Thursday, June 6, 2013

በግብጽ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው

በዛሬው እለት ለማለዳ ታይምስ ቅርበት ያላቸውን ወገኖች እንዳነጋገርናቸው ከሆነ በግብጽ መንግስት ክፉኛ የሆነ ክትትል እየተደረገብን ነው
እኛ ምንም አቅም የለንም በስራም በኩል ሆነ በጎዳናዎች ላይ ህብረተሰቡ ጥላቻውን አድርቶብናል ፣በተለያዩ ካፍቴሪያዎች ወንድሞቻችን እና
እህቶቻችን ተደብድበዋል በማለት ስሜታቸውን የገለጹት በተለይም በአሁኑ የኢትዮ-ግብጽ አጣብቂኝ ሁኔታ ሁላችንንም ውስጥ በመከራ
ከቶናል ሲሉ ተናግረዋል ።
በግብጽ የሚገኘውም የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ማናቸውንም ዜጎች ለጊዜው ኢትዮጵያዊ ነኝ ብለው እራሳቸውን ለአደጋ
እንዳያጋልጡ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ጠቁመዋል ።
በአባይ ግድብ ምክንያት እና መስመሩን በመቀየሱ ምክንያት ውጥረቱን ማየሉን
አስመልክቶ የተለያዩ የውጭ ዜጎችም ለውጭ ዜጎች ለግብጽ ማስጠንቀቂያ እሰጡ ቢሆንም ፣ በሌላም በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ኤምባሴ
በግብጽ ሰራዊት መከበቡን ከስፍራው የደረሰን ዘገባ አረጋግጦአል ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዜጎችን የማዳን እና ካሉበት ስፍራ ወደ ተሻለ ሁኔታ
ለማኖር የሚያስችለውን ተግባር የማድረግ ጥረት እንዲደረግ ርብርቦሹ እንዲጠናከር የማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል ይመክራል።

No comments: