Tuesday, September 17, 2013

የወያኔ ወኪሎች የዩኒቨርሲቲ መምህር ወንድሙ መኰንን ላይ ሊያደርሱ ያሰቡትና ያቀዱት ጥቃት።

September 17, 2013

Uk Maryamየርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ አድርጎ ሾሟቸው የነበረውን ሕዝብ በመክዳት ስልጣኔን ከምለቅ ቤተ ክርስቲያን ተዘግቶ ሕዝበ ክርስቲያንም ተበትኖ ሃይማኖቱም ቢሻው ጥንቅር ብሎ ይቅር በሚል አቋም የሰላምና የፍቅር ቦታ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን የጸብና የሁከት መድረክ ያደረጉት አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው በ30 August 2013 በዕለተ ዓርብ ምሽት ስብሰባ በማድረግ፡ በትምሕርት ገበታ ላይ ሳለ ጀምሮ ላለፉት 22 ዓመታት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰብዓዊ መብት መከበርና ለሰው ልጆች ነጻነት በመታገል በዘረኛው የወያኔ አገዛዝ ድምጽ አልባ ለሆነው ሕዝባችን ድምጽ በመሆን እውነትን ፍንትው አድርጎ በመናገርና በመጻፍ የሚታወቀው የዩኬ ከፍተኛ ትምህርት አካዳሚ ሙሉ “Fellow of Higher Education” ወንድሙ መኰንን የቤተክርስቲያኗ አባል በሆነበትና አስቀድሶ በሚቆርብበት በርዕሰ አድባራት ለንደን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረውን ሁኔታ አስመልክቶ በተለይም አባ ግርማ ከበደ የፈጸሙትንና በመፈጸም ላይ ያሉትን ከመነኩሴ የማይጠበቅ ተግባር ሁሌም እንደሚያደርገውና እንደሚታወቅበት ሥራው እውነትንና እውነትን ብቻ አብጠርጥሮ በመጻፉና ለሕዝብ በማሳወቁ ይህንን ሰበብ በማድረግ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው ታይቶም ሆነ ተሰምቶና ታስቦ በማያውቅ እጅግ በሚያስገርም ሁኔታ በፈጠራ ወንጀል ከግብረ ሰዶማውያን ነጻነት እንቅስቃሴ አባሎች (Gay right movement) ጋር ነገሩን እንደምንም ብለው ጎትተው አገናኝተው፣ በማበር የሚያስተምርበት University of Buckingham ድረስ በመሄድ የተቃውሞ ሰልፍ እናካሂድበት የሚል ዕቅድ በመንደፍ ተግባራዊ ለማድረግ መስማማታቸውን እራሳቸው ለተከታዮቻቸ ካሰራጩት ቴክስት (የተንቀሳቃሽ ስልክ መልዕክት) ለማወቅ ተችሏል። እንዲህ ነው እንጂ ክርስትና!

አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው በነደፉት ዕቅድ መሠረትም ሦስት አውቶብሶችን (coaches) ለራሳቸው በመከራየት ከዛም የግብረ ሰዶማውያን ነጻነት (Gay right movement) አባሎች በተጨማሪ በሁለት አውቶብሶች (coaches) ላይ በመሆን በድምሩ አምስት አውቶብስ ሙሉ ሰውን በመያዝ የተቃውሞ ትዕይንቱን ለማካሄድ መስማማታቸውን በቅጽል ስሙ Endexye የሚባለውና ትክክለኛ ስሙ እንዳለ ወንዳፍራሽ የተባለው ግለሰብ ካሰራጨው የtext መልዕክት ለማረጋገጥ ተችሏል።

የቴክስቱም ቀጥተኛ ቅጂ ቀጥሎ የተመለከተው ነው።


Endal Wondaferash Date: 31/08/2013 Sent from Endexye (his real name is: Endale Wondafrash “Yesterdays meeting went well!! As agreed we will be renting three coaches, our compatriots from the gay right movement will have another two coaches! We will drive to Buckingham university, as planned we will meet with student unions, and we will demonstrate against the imposter so called phd holder who according the university in Ireland who plagiaries his post graduate papers and banned from being named as Dr! Who writes unethical articles against our church leaders, and who vividly exhibits homophobic stances in his communication will be exposed to his colleagues and prospective students for comparing our monk and priest with terrorists that maimed and disturbed the peace of planet, because of his bitchy know it all character to full fill divisive mission to smear the integrity of our religion and clergy men.”

Respond from Dicon Mengesha Melke “Endex complaining to the university were Wondimu work should be practical because he damage the image of our church and the biography of our fathers and sisters.”



Uk Maryam ይህ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አስከፊ ስድብ ከመሳደብና ለአንባ ጓሮ ከመጋበዝ በስተቀር አንድም ቀን ከስሙ በፊት በሚጠራበት ድቁና አንዳችም የክህነት አገልግሎት ሲሰጥ ታይቶም ሆነ ተደምጦ የማይታወቀው መንገሻ ተክሌ የተባለው ግለሰብ፣ ዲያቆን ተብሎ ለመጠራት የቻለበትን የክህነት ማዕረግ ከየት እንዳገኘው የታወቀ ነገር ባይኖርም፣ ዲያቆን ነኝና፣ የካህናት ጉባኤ አባል ነኝ ባይ በማለት እንደውም ከካህናቱ ቀድሞ ለመታየት የሚዳዳው ነው። ይህንን ድርጊቱን ከአፉ፣ ለማረጋገጥ ይኬን ቪዲዮ ይመልከቱ።

http://www.youtube.com/watch?v=gnLIKSGIqJs



በUKም ሆነ በመላው ዓለም የምትገኙ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በአሁኑ ወቅት የወያኔ የጎሳ አፓርታይድ አገዛዝ በየዕለቱ ሰብዓዊ መብቱን በመረገጥ ድምጹን አፍኖ ግፍ ለሚፈጽምበት የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጽ በመሆን የሚጮሁትን የዲያስፖራ ታጋዮች ዝም ለማሰኘት ዕቅድ ነድፎ በመንቀሳቀስ በተለይ በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ወኪሎቹንና ሰላዮቹን አስርጎ በማስገባት በዲያስፖራው ውስጥ አሉ የተባሉ ሃገር ወዳዶችና የሰብዓዊ መብት ታጋይ ኢትዮጵያኖች እያደኑ የተለያየ ጥቃት እንዲደርስባቸው ማድረግ አንዱ ዘዴው በመሆኑ በዚህ እድሜውን ሙሉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሲጮህና ሲከራከር በኖረ ታጋይ ወንድማችን በወንድሙ መኰንን ላይ ለማድረስ የሚቃጣው ጥቃት የዚሁ አካል መሆኑን በመገንዘብ እነዚህ ስደተኛ በመምሰል ከስደተኛው ህብረተስብ ጋር በመቀላቀል የወያኔ የጥቃት መሣሪያ ሆነው በመሰለፍ በቤተ ክርስቲያንም ሆነ በሌላ ተቋማት የተሰገሰጉ ቅጥረኛ ባንዳዎችን መንጥሮ በማውጣትና በማጋለጥ ለድምጽ አልባው ሕዝባችን ድምጽ ሆነው የኖሩ ጀግኖቻችንን ከነሱ የጥቃት በትር መጠበቅና መከላከል ይኖርብናል።

ኢትዮጵያ በክብርና በነጻነት ለዘላለም ትኑር!!

http://ecadforum.com/

No comments: