Saturday, April 26, 2014

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ በሃይማትታችሁ ጣልቃ ለተገባባችሁ ኢትዮጵያውያን በሙሉ የተደረገ ጥሪ!

April 26, 2014
Ethiopia's Semayawi (Blue) party logoውድ ሃይማኖታችሁ ላይ ጣልቃ እየተገባባችሁ ያላችሁ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፡- ሰማያዊ ፓርቲ ኢትዮጵያውያን በነጻነት የፈለጉትን ሃይማኖት እንዲከተሉ፣ የፈለጉትን እምነት እንዲይዙ ባለው የጸና አቋም ገዥው ፓርቲ በሙስሊሙና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ላይ እያደረገ ያለውን ጣልቃ ገብነት ሲቃወም ቆይቷል፡፡ የሙስሊሙ ማህበረሰብ ገዥው ፓርቲ በሐይማኖቱ ጣልቃ መግባቱን ተቃውሞ የሚያደርገውን ፍጹም ሰላማዊ እንቅስቃሴ በማድነቅ ገዥው ፓርቲ ከህገ ወጥ ተግባሩ እጁን እንዲሰበስብ ምክር ከመለገስ አልፎ በሰላማዊ ሰልፍም ድምጹን አሰምቷል፡፡ በተጨማሪም የሙስሊሙን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የተወሰደው ህገ ወጥ እርምጃ እና በእስር ላይ እየደረሰባቸው ያለውን ስቃይም በጽኑ ሲቃወም ቆይቷል፡፡ ወደፊትም በዚሁ አቋሙ እንደሚቀጥል ይገልጻል፡፡
በተመሳሳይ በክርስቲያኖች በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ያለውን ጣልቃ ገብነትም በተመሳሳይ ሲቃወም ቆይቷል፡፡ ለአብነት ያህል በዋልድባ ገዳም ላይ የተወሰደውን ህገ ወጥ ተግባር በግልጽ ተቃውሟል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በተለይም በማህበረ ቅዱሳን ላይ ጫና እየተደረገ እንደሚገኝ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በማህበሩ ላይ ሊደረግ የታሰበው ሴራ እየተከታተለ ይገኛል፡፡ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንም ሆነ በማህበሩ ላይ እየተደረገ ያለውን ጫናም በጽኑ ይቃወማል፡፡
ውድ የሁለቱም እምነት ተከታዮች፡- ሰማያዊ ፓርቲ ህወሓት/ኢህአዴግ የሚያደርገውን ጫና እና ጣልቃ ገብነት በጽኑ እየተቃወመ፣ ማንኛውም በሐይማኖታችሁ ላይ የሚደረግን ጫና በግልጽ እንድትቃወሙ ጥሪ ያቀርባል፡፡ የሁለቱም የእምነት መጽሃፍቶች በአንዳችን ላይ የሚደርሰው ግፍ በሌላኛው ላይም እንዳይሆን መፈለግ እንዳለብን እንደሚገልጹት የእናንተ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ላይ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነትና ጫናም በመቃወም ለመርህ እንድትቆሙ ማሳሰብ ይፈልጋል፡፡
ሃይማኖት ለአንድ ማህበረሰብ ማንነት መሰረት እንደመሆኑ በአገር ግንባታ ቀላል የማይባል ሚና እንዳለው እናምናለን፡፡ ኢትዮጵያውያን ሐይማኖታች ሳይገድበን ተረዳድተን፣ ተባብረንና ተፈቃቅረን ኖረናል፡፡ ለዚህ አብሮ መኖርና መቻቻልም ሃይማኖታችን የራሱ የሆነ ሚና እንዳለው እናምናለን፡፡ ገዥው ፓርቲ በአሁኑ ወቅት በተለያዩ ሃይማኖቶች መካከል ብቻ ሳይሆን አንድ ሐይማኖት ውስጥ የሚገኙትን የአገራችን ዜጎች በጠላትና በወዳጅነት በመከፋፈል ኢትዮጵያውያን እርስ በእርሳቸው እንዲጠራጠሩ፣ ግጭት ውስጥ እንዲገቡና ሃይማኖታቸውን በነጻነት እንዳይከተሉ እያደረገ ነው፡፡ ይህም ለቀጣይ የአገራችን ሁኔታ አሉታዊ አስተዋጽኦው የጎላ በመሆኑ ፓርቲያችን በጽናት ይቃወማል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ በዚህ ጽኑ አቋሙ አግባብ ያልሆኑ የተለያዩ ስሞች ተሰትቶታል፡፡ አመራሮቹና አባላቱም ታስረዋል፡፡ ተደብድበዋል፡፡ ከተነጠቁት መብቶች መካከል ይህን የእምነት ነጻነት መብት እንዲከበር የሚጠይቁ ጥያቄ ባነሳበት በአሁኑ ወቅት እንኳ ከ50 በላይ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ማጎሪያ ቤት ውስጥ ይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያውያን መብት ይከበር ዘንድ የሚከፈለውን ዋጋ ለመክፈልም ቁርጠኛ መሆናችንን መግለጽ እንወዳለን፡፡
ገዥው ፓርቲ በሃይማኖታችን ላይ ጣልቃ በመግባት የዜጎቻችን አንዱንና ዋነኛውን መብት ቀምቷል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ይህን የኢትዮጵያውያን መብት ለማስመለስ ሚያዝያ 19 ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ በመሆኑም ይህን የተቀማችሁትን መብት ለማስመለስ በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ እንድትሳተፉ ጥሪውን ያቀርብላችኋል፡፡
ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፋንታ እንወስን!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ይኑር!

Multiple arrests in major crackdown on government critics

April 26/2014
The Ethiopian government is tightening its suffocating grip on freedom of expression in a major crackdown which has seen the arrest of numerous independent, critical and opposition voices over the last two days, said Amnesty International.
Six members of an independent blogger and activist group and a freelance journalist were arrested yesterday 25 April. Another journalist was arrested this morning. Meanwhile 20 members of the political opposition Semayawi (Blue) party have been arrested since Thursday.
"These arrests appear to be yet another alarming round up of opposition or independent voices" said Claire Beston, Ethiopia researcher at Amnesty International.
"This is part of a long trend of arrests and harassment of human rights defenders, activists, journalists and political opponents in Ethiopia."
Six members of the independent blogger and activist group ‘Zone 9’ were arrested on 25 April in Addis Ababa. Group members Befeqadu Hailu, Atnaf Berahane, Mahlet Fantahun, Zelalem Kiberet, Natnael Feleke and Abel Wabela were arrested from their offices or in the street on Friday afternoon. All six were first taken to their homes, which were searched, and then taken to the infamous Federal Police Crime Investigation Sector ‘Maikelawi’, where political prisoners are held in pre-trial, and sometimes arbitrary, detention.
At around the same time on Friday afternoon freelance journalist Tesfalem Waldyes was also arrested. His home was also searched before he was taken to Maikelawi. Another freelance journalist and friend of the Zone 9 group, Edom Kasaye, was arrested on the morning of Saturday 26 April. She was accompanied by police to her home, which was searched, and then taken to Maikelawi.
"The detainees must be immediately released unless they are charged with a recognisable criminal offence" said Claire Beston.
"They must also be given immediate access to their families and lawyers."
The detainees are being held incommunicado. Family members of those arrested reportedly went to Maikelawi on the morning of Saturday 26 April, and were told they could leave food for the detainees, but they were not permitted to see them.
The Zone 9 group had temporarily suspended their activities over the last six months after what they say was a significant increase in surveillance and harassment of their members. On 23 April the group announced via social media that they were returning to their blogging and activism. The arrests came two days later.
It is not known what prompted Waldyes’ arrest, but he is well known as a journalist writing independent commentary on political issues. 
In further arrests, the political opposition party, the Semayawi (Blue) Party, says that during 24 and 25 April more than 20 of its members were arrested. The party was arranging to hold a demonstration on Sunday 27 April. They had provided the requisite notification to Addis Ababa administration, and had reportedly received permission.
The arrested party members, which include the Vice Chairman of the party, are reported to be in detention in a number of police stations around the city, including Kazanchis 6th, Gulele and Yeka police stations.
The Chairman of the party, Yilkil Getnet, was also reportedly arrested, but was released late on Friday night.
Over the last year, the Semayawi party has staged several demonstrations, which have witnessed the arrests and temporary detention of organisers and demonstrators on a number of occasions.
In March, seven female members of the Semayawi Party were arrested during a run to mark International Women’s Day in Addis Ababa, after chanting slogans including “We need freedom! Free political prisoners! We need justice! Freedom! Don’t divide us!” The women were released without charge after ten days in detention. 
“With still a year to go before the general elections, the Ethiopian government is closing any remaining holes in its iron grip on freedom of speech, opinion and thought in the country” said Claire Beston. 

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለሚዲያ ማህበረሰቡ የተላለፈ ጥሪ

April 26/2014

ውድ የሚዲያ ማህበረሰብ አባላት፡- ባለፉት 23 ዓመታት ህወሓት/ኢህአዴግ በህገ መንግስቱ የሚዲያ ነጻነት እንደሚፈቀድ ቢደነግግም በተግባር ግን የራሱን ፕሮፖጋንዳ ከሚነዛባቸው ሚዲያዎች ውጭ ሌሎቹን ሲዘጋና ሲያሸማቅቅ ኖሯል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ህዝባችን ከገዥው ፓርቲ ፕሮፖጋንዳ ውጭ አማራጭ መረጃ ማግኘት አልቻለም፡፡ ጋዜጠኞች እየታሰሩ፣ እየተሰደዱ፣ ሚዲያዎች እየተዘጉም ቢሆን የተቻላችሁን ያህል ለህዝብ መረጃ ለማድረስ የሚዲያው ማህበረሰብ አባላት ለምታደርጉት ሁሉ ከፍ ያለ ክብር አለን፡፡ የታፈነውን የህዝብ ድምጽ ለማሰማት የምታደርጉትን ጥረትም እናበረታታለን፡፡ ሆኖም አሁንም ቢሆን በገዥው ፓርቲ አፋኝነት ምክንያት ህዝባችን የሚገባውን መረጃ እያገኘ አይደለም፡፡ እናንተም በሰበብ አስባቡ ጫና እየደረሰባችሁ እንደሆነ ፓርቲያችን ይገነዘባል፡፡ ገዥው ፓርቲ ላይ የሰላ ትችት የሚያደርሱ ጋዜጠኞች ‹‹አሸባሪ›› ተብለው ታስረዋል፡፡ ጋዜጦችና መጽሄቶች በስርዓቱ ተዘግተዋል፡፡ በርካታ ጋዜጠኞች አገራቸውን ጥለው ተሰደዋል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ዛቻ ደርሶባቸዋል፡፡ እየደረሰባቸውም ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ በሚያደርስባቸው ቀጥተኛም ሆነ ተዘዋዋሪ ጫና ከገበያ ወጥተዋል፡፡

በአጠቃላይ በአሁኑ ወቅት ለህዝባችን አማራጭ መረጃ የሚያደርሱ ሚዲያዎችና የሚዲያው ማህበረሰብ መብቶቻቸውን ተነጥቀው አደጋ ላይ ወድቀዋል፡፡ አማራጭ መረጃ ለዴሞክራሲና ለልማት ቀዳሚውን ሚና እንደሚጫወት የሚያምነው ፓርቲያችን ይህን የመብት ረገጣና አፈና ሲቃወምና ሲታገል ቆይቷል፡፡ አሁንም በጠነከረ መልኩ ይቃወማል፡፡ ፓርቲያችን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽን ጨምሮ የተነጠቁትን መብቶቻችን ለማስመለስ በመጣሩ አመራሮቹና አባላቱ በህገ ወጥ መንገደ እስር ቤት በሚገኙበት ተመሳሳይ ወቅት የዞን ዘጠኝ ወጣቶች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡

 ይህም ከመቸውም ጊዜ በላይ ጭቆናው እንደመረረ እና ሁሉን ማህበረሰብ ያቀፈ ትግል እንደሚያስፈልግ ዋነኛ ማሳያ ነው፡፡ ከዚህ የመረረ ጭቆና ህዝባችንን ነጻ ማውጣት የምንችለው እኛ ህዝቡን ማደራጀትና ማንቀሳቀስ የሚዲያ ማህበረሰቡም መደረጃውን ለህዝባችን ማድረስ ሲችል ብቻ ነው፡፡ ፓርቲያችን ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብትን ጨምሮ ገዥው ፓርቲ ከኢትዮጵያውያን የነጠቃቸውን መብቶች ለማስመለስ ተቃውሞ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ የሚዲያው ማህበረሰብ ይህን የተቃውሞ ሰልፍ ሂደት ለህዝብ በማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለው የታመነ ነው፡፡ በመሆኑም መብቶቻችን በህዝብ ትግል ይመለሱ ዘንድ እናንተም የተለመደው የበኩላችሁን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ ጥሪያችን እናስተላልፋለን፡፡ መረጃ ኃይል ነውና በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትገኙ የህትመትም ሆነ የብሮድካስት ውጤቶች የተነጠቁትን መብቶቻችን፣ የሰላማዊ ሰልፉን ሂደት፣ በሂደቱ በፓርቲያችንና በህዝቡ ላይ የሚደርሰውን በደል እና ሰላማዊ ሰልፉን ለህዝብ በማድረስ ግዴታችሁን እንድትወጡ አደራ እንላለን፡፡ በተለይ ሌሎች ሚደያዎች በታፈኑበት በአንጻራዊነት የህዝብ ድምጽ በመሆን ላይ በሚገኘው ፌስ ቡክ በኩል መረጃዎችን ለህዝብ በማድረስ ቀላል የማይባል ጫና መፍጠር የሚቻል በመሆኑ አጋጣሚውን በመጠቀም መብታችን ለማስመለስ እንድንታገልና በሰልፉም እንድንገኝ አደራችን እናስተላልፋለን፡፡ ኑ ራሳችን ነጻ በማውጣት የአገራችን እጣ ፈንታ እንወስን! ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

የ“ህዳሴው” ግድብ ተጽዕኖ ሌላ አቅጣጫ መያዙ አሳሳቢ ሆኗል

April 25/2014
የአቡነ ማቲያስ የግብጽ ጉብኝት ላልተወሰነ ጊዜ ተላልፏል

abay and church
ሃያ አምስት በመቶ እንደተጠናቀቀ የሚነገርለት የ“ህዳሴው” ግድብ በኢትዮያና በግብጽ መካከል ከፈጠረው የፖለቲካ ቁርቋሶ በተጨማሪ ወደ ሃይማኖት መንደርም እየዘለቀ ነው፡፡ ዛሬ (አርብ) ግብጽን ለመጎብኘት ቀጠሮ ተይዞላቸው የነበሩት አቡነ ማቲያስ ከግብጽ በኩል እንዳይመጡ በተላለፈላቸው መልዕክት መሠረት ጉብኝታቸውን ላልተወሰነ ጊዜ አስተላልፈውታል፡፡
በግብጽና በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የተለያዩ የዜና ዘጋቢዎች እንዳሉት ከሆነ መልዕክቱ ያስተላለፉት የግብጹ ፓትሪያርክ አቡነ ታዋድሮስ ዳግማዊ ናቸው፡፡ ፓትሪያርኩ ለአቡነ ማቲያስ ባስተላለፉት መልዕክት በበርካታ ቢሊዮን ዶላር የሚገነባው የአባይ ግድብ የፈጠረው ሁኔታ እንዳለ ሆኖ ይህንን ጉብኝት ማካሄድ የግብጽን ቤ/ክ “የሚያሳፍር” ይሆናል በሚል ነው ምክራቸውን ለአቡነ ማቲያስ የለገሱት፡፡
ስማቸውን ሳይጠቅሱ መረጃውን ለግብጽ የሚዲያ አካላት የተናገሩት ባለሥልጣን እንደሚሉት ከሆነ ሁለቱ ቤ/ክናት ለረጅም ጊዜ የቆየ ግንኙነት ቢኖራቸውም ግድቡን በተመለከተ ይፋዊ ያልሆነ ሽምግልና የማካሄዳቸው ሁኔታ የማያዛልቅ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሁለቱ ከፍተኛ የቤ/ክ መሪዎች በሚገናኙበት ወቅት ይህ ጉዳይ ሳይነሳ እንደማይታለፍ የታወቀ ነው፡፡
አቡነ ታዋድሮስ “አሳፋሪ” ያሉትን ጉዳይ በዝርዝር አልገለጹትም ሆኖም የግድቡ መሠራት ግብጽን ክፉኛ ያሳሰባት ጉዳይ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ በተለያዩ ጉዳዮች ውስጥ ጣልቃ ስትገባ ከመቆየት አልፋ ኢህአዴግን ለሚቃወሙ የመሣሪያና የመሳሰሉ ዕገዛዎችን ለማድረግ ስትንቀሳቀስ መቆየቷ የሚታወስ ነው፡፡
በሃይማኖቱ ዓለም ከፍተኛ ትስስር ያላቸው የግብጽና የኢትዮጵያ ቤ/ክናት ከ“ህዳሴው” ግድብ ጋር በተያያዘ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳቸው የውጥረቱን አሳሳቢነት የሚገልጽ ነው የሚሉ ክፍሎች ግብጽ መረጋጋት ስታገኝ የሚሆነውን ለመተንበይ ያስቸግራል ይላሉ፡፡ የሃይማኖት ተቋማት ለዕርቅና ሰላም መሥራት በሚገባቸው ጊዜ ከፖለቲካው በላይ መሆን አለመቻላቸው ሹመታቸውም ከዚያው የመነጨ ለመሆኑ ማስረጃ ነው፡፡ አገልግሎታቸውም ከፖለቲካው ሥልጣን በላይ መሆን ያልቻለ መሆኑን በግልጽ ያሳያል በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ፡፡
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ያነጋገራቸው ባለሙያ እንደሚሉት የግድቡ ሥራና በሁለቱ አገሮች መካከል የተፈጠረው ሁኔታ ሁሉንም ሊያሳስብ የሚገባ ነው ይላሉ፡፡ በተለይ ኢህአዴግ የግድቡን ሥራ ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ማዋሉ “አስከፊ ነው” ብለዋል፡፡ “አባይን የመገደቡ ጉዳይ አሁን የታሰበ ወይም የተጀመረ አይደለም፤ በንጉሡ ጊዜም ሆነ በደርግ ጊዜ የነበረ ነው፡፡ እኔ የፖለቲካ ተንታኝም ሆነ የታሪክ ምሁር አይደለሁም ነገር ግን በግድቡ ሥራ ላይ ባለኝ ሙያ በከፍተኛ ደረጃ እሳተፋለሁ፡፡ ህወሃት እና ኢህአዴግ ለራሳቸው ርካሽ ፖለቲካ መጠቀሚያነት ሲያውሉትና ሕዝቡን ከንቱ በሆነ አገራዊ ስሜት አስገብተው የራሳቸውን ፖለቲካ ለማራመድ የሚያደርጉትን ሁሉ በየቀኑ በሥራችን ላይ የምናየው አስከፊ ልምምድ ነው፡፡ እኔ የትግራይ ተወላጅ በመሆኔ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያዊነቴ አባይ ለዚህ መዋሉ ያስደስተኛል ነገር ግን ኅብረተሰቡ ሲጠይቅ “የግብጽ ደጋፊ ነህ፤ ጸረ-ልማት ነህ ወዘተ” ማለቱ የትም አያደርስም፡፡ በዚህ ላይ ከአገሪቷ ኢኮኖሚ አኳያ የግድቡ ወጪም ሆነ፣ የባለቤትነቱ ጉዳይ እንዲሁም ሌላ በርካታ ጉዳዮች ሊጠየቁ የሚገባቸው ጥያቄዎች ናቸው” ብለዋል፡፡
ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ዕቅድ ተይዞለት የነበረው የአቡነ ማትያስ የግብጽ ጉብኝት ላሁኑ ተላልፎ የነበረ ሲሆን የአቡነ ታዋድሮስ የመስከረም ወር የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውም በተመሳሳይ ምክንያት መሰረዙ ይታወሳል፡፡

Friday, April 25, 2014

[የሳዑዲ ጉዳይ] የዜጎቻቸውን ክብር እና የሃገራቸውን በጎ ገጽታ በማጉደፍ ስራ ላይ የተጠመዱ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ዲፕሎማቶች

April 25/2014

በሳውዲ አረቢያ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንገስት ዲፕሎማቶች ሪያድ ከተማ ውስጥ በሚገኝ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ስም በከፈቱት የፌስ ቡክ ገጽ ሰሞኑንን አንዲት ኢትዮጵያዊት አሰሪዎን በሰቃቂ ሁኔታ በመጥረቢያ ፈልጣ ገደለች በሚል ጥቂት የሳውዲ መገናኛ ብዙሃኖች ሲያሰሙ የከረሙትን የተለመደ የቁራ ጩሀት በማስተጋባት የህዝብ እና የሃገራቸውን በጎ ገጽታ በማጠልሸት ስራ ላይ ተጠምደው መክረማቸውን ምንጮች ከሪያድ ገለጹ፡፤ ይህ ኢትዮጵያውያኑን በአውሬነት የመፈረጅ ዘመቻ የተለመደ እና ቀደም ብሎ ሪያድ ከተማ ውስጥ በተለምዶ መንፉሃ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የጅምላ ግድያ እና ድብደባ ከመፈጸሙ በፊት ሳውዲ አረቢያ ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ የግል ሚዲያዎች በሃሰት ኢትዮጵያውያኑን ሲወነጅሉ እንደ ነበር የሚናገሩ የአይን እማኞች ሰሞኑን ሳውዲ ውስጥ በእንግሊዘኛ ቋንቋ የሚታተው አረብ ኒውስ http://www.arabnews.com/news/554481 የተባለ ጋዜጣ ሳውዲ አረቢያ ጣይፈ ከተማ አንዲት ኢትዮጵያዊት የ50 አመት የልጆች እናት የሆነች አዛውንት በመጥረቢያ ፈልጣ ገደለች የሚል ዜና መዘገቡን ተከትሎ በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች እና አንዳንድ ሃላፊነት የማይሰማቸው ምስለኔዎች ነገሩን በማጋነን በተለያዩ ሶሻል ሚዲያ ገጾቻቸው ላይhttps://www.facebook.com/ethiopian.embassy.5 በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ ከጋዜጣው በላይ እንደ ገደል ማሚቱ በማስተጋባት እያሰሙን ያለው መረን የለቀቀ ዘግናኝ ወሬ ከሃገራዊ ከህደት ተለይቶ እንደማይታይ ይናገራሉ፡፤

ሰሞኑን እራሱን አረብ ኒውስ እያለለ የሚጠራው ይህ ጋዜጣ ሳውዲ አረቢያ ጣይፍ ከተማ በስተደቡብ 130 ኪ/ሜ ርቀት ላይ የምትገኝ መንደር ውስጥ በአንድ ኢትዮጵያዊት ተፈጸመ ብሎ የተዘገበውን አስቃቂ ወንጀል ለኢትዮጵያውያን ክበር ተቆርቋሪ የሆኑ ወገኖች ቦታው ድረስ ሄደው ጉዳዩን ለማጣራት ባደረጉት ሙከራ በተጠቀሰው አካባቢ የሚኖሩ ወገኖች እየተነገረ ያለውን ነገር እንደማንኛውም ሰው በወሬ ደረጃ ከመስማት ውጭ መንደራቸው ውስጥ እንደዚህ አይነት ወንጀል መፈጸሙን ምንም እንደማያውቁ እንዳረጋገጡላቸው ጠቅሰው የጋዜጣው ዘገባ ከተለመደው በሬ ወለደ የስም ማጥፋት ዘመቻ እንደማያልፍ ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል።

በተለይ ይህንን ወሬ የሚያራግቡ አንዳንድ ኢትዮጵያዊነት መንፈስ የማይታይባቸው የዲፕሎማቱ ግብረ አበረ አበሮች የ50 አመቷ እማወራ በጸሎት ላይ ሳለች የተገደለቸው የክርስትና እምነት ተከታይ በሆነች ኢትዮጵያዊት መሆኗን በግል የማህበራዊ ገጾቻቸው የሌሎችን ቀልብ ለመሳብ የሚዘግቡትን አካላት የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን እነዚህ ግለሰቦች በመሃከላችን አለመተማመንን ለመፍጠር እየፈጸሙ ያለው ድብቅ አጀንዳ ሰሞኑን የአረብ ሚዲያዎች በወገኖቻችን ላይ እያሰራጩ ካለው ጥላቻ የማይለይ እና የብዙሃኑን ህይወት በአዲስ መልክ አደጋ ላይ ለመጣል ከሚቆፈር ጉድጓድ በመሆኑ ዲፕሎማቱ እና ጀሌዎቻቸው ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ከወዲሁ ሃይ ሊባሉ እንደሚገባ አስጠንቅቀዋል።

ጅዳ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በበኩላቸው በዲፕሎማቱ ተፈፀመ በተባለው ነገር አዝነው በአረብ ኒውስ ስለተዘገብው ዜና ዲፕሎማቱ የቱንም ያህል መርጃ ባይኖራቸው እንኳን ለሌሎች ኢትዮጵያውያን ደህነት ሲባል ኤምባሲው በስፋት የተወራውን ወንጀል አጣርቶ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ በማፈላለግ የህዝብን ደህነት እና የሃገሪቱን በጎ ገጻታ ማስጠበቅ ይገባቸው እንደነበር ገልጸው በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት እንዲሉ ዲፕሎማቱ ኢትዮጵያውያንን ጭራቅ አድርገው ለመሳል ከሚዳክሩ የአረብ ጋዜጣች ያገኙትን መረጃ ተቀብለው ህዝብን ያስተምራል በሚል አስፋሪ ተሞክሮ በኤንባሲው ስም በከፈቱት ድህረ ገጽ እያስተጋቡ ያለው ጩሀት ወደፊት በታሪክም በህግም እንደ ሚያስጠይቃቸው ተናግረዋል።

ቀደም ሲል በመዲናይቱ ሪያድ አንዲት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ የ 9 አመት የአሰሪዎን ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለች አስመስለው አንዳንድ የአረብ ጋዜጦች የኢትዮጵያውያንን ክበር እና የሃገራችንን በጎ ገጽታ በሚነካ መልኩ ለመዘገብ ያደረጉት ጥረት እንዳልተሳክ የሚገልጹ ወገኖች የሳውዲ ፖሊስ ነፍሰ ገዳይ ብሎ በቁጥጥር ስር ባዋላት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ ላይ ባደረገው ምርመራ የህጻኗ አሞሞት ከቤት ሰራተኘዋ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌው መሆኑን በማረጋገጥ ኢትዮጵያዊቷ የቤት ሰራተኛ በነጻ ማሰናበቷ ይታወሳል።

በሪያድ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ዲፕሎማቶች በኢትዮጵያ ኤምባሲ ስም በከፈቱት ሶሻል ሚዲያ በማርኛ ለጠፉ ስለተባለው ኢትዮጵያውያንን የሚወነጅል አስቃቂ ዜና ማብራሪያ ለመጠየቅ ያደረኩት ሙከራ ለግዜው አልተሳካም ።
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

“የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴን በተመለከተ በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች ላይ ያለን እምነት በመሟጠጡ ወደ አፍሪካ ኮሚሽን ወስደነዋል” – ዶ/ር አወል

April 25/2014
የህዝበ ሙስሊሙ የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ወደ አፍሪካ የሰብዓዊ መብቶችና ህዝቦች ኮሚሽን ሂደው በመንግስት ላይ ክስ መመስረታቸው ይታወቃል። ይህንን በማስመልከትም በድር ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (ቢቢኤን) የኮሚቴውን የክስ ሂደት በቅርበት ከሚከታተለው ዶ/ር አወል ቃሲም አሎ ጋር በዚሁ ጉዳይ ቆይታ አድርጓል። ዶ/ር አወል የአለም ዓቀፍ ህግ ምሁር ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በLondon School of Economics የሰብዓዊ መብት Fellow ነው።

ቢቢኤን፡- የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ጉዳያቸውን ወደ አፍሪካ ኮሚሽን ለመውሰድና ለመክሰስ ያሰቡት ለምንድን ነው? ጉዳያቸውን በኢትዮጵያ ፍርድ ቤቶች መጨረስ አይችሉም ነበር?

ዶክተር አወል፡- አመሰግናለሁ። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጉዳዩን ወደ አፍሪካ ኮሚሽን ለመውሰድ የተገደደበት ምክንያት በኢትዮጵያ ፍ/ቤቶች ላይ ያለው እምነት በመሟጠጡ ነው። እነዚህ ፍ/ቤቶች እንደዚህ አይነት ጉዳዮች ላይ የህግ የበላይነትን፣ ህገ መንግስቱን እና የራሳቸውን ህሊና መሰረት በማድረግ ሊወስኑ ይችላሉ የሚለው ተስፋ በመሟጠጡ ነው። ይህ ክርክር ደግሞ በዋናነት የእውነት ጉዳይ ስለሆነ መንግስት ከዚህ በፊት ሚዲያውን እና የተለያዩ የመንግስት ተቋማትን በአጠቃላይ እንደ መንግስት ያለውን ሙሉ ሀይል በመጠቀም መሬት ላይ ሲፈጥራቸው የነበሩ እውነታዎች እውነት እንዳልሆኑና ከዚያ በስተጀርባ ሌላ ነገር እንዳለ ይህም የተፈበረከ ነገር እንደሆነ ማሳየት የሚችሉት ገለልተኛና ዓለም አቀፍ የሆነ እንዲሁም የኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ ሌላ መንግስት ጫና ሊያሳድርበት የማይችልበት ተቋም ላይ በመሄድ ጉዳያቸውን አቤት ለማለት ነው ተከሳሾቹ ወደ አፍሪካ ኮሚሽን ሊሄዱ የቻሉት።

ቢቢኤን፡- እንግዲህ ይህን ጉዳይ ከመጀመሪያው ጀምረህ ስትከታተለው ነበርና የአፍሪካ ኮሚሽን ምን አይነት ድርጅት ነው? ምን ምን ጉዳዮችንስ ያያል?

ዶክተር አወል፡- በመጀመሪያ እኔ ጉዳዩን ከያዙት ጠበቆች አንዱ አይደለሁም። ለጠበቆቹ በተወሰነ ደረጃ የሰጠሁት እገዛ አለ፤ ጉዳዩን በቅርበት አውቀዋለሁ ነገር ግን ጉዳዩን ከያዙት ግለሰቦች አንዱ አይደለሁም። ወደ ጥያቄው ስንመለስ ኮሚሽኑ ምን ዓይነት ተቋም ነው ለሚለው የአፍሪካ ህብረት በውስጡ የተለያዩ ተቋማት አሉት ከነዛ ውስጥም አንዱ ይህ የአፍሪካ ህብረት የሰብዓዊና የህዝቦች መብት ኮሚሽን ነው። ይህ ኮሚሽን በ1987 በተፈረመው የአፍሪካ የሰብዓዊና የህዝቦች ቻርተር በሚል ሰነድ መሰረት የተቋቋመ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ነው።

ድርጅቱ ወይም ተቋሙ ሁለት መሰረታዊ ኋላፊነቶች አሉበት። የመጀመሪያው ይህን ሰነድ ፈርመው አባል የሆኑ አገሮች ኢትዮጵያን ጨምሮ ማለት ነው በምን ዓይነት መልኩ የተጣለባቸውን የሰብዓዊ መብት ግዴታቸውን እየተወጡ እንደሆነ፣ ምን ዓይነት የህግ ማውጣት፣ የዳኝነትና የአስፈፃሚ ተቋማትን እንደገነቡ መገምገም ነው። ስለዚህ ማንኛውም ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሰነድ መንግስታት በዚያ ሰነድ ውስጥ የተቀመጡ ሰብአዊ መብቶችን ለማሟላት ይቻል ዘንድ አስተዳደራዊ የህግ ማውጣት እንዲሁም የዳኝነት እርምጃዎችን እንዲወስዱ ይጠበቃል። ስለሆነም ኮሚሽኑ በዚህ በኩል የሚሰረው ስራ አገሮች ቻርተሩን ከፈረሙ በኋላ በዛ ቻርተር ውስጥ የተረጋገጡ መብቶችን በምን ዓይነት መልኩ ተግባራዊ እያደረጉ መሆኑንና ምን ዓይነት እርምጃዎችንስ እየወሰዱ ነው የሚለውን ነገር ከአገሮች ሪፖርት እየተቀበሉ ያንን መመርመር ነው።

ሁለተኛው የተቋሙ ስራ ግለሰቦች የሚያቀርቡትን አቤቱታ ተቀብሎ ማየት ነው። በዚህ ሰነድ መሰረት መብት የተሰጣቸው ግለሰቦች መንግስቶቻቸው እዚያ ሰነድ ላይ የተረጋገጡ መብቶቻቸውን የሚጥሱ ከሆነ ለኮሚሽኑ አቤት ማለት ይችላሉ። ኮሚሽኑ አቤቱታቸውን ተቀብሎ የማየት ስልጣን አለው። በአጠቃላይ የኮሚሽኑ ስራ ይሄ ነው።

በሌላ በኩል ኮሚሽኑ እንደዚህ አይነት ጉዳዮችን በሚቀበልበት ጊዜ የሚያያቸው ነገሮች አሉ። እነዚህ የሚቀርቡ አቤቱታዎች ሊያሟሉ የሚገቡ ቅድመ ሁኔታዎች አሉ። ከነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ዋናው ግዴታ ምንድን ነው ከሳሾች ወደ ኮሚሽኑ ከመሄዳቸው በፊት ሀገሮቻቸው ውስጥ ያሉ የዳኝነት መፍትሄዎችን መጀመሪያ አሟጠው መጠቀም ይኖርባቸዋል። ነገር ግን ይህ በ‘ሀገር ውስጥ ያሉ የዳኝነት መፍትሄዎች ከተሟጠጡ ብቻ ነው አቤቱታ የሚቀበለው’ የሚለው መርህ የሚሰራው እዚያ ሀገር ውስጥ ቀድሞውኑ መፍትሄ ሊሰጥ የሚችል የፍትህ ስርዓት ያለ እንደሆነ ነው። ስለዚህ የመጀመሪያው እርከን /stage/ ይሄ admissibility የሚባለው ማለት የክሱ የተቀባይነት ሂደት /process/ ሲያልፍ ነው። ከነዚህ ውስጥ አሁን እንዳልኩህ ዋናው መስፈርት አገር ውስጥ ያሉ መፍትሄዎችን ማሟጠጥ መቻል ነው።

የኮሚቴዎቻችንን ጉዳይ /case/ ስንመለከት አገር ውስጥ ያሉ መፍትሄዎችን አሟጠዋል ማለት አይቻልም። ምክንያቱም የክስ ሂደቱ እስካሁንም እንደቀጠለ ስለሆነ ማለት ነው። የክስ ሂደቱ ቢጠናቀቅና ቢፈረድባቸው እንኳ ተጠናቀቀ ማለት አንችልም። ምክንያቱም ለበላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማለት መቻል አለባቸው። ስለዚህ መደበኛ በሆነው አካሄድ መፍትሄ ያለበት ሀገር ውስጥ ከሆነ ከሳሾች ወደ ኮሚሽኑ የሚሄዱት አገር ውስጥ ያለውን የይግባኝ እድሎች ካሟጠጡ በኋላ ነው። እዚህ አቤቱታ ላይ የቀረበው መከራከሪያ ምንድን ነው ኢትዮጵያ ውስጥ effective እና practical የሆነ የሚሰራ መፍትሄ አካል ስለሌለ ኮሚሽኑ ሀገር ውስጥ ያሉ መፍትሄዎችን እንድናሟጥጥ መጠበቅ አይኖርበትም የሚል ክርክር ነው የቀረበው። ኮሚሽኑ ከዚህ በፊት ያለው jurispudence ምንድን ነው አንድ ሀገር የዳኝነት አካሏ ለተከሳሾች፣ ለሰብአዊ መብት ጉዳተኞች መፍትሄ መስጠት የማትችል ከሆነ እነዚያ ግለሰቦች ሀገር ውስጥ ያለውን መፍትሄ እንዲያሟጥጡ አይጠበቅም ብሏል።

በዚህ የኮሚሽኑ jurispudence መሰረትም ኮሚቴዎቹ እየተከራከሩ ያሉት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የዳኝነት አካል ሙሉ በሙሉ በመንግስት ቁጥጥር ስር ስለሆነና ምንም አይነት ተቋማዊ (institutional) አሰራርና ገለልተኝነት /functional independence/ ስለሌለው፣ የመንግስት ተለጣፊ ስለሆነ ባጠቃላይ ሀገር ውስጥ ልናገኘው የምንችለው ምንም አይነት መፍትሄ ስለሌለ ኮሚሽኑ ጉዳዩን ማየት መቻል አለበት የሚል ክርክር ነው ያቀረቡት። ኮሚሽኑ እዚህ ላይ በቅርብ ጊዜ ይወስናል ተብሎ ይጠበቃል። የኢትዮጲያ መንግስትም የኮሚቴዎቹ አቤቱታ ደርሶታል። መልስ እንዲሰጥ እየተጠበቀ ነው። በእርግጥ መልስ ይመልስ አይመልስ በአሁኑ ሰዓት እኔ መረጃ የለኝም። ነገር ግን እዚህ የመጀመሪያው step ላይ ኮሚሽኑ በቅርብ ጊዜ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ነው የሚጠበቀው። ከዚያ በኋላ ነው ወደ merit ማለትም ወደ ዋናው case የሚኬደው ማለት ነው።

ቢቢኤን፡- ኮሚሽኑ በአሁኑ ሰዓት ጉዳዩን አይቶ ለኢትዮጵያ መንግስት ምላሽ እንዲሰጥ ጥያቄ አቅርቦለታል ማለት ነው?

ዶ/ር አወል፡- ምንድን ነው እያልኩ ያለሁት ኮሚሽኑ አቤቱታውን ከተቀበለ በኋላ ያንን አቤቱታ ለተከሰሰችዋ አገር ይልካል። በእኛ ኬዝ ለኢትዮጵያ ማለት ነው። ከዚያም የኢትዮጵያ መንግስት ከሳሾች ላቀረቡት አቤቱታ መልስ ይሰጣል። መልስ የሚሰጠው እንዴት ነው? በአሁኑ ሰዓት ተከሳሾች ለምን ኢትዮጵያ ውስጥ መከራከርና ያለውን የፍትህ ስርዓት አሟጠው መጠቀም እንዳለባቸው፣ ለምን ኮሚሽኑ ይህንን ኬዝ ተቀብሎ ማየት እንደሌለበት ነው። ስለዚህ የመጀመሪያው ስቴጅ እንዳልኩህ ክሱ ተቀባይነት ይኑረው ወይስ አይኑረው የሚል ክርክር የሚደረግበት stage ነው። ክሱ ተቀባይነት አለው የሚል ውሳኔ ኮሚሽኑ ከወሰነ የሁለተኛው stage የሚሆነው የኢትዮጵያ መንግስት የሙስሊሙን ህብረተሰብና ኮሚቴ መብቱን ጥሷል ወይስ አልጣሰም ከተጣሰስ የትኞቹ መብቶች ናቸው የተጣሱት ወደሚለው ክርክር ይኬዳል ማለት ነው። ስለዚህ አሁን ያለነው የመጀመሪያው ስታጅ ላይ ነው። የኢትዮጽያ መንግስት ለኮሚሽኑ የገባው የከሳሾቹ አቤቱታ ግልባጭ ደርሶታል። መልስ እንዲሰጥም ይጠበቃል። በአሁኑ ጊዜ መንግስት መልስ ይስጥ አይስጥ እስካሁን የማውቀው ነገር የለም ግን አሁን ያለነው እዚህኛው stage ላይ ነው።

ቢቢኤን፡- በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ፍርድ ቤት ነፃ አለመሆኑን፤ ገለልተኛ አለመሆኑን ነው አቤቱታ እየቀረበበት ያለው። ስለዚህ ኮሚቴዎቹ በዚህ ፍርድ ቤት የማይተማመኑ ከሆነ ለምን አድማ በማድረግ በአፍሪካ ኮሚሽን ክስ ላይ ብቻ ትኩረት አልተደረገም? በሌላ በኩል በሀገሪቱ የፍትህ ስርዓት ፍትህ እናገኛለን ብለው የማያስቡ ከሆነ መጀመሪያውኑ እዚህ ክርክር ውስጥ በተለይ ከመንግስት ጋር በሚደረገው ክርክር ውስጥ ለምን ገቡ?

ዶ/ር አወል፡- እንደዚህ ዓይነት የመንግስት ፍላጎት ያለበት፣ አለመግባባቱ ቀጥታ በመንግስትና በተከሳሽ መሀከል በሚሆንበት የክስ ሂደት አንደኛው ፍርድ ቤቱ ነፃ አይደለም ስለዚህ የሚደረገውን የፍርድ ሂደት ክብር አለሰጠውም፣ legitimize አላደርገውም የሚባልበት አንዱ ሰትራቴጂ ከፍርድ ቤቱ ጋር ምንም አለመተባበር ነው፣ በክስ ሂደቱ ላይ አለመሳተፍ ነው፣ መከላለያ አለማቅረብ ነው. . . ወዘተ። ለምሳሌ ከ1997 ምርጫ በኋላ የቅንጅት መሪዎች በክስ ሂደቱ እራሳቸውን ለመከላከል የተጠቀሙት ስትራቴጂ ይሄ ነበር። ፍርድ ቤቱ ነፃነት ስለሌለው እንደዚህ ዓይነት ጉዳዮች ላይ ነፃ ሁኖ በህግና በህገ መንግስቱ መሰረት ሊወስን ስለማይችል ውሳኔውም መጨረሻ ላይ የሚመጣው ከመንግስት ስለሆነ የፍርድ ቤት ሂደቱ ላይ መሳተፍ የለብንም የሚል ውሳኔ ነበር እነሱ የወሰኑት። ኮሚቴዎቹ የወሰኑት ውሳኔ ግን ለየት ያለነው።

የዳኝነት ስራ ፍርድ ቤት ግለሰቦች ስለሄዱ ብቻ የሚሟላ አይደለም። የዳኝነት ስራ መሰረት የሚያደርጋቸው መሰረታዊ ነገሮች አሉ። አንደኛው ፍርድ ቤቱ በተከሳሽና ከሳሽ በሆነው መንግስት መሀከል ያለውን ሚዛን መጠበቅ መቻል አለበት። ተከሳሽ ማንኛውንም ነፃ መሆኑን ሊያሳዩ የሚችሉ መረጃዎችን የማቅረብ፣ የመከራከር፣ ዐቃቤ ህግ የሚያቀርባቸውን ማስረጃዎችና ምስክሮች ጥየቄ የመጠየቅና የመፈተሽ መብት አለው። እነዚህ መብቶች ሊጠብቅለት ይገባል። መንግስት ስንል በአንድ አገር ውስጥ ያለ መንግስት almost ማንኛውንም ነገር ማድረግ ይችላል ማለት እንችላለን። በጣም አቅም ያለው ትልቅ (ኋይል ነው)። ግለሰብ ግን በየትኛው ዓይነት መልኩ በመንግስት በቀላሉ ሊጨፈለቅ የሚችል አካል ነው። ዳኝነትን ዳኝነት የሚያስብለው ዋናው ነገር፤ ፍርድ ቤትን ፍርድ ቤት የሚያስብለው፤ የእውነት መድረክ የሚያስብለው፤ የፍትህ መድረክ የሚያስብለው መንግስትን የሚያክል ትልቅ ነገርና ግለሰብን የሚያክል በጣም ትንሽ ነገር ሚዛናዊነታቸውን ጠብቆ ሁለቱንም በህግ መሰረት በሰብዓዊ መብት ድንጋጌች መሰረት፣ በህገ መንግስቱ ድንጋጌዎች መሰረት እንዲከራከሩ እድል መስጠት ነው። በዛ ክርክር ሂደት እውነት እንድትወጣና በዛ እውነት መሰረት ፍርድ እንዲሰጥ ነው የክስ ሂደቱ ያለው። የዳኝነት ስራ ማለት ያ ነው። በርግጥ ፍርድ ቤት እነዚህን ግለሰቦች ምንም ዓይነት እራሳቸውን የመከላከል ዕድል ሳይሰጣቸው ዝም ብሎ ሊወሰን አይችልም። የሚወስን ከሆነ እራሱን ችግር ውስጥ ያስገባል ማለት ነው። እራሱን ችግር ውስጥ የሚያስገባው እንዴት ነው መጨረሻ ላይ ሂዶ ሂዶ ውሳኔው ከተወሰነ በኋላ ያ የወሰኑበት አካሄድ፣ የከለከሏቸውን መብት ምናልበት የህግ ስርዓቱ ዛሬ ተጠያቂ ላያደርጋቸው ይችል ይሆናል ነገር ግን በታሪክ ተጠያቂ ይሆናሉ፣ ይወቀሳሉ።

ቢቢኤን፡- ከኮሚሽኑ የፍርድ ሂደት በኋላ ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው ውሳኔ ምንድን ነው? ውሳኔውን እንዴት ነው ሊተገብር የሚችለው? ኮሚቴዎችን ከእስር ሊያስለቅቅ የሚያስችል የፖሊስ ኋይል አለው?
የዚህን ምላሽ በቀጣዩ ክፍል ይዘን እንቀርባለን።

Thursday, April 24, 2014

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ዛሬ ባቀረቡት ሪፖርት ያስገረሙኝ

April 24/2014

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም የዘጠኝ ወር ሪፖርት ለምክርቤት ዛሬ ሐሙስ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አቅርበው ጨረሱ።ከቤቴ ጀምሮ ትራንስፖርት እየሄድኩ በሞባይሌ ከአዲስ አበባ ኤፍ ኤም ላይ እየተከታተልኩ ነበር።ብዙ የሚባሉ ነገሮች ነበሩት።ነገር ግን ሁሉንም ለማንሳት ጊዜ የለኝም።ከእነኝህ ውስጥ ግን ያስገረሙኝን ብቻ ላንሳ።ቀድመው ወደስልጣን ሲመጡ የፎከሩበት ሙስናን አድበስብሰው ማለፋቸው አንዱ ነው።የዋናው ኦዲተር መስርያቤት ''ሀገር ተዘረፈ ለኢትዮጵያ ድረሱላት'' የሚል ሪፖርት ለምክርቤቱ ካቀረበ ዛሬ ሁለተኛ ቀኑ ነው።ሪፖርተር ጋዜጣም ዘግቦታል።ጉዳዩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የኦዲተር መስርያቤቱ ምን ያህል ነፃነት እንዳለው እያደነቁ በመንገር ሊሸውዱን መሞከራቸው አስገርሞኛል።እንደሳቸው ቀጥታ አባባል ''ማሳጅ'' ያልተደረገ ሪፖርት በማለት ጠርተውታል።የሪፖርቱን ታማኝነት በሌላ በኩል አረጋገጡ ማለት ነው። ሆኖም በጠራራ ፀሐይ አሰራር እና መመርያ ያልገደባቸው ሌቦች እንዴት ሀገር እንደሚዘርፉ እና የችግሩ ምንጭ እራሱ የመንግስታቸው እና የኢህአዲግ የሰው ኃይል በሙስና የተጨማለቀ መሆኑን ግን ለመንገር አልደፈሩም።

ሌላው ብድር የተበደርነው ''አበዳርዎቻችን ስለሚያምኑን ነው'' የሚል አባባል መጠቀማቸው ነው።እውን ጠቅላይ ሚኒስትር አሁን ባለንበት ዓለም ሃገራት ብድር የሚሰጡት ተበዳሪው ሀገር የመክፈል አቅም አለው በሚል ብቻ ነው? ለእዚህ ነው አበዳሪ ሃገራት ብድር ለሕንድ ከመስጠት ይልቅ ለመካከለኛው አፍሪካ ብድር የሚፀድቀው? የብድር ዓላማ አንዱ የመመለስ ዕድሉ ቢሆንም ሌላው የሃገራትን ፖሊሲ እጅ መጠምዘዣ መሳርያ ስለሆነም ጭምር ነው።አቶ ኃይለማርያም እየነገሩን ያሉት  ''የመመለስ አቅማችን ስላደገ ብቻ ነው'' የሚለው አባባላቸው አይዋጥልኝም።ይልቁን ከ 5 ቢልዮን ዶላር በላይ ብድር ተበድረን ለምን ለሙሰኛ እና ለሌባ ሲሳይ እንደሚደረግ ቢነግሩን ደስ ይል ነበር። መድበለ ፓርቲ በተመለከተ ያሉት ''ልብ ውልቅ'' ነው።ያደክማል።

''ኢንቨስተር የሀገር ሉዓላዊነትን አይነካም በተለይ በጋምቤላ የእዚህ አይነቱ አደጋ የለም''ላሉት።ኢንቨስተር በእራሱ ጠላት አይደለም ግን የሉአላዊነት አደጋ የመሆን አጋጣሚዎች ግን አሉ።በተለይ ኢንቨስተር ተቀባዩ ሀገር እና መንግስት እንደ እኛ በሙስና የተጨማለቀ ከሆነ የከፋ ነው።ወደ እኛ ሀገር ስንመጣ ኢንቨስተሮቹ መሬት ብቻ ሳይሆን ወንዞችን የግላቸው እያደረጉ ከመሆናቸው አንፃር ብቻ ስናየው ብዙ ነገሮች ይከሰቱልናል።ሲመጡም ውሃ ከሀገራቸው በሃይላንድ እያመጡ ልያጠጡ አይደለም የመጡት ወንዞቻችን እና ዝናማችንን ነው የፈለጉት።ኢንቨስተር የሀገር ሉዓላዊነትን የመዳፈር አጋጣሚ መኖሩን ለማየት ወደ ኃላ ታሪክ ቢመለከቱ አሰብ ላይ ጣልያን እግሯን የተከለችው ከአንድ ሱልጣን በገዛችው ቁራሽ መሬት (በኢንቨስተር ስም) መሆኑን ከእርስዎ አይሰወረም። ለመሆኑ 'የልማት ጥናት' ትምህርት እራሱ ድንበር ዘለል ኩባንያዎች multi-national corporations (MNC) በሀገሮች የውስጥ ጉዳይ እየገቡ ለብዙ ሃገራት የፀጥታ ችግር መሆናቸውን ያስተምር የለም እንዴ? በእዚህ ዙርያ በዓለማችን በርካታ ድርሳናት ለመፃፋቸው ጠቅላይ ሚኒስትራችን አላነበቡም? በአንድ ወቅት የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበረ ቀጥሎ ጠቅላይ ሚኒስትር የሆነ ሰው የአንዲት ሀገር ሉዓላዊነት አደጋዎች የመምጫ አቅጣጫዎችን አያውቅም ብሎ ማለት ይከብዳል።ግን ሃገሩ ኢትዮጵያ ሆነ እና ጠያቂ ጠፋ።

ጉዳያችን 

የወታደራዊ መኮነኖች ቅነሳ?! ህወሓት እየተዳከመ መሆኑ የሚያሳይ ሌላ ማስረጃ ደግሞ በተለያዩ ክልሎች ይሰሩ የነበሩ የህወሓት የደህንነት ሰዎች ከያንዳንዱ ክልል መባረራቸው ነው!

April 24/2014
አብርሃ ደስታ

ህወሓቶች ከትግራይ የሚቀነሱ ወታደራዊ መኮነኖች ሲኖሩ ከኦሮምያ፣ ደቡብና አማራ ክልሎች ደግሞ ይጨመራሉ የሚል መረጃ ያስደነገጣቸው ይመስላል። በዚህ መረጃ የደነገጠ የህወሓት ካድሬ ካለ በትክክል ስለ ህወሓት መረጃ የለውም ማለት ነው።
በወታደራዊ መኮነኖች ቁጥር መቀነስና መጨመር ጉዳይ ሙያዊ ትንታኔ መስጠት አስፈላጊ ይመስለኛል። ምክንያቱም ወታደራዊ መኮነንነት ማዓርግ እንጂ ሹመት አይደለም። የራሱ የሆነ ወታደራዊ ዲሲፕሊንና ሳይንስ አለው። ስለዚህ በዚህ ጉዳይ አስተያየት ለመስጠት የተሟላ ሙያዊ መረጃ ሊኖረኝ ይገባል። አሁን የምችለው ሙያዊ አስተያየት ሳይሆን ፖለቲካዊ አስተያየት መስጠት ብቻ ነው። በዚሁ መሰረት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የብሄር (ወይ የክልል) ተዋፅዖ መሰረት ያደረገ ሳይሆን የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ተዋፅዖ መሰረት ያደረገ ነው።

(ወታደራዊ ማዓርግ የብሄር ተዋፅዖ መሰረት ያደረገ መሆን አለበት ብዬ አላምንም። ልምድና ብቃት ያለው፣ ለደረጃ መኮነንነት የሚመጥን ስብእናና ዕውቀት ያለው እንዲሁም ለሀገሩ ለመስራት ፍቃደኛ የሆነ፣ አካላዊና አእምሮአዊ ብቃት ያለው፣ ሁሉ ወታደራዊ ማዓርጉ ማግኘት አለበት፣ ሀይማኖቱ፣ ብሄሩና የፖለቲካ እምነቱ ግምት ዉስጥ ሳይገባ።) መከላከያ ሰራዊታችን (በተለይ ወታደራዊ መኮነኖች) የብሄር ወይ ክልል ተዋፅዖ የለውም። የፓርቲ ተዋፅዖ ነው ያለው።

መኮነናዊ ማዓርግ የሚሰጠው በብሄር ሳይሆን በፖለቲካ ነው (የህወሓት፣ የብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደኢህዴን ምናምን እየተባለ)። ማንኛውም ትግርኛ ተናጋሪ ወታደራዊ ማዓርግ የሚሰጠው ይመስላችኋል? የህወሓት ደጋፊ (በውስጥ አባል) ካልሆነ በቀር? ወታደራዊ ማዓርግ የሚሰጠው በፖለቲካ አመለካከቱ ነው። እንኳን መኮነኖች የጉምሩክና ገቢዎች ሰራተኞችም በፓርቲ ተዋፅዖ የተዋቀሩ ናቸው። በዚሁ መሰረት የህወሓት ወታደራዊ መኮነኖች ሲቀነሱ፣ የብአዴን፣ ኦህዴድና ደኢህዴን መኮነኖች ሲጨምሩ ከመለስ ዜናዊ ሞት በኋላ የህወሓትን ዓቅም በሌሎች የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች እየተዋጠ መሄዱ የሚያሳይ ነው። የህወሓት የበላይነት እያበቃ መሆኑ ምስክር ነው። ህወሓት እየተዳከመ መሆኑ የሚያሳይ ሌላ ማስረጃ ደግሞ በተለያዩ ክልሎች ይሰሩ የነበሩ የህወሓት የደህንነት ሰዎች ከያንዳንዱ ክልል መባረራቸው ነው። አሁን በሌሎች ክልሎች ይሰልሉ የነብሩ ህወሓቶች ተባረው በትግራይ መቐለ ከተማ ተሰባስበዋል። ይህን ሁሉ የሚያሳየው የህወሓትን መዳከም ነው።

መከላከያ ሰራዊታችን ከአንድ ፓርቲ አገልጋይነት ወደ ሀገር አገልጋይነት (ሀገራዊ ሰራዊት) እናሸጋግረዋለን። ሰራዊቱ አይፈርስም ግን የፓርቲ ሳይሆን የሀገር (የመንግስት) ይሆናል።

AN URGENT APPEAL – From Mesfin Wolde-Mariam

April 24/2014

The UN Human Rights Commission
The African Union Human Rights Commission
The International Red Cross
Amnesty International
Human Rights Watch
And
All Men and Women of GOOD WILL
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu
Reeyot Alemu is a budding Ethiopian poet, essayist, and journalist. There are not many Ethiopians of her caliber inside the country. She has been languishing in the famous Ethiopian Prison in Qalliti for almost three years. She was charged of terrorism, a crime she totally abhors. She was sentenced first for eighteen years but later reduced to three.
With the exception of her mother and father, she is not allowed to communicate with anyone, including her sisters, brothers as well as her fiancée.
Reeyot, although constantly in agonizing pain and in need of help, is held in solitary confinement with a very old and sickly foreign woman who herself requires assistance.
Reeyot is suffering from some growth in her breasts. The prison authorities have been reluctant to take her to hospital for medical checkup, even when her parents were prepared to pay the bill. When she became seriously ill she was allowed to see a doctor as a result of which she was taken to the hospital and operated upon. But no sooner had the surgeon finished the operation than she was immediately taken back to prison even before she had fully recovered from the Anastasia.
She now suffers from a relapse on the operated breast and similar growth in her other breast. The prison authorities still demonstrate their reluctance to provide medical treatment even at the expense of her parents.
May God provide the necessary courage to all those institutions and organizations to cry out effectively for this young lady who is suffering at the hands of insensitive prison administration.

አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ቁጥር 3 ንቅናቄ ዝግጅት እንዲጀመር ወሰነ!! የሚሊዮኖች ድምፅ

April 24/2014

ንቅናቄው የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃና ፍትሐዊ ምርጫ (Millions of Voices for Free & Fair Election) የሚል መሪ ቃል ይኖረዋል፡፡
ከህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው ማክሰኞ ዕለት የአንድነት ስራ አስፈፃሚ አስቸኳይ ስብሰባ ካደረገ በኋላ ትግሉን ወደ ህዝቡ ማውረድና ህዝቡ የትግሉ ባለቤት እንዲሆን ለማስቻል የተጀመረው ንቅናቄ ተጠናክሮ የሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ተወያየ፡፡
ስራ አስፈፃሚው ወቅቱ 24 ሰዓት የሚሰራበት መሆኑን በማመን በሰላማዊ መንገድ ህዝቡን ያሳተፈ ትግል አቀጣጥሎ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻልና ለውጥ ማምጣት ከሚቻልባቸው መንገዶች አንዱ ሕዝባዊ ንቅናቄ መፍጠር እንደሆነ በማመን ከፍተኛ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
ከውይይቱ በኋላም በቅርቡ ይፋ የተደረገው የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባለቤትነት በተቀመጠው ዕቅድ መሰረት ከተጠናቀቀ በኋላ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃና ፍትሐዊ ምርጫ (Millions of Voices for Free & Fair Election) በሚል መሪ ቃል እንዲቀጥል፤ ምርጫውን መሰረት ያደረገ ሕዝባዊ ንቅናቄ እንዲጀመርና ለዚህ ሰፊ ዘመቻም ዝግጅት እንዲደረግ መወሰኑን እንዲሁም ይህንን ንቅናቄ የሚመራ ግብረ-ኃይል የሚቋቋምበት ሁኔታ በፍጥነት እንዲመቻች በሚል ከስምምነት መደረሱን መረጃ ያመለክታል፡:

Wednesday, April 23, 2014

በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ታሰሩ

April 23/2014
የሰማያዊ ፓርቲ ሚያዚያ 19 ቀን በአዲስ አበባ ለጠራው ሰልፍ፣ ቅስቀሳ ያደረጉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መታሰራቸውን የሰማያዊ ፓርቲ በፌስ ቡክ ገጹ ገለጸ።
በአዲስ አበባ አስተዳደር አካባቢ ከተገኙ ምንጮቻችን በደረሰን ዘገባ መሰረት፣ የአዲስ አበባ አስተዳደር ከደህንነት ሃላፊዎች ፣ ሚያዚያ 19 ቀን ለሰማያዊ እንዲፈቀድ መመሪያ መስጠታቸውን በመግለጽ ፣ «እስከ አሁን የሰማያዊ ፓርቲ፣ ለሚያዚያ 19 ቀን ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ ገና በእጁ ያልያዘ ቢሆንም ፣ በአስተዳደሩና በደህንነት ሃላፊዎች መካከል የተፈጠረው ዉዝግብ ነገሩን በሌላ አቅጣጫ ካልወሰደው በስተቀር፣ ሰማያዊ የእውቅና ደብዳቤ በጥቂት ቀናት ዉስጥ ያገኛል ተብሎ ይጠብቃል» ስንል መዘገባችን ይታወቃል።
የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ለጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዛሬ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ በርካታ አባሎቻቸው እንደታሰሩ ገልጸው፣ ከአስተዳደሩ እውቅና ገና እንዳላገኙም ተናገረዋል። በአዲስ አበባ አስተዳደር አካባቢ ያለውን ሁኔታ ለማጥራት ያደረግነው ሙከራ እስከአሁን አልተሳካም።
የታሰሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሚከተሉት ናቸው ፡
ቂርቆስ ፖሊስ መምሪያ /6ኛ ፖሊስ ጣቢያ/
1. መርከቡ ሀይሌ
2. ሰለሞን ፈጠነ
3. ዘሪሁን ተሰፋዬ
4. አናኒያ ኢሳያስ
5. ፋሲካ ቦንገር
6. ጀሚል ሽኩር
7. ሰይፈ ፀጋዬ
ጉለሌ ፖሊስ መምሪያ
1. የሽዋሰ አሰፋ
2. እመቤት ግርማ
3. ዮናስ ከድር
4. እየሩሳሌም ተሰፋው
5. አበራ ኃ/ማርያም
6. አበበ መከተ

በኢሕአዴግ የአዲስ አበባ አደረጃጀቶች ስለ አክራሪነት በተካሔደ ውይይት በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የተሰነዘረው ፍረጃና ክሥ ተሳታፊዎችን አስቆጣ

April 23/2014
  • ውይይቱ ቀጣዩ የአሰላለፍ ስልትና የምት አቅጣጫ የሚወሰንበት ሊኾን ይችላል
  • ተሳታፊዎች ፍረጃዎችንና ክሦችን በመረጃና በሐሳብ የበላይነት ማጋለጥ ይገባቸዋል
AFRO TIMES TUESDAY EDITION
(አፍሮ ታይምስ፤ ቅጽ ፩ ቁጥር ፯፤ ማክሰኞ እና ረቡዕ፤ ሚያዝያ ፲፬ – ፲፭ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም.)
ገዥው ግንባር ኢሕአዴግ በሃይማኖት ይኹን በማንኛውም ሽፋን የሚደረግን የፖሊቲካ ግጭት ለመመከት በሚል በአዲስ አበባ በተለያዩ አደረጃጀቶች ውስጥ ከታቀፉ አባሎቹ ጋራ ውይይት በማካሔድ ላይ መኾኑ ተገለጸ፡፡
በአዲስ አበባ ዐሥር ክፍለ ከተሞች 116 ወረዳዎች ካሉት ሰባት የግንባሩ አደረጃጀቶች ማለትም የሴቶች፣ ወጣቶች፣ መምህራን፣ የመንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች ሠራተኞች፣ የአነስተኛ ጥቃቅን ተቋማት ከእያንዳንዳቸው የተውጣጡ ስድሳ፣ ስድሳ አባላትን ያሳተፈና ሦስተኛ ሳምንቱን የያዘ ውይይት በመካሔድ ላይ ይገኛል፡፡
‹‹የሃይማኖት ተቋማትና ተከታዮች በሰላም አብሮ የመኖር ወርቃማ ተሞክሮና የማስቀጠል ፋይዳው››፣ ‹‹አዲሲቷ ኢትዮጵያና የሃይማኖት ብዝኃነት አያያዝ››፣ ‹‹አክራሪነትና ጽንፈኝነት ከሕገ መንግሥታችን ጋራ ያለው የማይታረቅ መሠረታዊ ቅራኔና መፍትሔው›› በሚሉ ርእሶች በቀረቡ ጽሑፎች ላይ የተመሠረተው ውይይቱ ለአራት ተከታታይ ዙሮች እንደሚካሔድ ተመልክቷል፡፡
‹‹የመደማመጥ መድረክ›› የተሰኙት የመጀመሪያዎቹ ኹለት ዙሮች፣ ከቀረቡት ጽሑፎች ጋራ በተያያዘ የተዘጋጁ የመወያያ ነጥቦችን አስመልክቶ የተሳታፊዎች ግንዛቤና አቋም ምንድን ነው የሚለውን ለማወቅ ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና አቋሞች በስፋት እንዲነሡና በዚህም ስልት በአባላት ውስጥ ያለውን ስሜት በቀጥታ ለማዳመጥ የታቀደበት መኾኑ ተገልጦአል፡፡
ባለፈው ሳምንት በተከናወኑት የውይይቱ ኹለተኛ ዙር መድረኰች÷ በአወያይነት በተመደቡት የወረዳ ጽ/ቤት ሓላፊዎች አማካይነት በየፈርጁ ተጠቃለው ለበላይ አመራር (ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር) ቀርበዋል ለተባሉት የተሳታፊዎች ጥያቄዎች፣ አስተያየቶችና አቋሞች የግንባሩና የመንግሥት አቋሞች፣ መረጃዎችና ዕቅዶች በምላሽነት እንደተሰጡ ታውቋል፡፡
በቀጣይ በሚካሔዱት ኹለት ዙሮች፣ በተናጠል ሲወያዩ የቆዩት የሰባቱ አደረጃጀቶች ስድሳ፣ ስድሳ ተሳታፊዎች በጋራ በመገናኘት በሥልጠና አመለካከታቸውንና ግንዛቤያቸውን ያስተካክሉበታል ተብሎ የሚጠበቅ የማጥራትና የመግባባት መድረክ እንደሚኾን ተጠቁሟል፡፡
በዚኽ መልኩ የሠለጠኑት የየወረዳው 420 የግንባሩ ‹‹የልማትና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ አደረጃጀቶች›› በቀጣይ በተመሳሳይ አጀንዳ ላይ እንደሚጠራ በሚጠበቀው የብዙኃን መድረክ ከሕዝቡ ጋራ ተቀላቅለው በተለያዩ ስልቶች በመሳተፍ መድረኰቹ በታቀደው አቅጣጫ እንዲመሩና ወደተፈለገው መደምደሚያ እንዲደርሱ በማድረግ ድርጅታዊ ተልእኮዎቻቸውንና ስምሪቶቻቸውን እንደሚወጡ ተመልክቷል፡፡
‹‹ጠባብነት፣ ትምክህትና አክራሪነት›› የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከቶች እንደኾኑና ከሕዝብ አቅም ግንባታ አኳያ ዋናው ርብርቡ በእነዚህ ላይ እንደኾነ መንግሥታዊ ጽሑፎች ይገልጻሉ፡፡ ሙስሊሙ ከጠባብነት፣ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኑ ከትምክህት ርእዮት ጋራ የመዳበል ባሕርያት እንደሚታይባቸው የሚገልጹት የመንግሥት ሰነዶች÷ በእኒኽ ባሕርያት በተቃኙ ‹‹ሃይማኖታዊ ርእዮቶች›› ላይ የተመሠረተ ሽብርተኝነትና ሃይማኖታዊ ግጭት ሊፈጠር እንደሚችል ታሳቢ አድርጎ ርእዮቶቹን ‹‹በትምህርትና ሥልጠና፣ በዴሞክራሲያዊ አኳኋን›› መታገልና የለዘብተኝነትና የመቻቻል ባህል እንዲዳብር የተጠናከረ ሥራ መሠራት እንዳለበት ያሳስባሉ፡፡
mahibere kidusanየመንግሥት የመልካም አስተዳደርና ልማት ጉዳዮች ተያይዘው በተነሡባቸው ባለፉት ኹለት የውይይት ዙሮች አንዳንድ የመድረክ አወያዮች ለስብሰባው አካሔድ ተቀምጧል ከተባለው ድርጅታዊና መንግሥታዊ አቋምና አቅጣጫ በተፃራሪ በኦርቶዶክሳዊው ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ያሰሙት ገለጻ፣ የውንጅላና የፍረጃ መንፈስ የተጠናወተው ከመኾኑም በላይ ያልተፈለገ አደገኛ ውጤት ሊያስከትልም እንደሚችል አስጠንቅቀዋል፡፡
በየካ፣ በቦሌ እና በልደታ ክፍላተ ከተማ የተለያዩ ወረዳዎች የተሳተፉ የአፍሮ ታይምስ ምንጮች ስምና ሓላፊነታቸውን ለይተው የጠቀሷቸው አወያዮች÷ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን መዋቅሩን አጥንቶ ፋይናንሱን እኔ ካልያዝሁትና ካልተቆጣጠርሁት ብሏል፤ ስለዚህ አክራሪ ነው››፤ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከሰጠችው ደንብ ውጭ ይንቀሳቀሳል፤ ስለዚህ አክራሪ ነው››፤ ‹‹መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ለመኾኑ አስገራሚ አስገራሚ መረጃዎች አሉት›› የሚሉና የመሳሰሉ ክሦችንና ፍረጃዎችን መሰንዘራቸውን አስረድተዋል፡፡
የት/ቤት(መምህራን) አደረጃጀት አባላት እንዲሁም የስብሰባው ተሳታፊ ካህናት በበኩላቸው፣ በቅርበት ጠንቅቀው የሚያውቋቸው በርካታ የማኅበሩ አባላት መኖራቸውንና ፍረጃውና ክሡ በማስረጃ መደገፍ እንዳለበት አለበለዚያ ማኅበሩን ይኹን አባላቱን ይገልጻቸዋል ለማለት እንደሚያዳግት በመጥቀስ ተቃውመዋል፡፡
አወያዮቹ ማስረጃ እንዲያቀርቡና አነጋገራቸውን እንዲያርሙ በጥብቅ ያስጠነቀቁት ተሳታፊዎቹ፣ ውይይቱ በዚህ መንፈስ የሚካሔድ ከኾነ በተሳትፎ ለመቀጠል እንደሚቸገሩ በማሳወቅ ስብሰባውን ጥለው ለመውጣት ተነሣስተው እንደነበርና አወያዩ አካል መድረኩን መሪዎች በሌሎች በመተካት አስቸኳይ እርማት በማደረጉ በተሳትፏቸው ለመቀጠል እንደቻሉ ተጠቁሟል፡፡
ሌሎች የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተሳታፊዎች በበኩላቸው፣ ማኅበሩ ቤተ ክርስቲያኒቱ አጽድቃ በሰጠችው መተዳደርያ ደንብ መሠረት እንደሚንቀሳቀስና የፈጸማቸውን ዐበይት ማኅበራዊና የልማት ተግባራት፣ የአገልግሎቱ ዕሴቶችና ትሩፋቶች ያስገኙትን አገራዊ ጠቀሜታዎች በመዘርዘር አስረድተዋል፤ በተሰነዘሩት ፍረጃዎችና ክሦች አንጻርም እውነታውን በመግለጽ ፍረጃውና ክሡ ሕገ መንግሥታዊውን ሃይማኖት ነክ ድንጋጌ የሚጥስ ጣልቃ ገብነት ነው በሚል ኮንነውታል፤ በሕግ አውጭነት ሉዓላዊ ሥልጣኗ አገልግሎቱን የፈቀደችለት ቤተ ክርስቲያ እንኳ ያላለችውን ሕዝብን ሰብስቦ ማኅበሩን በአክራሪነት መወንጀል የማኅበሩን ገጽታ በማጠልሸት ከሕዝቡ ለመነጠልና ሕዝቡን በማኅበሩ ላይ ለማዝመት ተይዟል ብለው የሚጠረጥሩት ዘመቻ አካል ነው ብለው እንደሚያዩትም አመልክተዋል፡፡
‹‹ከመቻቻል በላይ በፍቅር እየኖርን ነው፤ ከሕጋዊነትም በላይ በፍቅር እየኖርን ነው፤›› በማለት በመድረኩ ‹መቻቻል› እና ‹የሕግ የበላይነትን ማስከበር› በሚል ከተገለጸው ባሻገር ሕዝቡ በሰላም አብሮ የመኖር ዕሴቶቹን ጠብቆ በፍቅርና በመገናዘብ እየኖረ መኾኑን ይልቁንም በዚህ ረገድ ከአክራሪነትና ጽንፈኝነት ጋራ በተያያዘ የሚሰጡ ማብራሪያዎች አንዱን የድህነትና ኋላቀርነት ሌላውን የሥልጡንነት መለዮ የሚያስመስል ትርጉም እንዳያሰጡ ማስተዋልና ጥንቃቄ ሊደረግባቸው እንደሚገባ ተመክሯል፡፡
በተያያዘም ‹‹ታሪካችን ረዥም ነው የሚለውን ትምክህት መዋጋት›› በሚል ከመጀመሪያው ምእት ዓመት (34 ዓ.ም.) አንሥቶ የሚቆጠረው የቤተ ክርስቲያኒቱ ብሔራዊ ታሪክ በቅ/ሲኖዶስ አባላት ሳይቀር የመንግሥት ሓላፊዎች የተተቹበትና እንዲታረሙም የተጠየቁበት ኾኖ ሳለ ለውይይት በቀረቡት ጽሑፎች ውስጥ በአግባቡ አለመስፈሩ የመጽሐፍ ቅዱሱን እውነታ መቆነጻጸልና ጥንታዊነቷን የማደብዘዝ ውጥን እንዳለ የሚጠቁም ነው ተብሏል፡፡
እስልምና በሰላም ገብቶ እንዲስፋፋ ምክንያት ኾነዋል የተባሉትን ንጉሥ አርማህ ‹‹በወቅቱ የነበሩ ኢትዮጵያዊ ንጉሥ›› ከማለት በቀር ስማቸውንና ክርስቲያናዊነታቸውን በመግደፍ የቀድሞዎቹ ነገሥታት በአጠቃላይ ብዝኃነትን እንደ አደጋ የሚመለከቱና የአንድ ሃይማኖት ፖሊሲ የሚያራምዱ ነበሩ ማለትም በአነስተኛው አነጋገር ቅንነት የጎደለው እንደኾነ ተሳታፊዎቹ ለአፍሮ ታይምስ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
የመድረኩ አወያዮች በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ለሰነዘሯቸው ክሦችና ፍረጃዎች ቅሬታ አቅራቢ ተሳታፊዎችን በግልጽ ይቅርታ መጠየቃቸው ተገልጦአል፡፡ ፍረጃውና ክሡ ለውይይቱ ከተሰጣቸው ተሰብሳቢውን የማዳመጥ አቅጣጫ አልፈው የተናገሩት መኾኑን በማመን መሳሳታቸውን የገለጹትም ‹‹ማንንም እንዳትፈርጁ፣ ‘specific’ እንዳታደርጉ ተብለናል፤ የመላእክት ስብስብ አይደለንም፤ ሰዎች ነንና እንሳሳታለን›› በማለት ነበር፡፡
ይኹንና ይህ ነው የተባለ ማስረጃ ባይጠቅሱም መንግሥት በሕግ የሚጠይቃቸው አንዳንድ ግለሰቦች ሊኖሩ እንደሚችሉ ሳይጠቁሙ አላለፉም፤ መንግሥት በልዩነትና ግጭት ወቅት ሰላምና ጸጥታን ለማስጠበቅ በሚል ካልኾነ በቀር በሃይማኖት ጣልቃ እንደመግባት ተደርጎ የቀረበውን አስተያየትም አልተቀበሉትም፡፡
የውይይቱ ዓላማ ኢሕአዴግ መራሹ መንግሥት ከአባሉና ከአጠቃላይ ሕዝቡ አቋምና ግንዛቤ በመነሣት በትምክህትና ጠባብነት የሃይማኖት አክራሪነት ርእዮት አራማጅነት በሚፈርጃቸው ወገኖች ላይ በቀጣይ የሚይዘውን አሰላለፍና የምት አቅጣጫ ለመወሰንና ይኹንታ ለማግኘት የሚጠቅምበት ሊኾን እንደሚችል ብዙዎች ያምናሉ፡፡
በቀጣዮቹ ኹለት ውይይቶችና ከዚያም በኋላ በታቀዱ የሕዝብ መድረኮች የስብሰባ ጥሪ የተደረገላቸው ኹሉ እስከ አኹን እንደታየው መዘናጋት ሳይሆን በስብሰባ እየተገኙ አካሔዱን በሐሳብና የመረጃ የበላይነት ማጋለጥና ተገቢው አቋም ላይ እንዲደረስ መትጋት እንደሚገባቸው ያሳስባሉ፡፡

በጎንደር 30 ሺህ ቤቶች እንደሚፈርሱ ታወቀ – ‹‹በከተማዋ ውጥረት ነግሷል››

April 23/2014

ጎንደር፡- በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 ከ30 ሺህ በላይ ቤቶች የተገነቡባቸው ሶስት ሰፈሮች ሊፈርሱ መሆኑን በስፍራው የሚገኙ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አስታወቁ፡፡ በከተማዋ ቀበሌ 18 ከተመሰረቱ ከ7 አመት በላይ የሆናቸው አርማጭሆ፣ ገንፎ ቁጭና ህዳሴ የተባሉ ሰፈሮች ውስጥ የተገነቡ ከ30 ሺህ የሚልቁ ቤቶችን እንዲያፈርሱ ለነዋሪዎች ትዕዛዝ በተሰጠበት ስብሰባ የተካፈሉ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡

በስብሰባው ላይ ነዋሪዎቹ፣ ‹‹ህገ ወጥ ከሆነ ያኔ ሕገ ወጥ ነው ልትሉን ይገባ ነበር፡፡ ህገ ወጥ ነው ከተባለስ ይህ ሁሉ ዜጋ በርካታ ገንዘብ አፍስሶ ቤት ከሰራና ለ7 አመት ከኖረ በኋላ ህጋዊ ማድረግ አይቻልም ነበር? ይህም ካልሆነ ተለዋጭ ቦታ ተሰጥቶንና ሰፊ ጊዜና ተለዋጭ ጊዜ ተሰጥቶን
እንጂ በድንገት ተነሱ ልትሉን አይገባም›› የሚል መከራከሪያ ማንሳታቸው ታውቋል፡፡ በተጨማሪም፣ ‹‹እኛ የራሳችን አገርና ቦታ ላይ የምንገኝ ዜጎች ነን፡፡ ቤታችንን የሰራነው ማንም ሳያግዘን በራሳችን ጥረት ነው፡፡ የኤርትራ፣ የሱዳን፣ የሶማሊያ ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው ሲገቡ የሚገባቸው ነገሮች ይሰጣቸዋል፡፡ እኛ ግን ያለምንም ቅድመ ዝግጅት፣ ካሳና ተለዋጭ ታ ሳይሰጠን ቤታችሁን አፍርሱ መባላችን ዜግነታችንም ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ነው›› ብለዋል ነዋሪዎቹ፡፡

የከተማዋ ባለስልጣናት በበኩላቸው፣ ‹‹መንግስት ህገ ወጥ ነው ብሎ የሚያምነውን ሁሉ ማፍረስ መብቱ ው፡፡ አይደለም ጎንደር አዲስ አበባ ውስጥም ቤት ይፈርስባቸዋል፡፡›› በሚል ለማሳመን ሞክረዋል፡፡ ‹‹በዚህ ጊዜ ውስጥ ልጆቻችን ይዘን የት ልንሄድ ነው… ሽማግሌዎችስ የት ይደርሳሉ?›› የሚሉ ሌሎች አንገብጋቢ ጥያቄዎችን አንስተው አጥጋቢ ልስ ያላገኙት ነዋሪዎቹ ከባለስልጣናቱ ጋር ባለመስማማታቸው አብዛኛዎቹ ‹‹ማፍረስ ከተፈለገ እናንተው አፍርሱት እንጂ እኛ አናፈርስም፡፡›› በሚል ስብሰባውን አቋርጠው መውጣታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
ነዋሪዎቹ እስከ ሚያዚያ 7 አፍርሱ፣ ካለፈረሳችሁ እኛው ስለምናፈርሰው እቃችሁን አውጡ ቢባሉም አሁንም ድረስ በአቋማቸው ጸንተው የሚመጣውን ለመቀበል መዘጋጀታቸውን ምንጮቻችን ጨምረው ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ህዝቡ በክረምት ተፈናቅሎ የት ይደርሳል በሚልና እንዲፈርስ በሚፈልጉት

የከተማው ባለስልጣናት መካከል ውጥረት መንገሱን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በተጨማሪም ህዝብን አሳምጻችኋል የተባሉ 12 ሰዎች መታሰራቸውና ከጎንደር በተጨማሪ ቆላ ድባና ሌሎች ከተሞችም ቤቶች እንዲፈርሱ ትዕዛዝ መሰጠቱን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ በተመሳሳይ ከሰሞኑ በባህር ዳር ከተማ ነዋሪዎችን ከማፈናቀል ሂደት ጋር በተገናኘ ህዝብና ፖሊስ በመጋጨታቸው የሰው ህይወት ማለፉ ይታወሳል፡፡

አዲስ አበባ፣ ኦሮምያና ሕገ-መንግስቱ!

April 23/2014

የአዲስ አበባና የኦሮምያ ግንኙነት የፌደራል ስርዓቱ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ጊዜ አንስቶ እያወዛገበ ያለ ጉዳይ ነው። በቅርቡ ደግሞ የአዲስ አበባ አስተዳደር የ10 እና የ25 ዓመት የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላን በማዘጋጀት በተለምዶ “ፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ ከተሞችን ከአዲስ አበባ ጋር ለማቀናጀት ጥረት መጀመሩ ተድበስብሶ ያለፈውን የፌደራሊዝም ጥያቄ እንደገና እንዲያገረሽ አድርጎታል።
የተቀናጀ የጋራ ልማት ፕላኑ በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚገኙ የኦሮምያ ከተሞችን ወደ አዲስ አበባ ሊቀላቅል ነው በሚል ሥጋት በተቃዋሚ ጎራ የተሰለፉ የኦሮሞ ብሔር ፓርቲዎችና በክልሉ ገዢ ፓርቲ ኦህዴድ አመራርና አባላት ጭምር ጥያቄ እየተነሳ ነው። ጥያቄው የመርህ፣ የአፈፃፀም ችግሮችና ሕገ-መንግስታዊ ጥሰትን ያነገበ ቢመስልም በውስጡ ከማንነት ነጠቃ ጋር የተያያዘም መልዕክት አለው። ጥያቄው በመርህ፣ በአፈፃፀም መጓደል፣ የማንነት ነጠቃና ሕገ-መንግስታዊ ጥሰት መፈፀም የታጨቀ በመሆኑም ለመፍትሄ አሰጣጥ አስቸጋሪ አስመስሎታል።
የጥያቄውም አቀራረብ በገዢና በተቃዋሚ ጎራ ባሉ የኦሮሞ ልሂቃን ዘንድ እየተነሳ በመሆኑም ሁኔታውን ውስብስብ ያደረገው ይመስላል። የጥያቄውም ይዘት ቀደም ሲል “ፊንፊኔ የኦሮምያ ናት” የሚለውን ትቶ “ፊንፊኔ ወደ ኦሮምያ መስፋት የለባትም” ወደሚል ተቃውሞ መሸጋገሩም ሌላኛው አወዛጋቢ ሁኔታ ነው። ይህ ሁኔታ በእስራኤልና ፍልስጤም የሚታየውን የዘመናት አለመግባባት በአዲስ አበባ እና በኦሮምያም ይደገም ይሆን ያሰኛል።
በመርህ ደረጃ “ፊንፊኔ የኦሮምያ ናት” የሚል አመለካከት ካለ ከተማዋ ወደየትኛውም የኦሮምያ አካባቢዎች መስፋፋቷን መቃወም የግራን እጅ በቀኝ እጅ ከመቁረጥ አይለይም። በሌላ በኩል ደግሞ አዲስ አበባ እንደ ፌዴራሉ ስርዓት መቀመጫ ማደግና መስፋፋት ይኖርባታል። አዲስ አበባ የሀገሪቱ ሁሉም ሕዝቦች መኖሪያ የአህጉሪቱም መዲና እንደመሆኗ መጠን እድገቷ ወደላይ (Vertical) እንጂ ወደ ጎን (Horizontal) መሆን የለበትም የሚለው የኦሮሞ ሊሂቃን መከራከሪያ በቀጥታ የፌደራል ስርዓቱን በሙሉ ልብ ያለመቀበል ችግር መሆኑን ሊጠቁም ይችላል።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረንስ (ኦፌኮ) ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹና ዋና ፀሐፊው አቶ በቀለ ነጋ “ፕላንና ልማት” በሚል ሰበብ ሕገ-መንግስቱ መጣስ የለበትም ብለው ከሚከራከሩ የክልሉ ተወላጆች መካከል ግንባር ቀደሞቹ ናቸው።
በተለይ አቶ በቀለ ብሔር ብሔረሰቦች መተዳደር ያለባቸው በፌዴራል ስርዓቱ ነው ሲሉ ለሰንደቅ ጋዜጣ በሰጡት አስተያየት ይገልፃሉ። የፌዴራል ስርዓቱን ተማምነንበት የምንኖረው ካልሆነ መሸዋወድ የለብንም ይላሉ። የፌዴራል ስርዓቱ ለኦሮምያ ክልል የሰጠው ድንበር በልማትና በከተማ ልማት ስም ሊጣስ አይገባም። ክልሎችም እራስን በራስ የማስተዳደር መብት በሕገ-መንግስቱ የተረጋገጠላቸው በመሆኑ ሊከበር እንደሚገባም ያስረዳሉ።
አቶ ሙላት ገመቹም በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 49(5) ላይ ኦሮምያ ከአዲስ አበባ ማግኘት የሚገባት “ልዩ ጥቅም” አልተከበረም ሲሉ ሌላ መከራከሪያ ያቀርባሉ። በእርግጥም በተጠቀሰው አንቀፅ ላይ የኦሮምያ ክልል፣ የአገልግሎት አቅርቦት ወይም የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምና የመሳሰሉትን ጉዳዮች በተመለከተ እንዲሁም አዲስ አበባ በኦሮምያ ክልል መሐል የሚገኝ በመሆኑ የሚነሱ ሁለቱን የሚያስተሳስሩ አስተዳደራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ያለው ልዩ ጥቅም ይጠበቃል ሲል ገልጾ ዝርዝር ሕግ እንደሚወሰን ያስረዳል።
የሕገ-መንግስቱን ድንጋጌ መሬት ለማውረድ ዝርዝር ሕግ ማስፈለጉ ይዋል ይደር የሚባል ጉዳይ አይደለም። ያም ሆኖ በኦሮሞ ልሂቃን ዘንድ በተደጋጋሚ የሚነሳው ኦሮምያ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ልዩ ጥቅም ማግኘት አለበት የሚል የአንድ ወገን መከራከሪያ ያቀርባሉ። ይሁን እንጂ በዚሁ ሕገ-መንግስታዊ ድንጋጌ ውስጥ አዲስ አበባም በኦሮምያ ክልል ውስጥ ማግኘት የሚገባት ልዩ ጥቅም ማግኘት እንዳለባትም አሻሚ አተረጓጎም ያለው በሚመስልም አዲስ አበባም እንደ ፌዴራል ከተማ ከኦሮምያ ክልል ማግኘት የሚገባት ልዩ ጥቅም እንዳለም መረዳት ያስፈልጋል።
በሌላ በኩል አዲስ አበባ በድርብ የፌዴራል መንግስቱና የኦሮምያ ዋና ከተማ እንደመሆኗ መጠን የአዲስ አበባን ወደ ጎን መስፋፋት መቃወም ሌላ ጥያቄ ያጭራል። እነ አቶ ሙላት ግን አዲስ አበባ በድርብ የፌዴራል ስርዓቱና የኦሮምያ ክልል ዋና ከተማ ብትሆንም አዲስ አበባ በኦሮሞዎች እየተመራች አይደለችም የሚል መከራከሪያም ያነሳሉ። ይሁን እንጂ ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረና ከተማዋንም በከንቲባነት መተዳደር ከጀመረች ጊዜ አንስቶ በከንቲባነት የሚሾሙ ግለሰቦች ከኦሮሞ ብሔር ብቻ መሆኑን ማስታወስ ይቻላል።
አቶ ሙላትና ሌሎች በገዢውም ሆነ በተቃዋሚው ውስጥ የሚገኙ የኦሮሞ ሊህቃን የአዲስ አበባ መስፋፋት የኦሮምያ የቆዳ ስፋት (Size) ሊያንስ ይችላል የሚሉት በዋናነት የፌዴራል ስርዓቱንና ሕገ-መንግስቱን በመጥቀስ ነው። ነገር ግን ሕገ-መንግስቱም ሆነ የፌዴራል ስርዓቱ መሬት ላይ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር እየተጣጣመ የሚሻሻል እንጂ አንድ ቦታ የሚቆም እንዳልሆነ ይታወቃል። በፌዴራል ስርዓቱ ማዕቀፍ ውስጥ የተዋቀሩ ክልሎችን ድንበር የሀገር ሉአላዊነት አስመስሎ ተለጥጦ ሲቀርብም ይታያል።
የሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 48(1) ስለ ክልሎች አከላለል ለውጦች ያወሳል። በዚሁ ድንጋጌ ላይ የክልሎችን ግንኙነት እንደ “ድንበር” ሳይሆን እንደ “ወሰን” ያቀርባል። በክልሎችም መካከል የወሰን ጥያቄ ሲነሳ ከተቻለ በሚመለከታቸው ክልሎች ስምምነት እንደሚፈታ ያ ካልተቻለ ግን በፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሚወሰን ያስረዳል። የፌዴሬሽን ምክር ቤቱም የሕዝብን አሰፋፈርና ፍላጎት መሠረት በማድረግ እንደሚወስን ተደንግጓል።
በዚሁ ድንጋጌ መሠረት የፌዴሬሽን ምክር ቤት በአዲስ አበባ አስተዳደርና በኦሮምያ ክልል መካከል የወሰን አለመግባባት ሲከሰት የሕዝብ አሰፋፈርና ፍላጎትን መሠረት በማድረግ እልባት እንደሚሰጥ መረዳት ይቻላል። ይህም ማለት ክልሎች በሕገ-መንግስቱ የራሳቸው ወሰን ቢኖራቸውም በጊዜ ሂደት በሚነሱ የልማትም ሆነ የከተማ ልማት እቅድ ጥያቄ ወሰኑን በማሸጋሸግም ሆነ በሌላ አሰራር የሕዝብን አሰፋፈርና ፍላጎት በማየት መፍትሄ እንደሚሰጥ ይጠቁማል። በሌላ አነጋገር አዲስ አበባ ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ያላት ድንበር ላይ ቆማ ትቀራለች ማለት እንዳልሆነ ይልቁኑ በሕዝብ ፍላጎትና አሰፋፈር መሠረት ወሰኗ ወደ ኦሮምያ ክልል እየሰፋ ሊሄድ እንደሚችል መረዳት ይቻላል።
የእነ አቶ በቀለም ሆነ የሌሎች የኦሮሞ ልሂቃን ሌላው መከራከሪያ የኦሮምያ መሬት እየተቆረሰ ለአዲስ አበባ መሰጠት እንደሌለበትና አሰራሩም አንድ ቦታ መቆም እንዳለበት በአፅንኦት ይናገራሉ። ነገር ግን የክልሎችን ስልጣንና ተግባር በሚዘረዝረው የሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 52(2)መ ላይ ክልሎች መሬትና የተፈጥሮ ሐብትን የሚያስተዳድሩት የፌዴራል መንግስቱ በሚያወጣው ሕግ እንደሆነ ይደነግጋል። ይህም ማለት የኦሮምያ ክልል ሕዝብ በሕገ-መንግስቱ ተወስኖ በተሰጠው “ወሰን” ሕዝቡ እራሱን በራሱ የማስተዳደርና የመምራት መብት ቢኖረውም የኦሮምያን መሬትና የተፈጥሮ ሐብት የሚያስተዳድረው ግን የፌደራል መንግስቱ በሚያወጣው ሕግ መሆኑ ሊዘነጋ አይገባውም።
በእነ አቶ በቀለም ሆነ በሌሎች የኦሮሞ ልሂቃን ዘንድ የአዲስ አበባ መስፋፋት የኦሮሞ ተወላጆችን ያፈናቅላል፣ ከከተማዋ የሚወጣው ደረቅና ፈሳሽ ቆሻሻ የኦሮምያን ወንዞች እየበከለ ነው። ከዚያም አለፍ ሲል “የማንነት ነጠቃ” ነው። ቀደም ሲል በነበረው ሀገር የማቅናት ስም የኦሮሞን ሕዝብ እንደገና ገባር ለማድረግ ነው ሲሉም ስጋታቸውን ይገልፃሉ።
በመርህ ደረጃ ሕዝብን ማፈናቀል ሕገ-ወጥነት ነው። በሕገመንግስቱ አንቀጽ 40(4) ላይ የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች መሬት በነፃ የማግኘትና ከመሬታቸውም ያለመነቀል መብታቸው የተከበረ እንደሆነና አፈፃፀሙም በሕግ እንደሚወሰን፤ እንዲሁም በዚሁ ድንጋጌ አንቀፅ ንዑስ አንቀጽ 7 ላይ መንግስት ለሕዝብ ጥቅም ሲል ለሚወስደው መሬትም ሆነ ንብረት ተመጣጣኝ ካሣ እንደሚከፍል ያስገነዝባል። ስለሆነም በአዲስ አበባ መስፋፋት ሳቢያ የሚፈናቀሉ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች ወይም አርሶ አደሮች ተመጣጣኝ ካሣ አግኝተው ሊነሱ ይችላሉ እንጂ አዲስ አበባ አትስፋፋም ብሎ መቃወም የሕገ-መንግስቱን ድንጋጌ መቃወም ሊሆን ይችላል።
ከከተማዋ የሚወጣው አካባቢን የሚበክለው ቆሻሻም በተመለከተ በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 44 ላይ ተደንግጓል። መንግስት ዜጎች ንፁህና ጤናማ በሆነ አካባቢ እንዲኖሩ ኃላፊነቱን ይወጣል እንጂ አዲስ አበባ የኦሮምያን ክልል በቆሻሻ ስለበከለች ብቻ ከተማዋ ማደግና መስፋፋት እንደሌለባት አይደነግግም። በመሆኑም የአፈፃፀምና የመርህ ጥያቄዎችን አደባልቆ በማንሳት የከተማዋን እድገት ባለበት እንዲቆም ማድረግ ተገቢም ተመካሪም አይሆንም።
     የማንነት ነጠቃ እና ከሀገር ማቅናት ጋር ተያይዞ የተነሳው የገባርነት ስጋትም በተመለከተ በሕገ-መንግስቱ መግቢያ ላይ እንደቀረበው በሀገሪቱ ታሪክ አንዱ ሌላኛውን የሚያስገብርበት ስርዓት ግብአተ-መሬቱ መረጋገጡ፣ ይልቁኑ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እራሳቸውን በራሳቸው እያስተዳደሩ መሆኑን ይህም ተግባራዊ መሆኑን ያስረዳል። “የማንነት ነጠቃ” የሚለው አገላለፅም ከጠባብነት አመለካከት ጋር ሊዛመድ እንደሚችልም ያስጠረጥራል። አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ከተሜነትን (Urbanization) የአንድ የተወሰነ ብሔር ማንነት ነጠቃ አድርጎ መወሰዱ ጉንጭ የሚያለፋ ክርክር ሊሆን ይችላል።

ዋና ኦዲተር ለብክነት የተጋለጡ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሒሳቦችን አጋለጠ

April 23/2014

-ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተሰበሰበ ሒሳብ አለ
-785 ሚሊዮን ብር ሕጋዊ ያልሆነ ወጪ ታይቷል
-ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተሠራበት በጀት ተገኝቷል
የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ላለፉት በርካታ ዓመታት ለፓርላማ ሲያቀርበው እንደቆየው ሁሉ፣ ለብክነት የተጋለጠ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የመንግሥት ሀብት መኖሩን ባለፈው ሚያዝያ 14 ቀን 2006 ዓ.ም.
ለፓርላማው ይፋ አድርጓል፡፡ ተመሳሳይ ሪፖርቶችን ሲሰማ የቆየው ፓርላማው ፈጣን ዕርምጃ ከመውሰድ ይልቅ የአንድ ዓመት ገደብን መስጠት መርጧል፡፡

በዝቅተኛ የደመወዝ ክፍያ ምክንያት ሠራተኞችን ለማቆየት መቸገራቸውን የገለጹት የፌደራሉ ዋና ኦዲተር አቶ ገመቹ ዱቢሶ፣ ችግሩን ለመቅረፍ ራሳቸው ጭምር በቡድን መሪነት በተሳተፉበት የ130 የፌደራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶችን የ2005 ዓ.ም. በጀት ኦዲት በማድረግ፣ እንዲሁም በኦዲት ሰርቪስ ኮርፖሬሽን የስምንት መሥሪያ ቤቶችን ኦዲት በማሠራት፣ በአጠቃላይ የ138 መሥሪያ ቤቶችን ኦዲት በመተንተን የኦዲት ግኝቱን ለፓርላማ አቅርበዋል፡፡

ከቀረበው የፋይናንስ ሕጋዊነትን የተመለከተ የኦዲት ሪፖርት ውስጥ አንድ ቢሊዮን 527 ሚሊዮን ብር ተሰብሳቢ ሒሳብ መኖሩን፣ ሕጋዊ ሥርዓቱን በልተከተለ መንገድ የተለያዩ የመንግሥት ድርጅቶች 785 ሚሊዮን ብር ወጪ ማድረጋቸውን፣ የተፈቀደው በጀት በትክክል ሥራ ላይ መዋሉን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት ደግሞ 2.3 ቢሊዮን ብር ያልተሠራበት በጀት መገኘቱን ይፋ አድርገዋል፡፡

ውዝፍ ተሰብሳቢ ሒሳብ ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት በወቅቱ ካልተወራረደ ወይም ካልተሰበሰበ በቆየ ቁጥር የመሰብሰብና ወደ ሀብትነት የመለወጥ ዕድሉ አሳሳቢ መሆኑን የገለጹት ዋና ኦዲተሩ፣ ኦዲት ከተደረጉት መሥሪያ ቤቶች 77 በሚሆኑት ላይ 877.1 ሚሊዮን ብር በደንቡ መሠረት ሳይወራረድ መገኘቱን አስረድተዋል፡፡ 

ከላይ ከተጠቀሰው ያልተወራረደ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሒሳብ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ ከያዙት መካከል በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ቴክኒክ ሙያና ትምህርት ሥልጠና ማስተባበሪያ 173.6 ሚሊዮን ብር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 149.5 ሚሊዮን ብር፣ የትምህርት ሚኒስቴር 100 ሚሊዮን ብር ይገኙበታል፡፡

ዋና ኦዲተር የመንግሥት ገቢ በአግባቡ መሰብሰቡን ለማጣራት ባካሄደው ኦዲት 32.2 ሚሊዮን ብር ከገቢ ግብር፣ ከቀረጥና ታክስ እንዲሁም ከሌሎች ገቢ መሰብሰብ በሚፈቅዱ ደንቦች መሠረት አለመሰብሰቡን አረጋግጧል፡፡

ገቢ ሰብሳቢ መሥሪያ ቤቶችና ድርጀቶች አግባብ ባለው ሕግና ደንብ መሠረት የመንግሥት ገቢ በአግባቡ መሰብሰባቸውን ለማረጋገጥ በተደረገ ኦዲት 326.7 ሚሊዮን ብር ያልተሰበሰበ ውዝፍ ገቢ መኖሩ ተረጋግጧል፡፡ አብዛኛው ይህ ውዝፍ ያልተሰበሰበ ገቢ የሚመለከተው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንን እንደሆነ ከኦዲት ሪፖርቱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንን በጊዜያዊነት ወደ አገር የሚገቡ ዕቃዎች የጊዜ ገደባቸውን ካጠናቀቁ በኋላ፣ የጊዜ ገደቡ በሕግ አግባብ እንዲራዘም ካልተደረገ በስተቀር በዋስትና የተያዘውን ገንዘብ የመውረስ መብት በሕግ ተሰጥቶታል፡፡ ነገር ግን በጊዜያዊነት ገብተው የመቆያ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ በድምሩ 222.5 ሚሊዮን ብር የዋስትና ገንዘብ አለመሰብሰቡን የኦዲት ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

‹‹የሚሰበሰብ ገቢ መንግሥት ለሚያከናውናቸው የልማትና ማኅበራዊ አገልግሎቶች መስፋፋትና ለአገሪቱ የዕድገትና ትራንስፎሜሽን ዕቅድ መሳካት ወሳኝ ሚና የሚኖረው በመሆኑ፣ የመንግሥት ሕግና ደንብ ተከብሮ መሠራት አለበት፤›› ሲሉ ዋና ኦዲተሩ አቶ ገመቹ አሳስበዋል፡፡

ሕጋዊነት የጎደላቸው ወጪዎችን በተመለከተ ባቀረቡት ሪፖርት 785 ሚሊዮን ብር አግባብነት የጎደላቸው ወጪዎች መኖራቸውንም አስረድተዋል፡፡ ከዚህ ውስጥ በዋነኝነት የሚጠቀሰው በ25 መሥሪያ ቤቶች በወጪ ተመዝግቦ ነገር ግን የወጪውን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ማስረጃ ሊቀርብበት ያልቻለ 202.6 ሚሊዮን ብር በወጪ ተመዝግቦ ተገኝቷል፡፡

የግዥ አዋጁን እንዲሁም ደንብና መመርያን ያልተከተሉ ግዥዎችን በተመለከተ ደግሞ፣ 43 መሥሪያ ቤቶች 165.9 ሚሊዮን ብር ደንብና መመርያን በመጣስ ወጪ አድርገዋል ብለዋል፡፡ ሌሎች 41 መሥሪያ ቤቶች ደግሞ 76 ሚሊዮን ብር ደንብና መመርያን በመጣስ ክፍያ መፈጸማቸውን በሪፖርታቸው ገልጸዋል፡፡

ሒሳቦች በወጪነት የሚመዘገቡት የሚፈለገው አገልግሎት መገኘቱን ወይም የሚፈለገው ንብረት በአግባቡ በእጅ መግባቱ ሲረጋገጥ ቢሆንም፣ 13 መሥሪያ ቤቶች አገልግሎቱን ወይም ንብረቱን ሙሉ በሙሉ ሳያገኙ የከፈሉትን የ234.8 ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ በወጪ መዝገብ ይዘው ተገኝተዋል፡፡ በመሆኑም የተፈለገው አገልግሎት ወይም ንብረት ሙሉ በሙሉ እስኪፈጸም ድረስ በተሰብሳቢ መያዝ ይኖርበታል የሚል አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

በ104 መሥሪያ ቤቶች ደግሞ ለተለያዩ ግዥዎች አራት ሚሊዮን 471 ሺሕ ብር ያላግባብ በብልጫ መከፈሉን የኦዲት ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በተጨማሪም በአሥር መሥሪያ ቤቶች የንብረት ገቢ ደረሰኝ ያልቀረበለት 22.6 ሚሊዮን ብር ወጪ መኖሩን፣ በሌሎች ሰባት መሥሪያ ቤቶች ደግሞ 1.6 ቢሊዮን ብር ቀረጥ የተከፈለባቸው ንብረቶች ገቢ መሆናቸውን ለማረጋገጥ አልተቻለም፡፡

ቀረጥ ተከፍሎባቸው ንብረቶቹ ገቢ ለመሆናቸው ለማረጋገጥ ካልተቻለባቸው መሥሪያ ቤቶች ትልቁን ድርሻ የያዘው፣ የቅድሚያ ማስጠንቀቂያና ምላሽ ዳይሬክቶሬት ሲሆን፣ በቀጣይነት ደግሞ ጤና ጥበቃና ትምህርት ሚኒስቴር ተጠቅሰዋል፡፡

በ23 መሥሪያ ቤቶች የወጪውን ትክክለኛነት ማረጋገጥ ያልተቻለ 90.9 ሚሊዮን ብር መኖሩን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ 

የፌደራል መንግሥት ግዥ አፈጻጸም መመርያ በግንባታ ቦታ ላይ ላሉ ዕቃዎች፣ ወይም ግንባታ ላይ ላልዋሉ ክፍያ መፈጸምን የሚከለክል ቢሆንም፣ 11 መሥሪያ ቤቶች ይህንን በመጣስ 168.6 ሚሊዮን ብር መክፍላቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ መንግሥት የግንባታ ዕቃዎችን በብድር ሲያገኝ የተገኘው ቁስ መጠን ተሰልቶ ከግንባታ ወጪ ላይ መቀነስ የሚገባው ቢሆንም፣ አራት መሥሪያ ቤቶች ግን 18.3 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ በብድር የተገኙ የግንባታ ዕቃዎች ወጪን ሳይቀንሱና ለመንግሥት ካዝና ሳያስገቡ በኦዲቱ ተገኝተዋል፡፡

የተፈቀደላቸውን በጀት በትክክል ለሥራ አውለዋል ወይ የሚለውን ለማጣራት በተደረገ ኦዲት ደግሞ፣ በ96 መሥሪያ ቤቶች 2.3 ቢሊዮን ብር ያልተሠራበት በጀት ተገኝቷል፡፡ ይህ ሪፖርት ከቀረበ በኋላ መድረኩ ለውይይት ክፍት የነበረ ቢሆንም፣ የፓርላማው አባላት በቁጭትና በእልህ እንዳለፈው ዓመት ሲናገሩ አልተስተዋሉም፡፡

ብቸኛው የፓርላማ የግል ተወካይ የሆኑት ዶ/ር አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ የኦዲት ሪፖርቱን አስመልክተው፣ ‹‹በዚህ አገር ማንም ምንም ሊያደርግ አይችልም የሚሉ ባለሥልጣናት ያሉ ይመስለኛል፡፡ እርስዎ እንደዚያ ያስባሉ ወይ?›› የሚል ጥያቄ ዋና ኦዲተሩን አቶ ገመቹ ዱቢሶን ጠይቀዋል፡፡

አቶ ገመቹ ዱቢሶ በሰጡት ምላሽ፣ እንዲዚህ ዓይነት አስተሳሰብ ይኖራል ብለው እንደማይገምቱ፣ ነገር ግን ችግር መኖሩን እያወቁ የማያስተካክሉ ኃላፊዎች መኖራቸውን፣ አንዳንድ ጊዜ በሒሳብ ባሙያዎች የሚታለሉ ኃላፊዎች እንዳሉ መረዳታቸውን ገልጸዋል፡፡

መደረግ የሚገባውን በተመለከተ በዶ/ር አሸብር ለተነሳው ጥያቄ ዋና ኦዲተሩ የሰጡት ምላሽ በዋና ኦዲተርና በአፈ ጉባዔው መካከል በተደረገ ስምምነት በ2006 ዓ.ም. የኦዲት ሪፖርት ላይ የሚገኙ የኦዲት ግኝቶች እስካሁን በነበረው ግዝፈት የሚቀጥሉ ወይም የማይሻሻሉ ከሆነ፣ ሕጋዊ ቅጣት በመሥሪያ ቤቶቹ ኃላፊዎች ላይ ለመውሰድ ስምምነት መኖሩን አስረድተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የፓርላማው ቋሚ ከኮሚቴዎች የሚከታተሏቸውን አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች በይበልጥ መጠየቅ እንደሚገባቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ሚያዝያ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. የ2006 ዓ.ም. የዘጠኝ ወራት ሪፖርት ለማቅረብ በፓርላማው የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በዚህ ጉዳይ ላይ በስፋት ጥያቄ ይቀርብላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ 

እውቅና የተሰጠው የሚያዚያ 26ቱ የአንድነት ሰልፍ በደህንነቶች ትእዛዝ እውቅና ተነፈገ

April 23/2014

ከአዲስ አበባ የደረሰን ዜና እንደሚጠቁመው፣ የአንድነት ፓርቲ ሚያዚያ 19 ሰልፍ ለማድረግ ቢጠይቅም፣ የፖሊስ አዛዞች በዚያን ቀን በቂ ጥበቃ ማዘጋጀት አንችልም በማለታቸው፣ አስተዳደሩ ሚያዚያ 26 ቀን እንዲደረግ ጠይቆ የነበረ ሲሆን፣ ለሚያዚያ 26 የእውቅና ደብዳቤ ለመዉሰድ ወደ አስተዳደሩ ጽ/ቤት ያመሩት የአንድነት ከፍተኛ አመራሮች፣ የእውቅና ደብዳቤ ሳይቀበሉ መመለሳቸውን ያነጋገርናቸው የአንድነት አመራር አባል ገለጹ።
የአስተዳደሩ ሃላፊዎች፣ ከደህንነት ጽ/ቤት ለአንድነት ሰልፍ እውቅና እንዳይሰጡ በቀጥታ መታዘዛቸዉን የገለጹት የአንድነት አመራር ፣ አዲስ አበባ በከንቲባው ሳይሆን፣ የአዲስ ሕዝብ ባልመረጣቸው ከበስተጀርባ ሆነው በሚፈልጡና በሚቆርጡ ጥቂቶች መዳፍ ስር የወደቀችና በአምባገነኖች የምትገዛ መሆኑን አመላካች ነው ብለዋል።
አንድነት ፣ ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ፣ ሰልፍ ለማድረግ በአገዛዙ እውቅና ያልተሰጠበት የሚያዚያ 26 ቀኑ፣ አራተኛው ቀን ሲሆን፣ ከፋሲካ እሁድ ዉጭ ባሉ ሶስት እሁዶች ፣ መጋቢት 28፣ ሚያዚያ 5 እና ሚይዚያ 19 ቀንም ሰልፍ ለማድረግ ተጠይቆ በደህንነቶች ትእዛዝ እውቅና አለመሰጠቱ ይታወቃል።
ከሰልፍ ጋር በተገናኘም የአዲስ አበባ አስተዳደር ሚያዚያ 19 ቀን ሰልፍ ለማድረግ አንድነት ፓርቲ ጠይቆ እውቅና አልሰጥም ቢልም፣ ለአንድነት በተከለከለበት ቀን ለሰማያዊ ፓርቲ እውቅና እንዲሰጥ የደህንነት ሃላፊዎች መመሪያ መስጠታቸውን፣ በአዲስ አበባ ያሉ ምንጮቻችንን በመግለጽ መዘገባችን ይታወቃል።
በአንድነት ፓርቲ ላይ እየተደረገ ያለው ሕግ ወጥ እርምጃ፣ ከአስተዳደሩ ዉጭ ያሉ የደህንነት ሃላፊዎች፣ በቀጥታ የአስተዳደሩ የሰማያዊ ሰልፍ ፍቃድ ኦፊሰር የሆኑትን፣ አቶ ማርቆስን ፣ በማዘዝ እየፈጸሙት ያለ አሳዛኝ ተግባር እንደሆነ የገለጹት የአንድነት አመራር፣ ከከንቲባው ጽ/ቤት ሃላፊዎች ጋር የፓርቲዉ ከፍተኛ አመራሮች ችግሮችን ለመፍታት በስፋት እንደተነጋገሩ ገልጸዋል። አንድነት ሚያዚያ 19 ቀን ጠይቆ ፣ «ሌላ ዝግጅት አለ። በቂ ጥበቃ የለም» በሚል ሚያዚያ 26 ማድረግ እንደሚቻል እንደተነገራቸው የገለጹት የአንድነት አመራር፣ አሁን ሌሎች ድርጅቶች በሚያዚያ 19 ሰልፍ እንዲጠሩ እውቅና ለመስጠት መዘጋጀቱ፣ በቂ ጥበቃ ከየት ሊገኝ ቢችል ነው በሚል የአስተዳደሩን ሃላፊዎች ጠይቀዋል።
የአስተዳደሩ ሃላፊዎች ጉዳዩን ተከታትለው፣ ነገ ሚያዚያ 15 ቀን እንደሚያሳውቋቸው መግለጻቸዉን፣ የሚናገሩት የአንድነት አመራር አባል፣ አስተዳደሩ መጀመሪያ ለጠየቀዉ ፓርቲ፣ አስፈላጊዉን ቅድሚያ እንደሚሰጥና ሕግን አክብሮ በሕግ የተደነገገለትን ሃላፊነት እንደሚወጣ፣ ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
በሃያ ሶስቱም የአዲስ አበባ ወረዳዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ አባላትና ደጋፊዎች እንዳላቸው የገለጹት የአመራር አባሉ፣ አስተዳደር እውቅና ሰጠ አልሰጠም፣ በቅርብ ቀናት ዉስጥ ለሚያዚያ 19 ይሁን ሚያዚያ 26 ቅስቀሳ እንደሚጀምር አሳወቀዋል።
አገዛዙ የዜጎችን መብት ማፈን እንደማይችል ያስረዱት አመራር አባሉ፣ አንድነት በሰለጠነና በመግባባት ፖለቲካ ቢያምንም፣ ሕግ መንግስቱ የሚደነግግለት መብት ላይ እንደማይደራደር አረጋግጠዋል። «ሰልፉ ይደረጋል። ጥያቄዉ ፖሊስ ሕዝብን ይጠብቃል ወይንስ ከሕዝብ ጋር ይጋጫል? የሚለው ነው» ሲሉ ነበር የአንድነት ቁርጠኝነት ለማሳየት የሞከሩት።
ፓርቲዉ በዚህ ረገድ፣ እየትሰራ ያለዉን ደባ ለማጋለጥና ሕዝብ አጥርቶ እንዲያወቀው ለማድረግ፣ በመረጃ ላይ የተደገፈ መግለጫ እንደሚሰጥም ለማወቅ ችለናል።
የአዲስ አበባ አስተዳደርና አንድነት ከመግባባት ደረጃ ደርሰው፥ የታቀደው ሰልፍ ሕጉን በጠበቀ መልኩ ሚያዚያ 19 ይሁን ሚያዚያ 26 ይደረግ እንደሆነ፣ ያ ካልሆነ ደግሞ የአንድነት ፓርቲ ዉሳኔ ምን እንደሚሆን ተከታትለን ለማቅረብ እንሞክራለን።

Tuesday, April 22, 2014

ካልገደሉ አያቆሙንም – ሃብታሙ አያሌዉ (የአንድነት አመራር) ሰልፉን በተመለከተ

April22/2014

ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ፣ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ ባይሆንም፣ ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 26 የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡
የሰላማዊ ሰልፍ እውቅናን በተመለከተ ኃላፊ የሆኑት አቶ ማርቆስ ፎርም እንዲሞላ አዘዙ፤ የተባለውን ፎርም ሞላን፤ ያን ጊዜ የአቶ ማርቆስ የቢሮ ስልክ አንቃጨለ፤ አነሱት ……ቀጭን ትዕዛዝ ከወዲያ ማዶ……………
‹‹የአንድነትን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይቆይ›› አቶ ማርቆስ ፊቱ ተለዋወጠ ‹‹ ይቅርታ አድርግልኝ የኔ ችግር አይደለም›› ሌላ ቃል ካፉ አልወጣም፡፡
«አልገባኝም ….ቀጠልኩ ….የአንድነት ሰላማዊ ሰልፍ ተከለከለ እያልከኝ ነው ? »
መለሰ …..«እኔ ምን ላድርግ ? …..»
«የከለከለው ማነው የበላይ ኃላፊ ነው ? »
«አዎ» አጭር መልስ፡፡
ትቼው ወደ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊው አመራሁ፤ ስብሰባ ላይ ናቸው፡፡ ወደ ፓርቲ ጽ/ቤት ደውዬ ሁኔታውን አሳወኩ። የፓርቲው ፕሬዘዳንት ኢንጅነር ግዛቸውን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ፈጥነው ደረሱ፡፡ የአስተዳደሩ ስብሰባም ለሻይ እረፍት ተቋርጦ ኃላፊው ወደ ቢሯቸው ሲገቡ ተከታትለን ገባን፡፡ ላለማናገር ጥቂት አንገራገሩ ። የቢሯቸውን በር አንቀን አናግሩን በማለት ጸናን፡፡
‹‹ምንድነው ችግሩ የሰልፉ ጉዳይ ከሆነ ጨርሰናል፤ እውቅናውን ወሰዳችሁ አይደለም ? ›› አሉ።
ባጭሩ መልስ ተሰጣቸው ፤ «አልወሰድንም ። የአቶ ማርቆስ መልስ ተከልክሏል የሚል ነው፡፡ »
ጥያቄ አስከተልን ……«እርሰዎ መረጃ የለዎትም ? መንግስታዊ ኃላፊነቱ የርስዎ ነው፤ ማነው ከልካዩና ፈቃጁ ? »
መልስ የለም ። ጥቂት ዝም ብለው ‹‹የጠየቃችሁን ሚያዚያ 19 ለማድረግ ነበር፡፡ በዚያ ቀን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የጥበቃ እጥረት አለብኝ በማለት ስላመለከተ የእናንተ ሰልፍ ለሚያዚያ 26 እንዲደረግ ጠየቅናችሁ ። ተስማማን ከዚህ ውጪ የተደረገ ነገር ካለ በኔ በኩል መረጃ የለኝም። ማን እንደከለከለ አናውቅም››
« ስለዚህ ይህንን ከተማ ከንቲባው ካልሆነ ማን ነው የሚመራው? »
ከወዲያ ማዶ መልስ የለም……….ስልክ አነሱ እና አቶ ማርቆስን ወደ ቢሯቸው ጠሩ ። ሰውዬው መጡ ። ማጣሪያ ተጠየቁ። «መመሪያ ደርሶኛል» ሲሉ ለከንቲባው ጽ/ቤት ኃላፊ በኛው ፊት ተናገሩ፡፡ «መመሪያ ሰጪው ማነው?» ወደ አንዱ ቢሮ ዘው ብለን አንድ ሰው አናገርን ………..
‹‹እባካችሁ ይቅርባችሁ ደህንነቶቹ የሚውሉት እዚህ ግቢ ነው፡፡ አንድነቶች ከወጡ እርምጃ ይወሰድ ሲሉ ሰምቻለሁ›› አለን በማንሾካሾክ ድምጽ ………….
ጎበዝ ይሙት ሰነፍ ይኑር ቢሻው
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው………..
ፍርሃት ማነው ቢሉኝ ስሙን አላውቀውም
ሞትን በቁሜ እንጂ ሞቼ አልጠብቀውም፡፡
………………..ህወሓት ሊተኩስ ተዘጋጅቷል እኛም የነሱን ጥይት የሚሸከም ደረት …….እመነኝ ካልገደሉ አያቆሙንም፡፡፡

Ethiopia: Trapped By a Crippled Telecom

22 APRIL 2014 -
A soaring number of option-deprived customers and eye-watering packages continue to swell the earnings of the state monopoly Ethio telecom. In return the inglorious institution kept on crippling everything this country has achieved in the past with banks being the hardest hit Kalkidan Yibeltal
In February this year, while hosting his third presser with the local media since he assumed office as Prime Minister of Ethiopia, Hailemariam Desalegn was resolute in his response to a question from this magazine on whether or not his government was willing to assess the impact of running a dysfunctional state run telecommunication company on the economy.
His government, PM Hailemariam said, was not ready to privatize the telecom sector, “Not now, not in the near future.” Needless to say, that was not the right answer to the question, but it is the incumbent’s long held stand on the state monopoly, Ethio telecom. The giant service provider is spoiled by grave impairments and is often a source of growing public frustration.
Yet a soaring number of option-deprived subscribers especially to mobile phones and its eye-watering packages continue to swell its earnings. In the past six months alone Ethio telecom has amassed some $350 million (7 billion br.) in revenue. Numbers like this corroborate the ruling party’s recurring reference to the sector as a ‘cash cow.’
But it is a cash cow that is wreaking havoc to almost everything this country has achieved in the past two decades, particularly to most of the things the nation’s infant banking sector wanted to accomplish as of late.
Shake off traditional banking, and get stuck with a mediaeval telecom:
Three years after the collaps of the military Dergue regime in 1991, the country’s central bank, the National Bank of Ethiopia (NBE), was reconstituted by the Monetary and Banking Proclamation No 83/1994 as an autonomous financial regulatory organ. And more importantly, the subsequent Licensing and Supervision of Banking Business No 84/1994 laid down the legal basis for the participation of the private sector in the banking business.
The first privately owned commercial bank, Awash International (AIB), therefore, came into existence shortly afterwards. Today the Ethiopian banking industry comprises of 15 more private and two state owned commercial banks as well as one state owned development bank.
A dynamic move in opening new branches by many of these banks saw a dramatic fall in the bank-branch-to-population ratio from 1: 116, 847 in 2009/10 to 1: 69, 000 in 2011/12. The recent figures indicate the ratio might even be lower than 1: 50, 000, according to a data obtained from the NBE. However, Ethiopia’s law prohibits foreign nationals from involving in the financial sector, impending, among others, negotiations of accession to World Trade Organization (WTO), a process that has begun as far back as 2003, NBE admits.
The toddling domestic banks are not financially, technically and technologically competitive either, compared to the sector in neighboring countries, for example; liberalization of the sector is may be one issue, but it is not everything to it. Cocooned from global banking heavyweights, the localbanks are moving at a snail’s pace towards modern banking trends.
There are many reasons for that of which having a dysfunctional telecom system is the giant one. As part of the NBE’s national payment system, all authorized banks are required to acquire Centralized online Real-time Electronic System (Core banking), which creates an electronic link that enables a given bank’s branches access applications from centralized data centers. So far, about twelve banks have completed the implementation and interface of core banking, NBE told Addis Standard. Five banks have completed the implementation and are in the final stages of interface. The remaining two banks are in the procurement process.
Bank
Number of ATMs by a bank (2013)
CBE 120
Dashen 105
Wogagen 27
The state owned Commercial Bank of Ethiopia (CBE), which is going through a massive crusade of branch expansion since the past few years, opened 150 new local bank branches all over the country in 2013 alone, raising the number of its branches to 780 as of the end of the stated year and enabling it to sustain the quasi monopolistic power it holds – some estimate the CBE mobilizes around 80% of the country’s finances.
When the biannual report of CBE for 2013/14 (2005/6 Ethiopian calendar) fiscal year was presented in February this year in the lakeside city of Bahir Dar, the capital of the Amhara regional state 578 km North of Addis Abeba, the bank has announced that 470 of its branches were networked with Core banking solutions technology. It was possible to install 368 Automated Teller Machines (ATMs) and 367 Point of Sale (PoS) machines as well. As of September 30, 2013, the number of banks providing ATM services reached seven, collectively possessing 562 machines.
By 2013 Dashen Bank, the pioneer to start the service, has 105 ATMs and 254, 933 cardholders, making it the largest from the private banks in the country. It also offers 780 PoS terminals. Three banks, Awash International Bank (AIB), Nib International Bank (NIB) and united bank, have launched Premium Switch Solutions (PSS) S.C. to help them provide ATM services by deploying shared switch card payment system machines. A forth bank, Berhan International, has joined this group recently while a fifth one, Addis International Bank, is on the way.
After announcing the winning bidder that will supply 100 ATMs and 80 PoS terminals in May 2013, AIB became the second largest from the private banks to operate ATMs and PoS terminals in the country next to Dashen.
Some of the ATMs are being installed within bank branches, while the rest, known as lobby ATMs, are being installed in hotels and shopping malls. In theory, customers who hold AIB cards can get the service for free while customers of other banks under the umbrella of PSS will be charged 40 cents for every 100 birr withdrawal. Most banks in Ethiopia do not charge their customers at every ATM withdrawal to encourage the practice.
Head to Head
No of commercial banks
Kenya 43
Ethiopia 19
ATMs
Kenya 2205
Ethiopia 562
Internet penetration
Kenya 9.7
Ethiopia 0.1
Fixed broadband prices as %of GNI P.C
Kenya 49.3
Ethiopia 71
No network no money:
Apart from technical problems such as the breaking down of the machines or the deterioration of money notes, currently a major problem facing ATM services in Ethiopia is attributed to network failures, according to a document by the NBE. In the same manner the unreliability of telecom services is put forward as one of the challenges in implementing core banking.
In their study titled “Competition in Ethiopian Banking Industry” published on The African Journal of Economics in December 2013, Zerayehu Sime, Kagnaw Wolde and Teshome Ketama maintain “in less monetized countries like Ethiopia, whilst financial sector is dominated by banking industry, effective and efficient functioning of the latter has significant role in accelerating economic growth.” However recent telecom realities appear to make that road to efficiency and effectiveness intolerably bumpy.
Customers of banks in Addis Abeba and in major towns throughout the country are well acquainted with the unfortunate times when there is no internet connection at all not only for hours but for days. It is also becoming routine that hundreds of employees had to wait for days to get their salaries. Equally familiar is the sight of customers queuing around a network deprived ATM machine, hoping in despair that it may start working any minute.
The city’s hotels and recreational centers that have helped the service sector contribute to a tune of 46% to the national GDP are unable to host guests because of non-responding PoS machines. Ethio telecom, which has 27 million mobile phone and 4.5 million internet subscribers as of mid February 2014, complains 80% of its network problem is caused by the incessant power cuts, a claim that convinces no one. For starters it is Ethio telecom’s responsibility to prepare abackup power source, something banks are forced to do, according to a banker.
For banks that have interlinked all or many of their branches in core banking system, power outage around the headquarters where the central server is located means unless they have a power backup they are unable to conduct business in all the connected branches.
So they set up backup generators, although it means adding extra operational cost. But what they can’t do is have a replacement scheme to run the internet when it is no longer available.Occasionally when the cable networks are problematic, banks use expensive Enhanced Voice-Data Optimized (EVDO) network. But it is not unusual that both the cable and EVDO networks are unavailable at the same time.
An employee of a private bank who requested to remain anonymous told Addis Standard that many banks take three measures to tackle these difficulties. First, in the absence of sufficient information due to their inability to access the central data, branch managers sometimes risk in handling their known customers by offering them basic services without cross checking with their online database.
Second, many banks are forced to look into offline solution, which allows each bank branch to assemble enough data to be able to carry on offering limited services in the absence of connection to the main server. Third, some banks are attempting to strike a deal with Ethio telecom to enable them obtain exclusive network services from the later.
On top a mobile banking?
In a conference titled “Catalyzing Transformation through Technology: How Mobile Financial Services Contribute to the Growth of Ethiopia”, held in early February this year here in Addis Abeba, Dr. Debretsion Gebremichael, Minister of Communication and Information Technology (MCIT), with the rank of Deputy Minister, said that 80% of Ethiopians, currently estimated to be above 90 million, reside in rural areas.
“Because of that financial institutions have been unable to reach the majority of these people,”he said. Alternative ways to reach those people must be found, he said, adding it was his government’s belief that cheaper financial services with a better quality can be accessible. But that is an apple pie in the sky; something Ethio telecom can’t bring in as of yet.
In his 2012 study titled “Prospects and Challenges of Private Commercial Banks in Ethiopia,” Simeneh Terefe of the Department of Economics at Unity University identifies lack of appropriate technology and inflation as a major challenge banks in Ethiopia are facing today. In most parts of Africa mobile banking has revolutionized access to finance serving as a virtual bank, a PoS terminal, an ATM and an internet banking terminal all together when need be. In most Sub Saharan Africa, where having bank accounts is not common, mobile banking is offering an opportunity to millions of unbanked people.
Unfortunately though, it is a technology bypassing Ethiopia, one of the “fastest growing economies” in Africa, according to World Bank, and a country that is generating “more millionaires” than countries such as Tanzania and Ghana, according to New World Wealth.
For now Banks in Ethiopia have set their eyes fixed on bank branch expansion as a way of reaching out to more customers – a costly and ineffective move for financial institutions to venture into. Unfortunately however, the government of Hailemariam Desalegn thinks it is better to keep the ‘cash cow’ as it is than calculating the chaos it imposes on everything this country has achieved from the financial to the service providing industry.
Posted in: Africa, Entertainment, Op/Ed