Thursday, September 25, 2014

ጥቃቅንና አነስተኞች ቀጣዩን ምርጫ ‹እንዲያሳኩ› ታዘዙ

September 25,2014
• ‹‹ቃላችንን ካጠፍን የመለስን ቀን ይስጠን›› ባለስልጣናቱ

ከመስከረም 10/2007 ዓ.ም እስከ መስከረም 12/2007 ዓ.ም በጥቃቅንና አነስተኛ ለተደራጁ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተሰጠው የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› የማጥመቅ ስልጠና በምርጫው ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ኢህአዴግ እንዲመረጥ እንዲሰሩ ትዕዛዝ እንደተሰጣቸውና እቅዱን ካላሳኩ ሸዳቸውን መስሪያ ቦታውን እንደሚያጡ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡

ሰልጣኞቹ ‹‹ግብር በዝቶብናል፣ ደንብ አስከባሪዎች በየጊዜው እየመጡ ገንዘብ ይወስዱብናል፣ በየወረዳው የመልካም አስተዳደር ችግር መፍትሄ ልናኝ አልቻልንም፣ ስለዚህ እናንተን እንዴት ነው የምንመርጠው? በየምርጫው ቃል ትገባላችሁ? ካለፈ በኋላ ትረሱናላችሁ እንዴት እነመንላችሁ?›› ሲሉ ቅሬታቸውንና በገዥው ፓርቲ እምነት እንደሌላቸው መግለጻቸውን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በሌላ በኩል በስልጠናው የተገኙት ባለስልጣናት ገዥው ፓርቲ ቃሉን እንደሚያከብርና በአነስተኛና ጥቃቅን የተደራጁት ዜጎች የተባሉትን ስራ ካከናወኑ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ቃል ገብተውላቸዋል ተብሏል፡፡ ተሰብሳቢው በተደጋጋሚ ችግሮችንና ኢህአዴግ ቃል ገብቶ የማይተገብራቸውን ነገሮች በማንሳታቸው በስልጠናው ከተገኙት ባለስልጣናት መካከል አንዱ ‹‹ቃላችንን አናጥፍም፣ ቃላችንን ካጠፍን የመለስን ቀን ይስጠን›› ብለው እንደማሉ ሰልጣኞቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ሰልጣኞቹ በስተመጨረሻም የምስክር ወረቀት የተሰጣቸው ቢሆንም የምስክር ወረቀቱ ላይ የሰፈረውና የሰለጠኑት ግንኙነት እንደሌላቸው ተናግረዋል፡፡ ቀደም ሲል፣ ከስልጠናው በፊት በስልጠናው ያልተገኘ በሸድ ስራ እንደማይቀጥል የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ደርሷቸው እንደነበር ሰነዱን አያይዘን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ነገረ-ኢትዮጵያ

Wednesday, September 24, 2014

ዳኞቹ የኢህአዴግ አባል እንዲሆኑ እንደሚገደዱ ገለጹ

September 24,2014
ከሳምንት በፊት በአቶ በረከት ስምኦን የተከፈተውና 15 ቀን የሚፈጀው የ‹‹ፍትህ አካላት›› ባህር ዳር ላይ እያደረጉት በሚገኘው ስብሰባ ላይ ዳኞች ቅሬታቸውን እንዳሰሙ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡
ልማታዊ መንግስት ግንባታ ላይ ያተኮረ ነው በተባለው ስልጠና ላይ የክልሉ የከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ በክልሉ የሚገኙ ወረዳዎች የህግ ጉዳይ የስራ ሂደት አስተባባሪዎች፣ የክልሉ ማረሚያ ቤቶች፣ ጸረ ሙስና እና ሌሎችም አስተዳደርና ጸጥታ ጋር የተያያዙ መስሪያ ቤቶች ውስጥ የሚሰሩ አካላት መሳተፋቸው ተገልጾአል፡፡
በስብሰባው በተለይም ዳኞች በዳኝነት ስርዓቱ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዳለና የገዥው ፓርቲ አባል ካልሆኑ መስራት እንደማይችሉ በመግለጽ ቅሬታቸውን እንዳቀረቡ ተገልጾአል፡፡
የክልሉ አስተዳደር የሆኑት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በሚመሩት በዚህ ስብሰባ ዳኞች አባል እንዲሆኑ እንደሚጠየቁ በመጥቀስ ‹‹አባል ሁኑ እየተባልን እንዴት ነጻ ዳኝነት አለ ይባላል?›› ሲሉ መጠየቃቸውን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር የአንድ ፓርቲ የበላይነትና ዴሞክራሲ፣ የፌደራል አወቃቀር፣ በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ስር የሚገኙ ድርጅቶች ሃብት፣ የመሬት ጉዳይና የዳኝነት ነጻነት የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ጥያቄና አስተያየቶች ቢቀርቡም መልስ እንዳልተሰጠባቸው ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

ስዊድን የኤርትራ ዲፕሎማቶች በ48 ሰዓት ለቀው እንዲወጡ አዘዘች

September 24,2014
ኢሳያስ አፈወርቂ ጉዳዩ የኢትዮጵያና የአሜሪካ ሴራ ነው አሉ
ስዊድንና ኤርትራ በዲፕሎማቲክ የእሰጣ እገባ ውስጥ ከገቡ በርከት ያሉ ጊዜያት የተቆጠሩ ሲሆን በስዊድን የኤርትራ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች ባልተገባ ተግባር ተገኝተዋል በሚል የሀገሪቱ ዲፕሎማቶች ስዊድንን በ48 ሰዓት ለቀው እንዲወጡ የስዊድን መንግስት ውሳኔ ያስተላለፈ ሲሆን ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ድርጊቱ የኢትዮጵያና የአሜሪካ እጅ አለበት ብለዋል። በስዊድን የወጣውን አዲስ ሕግ ተከትሎ የስዊድን መንግስት በኤርትራ ሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈፅመዋል ባላቸው ከፍተኛ የኤርትራ መንግስት ባለስልጣናት ላይ በዚያው በስዊድን ክስ መመስረቱ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሻክሯል።
isayas afewerki
የኤርትራ መንግስት ዋነኛ የውጪ ምንዛሪ ገቢ በተለያዩ ሀገራት በሚኖሩ ኤርትራውያን ዲያስፖራዎች ላይ የጣለው ሁለት በመቶ የገቢ ታክስ ሲሆን በድርጊት በተለያዩ ሀገራት የሚገኙ ኤርትራውያን በኢምባሲያቸው ላይ ቅሬታ ሲያሰሙ ቆይተዋል። በስዊድን የሚገኙ ኤርትራውያንም ኢምባሲያቸው የሚጠበቅባቸውን የታክስ መጠን ካልከፈሉ የተለያዩ የዜግነትና የጉዞ ዶክመንቶችን ከመከልከል ባለፈ በኤርትራ የሚገኙ ቤተሰቦቻቸው በማያዣነት ተጠቅሞ እስከማስፈራራት ደርሷል በሚል ለስዊድን መንግስት ክስ ሲያሰሙ መቆየታቸው ታውቋል። የኤርትራ መንግስት በስዊድን በሚገኙ ኤርትራውያን እና የስዊድን ዜግነት ባላቸው ትውልደ ኤርትራውያን የተደራጀ ተቃውሞ እየገጠመው ሲሆን የተቃውሞ አደራጅ ግለሰቦችን ለይቶ ለመከታተል በስዊድን የሚገኘውን ኤምባሲውን እና ዲፕሎማቶችን ይጠቀማል በሚልም ጭምር ነው የስዊድን ባለስልጣት የኤርትራ ዲፕሎማቶችን ለማባረር በምክንያትነት ያስቀመጡት።
የኤርትራ መንግስት በየሀገሩ በሚገኙ ኤምባሲዎቹ አማካኝነት ከኤርትራ ዲያስፖራዎች በታክስ መልኩ በሚሰበሰበው ሁለት በመቶ ገቢ ሽብርተኞችና በፋይናንስ እያገዘ ነው በሚል በተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት አማካኝነት ማዕቀብ ከተጣለበት ዓመታት ተቆጥረዋል። ሆኖም ከማዕቀቡ በኋላ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ መንግስት በተለያየ ሀገራት ኤምባሲዎች በኩል ታክሱን ለመሰብሰብ የሚያደርገው ሙከራ በየሀገራቱ መንግስታት ተቃውሞ እያስነሳበት ነው። ከዚህ ቀድም በተመሳሳይ መልኩ ካናዳና ኤርትራ ውዝግብ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ የካናዳ መንግስት በቶሮንቶ የሚገኙ የኤርትራ ዲፕሎማቶችን በ48 ሰዓታት ውስጥ እስከማባረር ደርሷል።
የስዊድን እርምጃ ተከትሎ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በሰጡት ማብራሪያ ድርጊቱ የኢትዮጵያና የአሜሪካ ሴራ ነው ብለውታል፡፡ ሁለቱ ሀገራት የኤርትራ መንግስት ሁለት በመቶ ታክሱን የምስራቅ አፍሪካ ሀገራትን በሽብርተኝነት ለማተራመስ ይጠቀምበታል በሚል ማዕቀቡ እንዲጣልበት ሰፊ የዲፕሎማሲ ሚናን መጫወታቸውን በምስራቅ አፍሪካ ላይ ትኩረቱን አድርጎ የሚሠራው ጂስካ አፍሪካ ኦንላይን ዘግቧል። (ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው)

“ኣብራሃ ደስታን ኣላሰርኩም” የመቐለ ህወሓት (አምዶም ገብረስላሴ – ከትግራይ)

September 24,2014

የትግራይዋ ህወሓት ማለቴ በሰማእታት ሓወልት ፅሕፈት ቤትዋ ያደረገችው ህወሓት( ኣዲስ ኣበባ የህወሓት ኣንጃ ሰላለች ነው) “ኣብራሃ ደስታ የታሰረበት ምክንያት ኣላውቅም” ኣለች።

ይህ ኑዛዜ የተሰማው በኣገር ደረጃ ለመንግስት ሰራተኞች እየተሰጠ ያለው ስልጠና የሚሉት(ተቃዋሚና ያለፉት ስርዓቶች የሚሰድቡበት መድረክ ስለመሰለ ነው) በትግራይ ክልል ፅህፈት ቤት(ደጀን ቢሮ) የሚሰሩ ሰራቶኞች በፕላኔት ሆቴል እየተካሄደ ባለው መድረክ ነው።

በዚህ መድረክ እየተነሱ ያሉት ጥያቄዎችና ሃሳቦች እጅጉን ጠንካሮችና የህወሓት ተራ ኣባላትና ጥቂት ፈላጭ ቆራጭ መሪዎች ፍፁም ታላቅ ልዩነት መነሩ የሚያሳዩ ናቸው።

በዚህ መድረክ “…ኣብራሃ ደስታ ህገ መንግስት የስጠው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብቱን በኣግባቡ በመጠቀሙ ለምን በሽብር ኣምካኝታቹ ኣሰራቹት?…” ለሚለው ጥያቄ ሲመልሱ ነው የመቐለዋ ህወሓት ኣብራሃን እንዳላሰረችና” የማሳሰርያው ምክንያትም ኣላውቅም” ብላ የካደችው።

ስብሰባው እየመሩት የነበሩት የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ሃላፊ “..ስለ ኣብራሃ ደስታ መታፈንና መታሰር በፌስቡክ ስሰማ በቀጥታ ወደ ህወሓት ቢሮ ሂጀ ኣነጋጋርኳቸው። ከህወሓት ፅህፈት ቤት ያገኘሁት መልስ ምንም የሚያውቁት እንደሌለና ህወሓት እንዳላሳሰረው ረግረውኛል..” ሲሉ በስብሰባው ገልፀዋል።

ኣብራሃ ደስታን የመቐለዋ ህወሓት ካላሳሰርችው ሌላዋ ተጠያቂ የኣዲስ ኣበባዋ የህወሓት ኣንጃ ናት ማለት ነው።

ከፍተኛ ቁጣ የተላበሰው የፕላኔት ሆቴል ተስብሳቢ ህዝብ ለህወሓት መሪዎች ኣስፈሪ ነበር።

ኣገሪትዋ እየበጠበጥዋት ያሉት መላ የህወሓት ኣባላት ሳይሆኑ የተወሰኑና ጥቂት ሰዎች መሆናቸው በግልፅ በመላ ትግራይ ያሉ ስብሰባዎች የተነሱ ሃሳቦች ቁልጭ ኣድረገው እያሳዩ ናቸው።

ሌላው ከፍተኛ የመወያያ ኣጀንዳ በዓረና ኣባላት እየደረሰ ያለው ዓፈና፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ ኣማራጭ ሃሳብ ወደ ህዝቡ እንዳይቀርብ ማደናቀፍ የኣዲስ ኣበባዋ ኣንጃ ሳትሆን የመቐለዋ ኣንጃ ስራ መሆኑ በግልፅ ተነግራቸዋል።

እጅጉን ያስደስታል ህዝቡ ነፃነት ፈልጓል፣ ዲሞክራሲን ናፍቆታል፣ መልካም ኣስተዳደርን ቋምጣል። ለዚህ ማሳያ በዓረና የሚደረገው የማፍረስ፣ እንዳይንቀሳቀስ የመከልከል ተግባር ውጉዝ ከመኣርዮስ እያለው ይገኛል።

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ላይ ዋሽተው ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጉት

September 24,2014
የኢሳቱ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና መረጃ ፍለጋ ወ/ሮ አዜብ ጋር ደውሎ ድምፃቸውን ኢሳት ራድዮ ላይ አሰምቶናል። ጋዜጠኛ ሲሳይ ወ/ሮ አዜብ መሆናቸውን ካረጋገጡለት በኋላ መረጃ እንዲሰጡት ጠየቃቸው። አድዋ ስለሆንኩ መረጃ የለኝም በሚል ስልኩን ዘጉት። ለሁለተኛ ጊዜ ደወለላቸውና “ዶ/ር ካሱ ኢላላ ከእርስዎ ጋር ባላቸው አለመግባባት ስላላቸው የመለስን ፋውንዴሽን ለቀዋል የሚባል ነገር አለና ይህን እንዲያረጋገጡልኝ ወይም እንዲያስተባብሉልን ነው የደወልኩት” አላቸው። ምንም አይነት ችግር እንደሌለባቸው ከተናገሩ በኋላ መልሰው እርሳቸው ወ/ሮ አዜብ እንዳልሆኑ በድምጽ ተናግረው ዋሹ። “ድምጽዎት እኮ የአዜብ መስፍንን ይመስላል” አላቸው እርሳቸው ግን ልክ ይህን ሲላቸው ለሁለተኛ ጊዜ ስልኩን ዘግተውበታል። የዛሬው ኢሳት ራድዮ ለዚህ ዘገባ ምላሽ አለው ያድምጡት።

የኮብላዩ ሚኒስትር ወጎች – ከተመስገን ደሳለኝ (ጋዜጠኛ)

September 24,2014

በዚህ ተጠየቅ ጨርፈን የምንመለከተው በኮሙኑዮኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የነበረውና ዛሬ በስደት የሚገኘው የአቶ ኤርሚያስ ለገሰን “የመለስ ትሩፋቶች፣ ባለቤት አልባ ከተማ” የተሰኘው መጽሐፍን ነው፡፡ የመድብሉ ጻሐፊ ኤርሚያስን በግል አላውቀውም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁት አቶ በረከት ስምዖን እርሱን እና ሽመልስ ከማልን ምክትሎቹ አድርጐ በሚኒስቴር ዲኤታ ማዕረግ መሾሙን በግዮን ሆቴል ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረገበት ዝግጅት ላይ ነው፡፡ ከዚህ ለጥቆ፣ በኢትዮጵያ የቀድሞው የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ በኤምባሲው ግቢ በሚገኝ መኖሪያ ቤታቸው ባዘጋጁት የዕራት ግብዣ ላይ (ግንቦት 19/2001 ዓ.ም) ድንገት ተገናኝተን እጅ ለእጅ ተጨባብጠን ሰላምታ ተለዋውጠናል፤ ለመጨረሻ ጊዜ የተያየነው፣ በኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ግንቦት 7 እና እነጀነራል ተፈራ ማሞን በተመለከተ መግለጫ በተሰጠበት ዕለት እንደ አፄ ኃይለሥላሴ የክብር ዘብ፣ ከሽመልስ ከማል ጋር በረከት ስምዖንን ግራና ቀኝ አጅቦ በተገኘበት ወቅት ነው፡፡ በተቀረ በመንግስት ሥልጣን ሲገለጥ ብዙም አላስተዋልኩም፡፡ ከዚህ ይልቅም ኢህአዴግነቱን ለማሳየት የሞከረበትን አንድ ገጠመኝ አስታውሳለሁ፤ ይኸውም “የፍትሕ” ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ የነበረው እና አሁን በስደት ሀገር የሚገኘው ባልደረባዬ ማስተዋል ብርሃኑን ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባለው ቢሮው ድረስ በመጥራት ከባድ ዛቻና ማስፈራሪያ ከሰነዘረበት በኋላ፣ ዛሬ የቀድሞ ጓዶቹ ሥራዬ ብለው እንደቀጠሉበት አይነት በጋዜጣው ላይ የሀሰት ውንጀላ ደርድሮ ሲያበቃ፣ ከኃላፊነቱ ራሱን እንዲያገል አስጠንቅቆት እንደነበር ከራሱ ከባልደረባዬ ማስተዋል አንደበት ሰምቻለሁ፡፡
የሆነው ሆኖ አቶ ኤርሚያስ ከላይ በተጠቀሰው መጽሐፉ በተመላኪው ሰው አመራር “ሁሉን አዋቂነት” ላይ የቆመው መንግስት ምን ያህል በጠባብ የወንዝ ልጅነት የተተበተበ እና በዘራፊ ባለሥልጣናት የተዋቀረ እንደሆነ በስፋት ተርኮልናል፡፡ በተለይም ሙስና እና የህወሓት ካድሬዎች የበላይነትን በተመለከተ በማስረጃ አስደግፎ በተዋበ ስነ-ጽሑፋዊ ቋንቋ ዘርዝሮልናል (በርግጥ “የጋዜጠኛው” አሊያም “የደራሲው ማስታወሻ” የሚያነቡ እስኪመስልዎ ድረስ የመጽሐፉን አርትኦት ተስፋዬ ገ/አብ ወይም የተስፋዬ ብዕር ተፅእኖ ያለበት ደራሲ ብዙ እንደለፋበት በግልፅ ማስታወቁን መካድ አይቻልም)፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎንም ዛሬም ከአገዛዙ ጋር የተሰለፉ የቀድሞ ጓዶቹ ለህሊናቸው ሲሉ በድብቅ የሚፈፀሙ ሕገ-ወጥ ድርጊቶችን ደፍረው እንዲያጋልጡ በጠየቀበት ብዕሩ፣ የራሱንም ጥፋቶች እና በትዕዛዝም ይሁን በግል ተነሳሽነት በደል ያደረሰባቸውን ንፁሃን በይፋ ይቅርታ ቢጠይቅ መልካም ነበር፤ አሁንም ቢሆን ለዚህ አይነቱ ቅንነትና በጎ አርአያነት ገና አልረፈደም፡፡ ርግጥ ነው የስደት ምርጫው ባደረጋት ሀገረ-አሜሪካ ባሳተመው መጽሐፉ ውስጥ ድርጅቱ ኢህአዴግ ይሰራው በነበረው ሕገ-ወጥ ድርጊትና የጭካኔ እርምጃ አልፎ አልፎ ቢሮውን ዘግቶ እንደሚያለቅስ፣ ባስ ሲልም ህሊናውን ቆጥቁጦት ታምሞ አልጋ ላይ እንደሚውል በመግለፅ የራሱን ጲላጦሳዊነት ለመስበክ መልፋቱን ስናስተውል፤ ጸሐፊው የሥርዓቱ ጋሻ-ጃግሪ በነበረበት ወቅት የበደለውን ሕዝብ ይቅርታ የመጠየቅ ዝግጁነትም ሆነ ፍላጎት (ቢያንስ በዚህ ሰዓት) የለውም ብለን ማዘናችን አይቀርም፡፡
እንዲሁም ከሀገር እንዲወጣ የተገደደበት ምክንያት ተብሎ ስለተናፈሰው ወሬ ትንፍሽ አለማለቱ በበኩሌ አስተዛዛቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፤ በወቅቱ የስደቱ መነሾ ተደርጎ በከተማዋ በስፋት የተናኘው፣ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖቹ እና “የግንቦት 7 አባላት ናችሁ” የተባሉ ግለሰቦች ለእስር መዳረጋቸውን ተከትሎ ለአንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያ “ሙከራው መፈንቅለ መንግስት ነው” የሚል መግለጫ በመስጠቱ እንደነበረ ነው፤ በዚህም እጅግ የተበሳጨው ጠ/ሚኒስትሩ፣ አለቃው በረከት ስምዖን ላይ ጭምር የጭቃ-ጅራፉን ከማወናጨፉም በላይ፣ ኤርሚያስን ያለ ሥራ እንዳንሳፈፈው መወራቱን አስታውሳለሁ፤ ይህንን መረጃ አምኖ ወደመቀበሉ የሚገፋን ደግሞ በዚያው ሰሞን መለስ ዜናዊ ራሱ በቴሌቪዥን ቀርቦ ‘…የተደረገው ነገር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፣ ከአልቃይዳና አልሸባብ ጋር ሲነፃፀሩ የእኛዎቹ አማተሪሽ (ልምድ አልባ) ናቸው’ እያለ የሚኒስትር ዴኤታውን ንግግር ለማስተባበል ሲዳክር የመስተዋሉ እውነታ
ነው፡፡ እርሱም ቢሆን ከዚህ ግልፅ ሹክሹክታ በኋላ በትምህርት ሰበብ ሀገር ለቅቆ መሰደዱ የአንድ ሰሞን የከተማ ወሬ ሆኖ ነበር፡፡ እነሆም ወንድም ኤርሚያስ ለገሰ ይህንን ጉዳይ ዳጉስ ባለው መጽሐፉ ውስጥ ሽራፊ ገፅ ሊሰጠው አለመቻሉ እዚህ ጋ በትዝብት እንዳነሳው መገደዴን በትህትና እገልፃለሁ፡፡ አሸንፈሀልና በዝብዘህ ብላ!
ህወሓት-ኢህአዴግ ወደ ሥልጣን ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ፣ በግርማ ብሩ አነጋገር “ደሀ-ዘመም” (በመጽሐፉ የተጠቀሰ) እንደሆነ ለማሳመን የሚሞክርበት ብልጠት፣ ራሱን ለሙስና ፅዩፍ አስመስሎ በማቅረብ ነው፤ ይህን አይነቱን ስሁት አመለካከት በሕዝብ ውስጥ ለማስረፅ ጥቂት የፖለቲካ መታመን-ጉድለት ጥርስ ያስነከሰባቸውን ጉምቱ ጓዶቹን “ሙሰኛ” በሚል ወንጅሎ በወህኒ የቃየል መስዋዕት ሲያደርጋቸው ተስተውሏል፤ እርምጃውንም በፓርላማው መድረክ ሳይቀር ሲኩራራበትና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ሲያውለው ተመልክተናል (ከሩቁ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ታምራት ላይኔ እና መከላከያ ሚኒስትሩ ስዬ አብርሃ፤ ከቅርቡ ደግሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ዳይሬክተር መላኩ ፈንቴ፣ የደህንነት ኃላፊው ወ/ስላሴ እና መሰል ባለሥልጣናትን እስር ልብ ይሏል)፡፡ የሚኒስትር ዴኤታው መጽሐፍ፣ መለስ እና ጓዶቹ ካደነቆሩን በግልባጩ ‘የዘረፋ መሪዎች’ የሚላቸው ሁለት የህወሓት ሰዎች፣ በባላንጣነት ተሰልፈው እንዴት የሀገር ሀብት ለመቀራመት ይሽቀዳደሙ እንደነበር አጋልጧል፤ አዜብ መስፍንን እና አርከበ እቁባይን፡፡
“እነ አርከበ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ከመምጣታቸው ጥቂት ወራት በፊት በህወሓት ውስጥ መደናገጥ ተፈጥሮ ነበር፡፡ የህወሓት ዳግም መከፋፈል ምክንያት ደግሞ በወ/ሮ አዜብ እና አርከብ ቡድኖች መካከል አለመግባባቶች መፈጠራቸው ነበር፡፡ መነሻው መረን የለቀቀ የጥቅም ግጭት ሲሆን ዓላማው የህወሓት ኢንዶመንቶችን መቆጣጠር ታሳቢ ያደረገ ነበር፡፡” (ገፅ 25) ከዕለት ተዕለትም ይህ ሁኔታ የተካረረ ልዩነት ፈጥሮ፣ ፖለቲካዊ ቁመና በመላበሱ፤ አርከበ እቁባይ፣ ህወሓት መገፋቱን እና መለስ በበረከት በኩል የድርጅቱን ካድሬዎች እያስጠቃ ነው የሚል ክስ ከማጎኑም ባሻገር፤ ወደኋላ ተጉዞ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት የተጠናቀቀበትን መዛግብት አቧራ በማራገፍ፣ ተጠያቂነቱን ከፍ ሲል ወደ መለስ ዜናዊ፣ ዝቅ ሲል ደግሞ ወደ በረከት ስምዖን በመወርወር ማጠቋቆሩ ያመጣውን ውጤት እንዲህ ሲል ገልፆታል፡- “በሂደት አቶ አርከበ ይዞ ብቅ ያለው መቀስቀሻ የካድሬውን እና አባሉን ቁስል የነካ በመሆኑ ተቀባይነት አገኘ፡፡ በትግራይ ፕሮፓጋንዳ እና ድርጅት ተመድበው የሚሰሩ ቁልፍ ካድሬዎች ተቀላቀሉት፡፡” (ገፅ 26)
ይህንን ተከትሎ ወትሮም በደፋር ንግግሯ የምትታወቀውና አንጋፋ ታጋዮችን ሳይቀር በቁጣ የምታስረግደው ቀዳማዊት እመቤት የሰነዘረችው የመልስ ምት በመጽሐፉ ላይ እንደሚከተለው ሰፍሯል፡- “ወ/ሮ አዜብ በበኩሏ አርከበና ቡድኖቹ በሙስና ተዘፍቀዋል የሚል ክስ ይዛ ብቅ አለች፡፡ አርከበ በሚስቱና ቤተሰቦቹ የያዘውን ንብረት በመረጃ አስደግፋ አራገበች፡፡ ላውንደሪ ቤት፣ ፋርማሲ፣ ክሊኒክ፣ ሱፐር ማርኬት፣ መስታወት ማስመጣትና መሸጥ…፡፡ በትግራይና አዲስ አበባ የተፈጠሩት አዳዲስ ባለሀብቶች የአርከበና ቡድኖቹ እንደሆኑ በስም ዘርዝራ አሳወቀች፡፡ ስዬ በታሰረበት የሌብነት ወንጀል አርከበ እጁ እንደነበረ፣ በተለይም የስዬ ወንድም ለገዛቸው በርካታ መኪናዎች ቅናሽ እንዲያገኝ ማግባባቱን የፈፀመው አርከበ መሆኑን አጋለጠች፡፡” (ገፅ 26)
እዚህ ጋ አቶ ኤርሚያስ ‹‹አርከበ በሚስቱና በቤተሰቦቹ…›› ስለያዛቸውና አዜብ መስፍን በስም እየጠራች አጋለጠች ስላላቸው የንግድ ድርጅቶች በስም አንድ በአንድ እየጠቀሰ ይፋ ቢያደርግልን ኖሮ መረጃው ምሉዕ (ከ‹ኮሪደር ሀሜት› የዘለለ) ይሆን ነበር ብዬ አስባለሁ፡፡ ከሁሉም ቁጭታችንን የሚያንረው፣ ደራሲው የንግድ ተቋማቱን ባለቤቶች በስም መጥቀስ እየቻለ (አቀራረቡ ለይቶ እንደሚያውቅ ያሳብቃልና) በደፈናው ያለፈው ወንጀል (ሕገ-ወጥ ዘረፋ) ይህ ብቻ አለመሆኑ ሲገባን ነው፤ በዚሁ ገፅ ዝቅ ብሎ የሰፈረው እንዲህ ይላልና፡- “በወቅቱ ሁለቱም ቡድኖች ‹ያለ ኢኮኖሚ የበላይነት፣ የፖለቲካ የበላይነት አይመጣም› የሚል ፖሊሲ ቀርፀው የህወሓት ባለሀብቶችን ለመፍጠር ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በዚህ ፖሊሲ ምክንያት በአንድ ሌሊት ከሹፌርነት ወደ አስመጪና ላኪነት፣ ከጋራዥ ሰራተኛነት ወደ መኪና ዕቃ መለዋወጫ አስመጪነት፣ ከታጋይነት ወደ ሪል እስቴት ባለቤትነት፣ ከወታደርነት ወደ ፋብሪካ ባለቤትነት፣ ከህወሓት ምድብተኛ ካድሬ ወደግል ባንክ ከፍተኛ አክሲዮን ባለድርሻነት የተቀየሩ ሰዎችን መስማት የተለመደ ነበር፡፡” (ገፅ 26) እነዚህ ‹‹ተላላኪ›› እና ‹‹ሹፌር›› ባለሀብቶችን በስም አለመጥቀሱ ያስቆጫል፤ በተለይም ለመረጃው ከነበረው ቅርበት አኳያ ይሄ ጉዳይ እንደተራ ነገር በደፈናው ባይታለፍ ኖሮ፣ ለተቃውሞው ስብስብ በዋናነት ሁለት ታላላቅ የፖለቲካ ትርፍ ማስገኘቱ አይቀሬ ነበር፡፡
የመጀመሪያው በጅምላ ህወሓት፣ መላው ትግሪኛ ቋንቋ ተናጋሪን ተጠቃሚ ያደረገ የሚመስለው ኢትዮጵያዊ ስህተቱን እንዲያጠራ ስለሚያስችለው፣ በድርጅቱ እና በብሔሩ መሀከል ያለውን ነጭና ጥቁር ልዩነት እንዲያስተውል ይረዳው ነበር፤ ሌላው ደግሞ እነዚህን በፖለቲካ ውሳኔ ወደሀብት ማማ የወጡትን ግለሰቦች የትላንት ማንነት አብጠርጥሮ የሚያውቀው ቤተሰብ፣ ጎረቤት፣ ዘመድ አዝማድ… የዘረፋ ወንጀላቸውን ተፀይፎ በኢኮኖሚያዊ ማግለል (ሸቀጦቻቸውን ባለመግዛትም ሆነ አገልግሎታቸውን ባለመጠቀም) በተቃውሞ ጎራ እንዲሰለፍ ገፊ-ምክንያት ይሆነው ነበር የሚለው ጭብጥ ነው፡፡ ‹‹የመለስ ትሩፋቶች›› መጽሐፍ በሀገሪቱ ውስጥ ከመጋረጃው ጀርባ ስለተፈፅሙ ህልቆ-መሳፍርት ያሌላቸው አሳፋሪ የህወሓት ሕገ-ወጥ ድርጊቶች እና እብሪቶችን ተንትኖ አስነብቦናል፡፡ ከእነዚህ መሀልም የስምንቱ ኮሎኔሎች ‹‹ጀብድ››ን እዚህ ጋ መጥቀሱ አግባብነት አለው ብዬ አምናለሁ፤ ከ268-269 ባሉ ገፆች እንደተተረከው፣ በምርጫ 97 ማግስት በአንዱ ዕለት በወታደራዊ የደንብ ልብስ የተንቆጠቆጡ ስምንት ከፍተኛ መኮንኖች በሶስት ሄሌኮፕተር ተሳፍረው አሮጌው አውሮፕላን ማረፊያ ይደርሳሉ፤ በቀጥታም የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ከንቲባ ወደነበረው አባተ ስጦታው ቢሮ በማምራት፣ መሬት እንደሚሰጥ መረጃ ደርሷቸው ከጦር ግንባር እንደመጡ ይነግሩታል፤ እያንዳንዳቸውም ‹‹ዘመቻ ፀሀይ ግባት የቤት ማሕበር››፣ ‹‹ኃየሎም አርአያ የቤት ማሕበር››፣ ‹‹ዛላአንበሳ የቤት ማሕበር››… የሚል እና መሰል የማህደር ስያሜ ያላቸው የአስራ ሁለት መኮንኖች ስም ዝርዝርና ፊርማ የያዘ ወረቀት ይሰጡታል፤ እንደ ብራ መብረቅ ድንገት ባጋጠመው ክስተት ክፉኛ የተረበሸው ከንቲባም እንዲህ ያለ መመሪያ እንዳልወረደ ለማስረዳት ሲሞክር፣ ለዚህ ዓይነቱ እሰጥ-ገባ ጊዜ ያልነበራቸው የጦር አበጋዞቹ አብረቅራቂ ሽጉጦቻቸውን በመምዘዝ ግንባሩ ላይ ደቅነው በወቅቱ ፋሽን በነበረው ኢህአዴጋዊ ፍረጃ ‹‹የቅንጅት ተላላኪ መሆንህን ደርሰንበታል››፣ ‹‹ኢህአዴግ እንዲሸነፍ ያደረጋችሁት እንዳንተ ያሉ ሰርጎ-ገቦች ናቸው››፣ ‹‹እዚሁ ደፍተንህ እንሄዳለን››… የሚሉ ማስፈራሪያዎችን አዥጎድጉደው በማስጠንቀቅ ነፍስ-ውጪ፣ ነፍስ ግቢ ወጥረው ይይዙታል፤ ይህን ጊዜ የህወሓት አባል የሆነው ምክትል ከንቲባው ነጋ በርሔ፣ የአባተን ቢሮ በርግዶ ሳይታሰብ ዘው በማለቱ፣ አንደኛው ኮሎኔል ያነጣጠረውን መሳሪያ ከአይን በፈጠነ ቅፅበት አዙሮ ይደቅንበታል፡፡ ሁኔታውን ከጉዳይ ያልጣፈው ነጋ በርሔም ባለሽጉጦቹን የጦር አበጋዞች በባዶ እጁ እንዲህ ሲል ተጋፈጣቸው፡-
“ነፍጥ ከእናንተ በፊት አንግበን ተራራ ደርምሰናል፡፡ የምታስፈራሩትን ሂዱና ሌላ ቦታ አስፈራሩ!”
ከፍተኛ መኮንኖቹም በድንጋጤ መሳሪያዎቻቸውን በመዘዙበት ፍጥነት ወደአፎቱ መልሰውና የምክትል ከንቲባውን የስድብ ውርጅብኝ በፀጥታ አዳምጠው ሲያበቁ፣ አባተን ይቅርታ እንዲጠይቁት ይታዘዛሉ፤ እንዲያ በጥንካሬያቸው ለማንም የሰው ልጅ የማይበገሩ መስለው ሲንጎማለሉ የነበሩት ቆፍጣናዎቹ ኮሎኔሎች ባንዴ እንደፊኛ ተንፍሰው በፍርሃት የታዘዙትን ይፈፅማሉ፤ ከዚህ በኋላም ህወሓቱ ነጋ በርሔ በተረጋጋ አንደበት ዋናው ከንቲባውም ጭምር እንዲሰማ ድምፁን አጉልቶ የሚከተለውን ‹‹ምርጥ›› ምክር ለገሳቸው፡ –
“ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ጥያቄያችሁን ብታቀርቡ ኖሮ አባተ እንኳን ቤተሰባችሁን ጥላችሁ ግንባራችሁን ለጥይት ለምትሰጡት ቀርቶ ለሌላውም አይጨክንም፡፡ ያውም ከቀናት በኋላ ጠላት (ቅንጅት) ተረክቦ ለሚዘርፋት አዲስ አበባ!” (ገፅ 255) ከንቲባውም መሬቱን ፈቀደ፤ ነጋም ወደ መቀሌ እንዲዘዋወር ተደርጎ፣ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴን እና የትግራይ ክልል ካቢኔን ተቀላቀለ፤ ከጊዜ በኋላም በበረከት ስምዖን በተመራ ግምገማ ላይ በአስቸኳይ አዲስ አበባ መጥቶ ይህንን ጉዳይ እንዲያስረዳ ቢጠየቅ አሻፈረኝ ብሎ ይቀራል፡፡ ደራሲውም ‹‹ዘመን አለፈና አዲሱ ለገሰን ለማገዝ ኢህአዴግ ቢሮ የሥልጠና ማዕከል በምክትል ሚኒስትርነት ማዕርግ ተመደበ›› ሲል የሆሊውድ ፊልምን የሚያስንቀውን ታሪክ ይደመድማል፡፡ በርግጥ አባተም ቢሆን ይህ አስፈሪ ገጠመኙ እንደድንቅ ቃለ-ተውኔት ሁሉ፣ በህወሓት መሪዎች ተደርሶ በኮሎኔሎቹ እና በነጋ የተተወነ መሆኑን ለመረዳት በርካታ ወራት እንደፈጀበት ተጠቅሷል፡፡
በሌላ ምዕራፍ ደግሞ፤ በምርጫው ቀን እኩለ ሌሊት ተቋቁሞ፣ በአርከበ እቁባይ እና በጄነራል ታደሰ ወረደ እንዲመራ የተደረገው ‹‹የፖለቲካ ፀጥታ ጥምር ኮሚቴ››፣ ከ1978 ዓ.ም በፊት ወደ ትግል የገቡና ማዕረጋቸው ከኮሎኔል በላይ የሆነ የህወሓት መኮንኖች ቦሌ ላይ መሬት እንዲያገኙ ማመቻቸቱን አስነብቦናል፡፡ በአናቱም፣ ከኮሎኔል በታች ያሉ የህወሓት ታጋዮች በሌሎች ማስፋፊያ ከተሞች መሬት ማግኘታቸውን ተከትሎ የተፈጠረውን ሁኔታ ሚኒስትር ዴኤታው እንዲህ ያወጋናል፡- “…ወሬው ባድመና ጾረና ጦር ግንባር ድረስ ተዳረሰ፡፡ ወታደራዊ መኮንኖቹ ምሽጋቸውን እየለቀቁ በጦር ሂሊኮፕተሮች ጭምር እየተሳፈሩ አዲሳባን ወረሯት፡፡ የክፍለ ከተሞች ግቢ አቧራ በጠጣ የኮከብ ጋሻና ጦር ክምር የተሸከመ ካኪ ተጥለቀለቀ፡፡” (ገፅ 255-256) ዘመነኛው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ‹‹…አንዳንድ እንሰሳት ይበልጥ እኩል ናቸው›› በሚል ያልተፃፈ ሕግ ማደሩን ከውስጥ-አወቅ ምስክርነት የምንረዳው ከህወሓት ውጪ ያሉት ኢህአዴግን የመሰረቱ ድርጅቶች የአመራር አባላት ብቻ የወሰዷትን መሬት በግምገማ እንዲመልሱ መገደዳቸው በዚሁ መጽሐፍ መስፈሩን ስናስተውል ነው፡፡ በወቅቱም በግምገማው ፊት-አውራሪ በረከት ስምዖን የተዘጋጀ ‹‹ከምርጫው በኋላ የድርጅታችንን ስም ያጎደፉና የሕዝቡን ቅሬታ ያባባሱ ተግባራት›› የሚል ሃያ ገፅ ሰነድ የመነሻ ሃሳብ ሆኖ ቀርቦ ነበር፤ የግምገማው ውጤትም የተዘረፈ መሬት ማስመለሻ ፎርምን ህወሓት ያልሆኑ ከ600 በላይ የኢህአዴግ ካድሬዎች እንዲሞሉ አስገድዶ ተጠናቅቋል፡፡
ለአብነትም ደራሲው ‹‹ለታሪክ የተቀመጠው የይቅርታ ፎርም›› ብሎ በመጽሐፉ ያሰፈረውንና በአንድ የብአዴን አመራር የተሞላውን እንደወረደ ልጥቀሰው፡- “ለቦሌ ክፍለ ከተማ መሬት አስተዳደር እኔ ህላዊ ዮሴፍ ድርጅቴ ኢህአዴግና መንግስት የጣለብኝን አደራና ኃላፊነት ወደጎን በመተው ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ የመሬት ወረራ ላይ በመሰማራት አንድ መሬት ወስጃለሁ፡፡ በመሆኑም ይህን ያለአግባብ የወሰድኩትን መሬት አስተዳደሩ እንዲረከበኝ በማክበር እጠይቃለሁ፡፡ ድርጅቴ ኢህአዴግና በእሱ የሚመራው መንግስትም ይቅርታ እንዲያደርግልኝና ከእንግዲህ ወዲያ በየትኛውም የድርጅቴንና የመንግስት ስም በሚያጎድፍ ተግባራት ላለመሰማራት ቃል እገባለሁ፡፡
ከሰላምታ ጋር ህላዊ ዮሴፍ
ግልባጭ
ለአዲስ አበባ ጊዜያዊ ባለአደራ አስተዳደር
ለቦሌ ክፍለ ከተማ ጊዜያዊ ባለአደራ አስተዳደር
ለኢህአዴግ ጽ/ቤት” (ገፅ 257)
የሆነው ሆነ ኤርሚያስ ለገሰ በዚህ መጽሔት ላይ እንዲህ በቀላሉ ጠቅሰን የማንጨርሳቸውን በርካታ አይን ያወጡ ድርጅታዊ እና ግለሰባዊ ዘረፋዎችን ልባችን ቀጥ እስኪል ድረስ አስነብቦናል፡፡ ሌላው ቀርቶ ዛሬ በየመድረኩ ‹ኢህአዴግ ጌታ ነው!›፣ ‹መለስ መሲህ ነው!›… አይነት ፕሮፓጋንዳ በማድመቅ ግንባር-ቀደም እየሆነ የመጣው ጀግናው አትሌት ኃይሌ ገ/ስላሴ ራሱ የዘረፋው ተቋዳሽእንደነበረ እንዲህ ሲል ነግሮናል፡-
“ከሁሉም የሚያሳዝነው ሀገራችንን በዓለም መድረክ በማስጠራቱ የምንወደው ኃይሌ፣ በአስታራቂ ሽማግሌነቱ የምናመሰግነው ኃይሌ፣ በዓለም አደባባይ አልቅሶ ያስለቀሰን ኃይሌ ‹ኃይሌና አለም ሪል ስቴት› በሚል የድርጅት ስም በመስከረም 7/1998 ዓ.ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 18 ውስጥ 50,000 ካሬ ሜትር ሕጋዊ ሰውነት በነዋሪው ድምፅ ከተገፈፈው አርከበ እቁባይ እጅ ወስዷል፡፡ መቼም ታላቁ ሯጭ እየተካሄደ ያለው ውንብድና አዲስ አበባን ማጥፋት እንደሆነ ሳይገባው ቀርቶ አይመስለኝም፡፡” (ገፅ 400-401)
…የወዶ ተሳዳጁ የኦህዴድ ካድሬ፣ ከሁለት ዓስርታት በላይ ሲነገርና ሲፃፍ የነበረውን ርዕሰ-ጉዳይ ለማጠናከር በርካታ የመጽሐፉን ገጾች ሰውቷል፡፡ ይህ የህወሓት ብቸኛ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ጠቅላይነት ትርክት፣ ገዢ የተቃውሞው መከራከሪያ መሆኑን በሚገባ የሚያውቀው ኤርሚያስ፣ በተለይም ባገለገለበት አዲስ አበባ ዙሪያ ያልተገለጡ የሚመስሉ ሁነቶችን አስተሳስሮ ለመተረክ ጥሯል፡፡ በርግጥ ለእግረ-መንገድ ያህል አንድ ጥርጣሬ ጥለን እንለፍ፤ ይህን መስመር አብዝቶ ማብራራት፣ ተደማጭነትን እና የፖለቲካ ሁለተኛ ዕድልን እንደሚሰጥ ሚኒስትሩ ከመረዳቱ አኳያ፤ የተባሉትን በምልዐት መቀበሉ ጥቂትም ቢሆን አስቸጋሪ መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ አልፎም፣ የትግሪኛ ተናጋሪውን እና ህወሓትን ቀላቅሎ ወደመመልከት እንዳያሻግረን ብርቱ ጥንቃቄ ማድረጉም ሊታወስ ይገባል፡፡
(በሚቀጥለው ሳምንት ይህንኑ መጽሐፍ በማጣቀሻነት እያወሳን፣ የህወሓትን የፖለቲካ የበላይነት እና ጠቅላይነት የሚያሳዩ ወጎችን እንዳስሳለን)

Tuesday, September 23, 2014

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መስከረም 23 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

September 23,2014
የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች መስከረም 23 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

 በሽብርተኝነት ተከሰው ማዕከላዊ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ የጋሞጎፋ ዞን አመራሮች መስከረም 23/2007 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ 8፡00 አራዳ ችሎት እንደሚቀርቡ የሰማያዊ ፓርቲ የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ የጋሞጎፋ ዞን ምክትል ሊቀመንበር አቶ ፍቃዱ አበበ እንዲሁም የዞኑ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ ኢንጅነር ጌታሁን አርባምንጭ ውስጥ ወር ከ15 ቀን ያህል ታስረው የነበር ሲሆን ወደ ማዕከላዊ ከተዛወሩ ሁለት ሳምንት እንደሆናቸው የአደረጃጀት ጉዳይ ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

ታሳሪዎቹ በቤተሰብ፣ በኃይማኖት አባትና በጠበቃ እንዳይጠየቁ የተከለከሉ ሲሆን የምክትል ሊቀመንበሩ አቶ በፈቃዱ ባለቤትና አባት እንዳይጠይቁ መከልከላቸውን ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡: (ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ)
blue_party_ethiopia101370869814 (1)

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤክስፐርቶች ኢትዮጵያ ፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን ለሰብዓዊ መብት ጥሰት ትጠቀማለች ሲሉ ከሰሱ

September 23.2014
-ተቃዋሚዎች ተገቢ ሪፖርት ብለውታል
United-Nations-01-300x220የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብት ሁሉን አቀፍ የአቻ ለአቻ ግምገማ የውሳኔ ሐሳቦችን ለመገምገም የተሰበሰበው የተመድ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ኤክስፐርቶች ቡድን መስከረም 8 ቀን 2008 ዓ.ም. በጀኔቭ ስዊዘርላንድ ባደረገው ስብሰባ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፀረ ሽብረተኝነት አዋጁን ሐሳብን በነፃነት የመግለጽና የመደራጀት መብትን ለመጣስ መጠቀሙን እንዲያቆም አሳሰበ፡፡
ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ያቀረበችውን ብሔራዊ የሰብዓዊ መብት አፈጻጸም ሪፖርትና የሰብዓዊ መብት ይዞታን በአገሪቱ ለማሻሻል የተወሰዱትን ሕጋዊና አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች ተከትሎ፣ አባል አገሮች የተለያዩ የውሳኔ ሐሳቦችን መስጠታቸው ይታወሳል፡፡ ያደጉ አገሮች ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው እንዲሻሻል ወይም እንዲሰረዝ የጠየቁት ደግሞ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን ነው፡፡
የፀረ ሽብርተኝነት ሕግና የሰብዓዊ መብት ጥበቃ፣ የመደራጀትና የሰላማዊ ስብሰባ፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ የዳኞችና የጠበቆች ነፃነትና የኢሰብዓዊ አያያዝና ክብርን የሚያዋርድ ቅጣት መብቶች ልዩ ራፖርተሮች የሆኑት ቤን ኤመርሰን፣ ማይና ካያ፣ ዴቪድ ካዬ፣ ሚቸል ፎርስት፣ ጋብሪኤላ ክናውልና ጁአን ሜንዴዝ በጋራ ያወጡት ሪፖርት የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ላይ ያነጣጠረ እንደሆነ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከኢትዮጵያ የወጡ ሪፖርቶች ማመላከታቸውን ይገልጻል፡፡ ‹‹ግርፋትና ኢሰብዓዊ አያያዝ በኢትዮጵያ ማቆያዎች ውስጥ መስተዋሉ ከፍተኛ የመሠረታዊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፤›› ሲልም ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡
የኤክስፐርቶች ቡድኑ ሽብርተኝነትን መዋጋት አስፈላጊ ድርጊት ቢሆንም፣ ትግሉ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት መሥፈርቶችን ሳይጣረስ መከናወን እንዳለበት ግን አስምሮበታል፡፡ ‹‹ፀረ ሽብርተኝነትን የሚደነግጉ አንቀጾች በኢትዮጵያ የወንጀል ሕግጋት ውስጥ ግልጽ በሆነ ሁኔታ መተርጎም አለባቸው፡፡ ሕጎቹም ላልተገባ ዓላማ ጥቅም ላይ ሊውሉ አይገባም፤›› ሲልም ሪፖርቱ ያትታል፡፡
ሪፖርቱ በፀረ ሽብርተኝነት አዋጁ የተከሰሱ ግለሰቦች ፍትሐዊ የሆነ የፍርድ ሒደት እያገኙ እንዳልሆነም ይወቅሳል፡፡ በተለይም ከሕግ አማካሪዎችና ከጠበቆች ጋር የመገናኘት መብት እንደማይተገበርም ያስረዳል፡፡ ‹‹ፍትሐዊ የሆነ የፍርድ ሒደት የማግኘት መብት፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትና የመደራጀት መብት በፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ አፈጻጸም መጣሳቸው ቀጥሏል፤›› ሲሉም ኤክስፐርቶቹ ያሳስባሉ፡፡
‹‹የኢትዮጵያ መንግሥት ሽብርተኝነትን በመዋጋት ስም በዘፈቀደ በቁጥጥር ሥር ያዋላቸውን ሁሉንም ሰዎች እንዲፈታ እንጠይቃለን፡፡ ጋዜጠኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች፣ ተቃዋሚ ፖለቲከኞችና የሃይማኖት መሪዎች መደበኛና ሕጋዊ ሥራቸውን ያለ ዛቻና እስር ሳይፈሩ እንዲቀጥሉ ሊፈቀድላቸው ይገባል፤›› ሲሉም የተመድ ኤክስፐርቶች ጠይቀዋል፡፡ ኤክስፐርቶቹ ኢትዮጵያ የአዋጁን አፈጻጸም ከገባቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ግዴታዎች ጋር እያገናዘበች እንድታስኬድም ጥሪ አድርገዋል፡፡
የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን በመቃወም የሕዝብ ፊርማ እስከማሰባሰብ የደረሰው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ (አንድነት) ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ ግዛቸው ሽፈራው (ኢንጂነር) ሪፖርቱን አስመልከቶ ከሪፖርተር ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ‹‹ፓርቲያችን አንድነት የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ የሕግ ሳይሆን የፖለቲካ ሰነድ ነው ያለው ከየትኛውም ፓርቲ ቀድሞ ነው፡፡ አዋጁ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ከኢሕአዴግ የተለየ አቋም የሚያንፀባርቁ ግለሰቦችና ጋዜጠኞችን ለማፈን ታሳቢ ተደርጎ የወጣ ነው፤›› ብለዋል፡፡ አቶ ግዛቸው የሕጉን ተፅዕኖ በማየት ፓርቲያቸው በ2005 እና በ2006 ዓ.ም. ሕጉን ለማሰረዝ ፊርማ የማሰባሰብ ሥራ መሥራቱንም አስታውሰዋል፡፡
የተመድ ኤክስፐርቶች ሪፖርት በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር ምን ያህል ጠቃሚ ነው በሚል የተጠየቁት አቶ ግዛቸው፣ ተመድ ሕጉ ጉድለት አለበት ስላለ ሳይሆን አዋጁ ከኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት ጋር የማይጣጣም በመሆኑ ፓርቲያቸው ተቃውሞውን እንደጀመረ ገልጸዋል፡፡ ዜጎች ሐሳባቸውን በነፃነት የመግለጽ፣ የመሰብሰብና የመደራጀት መብታቸው በሕገ መንግሥቱ ቢከበርም እነዚህን መብቶች በመጣስ በሕጉ አማካይነት በርካታ የህሊና እስረኞችን ኢትዮጵያ እንዳፈራችም አመልክተዋል፡፡ አዋጁ ከሕገ መንግሥቱ ጋር ይጋጫል የሚሉ ከሆነ ለምን ጥያቄአቸውን ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ወይም ለሕገ መንግሥታዊ አጣሪ ጉባዔ እንዳላቀረቡ የተጠየቁት አቶ ግዛቸው፣ ከሕግ ክፍላቸው ጋር እየተነጋገሩ እንደሆነና በቅርቡ እንደሚያቀርቡ ጠቁመዋል፡፡
እንደ አንድነት ፓርቲ ሁሉ በአዋጁ ላይ የሰላ ተቃውሞ በማቅረብ የሚታወቀው የሰማያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ ይልቃል ጌትነት (ኢንጂነር) በበኩላቸው፣ የኤክስፐርቶቹ ሪፖርት የፓርቲያቸውን አቋም እንደሚያንፀባርቅ ገልጸዋል፡፡ ‹‹እንደ ፓርቲም እንደ ግለሰብም በሪፖርቱ በጣም ደስተኛ ነን፡፡ ኤክስፐርቶቹ ገለልተኛና በጉዳዮቹ ላይ ጥልቅ ዕውቀት ያላቸው ናቸው፡፡ ተዓማኒነት ያለው ሪፖርትም በማውጣት ይታወቃሉ፡፡ ይኼ ዲፕሎማሲያዊ ጫና ከመፍጠር አልፎ ተግባራዊ ዕርምጃ ለመውሰድም የሚያስችል ተፅዕኖ ይፈጥራል፤›› ሲሉም አስረድተዋል፡፡
ከነሐሴ 22 ቀን 2001 ዓ.ም. ጀምሮ የፀናው የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 ተጠቅሶ በርካታ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት፣ ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያንና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተከሰው ፍርድ ያገኙ ሲሆን፣ በቅርቡም በቁጥጥር ሥር የዋሉ ፖለቲከኞችና ጋዜጠኞች በዚሁ አዋጅ ተከሰው ጉዳያቸው በመታየት ላይ ነው፡፡ መንግሥት ግን ይሠሩት ከነበረው ሙያዊ እንቅስቃሴ ባሻገር በሽብር ተግባር ሲሳተፉ እንደያዛቸው በመግለጽ ራሱን ይከላከላል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በኢትዮጵያ ውስጥ አንድም የህሊና እስረኛ እንደሌለ መግለጻቸውን ባለፈው ረቡዕ ዕትም መዘገባችን ይታወሳል፡፡ በአሁኑ የተመድ ኤክስፐርቶች ሪፖርት ላይ የመንግሥትን ምላሽ ለማግኘት ሪፖርተር ያደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡

አሳዛኝ ዜና (ከቂልንጦ እስር ቤት)

September 23,2014
ዛሬ ከወደ ቂልንጦ የደረሰኝ መረጃ እጅግ የሚዘግንና እንቅልፍ የሚነሳ ነው ነገሩ እንዲህ ነው””
አበበ ካሴ ግንቦት ሰባት ነህ ተብሎ የታሰረ ወጣት . በቂልንጦ ይገኛል፡፡ በሚዘገንን መልኩ ቅጣት ብለው የ10 ጣቶቹን ጥፍሮች ነቅለዋቸዋል፡፡ ብልቱ ላይ ሀይላንድ እያንጠለጠሉ ሲያሰቃዩት ቆይተዋል፡፡ ከብልቱ ፈሳሽ መውጣት ጀምሯል ፡፡ እንዲያሳክሙት ቢጠይቅም እምቢ ብለዉ ህክምና ከልክለውታል፡፡ ይባስ ብለው የእስረኛ መለያ መታወቂያውን ቀምተውታል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በከፍተኛ ስቃይ ውስጥ ይገኛል፡፡ ይህ የጭካኔ ተግባር በምን አይነት ቋንቋ እንደሚገለጽ አላውቅም።

Systemic human rights concerns demand action by both Ethiopia and the Human Rights Council

September 23, 2014

amnesty.jpgAMNESTY INTERNATIONAL
PUBLIC STATEMENT
AI Index: AFR 25/005/2014
Systemic human rights concerns demand action by both Ethiopia and the Human Rights Council
Human Rights Council adopts Universal Periodic Review outcome on Ethiopia
With elections coming up in May 2015, urgent and concrete steps are needed to reduce violations of civil and political rights in Ethiopia.� Considering the scale of violations associated with general elections in 2005 and 2010, Amnesty International is deeply concerned that Ethiopia has rejected more than 20 key recommendations on freedom of expression and association relevant to the free participation in the elections and the monitoring and reporting on these. These include in particular recommendations to amend the Anti-Terrorism Proclamation, which continues to be used to silence critical voices and stifle dissent, and recommendations to remove severe restrictions on NGO funding in the Charities and Societies Proclamation.� The independent journalists and bloggers arrested just days before Ethiopia’s review by the UPR Working Group in May 2014 have since been charged with terrorism offences. Four opposition party members were arrested in July on terror accusations, and, in August, the publishers of five magazines and one newspaper were reported to be facing similar charges.
While Amnesty International welcomes Ethiopia’s statement of ‘zero tolerance’ for torture and cruel, inhuman or degrading treatment, and its commitment to adopt preventative measures,� it is concerned by its rejection of recommendations to investigate and prosecute all alleged cases of torture and other ill-treatment and to ratify the Optional Protocol to the Convention against Torture and Other Cruel, Inhuman or Degrading Treatment or Punishment.� The organization continues to receive frequent reports of the use of torture and other ill-treatment against perceived dissenters, political opposition party supporters, and suspected supporters of armed insurgent groups, including in the Oromia region. Amnesty International urges Ethiopia to demonstrate its commitment to strengthening cooperation with the Special Procedures by inviting the Special Rapporteur on Torture to visit the country.� Unfettered access by independent monitors to all places of detention is essential to reduce the risk of torture.
Ethiopia’s refusal to ratify the Convention for the Protection of All Persons from Enforced Disappearance is also deeply concerning in light of regular reports of individuals being held incommunicado in arbitrary detention without charge or trial and without their families being informed of their detention – often amounting to enforced disappearances.�
Ethiopia’s UPR has highlighted the scale of serious human rights concerns in the country. Amnesty International urges the Human Rights Council to ensure more sustained attention to the situation in Ethiopia beyond this review.
Background
The UN Human Rights Council adopted the outcome of the Universal Periodic Review of Ethiopia on 19 September 2014 during its 27th session. Prior to the adoption of the review outcome, Amnesty International delivered the oral statement above.
Amnesty International had earlier submitted information on the situation of human rights in Ethiopia: http://www.amnesty.org/en/library/asset/AFR25/004/2013/en/95f2e891-accc-408d-b1c4-75f20c83eceb/afr250042013en.pdf
Public Document
International Secretariat, Amnesty International, 1 Easton St., London WC1X 0DW, UK www.amnesty.org
****************************************
� Ethiopia accepted a recommendation to ‘take concrete steps to ensure the 2015 national elections are more representative and participative than those in 2010, especially around freedom of assembly and encouraging debate among political parties,’ A/HRC/27/14/Add.1, paragraph 14 (UK)
� A/HRC/27/14, paragraphs 158.22 (United States), 158.32 (Czech Republic), 158. 33 (Switzerland), 158.34 (Czech Republic), 158.35 (Slovenia), 158.36 (Slovakia), 158.37 (France), 158.38 (Ireland), 158.39 (Czech Republic), 158.40 (United States), 158.41 (Australia), 158.42 (Austria), 158.43 (Belgium), 158.44 (Netherlands), 158.45 (Norway), 158.46 (Sweden), 158.47 (Germany), 158.48 (Czech Republic), 158.49 (Hungary), 158.50 (Australia), 158.51 (Austria), 158.52 (Sweden) and 158.53 (United States).
� A/HRC/27/14, paragraph 11; A/HRC/27/14/Add.1, paragraph 10 (Spain).
� Ibid, paragraphs 158.2 (Tunisia), 158.3 (Uruguay), 158.7 (Denmark), 158.8 (Estonia) (Togo), 158.9 (Hungary), 158.13 (Paraguay), 158.29 (Costa Rica) and 158.30 (Austria);
� Ibid, paragraphs 155.48 (Hungary), 155.49 (Chile), 155.50 (Netherlands), 155.51 (Spain) and 157.9 (United Kingdom).
� A/HRC/27/14/Add.1, paragraphs 1 (Madagascar) and 2 (Cape Verde); A/HRC/27/14, paragraphs 158.2 (Tunisia), 158.3 (Uruguay) and 158.11 (France).

ሰኞን በቃሊቲ (ኤልያስ ገብሩ ጎዳና)

September 23, 2014

‹‹መጽሐፉ በመውጣቱ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡

‹‹መጽሐፌን በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቼም ቢያነቡት ደስ ይለኛል›› ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ

ዛሬ ረፋድ ላይ ከወዳጄ አቤል አለማየሁ ጋር ቃሊቲ ሄደን የቀድሞ የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ባልደረባችን የነበረውን ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን ለመጠየቅ ተቀጣጥረን ነበር፡፡ አቤል፣ ከቀጠሯችን 20 ደቂቃ ያህል ዘግይቶ መስቀል አደባባይ ደረሰና ደወሎ ተገናኘኝ፡፡ ሁለታችንም በ2007 ዓ.ም በአካል የተገናኘነው ዛሬ ነበር፡፡ ‹‹በ2007 ም ቀጠሮ አታከብርም?›› ብዬ ቀለድኩበት፡፡

ሚኒባስ ታክሲ ተሳፍረን ቃሊቲ ደረስን፡፡ የተለመደ ፍተሻውም ታለፈ፡፡ ነገር ግን፣ እስከዛሬ አጋጥሞኝ የማያውቀው አዲስ ፍተሻ መኖሩን አቤል ነገረኝ፡፡ በዘመናዊ ኤሌክትሮኒክስ ማሽን ጫማ እና ቀበቶን አውልቆ በድጋሚ መፈተሽ ግድ ነበር፡፡ ይህም ታለፈና ‹‹ሸራተን›› ተብሎ ወደሚጠራው የቃሊቲ እስር ቤት አመራን፡፡ ይህንንም የእስረኛ መጠየቂያ ቦታ ስመለከተው ለመጀመሪያ ጊዜ በመሆኑ በማያቸውን ነገሮች ላይ ትኩረት መስጠቴ አልቀረም፡፡

አንድ ጥግ ላይ፣ በአጭር ርዝመት በእንጨት የተሰራች መጠየቂያ ጋር ደርሰን ቆምን፡፡ ለአንዱ ጥበቃ ፖሊስ ውብሸትን
እንዲያሥጠራልን ነገርነው፡፡ ውብሸትም ከደቂቃዎች በኋላ ወደእኛ መጣ፡፡ ፊቱ በፈገግታ ተሞልቶ ነበር፡፡ ብርቱካናማ ቲ-ሸርት
አድርጓል፡፡ በቅድሚያ ያገኘሁት እኔ ነበርኩ፡፡ ተቃቅፈን ሰላምታ እየተለዋዋጥን እያለ ከለበሰው ልብስ አኳያ ‹‹የቀለም አብዮት
ልትጀምር ነው እንዴ?›› አልኩትና ትንሽ ተሳሳቅን፡፡ ከአቤልም ጋር ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ የጋራ ወጋችንን ቀጠልን፡፡ ብዙ
ሃሳቦች የተወያየነው በቅርቡ ለንባብ ስላበቃው ‹‹የነጻነት ድምጾች›› የሚል ርዕሥ ስላለው የመጽሐፍ ሁኔታ ነበር፡፡ በመጽሐፉ
መውጣት በጣም ደስ ብሎታል፤ ይህም ፊቱ ላይ በግልጽ ይነበባል፡፡ ብዙ መከራን አሳልፎ ይህንን ማየት መቻሉ በጨለማ ውስጥ
እንዳለች ሻማ ይቆጠራል፡፡

ለረዥም ወራት በኩላሊት ህመም እየተሰቃየ ከዝዋይ ወደቃሊቲ ለሕክምና መጥቶ እንኳን የረባ ሕክምና ሳይደረግለት ውሃ ጠጣ
ነበር የተባለው፡፡ ልብ አድርጉ፣ የዝዋይ ውሃ ጠጠር ያለበት መሆኑ እየታወቀ ወደ ዝዋይ እንዲመለስ ተደርጓል፡፡ የወላጅ አባቱን የሞት መርዶ የሰማው በዘዋይ እስር ቤት ነው፡፡ ሌሎች አስቸጋሪ ነገሮች በውብሸት ሕይወት ውስጥ አልፈዋል፡፡ የሚቀየር ነገር ከሌለ ደግሞ 11 የእስር ዓመታቶች ከፊቱ ይጠብቁታል፡፡ ይህ ሁሉ ታልፎ ይህቺን የተስፋ ብርሃን
እንኳ በእስር ቤት ማየቱ ከምር ደስ ይላል – ለሞራሉ!…ይህህ መጽሐፉን ሙሉ በሙሉ አንብቦ የጨረሰው ዓቤል፣ አንዳንድ ጥያቄዎችን ከመጽሐፉ በመነሳት ሲያቀርብለት እሱም ሲያስረዳ እና ሲመልስለት እያለ ወዳጃችን ሰለሞን ሞገስ አጠገባችን ደረሠ፡፡ የውብሸት ጠያቂዎችም ሶስት ሆንን፡፡

‹‹አሁን ከማን ጋር ነው የታሰርከው?›› ስል ጥያቄዬን አቀረብኩለት፡፡ ከገብረዋድ (የቀድሞ የገቢዎች እና ጉምሩክ ባለሥልጣን መ/ቤት ምክትል ዳይሬክተር እና በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ጉዳቸው በፍርድ ቤት እየታየ የሚገኝ) እና ከአንድ ሌላ ልጅ ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ነኝ›› አለን፡፡ ገረመኝ፤ አብረው ይሆናሉ ብዬ አልገመትኩም ነበር፡፡

‹‹ለአቶ ገብረዋድ አንድ ጥያቄ ጠይቅልኝ?›› አልኩት ለውብሸት፡፡
‹‹ምን?››

‹‹ከሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲቀርቡ ለፍርድ ቤቱ አንድ አቤቱታ አቅርበው ነበር፡፡ በወቅቱ እኔም በችሎት ነበርኩ፡፡ ‹በማዕከላዊ ሰብዓዊ መብታቸው መጣሱን ሲናገሩ ገርሞኝ ነበር ያዳመጥኩት፡፡ በእርግጥ ማንም ሰው በእስር ላይ እያለ ሰብዓዊ መብቱ መጣስ የለበትም፡፡ ነገር ግን፣ አቶ ገብረዋድ የመንግሥት ከፍተኛ ሹመኛ በነበሩበት ጊዜ የተቃውሞ ፓርቲ አመራሮች፣አባላት፣ ጋዜጠኞችና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይ የሚገኙ ዜጎች በተለያየ ምክንያት ተጠርጥረው ፍርድ ቤት ሲቀርቡ፣ በማዕከላዊ የምርመራ እስር ቤት ሰብዓዊ መብታቸው መጣሱን ለፍርድ ቤት አቤቱታ በተደጋጋሚ ሲያቀርቡ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መስማታቸው አይርቀም፡፡ ያኔ ዝም ብለው አሁን በራሳቸው ላይ ሲደርስ ስለመብት ጥሰት መናገራቸው ተገቢ ነበር ወይ? የመብት ጥሰት በራስ ላይ ሲደርስ ብቻ ነው ወይ ድምጽን ማሰማት የሚገባው?!›› አልኩት፡፡

ጥያቄዬን አድምጦ እጠይቅልሃለሁ አለኝ፡፡

የተለያዩ ነገሮችን እየተወያየን እያለ አንዲት ወጣት ልጅ ምግብ እና አነስተኛ ጥራቱን የጠበቀ ፍራሽ ይዛ በአቅራቢያችን መጣች፡፡ አቤል ‹‹ገብረዋድ ጋር ነች›› አለ፡፡ ወዲያው አቶ ገብረዋድ መጣ፡፡ ምቾት እና ነጻነት ባልተሰማው መንገድ ‹‹ሰላም ናችሁ›› የሚል ቃል ከአንደበቱ ወጣና ከውብሸት ጀርባ አልፎ ከምትጠይቀው ልጅ ጋር በትግርኛ ቋንቋ መነጋገራቸውን ቀጠሉ፡፡ ጠይቀን እንደተረዳነው ከሆነ ልጁ ነች፡፡ እኔም ጥያቄዬን ለአቶ ገብረዋድ ላቀርብለት አስቤ ከውስጤ ጋር አውርቼ ነበር፡፡ ነገር ግን፣ ከነበርንበት ቦታ አኳያ አመቺ ስላልነበረ ተውኩት፡፡ አቶ ገብረዋድም፣ ቀድሞን ወጣና ፍራሽ እና ምግቡን ይዞ ቻው ብሎን ሄደ፡፡
ውብሸትም መጽሐፉን አስመልክቶ እንዲህ አለን፡- ‹‹መጽሐፉ በመውጣቱ በጣም ደስ ብሎኛል፡፡ መጽሐፉን ሁሉም ሰው ቢያነበውም ደስ ይለኛል፡፡ ስለሀገራችን የእስር ቤት አስቸጋሪ ሁኔታ እና ስለሌሎች ሀገራዊ ጉዳዮች መጠነኛ መረጃ ያገኛል፡፡መጽሐፌን በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቼም ቢያነቡት ደስ ይለኛል፡፡›› ካለ በኋላ የዳያስፖራ ማኅበረሰብን በተመለከተ ይህቺን ሃሳብ አከለ፡፡

‹‹ዳያስፖራዎች ስለሀገራችን ሁኔታ ያገባናል ስለሚሉ ነው በተለያየ ጊዜ የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ድምጻቸውን በማሰማት ሰልፍ የሚወጡት፡፡ ይህን ባያስቡ ኖሮ በየካፌው ቡና እየተጠጣ ዝም ማለት ይቻላል፡፡ ከታሰርኩ በኋላ ‹‹ፍኖተ ነጻነት›› ጋዜጣን የማንበብ ዕድሉን አግኝቼ ነበር፡፡ አንዲት ሴት የእኔን ፎቶግራፍ ደረቷ ላይ አድርጋ [የታሰሩ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞች ይፈቱ! የሚል] የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ድምጻን ያሰማችበትን ምስል ተመለከትኩና፡፡ ሴትየዋ እኔን አታውቀኝም፡፡ ግን የእኔን የእስር ጉዳት ለመቃወም አደባባይ ወጥታለች፡፡ ይህ ለሀገር ከመቆርቆር የሚመነጭ ነው›› ባለኝ መረጃ መሰረት የውብሸት መጽሐፍ ጥሩ እየተሸጠ ይገኛል፡፡ ሁለተኛ ዕትምም በቅርቡ ይገባል፡፡

ከእኛ ራቅ ብሎ የሚገኘው ፖሊስ ከሌሎች ፖሊሶች ጋር ተነጋገረና ‹‹ሰዓት ሞልቷን፤ በቃችሁ›› አለን፡፡ እኛም ውቤን ‹‹አይዞን!›› በማለት አቀፈን የስንበት ሰላምታ ሰጥተነው ተለየነው፡፡ ‹‹አቶ ገብረዋድን ጠይቅልኝ ያልኩህን እንዳትረሳ›› በማለትም በድጋሚ አስታወስኩት፡፡

Monday, September 22, 2014

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስራ አጦች በየቤታቸው ለማባበያ ካርድ እያደለ ነው

September 22,2014
• ‹‹ምርጫ ሲደርስ የሚደረግ ነው››
• ‹‹ለኢህአዴግ ጥላቻ አለሽ በሚል አንመዘግብም ብለውኛል››

ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሴክተር ለስራ አጦች ‹‹ስራ እንሰጣችኋለን›› በሚል በየቤታቸው የስራ ፈላጊዎች መለያ መታወቂያ ካርድ እያደለ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡
የስራ ፈላጊዎች መለያ መታወቂያ ካርዱ የሚሰጠው የተማረም ሆነ ያልተማረ እስከ 60 አመት እድሜ ለሚገኝ ማንኛውም ስራ አጥ ነው እንደተባለ ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል ከዩኒቨርሲቲ የተመረቁት አዲስ ተማሪዎችና ከአሁን ቀደም ተመርቀው ስራ ያላገኙ ተማሪዎች ‹‹ቀበሌ መጥታችሁ ተመዝገቡ›› እንደተባለ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ካርድ የተሰጣቸው ነዋሪዎች የመዘገቧቸው ሰዎች ‹‹ስራ እንሰጣችኋለን፤ ተከታታይ ስብሰባ ስላለ ስራ ለማግኘት ስብሰባውን መሳተፍ ይጠበቅባችኋል›› እንዳሏቸው ገልጸዋል፡፡ካርዱ ከተሰጣቸው መካከል ያልተማሩም የሚገኙበት ሲሆን በተለያየ መስክ በዲግሪ ተመርቀው ስራ ያጡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ጨምሮ በርካታ ስራ አጦች እንዳሉ በመጠቆም ስራ የማግኘት ተስፋቸውን እንዲገልጹልን የጠየቅናቸው ነዋሪ ‹‹ስራ እንሰጣችኋለን ብለዋል፤ ከሰጡን ማየት ነው፡፡ ግን ለምርጫ ሳይሆን አይቀርም›› ሲሉ ጥርጣሬያቸውን ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ ከአሁን ቀደም በቤተሰብ ደረጃ 1ለ5 ተደራጁ ተብለው ሳይደራጁ የቀሩ የቤት እመቤት ‹‹ከአሁን ቀደምም በቤተሰብ ደረጃ 1ለ5 እንድንደራጅ ተጠይቀን ነበር፡፡ አልተደራጀንም፡፡ ምን አልባት ያ አልሰራ ሲል ይሆናል፡፡ ያው ምርጫ ሲመጣ ብዙ ነገር ይመጣል›› ሲሉ የተሰጣቸው ካርድ የምርጫ ማባበያ ሊሆን እንደሚችል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡በሌላ በኩል ለገዥው ፓርቲ አሉታዊ አመለካከት አላቸው የሚባሉ ዜጎች እንዳይመዘገቡ የተደረገ ሲሆን እንድትመዘገብ በተጠየቀችበት ወቅት ‹‹ካርዱን ተቀብለን ስንሰበሰብ አባል እንድንሆን አትጠይቁንም?›› የሚል ጥያቄ በማንሳቷ ‹‹ለኢህአዴግ ጥላቻ አለሽ፡፡ አንመዘግብሽም›› እንደተባለች ገልጻለች፡፡
ምንም እንኳ መዝጋቢዎቹ ‹‹ሊስትሮም ቢሆን ስራ ካለው እንዳትመዘግቡ›› መባላቸውን የሚገልጹ ቢሆንም ሱቅና በመሳሰሉት የንግድ ስራዎች የተሰማሩ ዜጎች ‹‹ስራ አጥ›› ተብለው እየተመዘገቡ ይገኛሉ፡፡ ይህም ስራ ከመስጠት ይልቅ ለምርጫ ለማባበልና መረጃ ለመሰብሰብ ሊሆን እንደሚችል ካርድ የተሰጣቸው ነዋሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡

የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ ለብድር ዕዳ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድሏ እየሰፋ ነው አለ

September22,2014
ሰሞኑን ለሦስት ቀናት ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ ስሪ ሙሊያኒ ኢንድራዋቲ፣ እያደገ የመጣው የብድር ዕዳ መጠን በኢትዮጵያ ላይ አደጋዎችን ሊያስከትል እንደሚችል ገለጹ፡፡
ኢንድራዋቲ ባለፈው ረቡዕ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ምንም እንኳን የአገሪቱ የብድር ዕዳ መጠን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት አኳያ ያለው ድርሻ አነስተኛ ቢሆንም፣ የዕዳውን መጠን በግልጽነት ለማስተዳደር የሚችልና ግልጽነት የሰፈነበት አስተዳደር ማስፈን የመንግሥት ግዴታ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አገሪቱ ያለባት ጠቅላላ የብድር መጠን 20 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፡፡ ከዚህ ውስጥ 12 ቢሊዮን ዶላር ከውጭ ምንጮች የተገኙ ብድሮችን የሚሸፍን የዕዳ መጠን ነው፡፡ በዚህ መሠረት ከጠቅላላ አገር ውስጥ ምርት አኳያ የዕዳው ድርሻ 44 ከመቶ መድረሱን ይጠቁማል፡፡
ኢንድራዋቲ እንደሚገልጹት፣ ይህ አኃዝ ዝቅተኛ በሚባለው የዕዳ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ነገር ግን የመንግሥት የኢንቨስትመንት ወጪዎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው ምክንያት የዕዳ መጠኑን በዚያው ልክ እያደገ በመሆኑ፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን በሚመለከት ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ከሚመለከታቸው ሚኒስትሮች ጋር መነጋገራቸውን አስረድተዋል፡፡ ከውይይቶቹ መካከልም በመንግሥት አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርሞች ላይ ያተኮረው አንዱ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ በዚህም መንግሥት በአስተዳደራዊ መዋቅሮቹ ላይ ማሻሻያ በማድረግ፣ ግልጽነትና ኢኮኖሚውን በብቃት የማስተዳደር ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን የኢንቨስትመንት ወጪን መነሻ በማድረግ፣ በኢትዮጵያ እየጨመረ የሚገኘውን የብድር ዕዳ መጠንና ሊከሰት የሚችለውን አደጋ ለመቋቋም የሚያስችል አሠራር ማምጣት እንደሚገባቸው መክረዋል፡፡
‹‹ይህንን ለማከናወን አስተማማኝ የፋናይናንስ ሪፖርት ያስፈልጋል፡፡ ግልጽነትና ወጥነት በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ ተዓማኒነት ያለው መረጃ መኖሩ ግድ ይላል፡፡ አሁን እየታየ ያለው የብድር ሁኔታ በኢትዮጵያ ላይ ተጨማሪ የተጋላጭነት አደጋ ማስከተሉ በእርግጠኝነት የማይቀር ነው፤›› ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ የብድር ዕዳዋን ለማቃለል የወጪ ንግድ ሚዛኗ ወሳኝ መሆኑን ኢንድራዋቲ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ባለፉት ሦስት ዓመታት በወጪ ንግድ መስክ አገሪቱ ዝቅተኛ ውጤት ስታዝመገዘብ መቆየቷ ለብድር ዕዳ ያላትን ተጋላጭነት አስፍቶታል ይባላል፡፡
አገሪቱ ስታዝመግብ የቆየችው የኢኮኖሚ ዕድገት መልካም የሚባል መሆኑን የጠቀሱት ኢንድራዋቲ፣ ይህም ሆኖ ኢኮኖሚው መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት ብዙ እንደሚቀረው ገልጸዋል፡፡ የኢኮኖሚው ዕድገት በርካታ የሥራ መስኮችን ሊፈጥሩ የሚችሉ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ለማምጣት ብዙ መንገድ ይቀረዋል ያሉት ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ፣ ባንኩ የኢንዲስትሪ ዞኖች ግንባታን ፋይናንስ እያደረገ እንደሚገኝም አስታውሰዋል፡፡ በአዲስ አበባ ቦሌ ለሚ ሁለተኛ ምዕራፍና በአቃቂ ቃሊቲ ቂልንጦ አካባቢ ለሚገነቡ ሁለት የኢንዱስትሪ ዞኖች የሚውል የ250 ሚሊዮን ዶላር ብድር መፍቀዱን፣ በኢትዮጵያ የባንኩ ዳይሬክተር ጉዋንግ ዚ ቼን ገልጸዋል፡፡
ባንኩ ለመሠረተ ልማት ከሚሰጠው ድጋፍ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ለመሠረታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራምም ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ተዘዋውረው በጎበኟቸው የሴፍቲኔት ጣቢያዎች ጥሩ ውጤት እንዳዩ ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ ተናግረው፣ እየጨመረ በመጣው የከተሞች የምግብ እጥረት ተጋላጭነት ሳቢያ በድምሩ አሥር ሚሊዮን ሰዎች በሴፍቲኔት ፕሮግራም ይታቀፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ይፋ አድርገዋል፡፡
ስሪ ሙልያኒ ኢንድራዋቲ የዓለም ባንክን ከመቀላቀላቸው አስቀድሞ የኢንዶኔዥያ የፋይናንስ ሚኒስትር በመሆን አገልግለዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኢኮኖሚ ጉዳዮች አስተባባሪ ሚኒስትር በመሆንም ሠርተዋል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2010 የዓለም ባንክን የተቀላቀሉት ኢንድራዋቲ፣ በምክትል ፕሬዚዳንትነት ደረጃ የሚመሯቸው በርካታ መስኮች አሉ፡፡ በማኔጂንግ ዳይሬክተርነት ሥልጣናቸው የባንኩን የአካባቢያዊ ሥራዎች በጠቅላላ የመምራት ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል፡፡

Sunday, September 21, 2014

የወያኔውን የከፋፍለህ ግዛ ስርዓት ለመጣል በአንድነት እንነሳ!!!

Septenber21,2014
ዛሬም እንደ ትናንቱ ምንም የማያውቁ ህጻናት ዋይታ!!! የሴቶችና አረጋዊያን ሌላ ዙር መፈናቀል! ሌላ ዙር የጅምላ ስደት መራር መርዶ ከወደ ጋምቤላ
የግጭቱ ስረ መሰረት እንዲህ ነው። የህወሓት አገዛዝየአካባቢውን ማኅበረሰብ በማፈናቀልና ለም መሬታቸውን ቀምቶ በኢንቨስትመንት ስም ባብዛኛው ካንድ አካባቢ ለመጡ የወያኔ አባላት ቀደም ሲል ለሰሩት ወንጀል ማካካሻ እንዲሆን ታስቦ ካቅማቸው በላይ ቸራቸው። እነሱም ያለምንም ይሉኝታና ያካባቢውን ማኅበረስብ ያኗኗር ሁኔታ በጭራሽ ከግምት ሳያስገቡ ጌታዋን እንደተማመነች በግ ያካባቢው ማኅበረሰብ ለዘመናት ሲወርድና ሲዋረድ ጠብቆ ያቆየውን ጥብቅ ደን እየመነጠሩ የጣውላና የከሰል ንግድ ላይ ተሰማሩ።
የአካባቢው ማኅበረሰብ ግን የበይ ተመልካች ሆነ፣ ቅሬታውን ለባለስልጣናት አቤት ቢልም ሰሚ አላገኘም። ጭራሽ ይባስ ብለው በቀየው የተገኘውን ሴት ወንድ ሳይመርጡ በፌደራል ፖሊስ በመቀጥቀጥ ብዙዎችን ለሞት ሲዳርጓቸው ሌሎችን ደግሞ ቁስለኛ አድርገዋል። ከሞትና ከመቁለት የተረፉትም ተፈናቅለው ዱር ገደሉን ቤታቸው አድርገዋል። በሌላም በኩል የግጭቱ ሰለባ የሆኑት ከሌላ ክልል መጥተው ለረዝም ጊዜ ባካባቢው ኑዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊን ዜጎችም የግጭቱ ሰለባ ከመሆነ አልተረፉም ፣እነሱም ሞትና ቁስለኛ ሆነዋል። ከሞትና ከመቁሰልም የተረፉት በቴፒ ከተማ አውላላ ሜዳ ላይ ተበትነው ምንም የማያውቁ ሴቶችና ህጻናት ቀን በጸሀይ ሌሊት በቁር እየተጠበሱ ይገኛሉ። እጅግ የሚያሳዝነው ግጭቱን የሚባብሱትና በዋና ተዋናይነት የሚተውኑት የወያኔው ቅጥረኞች የሆኑ የአካባቢ ካድሬዎችና መሬቱን ያላግባብ የቀሙ ያንድ አካባቢ ተወላጆችና ያንድ አካባቢ የፌደራል ፖሊስና የመከላከያ የበላይ ሹማምንት መሆናቸው ነው።
እንዲህ ዓይነቱ የወያኔ ሴራ ዛሬ የተጀመረ አዲስ ክስተት አይደለም። ህወሓት ገና ከመጀመሪው ሲፈጠር አብሮት የነበረና ላለፉት ሃያ ሶስት ዓመታት የቀጠለ እዳ ነው። ይህ ህወሓት ኢትዮጵያዊያንን እርስ በራስ በማጋጨት ለዘመናት ለመግዛት አስቦና አልሞ የተነሳበትና ከኢጣሊያን ቅኝ ገዝ የተማረው ስልት ነው፤ ይህ የህወሓት ባንዳነት ውጤት ነው።
ባለፉት አመታት በጉራ ፈርዳና በቤንሻንጉል ክልል የተፈናቀሉትን ኢትዮጵያዊን ለዘመናት ከኖሩበት ስፍራ ሲፈናቀሉ ያየነውም ይህንኑ የፋሽስታዊ ስርዓታቸው መገለጫው የሆነውን ዘር ለይቶ ማፈናቀልና ማሳደድን ነው።
በጋምቤላ ክልል በሜጢ ከተማና አካባቢው የንጹሀን ዋይታና ሰሚ ያጣ ጩኸት ሁላችንንም፤ ማለትም ኢትዮጵያዊያንን ሁሉ በእጅጉ ሊያሳስበንና ይገባል። በቶሎ ባንድነት ተረባርበን ካላስቆምነው መዘዙ የምንወዳት ሀገራችንን እንዳልነበረች ሊያደርግ የሚችል አደገኛ ሁኔታ ነው።
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን ተገነዝቦ ስርዓቱን በሁለገብ ትግል ለመስወገድ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ይገኛል፣ በመሆኑም የህዝብ ወገኖች በሙሉ ትኩረታችንን ወያኔ ላይ ብቻ እናድርግ። የወያኔን ከፋፍለህ ግዛ እምቢ በማለት ስርዓቱን ከጫንቃችን አውርደን ለመጣል በሚደረገው ትግል ላይ እንድንረባረብ ግንቦት 7 ጥሪውን ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!

ተጠያቂነት የማያረጋግጥ የመልካም አስተዳደር ንቅናቄ (ግርማ ሠይፉ ማሩ)

September 21,2014
Girma Seifu
ግርማ ሠይፉ ማሩ
ባለፈው ሳምንት ማጠናቀቂያ በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሰብሳቢነት የመንግሰት ከፍተኛ ባለስልጣኖች የ2006 የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ ሁሉም ሪፖርት አቅራቢዎች “ፖወር ፖይንት” በሚባል የማይክሮ ሶፍት ፕሮግራም የተጠቀሙ ሲሆን አብዛኞቹ ይህን ፕሮግራም በቅጡ ለመጠቀም በግል ያላቸውን ዝቅተኛ ችሎታ ያሳየ ብቻ ሳይሆን በየመስሪያ ቤታቸው ሞያ ያላቸውን ሰዎች መጠቀም ያለመቻልና ያለመፈለግን ቁልጭ አድርጎ ያሳየ ነበር፡፡ የተፈቀደላቸውን አጭር ጊዜ ያመጣጠነ ዝግጅት ማድረግ ሳይችሉ ቀርተው ያዘጋጁትን የፅሁፍ ሪፖርት ሲያነቡ ጊዜ አለቀ እየተባሉ ማስተላለፍ የሚፈልጉትን ቁም ነገር (ካለቸው ማለቴ ነው) ትተው በመግቢያና በሪፖርት ይዘት ጊዜ ሲያባክኑ መታዘብ አሰገራሚ ነበር፡፡ ከዚህ አንፃር የውሃ መስኖ ኢነርጂ ሚኒስትሩ አቶ አለማየሁ ተገኑ በንፅፅር የተሻሉ ነበሩ ማለት ይቻላል፡፡ ቴክኖሎጂ የመጠቀም አስፈላጊነቱም ሰዓትን በአግባቡ በመጠቅም ተገቢውን መልዕክት ለማስተላለፍ ነው፡፡ ረፖርት አቅራቢዎች ስዓት በአግባቡ መጠቀም ባለመቻላቸው ሊያቀርቡ ያሰቡትን በሙሉ ካለማቅረባቸው በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ የሰዓት ቁጥጥር ስራ ጨምረውባቸው ነው የዋሉት፡፡ እርግጠኛ ነኝ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሆኑ ኖሮ እንዴት ሊበሳጩባቸው እንደሚችሉ፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ሚኒሰቴር ሚኒስትሯ ወ/ሮ አስቴር ማሞ ድርጅታቸው ኢህአዴግ ንቅናቄውን እንደ ፓርቲ የምርጫ ቅስቀሳ ግብዓት ለመጠቀም መወሰኑን በሚያሳብቅ ሁኔታ መሪ ድርጅታችን ኢህአዴግ አና መንግስታችን በሰጡት ትኩረት በሚል ነበር ንግግራቸውን የጀመሩት፡፡ የመሪ ድርጅታችን ኢህአዴግ በንግግሩ መግባት መልዕክት ለተሰበሰቡት የመንግስት ሹሞች ሳይሆን ጥሪ ለተደረገላቸው እና በአዳራሹ በብዛት ለታደሙት በኢህአዴግ አጣራር “የህዝብ አደረጃጀት” በመባል ለሚታወቁት የኢህአዴግ አፍቃሪዎች ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ቢሆን የስብሰባ ታዳሚዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ ለማለት “ውድ” የሚል ተቀፅላ ያገኙት እነዚሁ የህዝብ አደረጃጀቶች ናቸው፡፡ እርግጥ ነው በቀጣዩ ምርጫ በአሸናፊነት ለመውጣት የእነዚህ የህዝብ አደረጃጀቶች ሚና የላቀ ነው፡፡ በተለይ በአዲስ አበባ ተቃዋሚዎች ተጠናክረው ታዛቢ ካስቀመጡ ምርጫ ቦርድ ያለነዚህ የህዝብ አደረጃጀት ንቁ ተሳትፎ ቢሮ ቁጭ ብሎ ኢህአዴግን ብዙ ሊረዳው አይችልም፡፡ ጠቅላይ ሚኒሰትሩም ሆነ ፓርቲያቸው ይህ በቅጡ የገባቸው ይመስለኛል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመልካም አስተዳደር ጉዳይ እዚህና እዚያ የጎደሉ አግልግሎቶችን በማስተካከል ብቻ የሚያበቃ እንዳልሆነ ይልቁንም የመልካም አስተዳደር ችግር በቀጣይ የሚያመጣው “መዘዝ” ብዙ መሆኑን አበክረው ገልፀዋል፡፡ እርሳቸው “መዘዝ” ያሉትን እኛ አብዮት ስንለው የመንግሰት ሚዲያዎች ደግሞ ተቀብለው “የቀለምና የፍራፍሬ አብዮት” ይሉታል፡፡ ተመስገን ደሳለኝ አብዮት ብቻውን የማይጥም ከሆነ ብሎ ይመስለኛል “የህዳሴው አብዮት” ብሎታል፡፡ ለማነኛውም በዚህች ሀገር የተንሰራፋው የመልካም አስተዳደር ችግር መዘዙ ብዙ መሆኑ በጠቅላይ ሚኒስትር ደረጃ ከታመነ ይህ መዘዝ የተባለው ነገር ስሙ ብዙ አያስጨንቀንም፡፡ የሚያስጨንቀን ይህ መዘዝ እንዳይከተል ምን ማድረግ ይኖርብናል ነው፡፡ በተለይ መንግሰት ይህን መዘዝ ለመከላከል ብሎ ለናይጄሪያ ሽብርተኝነትን ለመከላከል ልምድ ይሆናል ተብሎ የተነገረለትን “የፀረ ሽብር” ህግ እንደመፍትሔ አሰቦት ከሆነ ከመዘዙ እየራቀ ሳይሆን ወደ መዘዙ በፍጥነት እየተጠጋ መሆኑን መረዳት ይኖርበታል፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆኖ ሌሎች ሚኒሰትሮች በተደጋጋሚ ያነሱት ሌላ አብይ ነገር የኪራይ ሰብሳቢነት የሚመለከት ሲሆን ይህን የኪራይ ሰብሳቢነት የገለፁት የኪራይ ስብሳቢነት መረብ በሚል ነበር፡፡ በዕለቱ ያነበብኩት ጋዜጣ ደግሞ በኮንትሮባንድ ሊገባ የነበረ ወተት በኬላ መያዙን የሚገልፅ ክፍል ነበረው፡፡ ታዲያስ ስብሰባ ላይ ቁጭ ብዬ “የሰው ለሰው ድራማ” አስናቀ እና ኢህአዴግ ቁልጭ ብለው ይታዩኝ ጀመር፡፡ ይህን መረብ ለመበጠስ እሰከ አሁን እንዳልተቻለ እና ከፍተኛ ትግል እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒሰትሩን ጨምሮ ሚኒስትሮቹ  እየገለፁ ኢቲቪ ደግሞ አሰናቀ ለፍርድ ሳይቀርብ ለምን ሞተ ብሎ ዶክመንተሪ ይሰራል፡፡ የኪራይ ስብሳቢነት መረብ እስኪበጣጠስ ድረስ አስናቀ መኖር እና ማጋለጥ ነበረበት የሚል አቋም አለኝ፡፡ እናንተስ ምን ትላላችሁ ጎበዝ? አሁን አንድ የቴሌቪዥን ድራማ አጨራረስ እንዴት መሆን እንዳለበት ዶክመንተሪ ያስፈልገዋል? ለማንኛውም የሰው ለሰው ድራማ ደራሲና አዘጋጆች የህዝቡን እንጂ “ባለሞያ” ተብዬዎች በኢቲቪ ያቀረቡትን አስተያየት እንደማትሰሙ እርግጠኛ ነኝ፡፡
ዶክተር ደብረፅዮን በዕለቱ ሪፖርት ከሚያቀርቡት ሚኒስተሮች ቀዳሚውን ቦታ ያገኙ ነበሩ፡፡ ሪፖርት ያቀረቡት በዋነኝነት የቴሌኮሚኒኬሽን ሴክተሩን  በሚመለከትነው፡፡ ከሚመሩት መስሪያ ቤት አንፃር ሲታይም ቴክኖሎጂ በመጠቀም የተሻለ መሆን ሲጠበቅባቸው ማድረግ አልቻሉም፡፡ የቀረበው ሪፖርትም በፍፁም በመሬት ላይ ካላው የቴሌ ችግር ጋር የሚጣጣም አይደለም፡፡ በሪፖርቱ መስረት ሁሉም ችግሮች በእቅድ ከተያዘው ጊዜ ቀደም ብሎ የተተገበረ ሲሆን በአሁኑ ስዓት በተለይ በአዲስ አበባ ይህ ነው የሚባል ችግር እንደሌለ ነው ያበሰሩን፡፡ ይህ ግን በምንም መመዘኛ ተቀባይነት እንደሌለው ለመረዳት ከሪፖርታቸው በኋላ በሻይ እረፍት የተሰበሰቡት ሹመኞች ሳይቀሩ ሲያፌዙ እንደነበር ልነግራቸው እወዳለሁ፡፡ ዶክትር ደብረፅዩን ከአቀረቡት ሪፖርቱ ውስጥ የቴሌን ሰራ ለመስራት የፈጠሩት አደረጃጀት አንድ ጥሩ ነገር ጠቆም አድርጎን አልፏል፡፡ ይህም ፓርላማው ማፅደቅ የማያስፈልገው የቴሌን አገልግሎት በአሰራ ሦስት ክበቦች ወይም ክልሎች መከፋፈላቸው ነው፡፡ ይህም የተደረገው ለአሰራር ቅልጥፍና ሲባል እንደሆነ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህ ተቀባይነት ያለው በጎ ጅምር ነው፡፡ በዚህ አደረጃጀት ሀረሪ ወይም ድሬዳዋ በምንም መለኪያ አንድ ክልል ሊሆን አይችሉም፡፡ አዲስ አበባ እንኳን አንድ ክልል ሊሆን አልቻለም፡፡ ሌሎችም በተመሳሳይ እንዲሁ፡፡ ይህ ለቴሌ አገልግሎት ምቹ የሆነ አደረጃጀት ለሌሎች የመልካም አስተዳደር እንዲሁም ማህበራዊ፣ ኤኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጠቀሜታ በሚመች መልኩ የፌዴራል ስርዓቱ ይዋቀር ለምንል ሰዎች እንደ ጥሩ መግቢያ ሊያገለግል ይችላል የሚል እምነት አለኝ፡፡የፌዴሬሽን ምክር ቤት ይህን ሀሳብ ከዶክተር ደብረፅዮን ወስዶ የህዝቦችን ቋንቋ እና ስነ ልቦና መሰረት ባደረገ ሁኔታ ቢየጠናው ጥሩ ሀሳብ ይመስለኛል፡፡ እሰኪ አንዴ ከያዝነው አስተሳሰብ ወጣ ብለን በተለየ መንገድ ለማሰብ እንሞክር፡፡ ዶክተር ደብረፅዩን ያቀረቡት ሀሳብ በሌሎች ፌዴራል መስሪያ ቤቶችም ሊሞከር ይችላል፡፡ ይህ የምክር ቤት ውሳኔ አይጠይቀም ብለዋልና፡፡
የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔ ባለፈው ዓመት ሰኳር እና ስንዴ እጥረት እንደነበረ በይፋ አምነዋል፡፡ ያቀረቡት ምክንያትም ሰኳር ይደርሳል ተብሎ ተገምቶ በፊንጫ እና ተንዳሆ ሰኳር ፋብሪካ በእቅዱ መሰረት ባለመድረሱ ችግር መከሰቱን ነው፡፡ እኛም ሰንል የነበረው ችግር አለ በእቅድ መስራት አልቻላችሁም እንዲሁም አትችሉም ነው፡፡ የሰንዴም የሰኳርም እጥረት የለም ሲሉን እንዳልነበር አሁን ችግር መኖሩን አምነው ከውጭ ግዥ እየተፈፀመ እንደሆነ ነግረውናል፡፡ ይህች ሀገር በሌላት የውጭ ምንዛሪ በሀገር ውስጥ ሊመረት የሚችልን ምርት ከውጭ እንድታሰገባ እያደረገ ያለን ፖሊሲና ፈፃሚዎቹ ተጠያቂ ሊያደርግ አልቻለም፡፡ ሰኳርና ስንዴ ማቅረብ ያልቻለ የሃያ ዓመት አገዛዝ መዘዝ ሊመጣበት እንደሚችል ቢፈራ ተገቢ ነው፡፡ አንድ በግብርና ላይ የተሰማሩ ባለሀብት ፈራ ተባ አያሉ “ስንዴ ከውጭ ታዞ የሚመጣበት ገዜ እና በሀገር ውስጥ ቢመረት የሚወሰደው ጊዜ ተቀራራቢ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ አስከትለውም “ኢትዮጵያ ሰንዴና ሰኳር ኤክስፖርት የምታደርግ ሀገር እንጂ ከውጭ የምታስገባ መሆን የላባትም፡፡” በማለት ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል፡፡ ግብርና ግን መሬት ይፈልጋል መሬት ደግሞ በመንግሰት እጅ ሆኖ እንደልብ የሚገኝ አይደለም፡፡ የመሬት ፖሊሲያችን ይፈተሸ ስንል ለምን ጫጫታ ይበዛል?
የፍትሕ ሚኒሰትር ሪፖርት በጥቅምት ወር ባቀረቡት እቅድ በግርፊያ ምርመራ ያደርጋሉ ያሉዋቸውን ፖሊሶች እንዴት እንደተቆጣጠሩ ሳይነግሩን ቢጫ ታክሲ ማህበራት ጋር ስብሰባ አድርገናል እና የመሳሰሉትን ሪፖርት ማድረግ ምን ፋይዳ እንዳለው መረዳት ከባድ ነው፡፡ አስገራሚው ደግሞ ፍትህ ሚኒስትር የሚያዘጋጀው የዜጎች ቻርተር ነው፡፡ በእኔ እምነት ፍትህ ሚኒስትር ከህገ መንግሰቱ የተሻለ ሌላ የዜጎች ቻርተር የሚያስፈልገው አይመስለኝም፡፡ በፍትህ ሰርዓቱ እምነት እንዲኖረን ህገ መንግሰቱን ማስከበር ላይ ትኩረት መስጠት ይኖርበታል ብዬ አምናለሁ፡፡ ከሌሎች የመንግሰት አካላት ጋር ተባብሮ የህገ መንግስቱን መስረታዊ ድንጋጌዎች መናድ ማቆም አለበት፡፡ ለዚህም ማሳያው በቅርቡ በመፅሔቶች እና ጋዜጦች ላይ በመንግሰት ሚዲያ የተጀመረውን ስም ማጥፋት ተከትሎ በፍትህ ሚኒስትር መሪነት ወደ ፍርድ ቤት ማምራቱ ነው፡፡ ዘጠና ሚሊዮን ለሚሆን ህዝብ ቢበዛ 20 ሺ ኮፒ ለሚያትም  አንድ መፅሔት ሀገር ሊያጠፉ ነው የሚል መዓት ማውራት ምን አመጣው? ለነገሩ የፈሪ ዱላ የሚባለው ብዒል አንደሆነ መገመት አያሰቸግረም፡፡ ግለሰቦችን እያሳደዱ በማሰር እና አሰሮ ማሰረጃ እያፈላለኩ ነው ከሚል ፌዝ  መውጣት ይኖርብናል፡፡ መንግሰት “የፀረ ሸብር ህግ” ያሰፈልገናል ሲል የነበረው ሰዎችን ሳይዝ በቂ ማሰረጃ ለመሰብሰብ ይጠቅመኛል በሚል እንደነበር እናስታውሳለን፡፡
የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ኃይሌ ይህ ነው የሚባል ነገር ሳያቀርቡ ሰዓት ሰዓት አልቋል ቢባሉም በከተማው የተንሰራፈውን የቤት ችግር ለመቅረፍ በተለይ በማሕበር ለመገንባት ገንዘባቸውን ባንክ ላስገቡ፣ ቅድሚያ ታገኛላችሁ ተግለው ከሚፈለገው 40 ከመቶ በላይ ባንክ ያስገቡ በ40/60 የተመዘገቡ እና በውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊየን በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የቤት አቅርቦት ማሳካት አለመቻል አንድም ነጥብ ሊያነሱ አልቻሉም፡፡ ዜጎች ቤት እናገኛለኝ ብለው ተብደረው ባንክ ያሰቀመጡትን ገንዘብ የመንግሰት ባንክ እየነገደበት ትርፍ በትርፍ ሲሆን ዜጎች ቀጣይ ተሰፋቸው ምን እንደሆነ እንኳን ማሰረዳት አልቻሉም፡፡ አዲሱ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምዝገባ የተጀመረ ሰሞን አንድ ፅሁፍ አቅርቤ እንደ ነበር ይታወሳል፡፡ በሚቀጥለው ዓመት የቤቶች ግንባታን አስመልክቶ ሂሳብ ማውራረድ ስለሚኖር ለዛሬው በዚሁ ማለፍ ይሻላል፡፡ ዜጎች ግን አሁንም ተሰፋ እያደረጉ ነው?
በመጨረሻ ሁሉም ሪፖርት አድራጊ መስሪያ ቤቶች እንደ ችግር ያነሱት “የከፍተኛ አመራር እና ፈፃሚዎች የአመለካከት ችግር መኖር” የሚለው ይገኘበታል፡፡ ይህ ችግር ሁሌም በኢህአዴግ ሰፈር እንዳለ የምንረዳው ስለሆነ መፍትሔው በየአዳራሹ እየመሸጉ ሰልጣና፣ ስልጣና እየተባለ የሀገር ሀብትና ንብረት ከማባከን ተጠያቂነት የሚያሰፍን ሰርዓት በመዘርጋት ኃላፊነቱን ብቃት ላለው ዜጋ ማስረከብ ነው፡፡ አሁን በኢህአዴግ አባልነት በመንግሰት ስልጣን ላይ የሚገኙት በአብዛኛው ከዝቅተኛ ደረጃ እስከ ማስተርስ እና ከዚያም በላይ በርቀትም ሆነ በመደበኛ ይህች ሀገር አስተምራለች፡፡ እነዚህ ኃለፊዎች ባለፉት ሃያ ዓመታት የሰለጠኑ ቢሆንም ለህዝብ መልካም አስተዳደር ለማስፈን የሚያስችል አመለካከትና ክዕሎት ማደበር አልቻሉም፡፡ ስለዚህ ቦታውን መልቀቅ ግድ ይላቸዋል ብንል ድፍረት ሊሆን አይችልም፡፡ ቦታውን የማስለቀቅ ኃለፊነት ደግሞ የህዝብ ነው፡፡ የህዝብ ድምፅ ይከበር ዘንድ ሁሉም የድርሻውን መወጣት አለበት፡፡ ማንም የማንም ነፃ አውጪ አይደለም፡፡

ቸር ይግጠመን!!!

ሕዝቡና ተማሪው በአገር ጉዳይ ከኢህአዴግ ጋር መግባባት አልቻልንም በማለት ስልጠናው እንዲቋረጥ ጠየቀ።

September 21,2014
ምንሊክ ሳልሳዊ
የጎንደር ዩንቨርስቲ ተማሪዎች ብሶታቸውን በከፍተኛ ቁጣ ገልጸዋል።

- ለወያኔ ባለስልጣናት የቀረበው ሪፖርት እንደሚያሳየው ስልጠናው ምንም የስኬት ፍንጭ አላሳየም።

- የሃምሳ አመት እቅድ ለምን አስፈለገ የስልጣን ጥመኝነትን ያሳያል።

- ለሶስተኛ ዙር ስልጠና ምዝገባ እየተካሄደ ነው።

- በኢሕአዴግ ውስጥ ያሉ አመራሮችም ይሁኑ አባላቶቹ የአስተዳደር ብቃት የላቸውም።

- ኢትዮጵያውያን በህግ ፊት እኩል የሚሆኑት እና ፍትህ የሚነግሰው ቀን እንናፍቃለን።

- በቫት ስም መንግስት ዘረፋ ይዟል በህጉ ቫት አይከፈልበትም የተባለው የጤና ዘርፍ ሳይቀር ቫት እየቆረጠ ነው።

በየአከባቢው እየተካሂደ ያለው ልማታዊነትን ሽፋን አድርጎ የስልጣን ማስረዘሚያ ሰበካ (ስልጠና) እንደቀጠለ ቢሆንም በህዝቡ እና በአሰልጣኞች መካክል ከፍተኛ የሆነ አለመግባባት ከመከሰቱም በላይ ህዝቡና ተማሪው በአገራችን ጉዳይ ከኢህአዴግ ጋር ልንግባባ አልቻልንም ስለዚህ አበል ይቅርብን እና ስልጠናውን አቋርጡልን በማለት እየጠይቀ መሆኑን ዘገባዎች አመልክተዋል። ሰልጣኞች እንደሚሉት እየተካሄደ ያለው ስልጠና ሳይሆን የፖለቲካ ሰበካ ነው ይህ ደሞ የተለያየ አስተሳሰብ ያላቸውን ህዝቦች ለማደናቆር ካልሆነ በስተቀር ተቀባይነት የለውም። ስለዚህ የያዛችሁን ስልት ቀይራችሁ ህዝብ መሃል ግቡና አናግሩን እንጂ በ አበል እና በቀበሌ ጥቅማጥቅም አታስገድዱን፡ አያዋጣችሁም ሲሉ ተናግረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለአዲስ አበባ የኢሕአዲግ ጽ/ቤት ቅርብ የሆኑ ምንጮች እንደጠቆሙት እስከዛሬ በተሰጡ ስልጠናዎች የተሰብሰቡ ሪፖርቶች እንደሚይመለክቱት ሕዝቡም ይሁን ተማሪው በተጻራሪነት እንደቆሙ እና በድርጅቱ ላይ ከፍተኛ ጥላቻ እና ማንጓጠጥ ያሳዩ መሆኑን የጠቆመ ሲሆን ስልጠናው ምንም የስኬት ፍንጭ አላሳየም ብሏል።

በጎንደር ዩንቨርስቲ ለየት የሚያደርግው ተማሪው ብሶቱን በከፍተኛ ቁጣ መግለጹ ነው።

በጎንደር ዩንቨርስቲ ተማሪው በዩንቨርስቲው ትምህርት ላይየና በመምህራን ጉዳይ ከፍተና ቁጣ በማሰማት ላይ ሲሆን ዩንቨርስቲው በመልካም አስተዳደር እጦት እና በሙስና እየታመሰ መሆኑን ተነግሯል በአንድ ምት ጊዜ ውጽት ብቻ 3 ፕሮፌሰሮች 3 ዶክተሮች 14 ሁለተኛ ዲግሬ ያላቸው ምሁራን ልምድ ያላቸው መምህርን ጎንደር ዩንቨርስቲን ለቀዋል።ለዚህ ምክንያቱ ደሞ የዩንቨርስቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር መንገሻ አምባገነንነት እና ፈላጭ ቆራጭነት መሆኑን ተማሪዎቹ አስምረውበታል።

የዩንቨርስቲው አመራር እና ቦርዱ አምባገነን ናቸው ያሉት ተማሪዎች በሙስና እና በወገንተኝነት የተዘፈቁ ስለሆኑ በዩንቨርስቲው ከ20 አመት በላይ ያገለገሉ ምሁራን እንዲለቁ ምክንያት ህነዋል።በ2007 ይነሳሉ ተብለው የነበሩት እና በጣም አስቸጋሪ ባህሪ እንዳላቸው የሚነግርላቸው የዩንቨርስቲው ፕረዚደንት ፕሮ.መንገሻ በኢሕ አዴግ ብባለስታን ድ/ር ስንታየው ትእዛዝ እንዲቀጥሉ መደረጉን ተማሪውን አስቆጥቷል።

ህዝቡና ተማሪው ዛሬ በጠዋቱ እነዚህን ሲናገሩ አርፍደዋል።

1 ኢሕአዲግ የሃምሳ አመት እቅድ አውጥቷል መጀመሪያ ደረጃ የ50 አመት እቅድ በማን ማንዴት ነው የሚያውጣው ሃምሳ አመት ከህዝብ ፍቃድ ውጪ የመግዛት እቅድ ኢሕአዴግ አለው ማለት ነው ይህንን አንቀበልም ሃገሪቷን ሌላ አደጋ ውስጥ ለመክተት ካልሆነ በቀር ማንም መንግስት እንዲህ አያቅድም።

2 ኒኦሌቤራሊዝምን እና ሶሻሊዝምን እየጠላችሁ ልማታዊ ዲሞክራሲ ትሉናላችሁ ከየትኛው የትናው እንደሚሻል እንኳን ግንዛቤ የላችሁም በውቀት ያልጠገባ አመራር እና አባል ታቅፋችሁ ሃገር እንዲት እንደምትመሩ በፍጹም አቅቷቹሃል እና አስቡበት

3 የትምህርት ጥራት አውርዶ የዩንቨርስቲዎችን ቁጥር ማብዛቱ፡ተቀሜታው ምንድነው ? በጎንደር ዩንቨርስቲ ዋና ነጥብ የሆነው በዩንቨርስቲው ውስጥ ያለው ትምህርትን የመግደል አምባገነናዊ አስተዳደር በስፋት ተነስቶ እንደነበር ሰልጣኖች ጠቁመዋል።

4. የከተሞችን እድገት በተመለከተ አንጻራዊነት አይታይም የይስሙላ ልማት ፕሮፓጋንዳ እንጂ እድገት የለም መንግስት ባወጣው ህግ በጤናው መስክ ፋርማሲዎች ቫት አያስከፍሉም ይባላል በተዘዋዋሪ ግን የቫት ማሽን አስገብተው እያስከፈሉ ነው ይህ የመንግስትን በዝባዥነት ያሳያል ።ብነጻ ገበያ ሰበብ መንግስት እጁን በገብያ ውስጥ እየከተተ የህዝቡን ንሮ እያደፈረሰ ነው ።ጎን ለጎን የጉምሩክ ቀረጥ የሚጠየቀው ከ እቃው በላይ ነው ይህ ደሞ የከብያውን ትራንዛክሽን እየጎዳው ነው የሚሰራው ለህገር ነው ወይንስ ለዘረፋ ህዝቡ ተማሯል መፍትሄ እንጅ ስልጠና አንፈልግም።

5 መንግስት ሙስኛ ባለስልጣናት ተንሰራፍተዋል እያለ ነው ራሳችሁ ያመናችሁበትን እርምጃ ክመውሰድ ይልቅ እናንተ እርምጃ የምትወስዱባችው ከኢህአዲግ ፖለቲካ ጋር ሲኳረፉ ነው ይህ አግባብ አይደለም ሁሉም ስው በህግ ፊት እኩል መሆኑ ማረጋገጥ የተሳነው መንግስት እንዴት ስልጠና ይሰጣል።



በመቐለ ከተማ 20 ሰዎች ታሰሩ

September21,2014
(አምዶም ገብረስላሴ – ከመቐለ)
በመቐለ ከተማ ሓወልቲ ክፍለ ከተማ በመሬት የነባር ይዞታ ለማረጋገጥ ተብሎ በተጠራ ስብሰባ በተፈጠረ ኣለመግባባት ተከትሎ 4 ሴቶች የሚገኙባቸው 20 ሰዎች ለእስር ተዳርገዋል።
ሓሙስ 08 / 01 / 2007 ዓ ም የሓውልቲ ክፍለ ከተማ ከ 1 ሺ በላይ የኣካባቢው ኑዋሪዎች “….የነባር ይዞታ ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ይሰጣቹሃል…” ብለው ከሰበሰቡ በሁዋላ 200 ሰዎች ማረጋገጫ ሰጥተው የተቀረው “..ኣይመለከታቹም..” ብለው ሲመሉሷቸው በርካታ እናቶች በማልቀሳቸው ምክንያት ኣስተዳዳሪዎቹ ፖሊስ በመጥራት ድብደባ በማድረሳቸው ያካባቢው ወጣቶችም ድብደባው ለመከላከል መኩረዋል።
በዚህ መሰረት 20 ሰዎቹ በክፍለ ከተማዋ ኣስተዳዳሪ ኣቶ በርሀ ፀጋይ የእስር ትእዛዝ በማውረድ እንዲታሰሩ ኣድርገዋል።
የክፍለከተማዋ ኣስተዳደር ሆን ብሎ ያዘጋጀው ድራማ እንደነበርና ድብደባው ለመከላከል የመኮሩት ወጣቶች የቪድዮ ካሜራ ባለሞያ ኣዘጋጅተው ጠብቀው ቀረፃ በማካሄድ የውንጀላ ሴራ ሊጠቀሙበት ኣስበዋል።
የመቐለ ከተማ ኣስተዳደር በመሬት ኣስተዳደር ጉዳይ ዜጎች መደብደብ፣ ማሰር፣ ኣስለቃሽ ጋዝ በመርጨት፣ ንብረታቸው በ ኣፍራሽ ሃይል ማውደም የተለመደ ተግባሩ መሆኑ የሚታውቅ ነው።

Saturday, September 20, 2014

በሰሞኑ የኢህአዴግ ስልጠና ላይ የመምህራኑ ምላሽ

September 20,2014
ከመስከረም 5,2007 አ.ም ጀምሮ መንግስት የአቅም ግንባታ እያለ የጠራው ስልጠና እየተካሄደ ይገኛል:: ገዢው ፓርቲ ስልጣን ከያዘበት 1983 አ.ም ጀምሮ የተለያዩ ስልጠናዎችን ሲሰጥ መቆየቱ የሚታወቅ ሲሆን የዘንድሮውም ከበፊቶቹ ምንም የተለየ ሀሳብ ያለተነሳበት እና ድግግሞሽ የበዛበት ብሎም ገዢው ፓርቲ ለኢትዮጵያዊነት እና ለመምህርነት ሙያ ያለውን አይን ያወጣ ጥላቻ ያሳየበት ነበር::

18ስልጠናው እንደተጀመረ መምህራኑን የማሰልጠን ድፍረቱን እና እድሉን ያገኙት አቶ ኤፍሬም ግዛው የተሰኙ የአዲስ አበባ ከተማ አሰተዳደር ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሀላፊ ናቸው:: አቶ ኤፍሬም በንግግራቸው ወቅት በተደጋጋሚ ሀገሪቷ ከየትኛውም ዘመን በተለየ በኢኮኖሚያዊ እድገቱ እና ሰላም በማረጋገጡ ዘንድ ስኬታማ መሆን እንደቻለች ለማስረዳት ሞክረዋል::

እንደ የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ እምነት ከሆነ የኢህአዴግ ትልቁ ችግር እራሱን ሞቶ ከተቀበረው የደርግ ስርአት ጋር እያነጻጸረ ህዝቡን ለመሸወድ የሚያደርገው ቀቢጸ ተስፋ ነው:: እድገት ውድድር መሆኑን እናምናለን ሆኖም ይህ ስርአት መወዳደር ካለበት ባላፉት 24 አመታት በእነጋና ቦትስዋና እና ደቡብ አፍሪካ ከታዩት ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገቶች ጋር እንጂ ከሞተ ስርአት ጋር ሊሆን አይገባውም:: ሌላው የሰላም ጉዳይ ሰላም አንድ አይነት ትርጓሜ የለውም የጥይት ድምጽ ወይም የቦንብ ፍንዳታ አለመስማት ብቻውን ሰላም አለ ሊያስብል የሚችልበት ምንም አይነት መርህ አይኖርም::


ማሰብ ለቻለ እና ህሊና ላለው ሰው አዛውንቶች እና ህጻናት ጎዳና ወድቀው መመልከት ሰላምን ይነሳል, በሀገራቸው መኖር ስላልቻሉ በስደት አለም የበረሀው ሙቀት የባህር ራት የሆኑት ኢትዮጵያዊያንን ጉዳይ መስማትም ሰላምን ይነሳል, አንድ የሚበላው ያጣ ህጻን ከውሻ ጋር ተሻምቶ ሲመገብ መመልከትም ሰላምን ይነሳል:: በአጠቃላይ በግልጽ የጥይት ድምስ አለመስማት እንደስኬት ልንቆጥረው የሚገባ አይደለም ድምጽ ሳይሰማ የተገደሉ ኢትዮጵያውያንን ጊዜ ይቁጠራቸው:: ው ግለሰብ ናቸው::

እኚህ ግለሰብ በተደጋጋሚ ነፍጠኛ, ጠባብ ትምክህተኛ እና ጨለምተኛ በማለት መምህራኑን ብሎም ሰፊውን የሀገራችንን ህዝብ ሲሳደቡ ውለው ከርመዋል ነገር ግን እንደ የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ እምነት ከሆነ በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ያለው ብቸኛው ነፍጠኛ, ጠባብ ትምክህተኛ እና ጨለምተኛ ለእኔ ብቻ ተዉት እያለ ያለው ኢህአዴግ ብቻ እና ብቻ ነው::
ከዚህ ስልጠና ለመታዘብ እንደቻልነው ገዢው ፓርቲ ትልቅ የተማሩ ሰዎች እጥረት አለበት ይህንንም እራሱ ኢህአዴግ ሆን ብሎ ያደረገው በመሆኑ እነደ መምህር የዚህችን ሀገር የነገ እጣ ፋንታ ስንመለከት ያስፈራል::


በመጨረሻ እ|ኛ መምህራን ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥል ሲል የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ ጥሪውን እያስተላለፈ ሌሎች አካላትም ከመምህራኑ ጊዜያዊ ኮሚቴ ጋር ይቆሙ ዘንድ ጥሪውን ያቀርባል::
ድል ለመምህራን
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ
የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ
መስከረም 10,2007 አ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ የጻፈው “የነፃነት ድምጾች፤ ከማዕከላዊ እስከ ዝዋይ ግዞት” መጽሐፍ ወጣ

September 
14 ዓመት ተፈርዶበት እስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ የጻፈው “የነፃነት ድምጾች፤ ከማዕከላዊ እስከ ዝዋይ ግዞት” መጽሐፍ በገበያ ላይ መዋሉን ከአዲስ አበባ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመከተ።
በዝዋይ ጨለማ እስር ቤት ውስጥ እንደጻፈው በሚነገው በዚህ መጸሐፍ ጋዜጠኛው ክስ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ እስከአሁን ድረስ የገጠመውን ውጣ ውረድ ዘርዝሮ ጽፎታል።
በአራት ም ዕራፎች እንደተከፈለ በተነገለጸለት በዚህ “የነፃነት ድምጾችን ከማዕከላዊ እስከ ዝዋይ ግዞት” መጽሐፉ ስለእስረኞች አያያዝ፣ ከፖሊሶች ጋር ስላለው መስተጋብር፣ ስለሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የአገሪቱ ትልልቅ ባለስልጣናት ከነበሩ እስረኞች ጋር ስላደረገው ቃለ ምልልስና ስለታሰረባቸው ወህኒ ቤቶች ገጽታ ያስቃኛል ተብሏል፡፡ መጽሐፉ በኢትዮጵያ በ50 ብር ከ60 ሳንቲም እየተሸጠ ነው።
yenestanet dimstoch