Wednesday, November 5, 2014

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ተከሳሾች ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው

November 5,2014
• ‹‹እስላማዊ መንግስት ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም ተሳትፈዋል›› የተባሉ ሌሎች ተከሳሾ በሽብር ተከሰዋል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርት

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብር የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ዛሬ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት የዋስትና ጉዳያቸውን ለማየት ለህዳር 2/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ሀብታሙ አያሌው፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታና ዳንኤል ሺበሺን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ከቀናት በፊት መመስረቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የዋስትና ጉዳያቸውን አይቶ ብይን ይሰጣል ቢባልም የተከሳሽ ጠበቆች አጭር የጊዜ ቀጠሮ በጠየቁት መሰረት ለህዳር 2/2007 በአምስት ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ከ1-5ኛ እና የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ የተከሳሾች የዋስትና ጉዳይ ከመታየቱ በፊት በተከሳሾች ላይ የቀረበው ማስረጃ የገጽ ብዛት ተጠቅሶ ለጠበቃዎቹ እንዲደርሳቸውና የአቃቢ ህጎቹ ስም እንዲጠቀስ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

ጠበቃው የዋስትና ጉዳዩን በተመለከተ በቃል ጥያቄውን ማድረስ እንደሚችሉ ገልጸው፣ ነገር ግን ጊዜ ተሰጥቷቸው በጽሑፍ ለዳኞቹም ለአቃቤ ህጎቹም ማቅረብ እንደሚችሉ ለችሎቱ በጠየቁት መሰረት ለቀጣይ ቀጠሮ በጽሑፍ አዘጋጅተው እንዲቀርቡ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ ያለውን የሰነድ ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ ማቅረቡን በመግለጽ የሰው ማስረጃዎችም እንዳሉት አስረድቷል፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አያሌው 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ሌሎች ተከሳሾች ደግሞ 1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ፣ 3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ፣ 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ፣ 5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ፣ 6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ፣ 7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን፣ 8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ፣ 9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ፣ እና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ 7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም በዋና ወንጀል አድራጊነት ተሳትፈዋል በሚል አቃቤ ህግ ዛሬ ክስ እንደመሰረተባቸው ታውቋል፡፡
ተከሳሾቹም፡-
1ኛ. ተከሳሽ ጃፋር መሀመድ
2ኛ. መሀመድ ኑሩ
3ኛ. መሐመድ ሰሊም
4ኛ. ኑረዲን ጀማል
5ኛ. መሀመድ አባብያ
6ኛ. አኑዋር ጃኒ
7ኛ. ጀማል አብዱ ናቸው፡፡
Photo: በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ተከሳሾች ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው

• ‹‹እስላማዊ መንግስት ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም ተሳትፈዋል›› የተባሉ ሌሎች ተከሳሾ በሽብር ተከሰዋል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርት

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብር የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ዛሬ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት የዋስትና ጉዳያቸውን ለማየት ለህዳር 2/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ሀብታሙ አያሌው፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታና ዳንኤል ሺበሺን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ከቀናት በፊት መመስረቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የዋስትና ጉዳያቸውን አይቶ ብይን ይሰጣል ቢባልም የተከሳሽ ጠበቆች አጭር የጊዜ ቀጠሮ በጠየቁት መሰረት ለህዳር 2/2007 በአምስት ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ከ1-5ኛ እና የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ የተከሳሾች የዋስትና ጉዳይ ከመታየቱ በፊት በተከሳሾች ላይ የቀረበው ማስረጃ የገጽ ብዛት ተጠቅሶ ለጠበቃዎቹ እንዲደርሳቸውና የአቃቢ ህጎቹ ስም እንዲጠቀስ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ 

ጠበቃው የዋስትና ጉዳዩን በተመለከተ በቃል ጥያቄውን ማድረስ እንደሚችሉ ገልጸው፣ ነገር ግን ጊዜ ተሰጥቷቸው በጽሑፍ ለዳኞቹም ለአቃቤ ህጎቹም ማቅረብ እንደሚችሉ ለችሎቱ በጠየቁት መሰረት ለቀጣይ ቀጠሮ በጽሑፍ አዘጋጅተው እንዲቀርቡ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ ያለውን የሰነድ ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ ማቅረቡን በመግለጽ የሰው ማስረጃዎችም እንዳሉት አስረድቷል፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አያሌው 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ሌሎች ተከሳሾች ደግሞ 1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ፣ 3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ፣ 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ፣ 5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ፣ 6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ፣ 7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን፣ 8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ፣ 9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ፣ እና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ 7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም በዋና ወንጀል አድራጊነት ተሳትፈዋል በሚል አቃቤ ህግ ዛሬ ክስ እንደመሰረተባቸው ታውቋል፡፡ 
ተከሳሾቹም፡- 
1ኛ. ተከሳሽ ጃፋር መሀመድ
2ኛ. መሀመድ ኑሩ
3ኛ. መሐመድ ሰሊም
4ኛ. ኑረዲን ጀማል
5ኛ. መሀመድ አባብያ
6ኛ. አኑዋር ጃኒ
7ኛ. ጀማል አብዱ ናቸው፡፡



No comments: