Sunday, June 16, 2013

ኢሳትን ሲመለከቱ የነበሩ 60 ሰዎች መታሰራቸው ተሰማ

ሰኔ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በባሌ ሮቤ እና በጎባ ከተማ በቅርቡ ኢሳትን ሲመለከቱ የተገኙ ሰዎች ገናሌ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት ውስጥ መታሰራቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።

ግለሰቦቹ የተያዙት በተለያዩ ሰበቦች ቢሆንም ፍርድ ቤት ሲቀርቡ የሚቀርብባቸው ክስ ግን የተቃዋሚ ጣቢያ የሆነውን ኢሳትን ሲመለከቱ ተገኝተዋል የሚል ነው።

ከታሰሩት መካከል ወጣቶች እና አረጋውያን እንደሚገኙበት የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

የፕሬስ ነጻነት ተከብሮአል በሚባልባት ኢትዮጵያ የባሌ ሮቤ እና ጎባ ከተማ ባለስልጣናት የወሰዱት እርምጃ ተገቢ አለመሆኑንና የተያዙት ግለሰቦች እንዲፈቱ የኢሳት ማኔጅመንት ጠይቋል። ማንኛውም ዜጋ ከየትኛውም አቅጣጫ የሚመጣን መረጃ ያለምንም ተጽኖ ማግኘት እንደሚችል በህገመንግስቱ የተቀመጠ መብት መሆኑን የገለጸው ማኔጅመንቱ፣ ህበረተሰቡ አንዳንድ ባለስልጣናት አለቆቻቸውን ያስደሰቱ እየመሰላቸው በሚወስዱት እርምጃ ህብረተሰቡ ሳይደናገጥ ኢሳትን መመልከቱን እንዲቀጥል  ፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትም የታሰሩ ሰዎች በአፋጣኝ እንዲፈቱ እንዲያደርግ ጠይቋል።

ኢሳት ካለፉት ስድስት ወራት ጀምሮ ስርጭቱን በቀጥታ በተሌቪዥን ለኢትዮጵያውያን እያስተላለፈ ይገኛል

No comments: