Monday, November 10, 2014

ለአንድ ወር የጠፋችው የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ አስከሬን ከነመኪናዋ ጭቃማ ኩሬ ውስጥ ተገኘ

November11,2014
(ዘ-ሐበሻ) የቴክሳስ ፖሊስ ከኦክቶበር 2 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ የጠፋችውን ኢትዮጵያዊት እናት አስከሬን ከሃይቅ ያነሰ ውሃ (ኩሬ) ውስጥ ከነመኪናዋ ገብታ ማግኘቱን አስታወቀ::

በመዲ ክሬክ የገበሬዎች ከሃይቅ አነስ ያለ ውሃ ውስጥ አንድ ቫን መኪና የተገኘ ሲሆን ፖሊስ ባደረገው ምርመራ የኢትዮጵያዊቷ አልማዝ ገብረመድህንን ሰውነት እንዳገኘ ጠቁሟል:: የወ/ሮ አልማዝ ሰውነት የተገኝበት ጭቃማ ኩሬ የሚገኘው ከምትሰራበት ቦታ በ3 ማይልስ ርቀት ላይ የሚገኝ ነው:: ፖሊስ የአልማዝ ሰውነትን ከነ ሼቭሮሌት መኪናዋ እንዳገኘ ለቤተሰብ ያስታወቀ ሲሆን አሁን እንዴት መኪናው እዚያ ውሃ ውስጥ እንደገባ በምርመራ ላይ ይገኛል::ተጨማሪ መረጃ ተመልሰን ይዘን እንመጣለን…
almaz


No comments: