽሽት ላይ እንዲያተኩሩ አድርጓቸዋል::ህዝቡም ይህን ተከትሎ እንዲሁም በፖሊሶች በደህንነት አባላት በቅጥረኛ የመንግስት አሸባሪዎች በጥቂት የከተማ ወታደራዊ ኮማንዶዎች ህግ ሲጣስ እየተመለከተ ስለሆነ አንድም መንፈሱ ሲጎዳ ሌላም አለው ስርኣት ላይ አመኔታ በማጣቱ ድምጹን እንዲቋጥር አስገድዶታል::በሃገሪቱ የፍትህ አካላት ላይ የመንግስት ባለስልጣናት ጣልቃ ገብነት የፖለቲካ የበላይነት መከሰቱ ህዝቦች አንገታቸውን በፍትህ አካላት ፊት እንዲሰብሩ እንዲሸማቀቁ አድርጎታል::
በየመንግስት ተቋማት፣ ከሚኒስቴር ጀምሮ እስከ ተራ የቀበሌ ካድሬ ቢሮ ጠረጴዛ፣ በፍርድ ቤቶች እና በፍትህ አካላት ፍትሕ የተነፈጉ፣ ሕገ መንግሥትና ሥርዓት እንዲከበር የሚጠይቁና አቤት የሚሉ በርካታ መዝገቦች ሰሚ ጆሮ አጥተዋል፡፡ ለሕግና ለሥርዓት ቅድሚያ የሚሰጥ አዕምሮ፣ ጆሮና ዓይን ተነፍገዋል፡፡ ልዩ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል፡፡ ምንሊክ ሳልሳዊ ሕገ መንግሥቱና ሕግ ያስገድዳሉ፡፡ቢሆንም ምንም አይነት መልስ ሲሰጣቸው ይሁን ሲገመገሙ ታይቶ አይታወቅም በተዋረድ የመንግስት አሰራር አለመኖር በስልክ እና በቀላጤ ህግ እየተጣሰ ከህዝብ በሚሰበሰብ ግብር የሚተዳደሩት ፖሊስ እና የፍትህ አካላት በግለሰቦች ትእዛዝ ህዝባዊ ሂደቶችን ሲያመክኑ ህግን ሲጥሱ ህገወጥ እርምጃዎች ሲፈጸሙ ከህግ ውጭ የህዝቦችን መብት ሲደፍሩ እየታየ መንግስት ነኝ የሚለው አካል ዝምታን መርጧል::ይህ ደግሞ የሚያመለክተው በሃገሪቱ ውስጥ ስብርባሪ ትንንሽ መንግስታት መፈጠራቸውን ነው::ባለስልጣናት ለህግ እና ለስርኣት ተገዢ አለመሆናቸው ህግና ስርኣት ለእነሱ ተገዢ እንዲሆን ማድረጋቸው ጸሃይ የሞቀው ሃቅ ነው;: እነዚህ ስርኣቱ የወለዳቸውን ባለስልጣናት እና ካድሬዎች ከኢትዮጵያ ምድር ወደ ከርሰ መቃብራቸው ከቶ ህዝብን ለነጻነት ለማብቃት በጋራ መታገል ግዴታችን መሆኑን አውቀን በአንድነት ስርኣቱን ማስወገድ ማንኛውም ሃገሬን እወዳለሁ የሚል ዜጋ ሊነሳለት እና ሊተገብረው የሚገባ መሆኑን ለማስገንዘብ እወዳለሁ::ምንሊክ ሳልሳዊ

No comments: