Saturday, February 22, 2014

[የረዳት አብራሪው ጉዳይ] ሕዝብን አፍኖ እና ረግጦ በመግዛት የስልጣን እድሜን ማራዘም አይቻልም (በገዛኸኝ አበበ ኖርዌይ)

February22/2014

ዘረኛው እና  አምባገነኑ የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ወደስልጣን ወንበር በሀይል ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያን ሕዝብ አፍኖና ረግጦ መግዛትን ተያይዞታል:: በአሁኑ ጊዜ ወያኔ የሚያራምደው በዘረኝነት የተሞላው የተሳሳተ እና የተወላገደ ፖለቲካ ሕዝቡን ከማማርር ባለፈ የኑሮ ውድነቱ፣ ስራ አጥነቱ፣ እና በሀገሪቷ ላይ ክፉኛ ወንጀል መበራከቱ እና  በየሁሉም መስሪያ ቤቶች ከቀን ወደ ቀን ሙስና፣ ሌብነትና አይን ያወጣ ዝርፊያ  እየጨመረ መምጣቱ  የኢትዮጵያ ህዝብ  የሰቋቋ እና የመከራን ኑሮ መኖርን ተያይዞታል::  ወያኔ እያራመደው ያለው በዘር የተሞላ ፖለቲካ አንዱን ዘር ከአንዱ ዘር በማበላለጥ እና በመከፋፈል አንዱን ዘር ከፍ ሌላውን ዘር ዝቅ በማድረግ ፣ እያወረደ እና እየናቀ ዜጓች በገዛ ሀገራቸው እና ምድራቸው ላይ በሰላም እና በነጻነት እንዳይኖሩ ይኼው የወያኔ መንግስት ሲፈልግ ነፍጠኛ፣ ጉርጠኛ፣ትምክህተኛ፣ ተገንጣይ፣አሸባሪ ወዘተ.....  በማለት ሕዝቦችን በማስፈራራት እና ነጻነትን በማሳጣት  በሀይል እና በጉልበት  አፍኖ  እየረገጠ በመግዛት ላይ ይገኛል::

በአሁኑ ወቅት ተማሪው ተምሮ ስራ ለማግኘት እና ለመቀጠር ሰራተኛውም በስራው ገበታው ላይ ለመቆየት እና ስራውን በነጻነት ለመስራት በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝ የታወቀ ሲሆን ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ጥራት በሌለው የወያኔ የትምህርት ፖሊሲ ከመንግስትም ሆነ ከግል ዩንቨርስቲ እና ኮሌጆች ብዙ ወጣት ተማሪዎች በሀገሪቷ ላይ ትምህርታቸውን ጨርሰው ቢመረቁም በስራ አጥነት እየተንከራተቱ የሚገኙ ዜጓች ቁጥራቸው ከቀን ወደቀን እየጨመረ መምጣቱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን  በአሁን ጊዜ በኢትዮጵያ አንድ ሰው የሆነ መስሪያ ቤት ውስጥም ሆነ ድርጅትውስጥ  ስራ ለማግኛት እና  ለመቀጠር የግድ የወያኔ ኢህአዲግ አባል መሆን የሚጠበቅበት ሲሆን በስራ ገበታም ላይ  ያሉ ሰዎች ቢሆንም እንኮነ በሚሰሩበት ቦታ የግድ የወያኔ አባል እስካልሆኑ ድረስ ነጻነት እንደሌላቸው ፣ ስራቸውንም በነጻነት መስራት እንደማይችሉ የተለያዩም ግፍ እና ጭቋናዎች እንደሚደርስባቸው የታወቀ ነው::

በቅርቡ መምህር አማኑኤል መንግስቱ የተባለ የማዝገበ ብርሀን አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ትምህርት ቤት መምህር የአንድነት አባል በመሆኑ በሚያስተምርበት ትምህርት ቤት የወያኔ ካድሬ በሆነ በትምህርት ቤቱ  አስተዳደር የተለያዩ ዛቻዎችና ማስጠንቀቂያዎች እየደረሱበት እንደሆነ እና ከስራም ሊባረር እንደሚችል የማስንጠቀቂያ ደብዳቤ ከትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር እንደደረሰው የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ መዘገቡን አስታውሳለው:: ይህን እንደምሳሌ አልኩኝ እንጂ በጣም ብዙ ዜጓች ናቸው በየሚሰሩበት መስሪያ ቤቶች በዘር በተበላሸ በወያኔ ፖለቲካ አመለካከት የኢህአዲግ አባል ባለመሆናቸው የሚጨቁኑት ነጻነታቸውን አተው በሀገራቸው ተሸማቀው በወያኔ ካድሬዎች ታፍነውነው እና ተረግጠው የሚኖሩት :: 

የወያኔ ባለስልጣናት ሊያውቁ የሚገባው ነገር ሕዝብን አፍኖ  እና ረግጦ  በመግዛት የስልጣን እድሜን ማራዘም እንደማይቻል ነው :: ዚህ በዚህ ሳምንት የተከሰተው እና የአለም መነጋገሪያ እየሆነ ያለው እና የብዙ አለማት ሚዲያን ቀልብ የገዛው የረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ የአውሮፕላን ጠለፋ ትምህርት ሊሆናቸው ይገባል :: ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ በእኔ አመለካከት ጀግና ነው ክብርም ይገበዋል :: ምንም እንኮን የሰራው ስራ የሚያስፈራ እና ዋጋ የሚያስከፍልም ቢሆንም በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው  የወያኔ የተበላሸ  የፖለቲካ አካሂድ  ምን ያክል የከፋ እንደሆነ ፣ የደህንነት ስጋት ፤የአስተዳደር ብልሹነት እና የዘረኝነት መድልዎን ከመቼውም ጊዜ የባሰ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ  ለአለም ሕዝብ ያመላከተበትን ጀብዱ ፈጽሞል:: ስለዚህ ፓይለት ሃይለመድህን አበራ በዘር ለተረገጦ ፣ ለተገፉ እና ለተጨቋኑ ኢትዮጵያኖች ድምጽ ሆኖል ነው የምለው ::


ፓይለት ሃይለመድህን አበራ አስቦ እና አቅዶ የተነሳበት ዋንኛው አላማ ይኼው ይመስለኛል::  የመንግስት ቃል አቀባይ ተብዪው አቶ ሬድዋን  ፓይለት ሃይለመድህን ሙሉ ጤነኛ ሰው እንደሆነ ለአምስት አመታት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪ ሆኖ እንዳገለገለ ፣ የሽንገን ቪዛ እንዳለው ፣ነጻ ትኪት እንደሚያገኝ እና የትም ሀገር ሂዶ ትምህርቱን መቀጠል እንደሚችል ነገር ግን ፓይለት ሃይለመድህን  ለእራሳቸውም እንደገረማቸው እና እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው ሲናገሩ ተደምጠዋል  በርግጥ ልክ ነው ወጣቱ ፓይለት ሃይለመድህን የትም ሀገር ሂዶ አሳይለም የመጠየቅ እድል (opportunity) ይኖረው ነበር  ብዙም ሰዎች በዚህ ጉዳይ ላይ የራሳቸውን ሀሳብ እየሰነዘሩ ሲሆን  በኢትዮጵያ አየር መንገድ በበረራ ደህንነት ስራ ውስጥ ለረጅም ጊዜ ያገለገለውና በክትትልና ደህንነት ስጋት ከአመት በፊት ድርጅቱን ለቆ በስዊዘርላንድ ጥገኝነት የጠየቀው አንድ የቀድሞው የድርጅቱ ሰራተኛ  አቶ ሚካኤል መላኩ የካፒቴን ሃይለመድህን አበራ የጠለፋ ምክንያት በአየር መንገዱ ውስጥ የሚታየውን የአስተዳደር መበላሸት ለአለም ለማሳየት ሊሆን ይችላል የሚለው ምክንያት አሳማኝ ነው ሲል ከኢሳት ጋር ባደረገው  ቃለምልልስ  የተናገረው ነገር ትክክል ነው ብዪ አምናለው::

ፓይለት ሃይለመድህን አበራ በድፍረት የተሞላ ጀብዶ መፈጸሙ የወያኔን ባለ ስልጣናቶች ያስደነገጠ፣ ያሳፈረ እና ያሸማቀቀ ተግባር ሲሆን  በወያኔ መንግስት በዘር፣በሀይማኖት ተገፍቶ እና ተጨቆኖ ላለው ምስኪኑ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ደስ የሚያሰኝ ተግባር ነው :: ምክንያቱም ህወሃት መራሹ መንግስት እያራመደ ባለው የዘረኝነት ፖለቲካ በሀገሪቱ ላይ ያላው የደህንነት ስጋት፣ አፈና እና ሰበሃዊ መብት ረገጣ ምን ያህል እየከፈ መምጣቱን ለአለም ሕዝብ ያመለከተበት ተግባር በመሆኑ:: ስለዚህ የወጣት ፓይለት ሃይለመድን ጀግንነት የተሞላበት ተግባር ወኔ እና ብርታት ሆኖን በወያኔ ታፍኖ እና ተረግጦ መገዛትን እንቢ በማለት እና የወያኔን በዘረኝነት የተሞላውን ፖለቲካ በመቃወም በአደባባይ በማውጣት ወያኔን በማስረበሽ እና በማስደንገጥ የስልጣን እድሜውን ማሳጠር የመላው ኢትዮጵያኖችን ነጻነት መወጅ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የዜግነት ግዲታ መሆን ይጠበቅበታል::

ፍትህና ነጻነት ለሚናፍቅ ኢትዮጵያዊ የማስተላልፈው መልህክት  ህወሃቶች ዜጎችን ከሰው በታች አድርገው ለመግዛት እንዲመኙ ያደረጋቸው በእብሪት የተሞላ የፖለቲካ አካሄድ የሚተነፍስበት ዘመን እሩቅ አይሆንምና አሁንም አትፍሩ።

  ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

gezapower@gmail.com

No comments: