Monday, November 18, 2013

ጉዞ በኢሕአዴግ ዴሞክራሲ ባቡር

November 18/2013

መድረክ ህዳር 8 ቀን 2006 ዓ . ም በአረብ ሃገር የሚገኙ ወገኖቹን ድምፅ ለማሰማት በአ / አበባ ሳውዲ ኤምባሲ ቅዋሜ ለማቅረብ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ መከልከሉን ሰማሁ . ምን መስማት ብቻ የአ / አበባ መስተዳድርን የክልከላ ደብዳቤ አነበብኩት . የክልከላ ደብዳቤው በከፊል እንዲህ የሚል ነው , -

" ሆኖም ግን በዕለቱ በከተማዋ ተደራራቢ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎች በማካሄድ ላይ ያሉ እና በቅርቡም ለማካሄድ ዝግጅት ያጠናቀቁ ስለ አሉ እውቅና የተጠየቀበትን የሰላማዊ ሰልፍ ተገቢውን የፖሊስ ጥበቃ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመኾኑ የተጠየቀውን የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መኾኑን እንገልጻለን . "

ገርሞኝ የክልከላ ደብዳቤውን ደጋግሜ አነበብኩት . ደጋግሜ ባነበብኩት ቁጥር የ " ዲሞክራሲያችን ባቡር " ጉዞ ታሰበኝ . " ዲሞክራሲ " እና " ባቡር " የሚባሉት ቃሎች ደግሞ የአሜሪካንን ተረት አስታወሱኝ . ምነው ቢሉ ? በዲሞክራሲ መንገድ ከ 200 ዓመት በላይ የተጓዘች አሜሪካ ነቻ - እንደነገሩን . ታዲያ ከእነሱ ተረት ካላጣቀስን ከማን ልናጣቅስ ነው ? ሆሆሆ .... !

የሆኖ ሆኖ እንደተረታቸው እንተርት .

አሜሪካኖቹ በባቡር እየተጓዙ ነው አሉ . ጉዞው 24 ሰዓት ሙሉ ካለዕረፍት የሚደረግ ነው ; እረፍት ቅብርጥሴ ; አቁሙልኝ .... ምናምን ብሎ ነገር የለም . በዚህ የተነሳ ሁሉም የራሱን ስንቅ ይዟል . አናም ባቡሩ ጉዞውን ቀጥሏል .... ጠዋት የተነሳው ባቡር እኩለ ቀን አጋመሰ . የምሳ ሰዓት ደረሰ . ሁሉም ሰው ምሳውን አውጥቶ መብላት ጀመረ . የአጋጣሚ ነገር ሆኖ ከአንድ ሰው በቀር ሁሉም አንድ ዓይነት ምግብ ነው የሚመገበው . ያ ብቸኛ ሰው ግን ምሳውን አሳ ነው የያዘው . ደግሞም አበላሉ ቄንጠኛ ነው . አሳውን ያወጣና ጭንቅላቱን ቅንጥስ አድርጎ ለብቻ ያስቀምጥና ሌላውን ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል . እንደገና ሌላ አሳ ያወጣና ጭንቅላቱን ቆርጦ ያስቀምጥና የተቀረውን የአሳ ክፍል ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል .

በዚህ አበላሉ የተገረመው አጠገቡ የተቀመጠው ሰውዬ አሳ በሊታውን እንዲህ አለው -

" የአሳው ጭንቅላት ይበላል እኮ "

" አውቃለሁ " አለ አሳ በሊታው . " የአሳ ጭንቅላት ከአፉ ጀምሮ ኩርሽምሽም እየተደረገ እንደሚበላ አውቃለሁ "

" ታዲያ ለምን አትበላውም ? "

" ጭንቅላቱን የማልበላው ; ልሸጠው ስለፈለግኩ ነው " አለ - በኩራት .

" ለማን ነው የምትሸጠው ? "

" ጭንቅላታቸው ለማይሰራ ! "

ይኼኔ ጠያቂው ሰውዬ አሰበ . አሰበ አሰበና እንዲህ አለው -

" ታዲያ ለምን እኔ አልገዛህም "

" ይቻላል ! "

" ስንት ስንት ነው የምትሸጠው ? "

" ሁለት ሁለት ዶላር "

በዚሁ ተስማሙ . እናም ተገበያዩ . ገዢው አንዱን የአሳ ጭንቅላት አነሳና ከአፉ ጀምሮ መኮርሸም ጀመረ . አንዱን የአሳ ጭንቅላት እየበላ ግማሹ ላይ ሲደርስ አንዳች ነገር ታወሰውና ወደ ሻጩ ዞር አለና እንዲህ ሲል ጠየቀው -

" ግን አንተ ሙሉውን አሳ ስንት ነው የገዛኸው ? "

" አንድ ; አንድ ዶላር ..... "

ይኼኔ ገዢው ተናደደ . በንዴት " እንዴት ታታልለኛለህ " እያለ ተንጨረጨረ .

ገዢው እየደጋገመ " እንዴት ታታልለኛለህ ? " እያለ ሲንጨረጨር ሻጩ የሰጠው መልስ ነው የተረቱ መቋጠሪያው .

" ምን አታልልሃለሁ ! ይኸው ጭንቅላትህ ሰራ ! " የሚል ምላሽ ነበር የሻጩ ምላሽ .

እና እኔ ይህን ተረት ለምን መጥቀስ ፈለግኩ ?

ኢህአዴግ ባለፉት በርካታ ዓመታት ስለዲሞክራሲ ምሉዕነት ሲጠየቅ , " የዲሞክራሲ ጉዞ ረዥም ነው " የሚል መልስ ነበር የሚሰጠው . በሌላ አገላለፅ " በዲሞክራሲ ሥርዓት ባቡር ውስጥ ነን ; ጉዞውን ለመፈፀም ረዠም ርቀት መጓዝ ያስፈልጋል ," ሲለን ነበር .

የሆኖ ሆኖ የዲሞክራሲው ባቡር በተባለው ጉዞ ውስጥ ተሳፈርን . ተጓዝን . ተጓዝን . ተጓዝን . የኢህአዴግ ዲሞክራሲ መቁረስ ላይ ታደምን .

ከዚያስ ?

እኛ አሳ ይዘን ተገኘን .

ኢህአዴግ " ልግዛችሁ " አለን .

እኛም " ግዛን " አልነው .

ከ " ገዛን " በኋላ " ምን ታታልኙላችሁ " እያለ የሚንጨረጨር ይመስላል - ኢህአዴግ .

ከላይ በተረቱ ውስጥ የአሳ ጭንቅላት የገዛው ሰውዬ ስህተቱ አንድ እና አንድ ነው . የሙሉውን አሳ ዋጋ አስቀድሞ አለመጠየቁ ነው ስህተቱ . የኢህአዲግም ስህተት ተመሳሳይ ነው . የሙሉውን ዲሞክራሲ ዋጋ በውል ለይቶ አለማወቁ ነው . ስለዚህ ነው ሰባራ ሰንጣራ ሰበብ እየፈለገ የዲሞክራሲውን ጉዞ በክልከላ የሚያጅበው .

ስለዚህ ኢህአዴግና ኢሕአዴጋውን ከሁሉ አስቀድሞ ይህ የክልከላ ዲሞክራሲ ባቡር ጉዞ መጨረሻው የት ነው ? ብለው ራሳቸውን ቢጠይቁ ነው የሚሻለው .

እንደው ለማለት ያህል እንጂ ; ............ ?
================= ጉዞ በኢሕአዴግ ዴሞክራሲ ባቡር ============

መድረክ ህዳር 8 ቀን 2006 ዓ . ም በአረብ ሃገር የሚገኙ ወገኖቹን ድምፅ ለማሰማት በአ / አበባ ሳውዲ ኤምባሲ ቅዋሜ ለማቅረብ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ መከልከሉን ሰማሁ . ምን መስማት ብቻ የአ / አበባ መስተዳድርን የክልከላ ደብዳቤ አነበብኩት . የክልከላ ደብዳቤው በከፊል እንዲህ የሚል ነው , -

" ሆኖም ግን በዕለቱ በከተማዋ ተደራራቢ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎች በማካሄድ ላይ ያሉ እና በቅርቡም ለማካሄድ ዝግጅት ያጠናቀቁ ስለ አሉ እውቅና የተጠየቀበትን የሰላማዊ ሰልፍ ተገቢውን የፖሊስ ጥበቃ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመኾኑ የተጠየቀውን የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መኾኑን እንገልጻለን . "

ገርሞኝ የክልከላ ደብዳቤውን ደጋግሜ አነበብኩት . ደጋግሜ ባነበብኩት ቁጥር የ " ዲሞክራሲያችን ባቡር " ጉዞ ታሰበኝ . " ዲሞክራሲ " እና " ባቡር " የሚባሉት ቃሎች ደግሞ የአሜሪካንን ተረት አስታወሱኝ . ምነው ቢሉ ? በዲሞክራሲ መንገድ ከ 200 ዓመት በላይ የተጓዘች አሜሪካ ነቻ - እንደነገሩን . ታዲያ ከእነሱ ተረት ካላጣቀስን ከማን ልናጣቅስ ነው ? ሆሆሆ .... !

የሆኖ ሆኖ እንደተረታቸው እንተርት .

አሜሪካኖቹ በባቡር እየተጓዙ ነው አሉ . ጉዞው 24 ሰዓት ሙሉ ካለዕረፍት የሚደረግ ነው ; እረፍት ቅብርጥሴ ; አቁሙልኝ .... ምናምን ብሎ ነገር የለም . በዚህ የተነሳ ሁሉም የራሱን ስንቅ ይዟል . አናም ባቡሩ ጉዞውን ቀጥሏል .... ጠዋት የተነሳው ባቡር እኩለ ቀን አጋመሰ . የምሳ ሰዓት ደረሰ . ሁሉም ሰው ምሳውን አውጥቶ መብላት ጀመረ . የአጋጣሚ ነገር ሆኖ ከአንድ ሰው በቀር ሁሉም አንድ ዓይነት ምግብ ነው የሚመገበው . ያ ብቸኛ ሰው ግን ምሳውን አሳ ነው የያዘው . ደግሞም አበላሉ ቄንጠኛ ነው . አሳውን ያወጣና ጭንቅላቱን ቅንጥስ አድርጎ ለብቻ ያስቀምጥና ሌላውን ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል . እንደገና ሌላ አሳ ያወጣና ጭንቅላቱን ቆርጦ ያስቀምጥና የተቀረውን የአሳ ክፍል ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል .

በዚህ አበላሉ የተገረመው አጠገቡ የተቀመጠው ሰውዬ አሳ በሊታውን እንዲህ አለው -

" የአሳው ጭንቅላት ይበላል እኮ "

" አውቃለሁ " አለ አሳ በሊታው . " የአሳ ጭንቅላት ከአፉ ጀምሮ ኩርሽምሽም እየተደረገ እንደሚበላ አውቃለሁ "

" ታዲያ ለምን አትበላውም ? "

" ጭንቅላቱን የማልበላው ; ልሸጠው ስለፈለግኩ ነው " አለ - በኩራት .

" ለማን ነው የምትሸጠው ? "

" ጭንቅላታቸው ለማይሰራ ! "

ይኼኔ ጠያቂው ሰውዬ አሰበ . አሰበ አሰበና እንዲህ አለው -

" ታዲያ ለምን እኔ አልገዛህም "

" ይቻላል ! "

" ስንት ስንት ነው የምትሸጠው ? "

" ሁለት ሁለት ዶላር "

በዚሁ ተስማሙ . እናም ተገበያዩ . ገዢው አንዱን የአሳ ጭንቅላት አነሳና ከአፉ ጀምሮ መኮርሸም ጀመረ . አንዱን የአሳ ጭንቅላት እየበላ ግማሹ ላይ ሲደርስ አንዳች ነገር ታወሰውና ወደ ሻጩ ዞር አለና እንዲህ ሲል ጠየቀው -

" ግን አንተ ሙሉውን አሳ ስንት ነው የገዛኸው ? "

" አንድ ; አንድ ዶላር ..... "

ይኼኔ ገዢው ተናደደ . በንዴት " እንዴት ታታልለኛለህ " እያለ ተንጨረጨረ .

ገዢው እየደጋገመ " እንዴት ታታልለኛለህ ? " እያለ ሲንጨረጨር ሻጩ የሰጠው መልስ ነው የተረቱ መቋጠሪያው .

" ምን አታልልሃለሁ ! ይኸው ጭንቅላትህ ሰራ ! " የሚል ምላሽ ነበር የሻጩ ምላሽ .

እና እኔ ይህን ተረት ለምን መጥቀስ ፈለግኩ ?

ኢህአዴግ ባለፉት በርካታ ዓመታት ስለዲሞክራሲ ምሉዕነት ሲጠየቅ , " የዲሞክራሲ ጉዞ ረዥም ነው " የሚል መልስ ነበር የሚሰጠው . በሌላ አገላለፅ " በዲሞክራሲ ሥርዓት ባቡር ውስጥ ነን ; ጉዞውን ለመፈፀም ረዠም ርቀት መጓዝ ያስፈልጋል ," ሲለን ነበር .

የሆኖ ሆኖ የዲሞክራሲው ባቡር በተባለው ጉዞ ውስጥ ተሳፈርን . ተጓዝን . ተጓዝን . ተጓዝን . የኢህአዴግ ዲሞክራሲ መቁረስ ላይ ታደምን .

ከዚያስ ?

እኛ አሳ ይዘን ተገኘን .

ኢህአዴግ " ልግዛችሁ " አለን .

እኛም " ግዛን " አልነው .

ከ " ገዛን " በኋላ " ምን ታታልኙላችሁ " እያለ የሚንጨረጨር ይመስላል - ኢህአዴግ .

ከላይ በተረቱ ውስጥ የአሳ ጭንቅላት የገዛው ሰውዬ ስህተቱ አንድ እና አንድ ነው . የሙሉውን አሳ ዋጋ አስቀድሞ አለመጠየቁ ነው ስህተቱ . የኢህአዲግም ስህተት ተመሳሳይ ነው . የሙሉውን ዲሞክራሲ ዋጋ በውል ለይቶ አለማወቁ ነው . ስለዚህ ነው ሰባራ ሰንጣራ ሰበብ እየፈለገ የዲሞክራሲውን ጉዞ በክልከላ የሚያጅበው .

ስለዚህ ኢህአዴግና ኢሕአዴጋውን ከሁሉ አስቀድሞ ይህ የክልከላ ዲሞክራሲ ባቡር ጉዞ መጨረሻው የት ነው ? ብለው ራሳቸውን ቢጠይቁ ነው የሚሻለው .

እንደው ለማለት ያህል እንጂ ; ............ ?

የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስደተኛ እንጂ ህገወጥ/ወንጀለኛ ዜጋ የለንም:

November 18/2013

- ይህ በአለም ላይ የማይካድ እውነት ነው :: ምንም ከሃገሩ ካለምክንያት አይሰደድም የአንድን ሃገር ድንበርም ጥሶ ካለምክንያት አይዘልቅም :: ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ወደ አረብ አገራት ገብተዋል :: የይልፍ ወረቀት ገዝተው በአየር የወጡትን ጉዳይ ለጊዜው ተወት እናድርገው እና ​​በዛሬው ወቅት ህገወጥ እየተባሉ በአረቦቹ እና በስርኣቱ መሪዎች ስለሚወነጀሉት ኢትዮጵያውያን አጠር ያለ ነገር እናንብብ ::

ወደ አረብ አገራት የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን በሁለት ይከፈላሉ እነዚህ ስደተኞች አብዛኛዎቹ በባህር አቋርጠው እና አስቸጋሪ ፈተናዎችን አልፈው በሰላም ወደ ፈለጉበት የደረሱ የሸሹ የተደበቁ እጅግ አሳዛኝ ዜጎች ናቸው :: በሁለት ከፍለን ስናያቸው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስደተኞች ብለን እናስቀምጣቸዋለን : ; እነዚህ የሁለት ፈርቅ ስደተኞች በጅቡቲ እና በሱማሌላንድ ወደቦች በጀልባዎች ተጭነው የተረፈ ተርፎ የገባ ገብቶ አሁን ላሉበት ሁኔታ ደርሰዋል :: እስኪ ከፍለን እንመልከታቸው

የፖለቲካ ስደተኞች
እንዚ የፖለቲካ ስደተኞች በብዛት የተሰደዱት ከኦሮሚያ ክልል ሲሆን እነዚህ ኢትዮጵያዊ ስደተኞች በተለያየ ጊዜ የእነግ አባላት ናችሁ የኦነግ ጦር ረዳቶች ናችሁ ኦነግን ትደግፋላችሁ በሚል የተለያዩ ችግሮች እና መከራዎች ሲደርሱባቸው ድብደባ እና እስር ሲፈጸምባቸው ይህንን በመሸሽ እንዲሁም የቤተሰቦቻቸውን እና የራሳቸውን የእርሻ መሬት ሲነጠቁ የስራ እድላቸው በፖለቲካ እምነታቸው ሲጋረድባቸው ስርኣቱ በፈጠረው የፖለቲካ ጫና ቤተሰብ ማስተዳደር ሲሳናቸው ወደ የመን ሳኡድ አረቢያ ደቡብ አፍሪካ እና የተለያዩ አገሮች በምድር ጉዞ ይሰደዳሉ : ; እንዲሁም ሴት ልጆች በቤተሰባቸው ላይ ፖለቲካው የፈጠረን ጫና ለማሸነፍ ሲሉ እንዲሁ ይሰደዳል :: እንዚህ የፖለቲካ ስደተኞች ራሳቸውን ለማሸነፍ ሲፍጨረጨሩ ህገወጥ ወይንም ወንጀለኛ አድርጎ ማየት ሃላፊነት የጎደለው አስተሳሰብ ነው ::

የኢኮኖሚ ስደተኞች
በሃገሪቱ የተንሰራፋው የዘረኝነት ጁንታ አብዛኛው ህብረተሰብ እንዳይሰራ ግሬጣ ከመሆኑም በላይ የፖለቲካው አናት የንግድ ድርጅቶቹን በማስፋፋት በሃገሪቱ አንጡረ ሃብት እየተጫወታ ዜጎችን ለድህነት አገሪቱንም ለድቀት ዳርጓል :: የሃገሪቱ የትምህርት ጥራት ትውልድ እንዳያፈራ ተደርጎ አመድ ከተለወሰ በኋላ የስራ አጥ ቁጥሩ በእጥፍ ጨምሯል :: የምእራባውያኑ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን እድገት ስለማይፈልጉ አምባገነንነትን በማበረታታት የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ይነዛሉ :: እንዲሁም እንደ ቻይና የመሳሰሉት አገራት ከቀን ሰራተኛ ጀምሮ በተለያዩ ለውጪ ዜጎች በማይፈቀድ የስራ ዘርፍ ተሰማርተው የአገሪቱን ወጣት በስራ አጥነት እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ አድርገውታል :: ይህ አይነቱ መንግስት ባለስልጣናት ነጋዴነት ሙሰኝነት የውጪ ዜጎች ካለደረጃቸው ዝቅ ብለው የሚበጠብጡት የስራ እድል አሻሚነት ተደማምሮ በአመት ከ 800,000 በላይ ስራ አጥ ስለሚፈጠር የስደት መንስኤ ሊሆን ችሏል :: ወደ አረብ አገራትም የሚሰደዱ ዜጎች የዚህ እና የተያያዥ የኢኮኖሚ ችግሮች ሰለባ ከመሆናቸውም በላይ ይህ ደግሞ የስርኣቱ ለዜጎች የኑሮ እድገት ግዴለሽነት ያመለክታል ::

ይህ በእንዲህ እንዳለ የብሄራዊ እፍረት መንስኤ የሆነው ስርኣት በሚከተለው የፖለቲካ እና የእኮኖሚ ፖሊሲ ምክንያት ዜጎች አገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እና ለሞት ለእስር ለስቃይ እና ለመንገላታት እንዲዳረጉ ሚናውን ተጫውቷል :: ይህንን መፍትሄ ለማምጣት የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስር ነቀል ለውጥ ያስፈልገናል በጋራ አገር ላይ በጋር እንድንሰራ እኛ እናውቅላቹዋለን የሚል ስርኣት ከነአካቴው ሊቆም እና ሃይ ሊባል ይገባዋል : ኢትዮጵያውያን በአረብ አገራት እየደረሰ ያለው መከራ የምን ውጤት ነው መፍትሄውስ ምንድነው ብለን ቆም ብለን የምናስብበት ጊዜ ነው :: ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር ስርኣቱ አሁንም ካለው እኩይ አድራጎቱ ሊቆጠብ ስለማይችል ነገ በሌላም አገር የምንኖር ኢትዮጵያውያን ችግሮች ቢደርሱብን የገዛ ዜጎቼ ሳይሆን የሚለው አብሮ ህገወጥ እና ወንጀለኛ ብሎ በመፈረጅ ለሞት እና ለስቃይ ከመዳለግ ወደኋላ ስለማይል የትግል አድማሳችንን በማስፋት ወንጀለኛው ህገወጡ በሃገሪቱ የተንሰራፋው ስርኣት መሆኑን የማጋለጥ ግዴታ አለብን ; ጎን ለጎንም የመፍትሄ ሰዎች እየሆንን ባለው ስርኣት ላይ ጫና በማሳደር መትጋት ድርሻችን ነው ::
ምንሊክ ሳልሳዊ 






Sunday, November 17, 2013

“እንግዲህ ብታስሩንም እሰሩን እንጂ የታሰሩብንን አባላት ወህኒቤት ሄደን መጠየቃችን አይቀርም” Girma seifu

November 17/2013

 
ባለፈው ሰሞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት በሽብርተኝነት ዙርያ ያደረጉትን ውይይት —- ኢቴቪ ነፍሴ ስንቴ እንደደጋገመው አልነግራችሁም። (ውይይት በድጋሚ ይካሄዳል እንዴ?) እኔ የምለው ግን —- ኢቴቪ “የ24 ሰዓት ሥርጭት የጀመርኩት ቢቢሲ ኢንስፓየርድ አድርጎኝ ነው” እያለ ያስወራል የሚባለው ከምር ነው እንዴ? ቢቢሲ ይሄን ቢሰማ እኮ ኢቴቪን አይለቀውም፡፡ ያለአንዳች ምህረት ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ነበር የሚገትረው – እንደ አምባገነኖቹ የአፍሪካ መሪዎች። አሃ— ከ“ግድያ” የማይተናነስ የስም ማጥፋት እኮ ነው፡፡ እስቲ አስቡት— ሰው “በቢቢሲ ተነሽጬ ነው” ብሎ የ24 ሰዓት “የፕሮፓጋንዳ ጣቢያ” ይከፍታል እንዴ? ኢቴቪ ዶክመንተሪ ፊልሞችም የሚሰራው ቢቢሲን ሞዴል አድርጎ ነው ሲባል ሰምቼ አፌን ይዣለሁ፡፡ (እነ“ሃረካት” እና “አኬልዳማ” እኮ ናቸው ዶክመንተሪ የተባሉት!) አያችሁልኝ የእኔን ነገር — የጀመርኩትን ወግ አንጠልጥዬ ኢቴቪን መተግተግ ያዝኩ፡፡ ደግሞ እኮ የሚሰማ ቢሆን ግዴለም ቀስ እያለ ከስህተቱ ይማራል እንል ነበር፡፡ እሱ ግን “የነቀፈኝ ሁሉ ጠላቴ” ብሎ ሳይደመድም የቀረ አይመስለኝም፡፡ በሉ ወደ ዋናው ጉዳይ ሸርተት እንበል፡፡
እናላችሁ — በሽብርተኝነት ዙሪያ በተደረገው ውይይት ላይ በፓርላማ ብቸኛው የተቃዋሚ ተወካይ የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፤ እንደተለመደው ኢህአዴግ “ከእንግሊዝ ከእነኮማው ቀድቼዋለሁ” የሚለውን የፀረ-ሽብርተኝነት ህግ ሞገቱ ሞገቱና ሲያቅታቸው “እንግዲህ ብታስሩንም እሰሩን እንጂ የታሰሩብንን አባላት ወህኒቤት ሄደን መጠየቃችን አይቀርም” አሉ፤ በተስፋ መቁረጥ። ለነገሩ ይህቺን እግረመንገዴን አነሳኋት እንጂ ዋና ጉዳዬስ ሌላ ነበር፡፡ ይኸውላችሁ —- በዚሁ ውይይት ላይ ከኢህአዴግም ከተቃዋሚም ጎራ የማይመስሉ አንድ “ሃኪም ነኝ” ያሉ ተሰብሳቢ፤ አስገራሚ አስተያየት ሰነዘሩ፡፡ (ምናለ የጦቢያን ፖለቲከኞች ቢያክሙልን?!) “ሃኪም ብዙ ባይናገርም እኔ ግን እድሉን ካገኘሁ እናገራለሁ” ያሉት ተሰብሳቢው፤ “የሚኒስትርነት ሹመት የሚሰጠው የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙር በመዘመር ቢሆን ኖሮ አብዛኞቹ ሚኒስትሮቻችን ፈተናውን ይወድቁ ነበር” ሲሉ የኢህአዴግ ሚኒስትሮችን ሸነቆጡ፡፡ ሽንቆጣውን ተከትሎ በአዳራሹ ውስጥ ከዳር እስከዳር የተስተጋባው ሳቅ ግን ግራ አጋባኝ፡፡ (የራሳቸው የሚኒስትሮቹ ሳይሆን አይቀርም!) ሃኪሙ ሳቁ ገታ እስኪል ጠበቁና፤“ይሄ ሳቅ የተናገርኩት ነገር እውነት መሆኑን ያረጋግጥልኛል” አሉ፡፡
አሁንም ያው ሳቅ ተስተጋባ፡፡ ይኼኔ ጆሮዬን ተጠራጠርኩት። “የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙር ችላችሁ አትዘምሩትም ማለት ያስቃል እንዴ?” ስል ጠየቅሁ – ሚኒስትሮቹን ሳይሆን ራሴን፡፡ ትንሽ ቆይቼ ግን “ግዴለም– ይሳቁ!” አልኩኝ፡፡ (ባለሥልጣናት ሲስቁ አይቼ አላውቅማ!) አንድ ጥያቄ አለኝ፡፡ “ልማታዊ መንግስት” ሳቅ ላይ ያለው አቋም እንዴት ነው? እኔ የምለው ግን— ከሚኒስትሮቻችንና ከሌሎች የመንግሥት ሹመኞች መካከል ምን ያህሉ ብሄራዊ መዝሙራችንን በትክክል ጀምረው ይጨርሱታል? (ዶክተሩ ጉድ አፈሉ እኮ!) አይዟችሁ — መዝሙሯ የሹመት መስፈርት እንድትሆን “ሎቢ” የማድረግ ወይም “ፒቲሽን” የማሰባሰብ እቅድ የለኝም፡፡ አንዲት ከፓርላማ የማትጠፋ የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኛ (ይቅርታ “ነፃ ፕሬስ” የለም፤ “የግል ፕሬስ” እንጂ ተብሏል ለካ!) ምን አለችኝ መሰላችሁ? “አብዛኞቹ የፓርላማ አባላትም መዝሙሩን የሚችሉት አይመስለኝም” ስትል ጥርጣሬዋን ሹክ አለችኝ፡፡
“እንዴት አወቅሽ?” አልኳት በጥርጣሬ እያየኋት። “ መዝሙር ሲዘመር አፋቸውን እየው እስቲ–አይነቃነቅም እኮ!” (“የኢትዮጵያን መዝሙር ሳያውቁ ኢትዮጵያን መምራት???”) በነገራችሁ ላይ — ከብሔራዊ መዝሙራችን ጋር በተገናኘ ሰሞኑን አንዲት ድንቅ የሆነች ኦሪጂናል የቢዝነስ አይዲያ ብልጭ ብላልኛለች፡፡ ምን መሰላችሁ? የሚኒስትሮቻችን ሞባይል ላይ ብሔራዊ መዝሙር መጫን ነው፡፡ ከዚያማ በቃ በፈለጉ ሰዓት ከሞባይላቸው ላይ እየከፈቱ Rehearse ያደርጋሉ – ይለማመዳሉ፡፡ ዝም ብሎ ቱባ ቱባ ሹማምንትን “ብሔራዊ መዝሙር አይችሉም” እያሉ ከማማት— እንዲህ እንደኔ ከእነ መፍትሄው ማቅረብ ብልህነትም ቅንነትም ይመሥለኛል፡፡ እንግዲህ—የብሔራዊ መዝሙራችንን ነገር በዚሁ እንግታና ወደ ሌላ ትኩስ የፖለቲካ አጀንዳ ደግሞ እንለፍ፡፡ እኔ የምላችሁ… ኢህአዴግ እንዴት “አውራ ፓርቲ” ሊሆን እንደቻለ በቅርቡ የተሰጠውን “ሳይንሳዊ” (ይቅርታ አብዮታዊ ማለቴ ነው!) ትንታኔ ሰምታችሁልኛል? የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አባ ዱላ፤ ስለኢህአዴግ “አውራ ፓርቲነት” ሲተነትኑ ፤ “የህዝቡና የፓርቲው ትክክለኛ መስተጋብር ውጤት ነው” ብለዋል፡፡
ይሄንን ብቻ አይደለም አፈጉባኤው ያሉት “ኢህአዴግ እያሸነፈ የሚቀጥልበትና ተቃዋሚ በተቃዋሚነት የሚቀጥልበት ሁኔታ ተፈጥሯል” ሲሉም የገዢውንና የተቃዋሚውን ጎራ የወደፊት እጣፈንታ በ“ግምታዊ ጥናት” ላይ ተመስርተው ተንብየዋል፡፡ አይገርማችሁም? እኔ እኮ ኢህአዴግ ድንገት ተነስቶ “አውራ ፓርቲ” ነኝ ያለ ነበር የመሰለኝ፡፡ ለካስ በጥናት ላይ ተመስርቶ ነው (በአብዮታዊ ጥናት ላይ ማለቴ ነው!) ባለፈው ዓመት ትዝ ይላችኋል አይደል —አቦይ ስብሃትን ጨምሮ በርካቶች “ፓርላማ አስደናቂ መነቃቃት አሳይቷል” ሲሉ፤ አፈጉባኤውን ጨምሮ በርካታ የምክር ቤቱ “ኢህአዴጎች” ሽምጥጥ አድርገው እንደካዱ? (ኢህአዴግ አንዳንዴ አድናቆትና ነቀፋ አይለይም ልበል?) በነገራችን ላይ — የኢህአዴግ “ወዶ-ገብ” የሆኑት በፓርላማ የግል ተመራጭ ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ሳይቀሩ “ዘንድሮ ፓርላማ ጥርስ አውጥቷል” በሚለው ሃሳብ እንደማይስማሙ ሽንጣቸውን ገትረው ተከራክረዋል፡፡ (ድሮም ጥርስ አለው ለማለት እኮ ነው!) የሚገርመው ግን ምን መሰላችሁ? ሰሞኑን አፈጉባኤ አባ ዱላ ከምክር ቤት አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ፓርላማው ጥርስ ብቻ ሳይሆን መንጋጋ ለማብቀል እየሞከረ እንደሆነ የሚጠቁሙ ፍንጮች አሳይተዋል፡፡ እንዴት አትሉኝም? በአፈ-ጉባኤው የተነቃቁ ንግግሮች በኩል ነው! እናማ ወዳጆቼ—ዘንድሮ ፓርላማው እሳት የላሰ ባይሆን ምን አለ በሉኝ! እንዴ — የተከበሩ አባ ዱላ እኮ ቀጥ በቀጥ ባይሆንም “እንደድሮው መፋዘዝ የለም” ብለዋል (አድናቂያቸው ነኝ!) ምናልባት እሳቸው ባሳቡት መንገድ ከሄደላቸው እኮ “Best African Parliament” የሚል አዋርድ ልናፍስ ሁሉ እንችላለን፡፡
እኔን ትንሽ ያልተመቸኝ ምን መሰላችሁ? ይሄ በኢህአዴግ አመራሮች ዘንድ የሰፈነው ተቃዋሚዎችን የመፍራት አባዜ (phobia) ነው፡፡ እኔ እኮ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም በቅርቡ ፓርላማ ውስጥ በሰጡት ማብራርያ “መንግስት አይፈራም፤ ባህሉም አይደለም–”ሲሉ ኢህአዴግንም ማለታቸው መስሎኝ ነበር፡፡ መሳሳቴ የገባኝ ዘግይቶ ነው፡፡ እውነቱን ልንገራችሁ አይደል —- ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን ወይ ይፈራቸዋል አሊያም ይጠላቸዋል፡፡ (ሁለቱም ደግሞ አክሳሪ ናቸው!) በቅርቡ አፈ-ጉባኤ አባ ዱላ፤ በአውራው ፓርቲ አባላት ከጥግ እስከ ጥግ ስለሞላው ም/ቤት ጥንካሬ ሲናገሩ፤ “ከየትኛውም ተቃዋሚ የበለጠ የኢህአዴግን (መንግሥትን) ጉድለቶች ነቅሶ የማውጣት ብቃት አለው” ብለዋል (ይሁንላቸው ባይመስልም!) አክለውም፤ እንደ ተቃዋሚ ግን ለማጋለጥ አይደለም የሚሰራው፤ ለማሻሻል እንጂ ብለዋል፡፡ (ወይ ማጋለጥ!) እኔ ደግሞ ምን እላለሁ መሰላችሁ — መልካም ሥራ በቅጡ መደነቅና መመስገን እንዳለበት ሁሉ መጥፎ ሥራ ደግሞ በደንብ መጋለጥ አለበት ባይ ነኝ፡፡ አሁን ለምሳሌ ሙሰኞችን ከማጋለጥ ውጭ ሌላ ምን አማራጭ አለ? (ምክርና ተግሳፅ ለ“ስኳር” አይሰራም!) እናም አውራ ፓርቲያችንን የምመክረው– የተባለውን ሁሉ አጨብጭበው ከሚቀበሉ “አባላት” ይልቅ ለጊዜው ቢኮሰኩስም ያለአንዳች ምህረት ስህተትንና ጉድለትን የሚያጋልጡ ተቃዋሚዎች ይሻላሉ፡፡

የጂዳ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ባልታወቀ ሁኔታ ላልተወሰነ ጊዜ ተዘጋ

November 17/2013
የኢትዮጵያ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት በጂዳ ስራውን ማቆሙን እና ላልተወሰነ ጊዜ መዘጋቱን መንግስት አሳወቀ ።የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፖብሊክ ቆንጽላ እንደገለጸው ከሆነ ምንም በማይያውቁት ሁኔታ በጂዳ የሚገኘውን መስሪያቤት መዝጋቱን ያሳወቀ ሲሆን በጂዳ የምትገኙት ኢትዮጵያኖች ፣ጉዳአችሁን እራሳችሁ ተወጡት እኔ ለእናንተ አገልግሎት ብቃት የመስጠቱ ብቃት የለኝም ሲል ማግለሉን እንድታውቁት የግርግዳ ላይ ወረቀት ለጥፎላችኋል ::
embassy letter
በሌላም በኩል አቶ ቴዎድሮስ አድሃኖም በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙትን ዜጎቻችንን ለመርዳት ስንል የጂዳውን ቆንጽላ እንድንዘጋው ተገደናል ሲሉ በመገናኛ ብዙሃኖች ገልጸዋል ።ሆኖም ግን አጋዥ ሃይል ከተገኘ ከኢትዮጵያ ወደ ሳኡዲ አረቢያ ሊላኩ የሚገባ የኢምባሲ ሰራተኞች መላክ የሚቻል እና 24/7 አገልግሎት እየሰጡ ወገኖቻቸውን ለማዳን ፈጣን የሆነ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ መሆኑን ሳንገልጽ አናልፍም ።
ኤልሳቤጥ ተስፋዬ ከሜሪላንድ እንዲህ ብላናለች »»»"እሁዳችንን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ አስጀምረውናል! አሪፍ ቁርስ ናት ጎበዝ¡ ለነገሩ ክፍት ቢሆንስ ምን ይጠቅማል። በዱላ ከሚመልሱን በር ዘግተው ቢገላግሉን ይሻለል። ክፍት ሆኖም ዝግ ነበረ እኮ! ዝግ ጭንቅላት ተቀምጦበት በሩ ክፍት ቢሆን ከተዘጋ በር ምን ይለየዋል? እኔ የምለው ቆይ የትኛው ከሳውዲ ጋር ያላቸው ወዳጅነት ነው የወገኖቻችንን ደም እያስከፈለን ያለው? አቤት ወላድ ለጉድ ፈጥሮሽ በምን ቀን ነው ልጆችሽን ወደዛች ሀገር የሰደድሽው?
እባካችሁ ይሄን ያህል ብር ተመድቦ ይሄን ያህል ሰው በቀን እየገባ ነው ብላችሁ ኮመንት አድርጋችሁ ይባስ እንዳታሳምሙኝ። ትላንት ከአንድ ወዳጄ ጋር ስንጫወት "እየተደረገ ያለው ወደ ሀገር የመመለሱ ሂደት አባይን በጭልፋ እንደማለት ነው" ብሎኝ ነበር እውነቱን ነው። ጭልፋው እየጨለፈ,,,, እየጨለፈ,,,, ዝሎ ይወድቃል እንጂ ውሃውን ጨልፎ አይጨርሰውም፣ ዝሎ ባይወድቅ እንኳን ምን ያህል ጊዜና ምን ያህል አቅም ያስፈልገው ይሆን?! መንግስት ከብዛታቸው ጋር የሚመጣጠን አቅም ከሌለው ወይ በሰላም ወይ በተቃውሞ ለምን አይፈታውም? ወይም ሌላ መንግስት በመንግስትነቱ ለዜጎቹ ማድረግ ያለበትን ነገር ለምን አያደርግም? መንግስት ያለው ህዝብ እኮ በህይወት ነው ሀገሩ መግባት ያለበት። እየተደረገ ያለው እርዳታ እኮ እንኳን ለህይወታቸው ለአስከሬናቸውም መድረሱ ያጠራጥራል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የሳውዲው ቆንፅላ በሩን ዘገቶ ከጉዳዩ ራሱን ቢያገል ምን ይደንቃል የገዛ መንግስታችን በፌደራል አስጠብቆ አስከብሮት የልብ ልብ እንዲሰማው አድርጎታል። ወይ ጉድ ጭራሽ በር ዘግተው የእህት ወንድሞቻችንን አስከሬን በበሩ ቀዳዳ አጮልቀው ይቆጥሩ ጀመር አይ የኢትዮጵያ አምላክ ከመንበርህ የለህማ!" አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ደግሞ ይህንን አክሎአል "እነ ዶ/ር ቴድሮስ አድሐኖም የኢትዮዽያ ቆንስላ (በጅዳ) አገልግሎት እንዳይሰጥ የተዘጋው የቆንስላው ሰራተኞች ስደተኞቹን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እንዲያግዙ ስለተፈለገ ነው ይላሉ። ከሆነ ጥሩ ነው። ሰራተኞቹ ስደተኞቹን ሲተባበሩ ኢትዮዽያዊ ዜግነታቸው መሰረት አድርገው እንጂ በፖለቲካ አመለካከታቸው እንደማይመዝኗቸው ተስፋ አደርጋለሁ።
ግን.... ስደተኞችን ለመርዳት ቆንስላ መዝጋት??? እንዴት ነው ነገሩ? ስደተኞችን ለመርዳት ቆንስላው በሙሉ ዓቅሙ (እስከ ሃያ አራት ሰዓት ድረስ) ክፍት መሆን አለበት። የቆንስላው ሰራተኞች ስደተኞቹ ወደ ሚገኙበት ቦታ ተንቀሳቅሰው ዜጎችን እየረዱ ከሆነ ቆንስላው እየሰራ ነው ይባላል እንጂ ዝግ ነው አይባልም። በማስታወቅያውም ቢሆን ቆንስላው የተዘጋበት ምክንያት አይጠቅስም። የቆንስላው ሰራተኞች ስተደኞችን እየረዱ ከሆነ ስለ ቆንስላ መዘጋት ማስታወቅያ መለጠፍ አስፈላጊ አልነበረም ብዬ አስባለሁ። ለማኛውም ጥረት ከተደረገ መልካም ነው።
It is so!!!"

Saturday, November 16, 2013

የወያኔ መንግስት ያጓጓዛቸው ስደተኞች ብዛት 107 ነው 35,000 ስደተኞች በስቃይ ላይ ይገኛሉ

 November 16/2013

መንግስት እስካሁን ወደ ሃገር ቤት የመለሰው በ3 ቀን 107 ዜጎችን ብቻ ነው፤ 35,000 ሰው ለማመላለስ ስንት ቀን ይፈጃል?

 የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵ ያውያንን የማስመለሱ ጥረት ተሳክቶ ዜጎችን እያስመለስን ነው ካሉ በኋላ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ወደ ሀገራቸው መመለስ እንደጀመሩ ቢናገሩም በሳዑዲ ያሉት ኢትዮጵያውያን ቁጥር እና እየተደረገ ያለው የማስመለስ ጥረት ግን በጣም ደካማና የችግሩን ዕድሜ በጣም የሚያራዝም ነው ተብሏል። ማስመለሱ የተጀመረ ዕለት 23፣ ከትናንት በሥቲያ ቀትር ላይ 34 ትናንት ማምሻውን ደግሞ 50 ኢትዮጵያውያን ብቻ የተመለሱ ሲሆን በድምሩ እስካሁን የተመለሱት ዜጎች 107 ብቻ ነው።
(የመንግስት ሚዲያዎች ወደ ሃገራቸው ተመለሱ ሲሉ ያሳዩዋቸው ኢትዮጵያውያን በአዲስ አበባ ኤርፖርት)
እንደ አምባሳደር ዲና ገለጻ፤ በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወደ አገራቸው የሚመለሱ ዜጎችን እየመዘገበ ነው ቢሉም ኢምባሲው ግን ስልኩ የማይነሳ ከመሆኑም በላይ ቦንድ የገዛ፣ የተመረጠ ብሄር አባል የሆኑትን እየመረጠ ቅድሚያ እንደሚሰጥ ኢትዮጵያውያኑ ከሳዑዲ አረቢያ ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል። የውጭ ሚዲያዎች ወደ ሃገራቸው ለመመለስ እጅ የሰጡ ዜጎችን ቁጥር 25 ሺህ የሚያደርሱት ሲሆን በሳዑዲ የሚገኙ ወገኖች ግን 35 ሺህ እንሆናለን ይላሉ። እነዚሁ ዜጎች ወደ ሃገራችሁ ትመለሳላችሁ በሚል የታጉሩበት ሥፍራ ላይ ካለመጸዳጃ፣ ካለ ውሃ፣ ባልተመቻቸ መኝታ እየተሰቃዩ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት በቀን ይህን ያህል ሰው ብቻ ማመላለሱ ችግሩን እንደሚያባብሰው ገልጸዋል።
    
“መንግስት በ3 ቀናት ውስጥ 107 ሰዎችን ብቻ ነው የመለሰው፤ ለኛ የተገለጸልን በቀን 400 ሰው እንልካለን የሚል ነበር” የሚሉት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን በቀን 400 ሰው የሚያመላልሱ ከሆነ በ87 ቀን ይፈጃል ብለን ነበር፤ አሁን ግን በመንግስት ሚድያዎች እንደሚገለጸው 20 እና 30 ሰው ብቻ በቀን ወደ ሃገሩ የሚመለስ ከሆነ በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ይህ ሁሉ ሺህ ሕዝብ መቼ እንደሚመለስ ግራ ገብቶናል ሲሉ በስቃይ ላይ ያሉት ወገኖች ለዘ-ሐበሻ ብሶታቸውን ገልጸዋል።
“ወገኖቻችን ሊደርሱልን ይገባል፤ ኢትዮጵያውያን ለቀይ መስቀል እና ለአይ ኦ ኤም ችግራችንን ሊያስረዱልን ይገባል” የሚሉት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን ችግራችንን ስንገልጽ በኢትዮጵያ ኢምባሲ “ማን ኑ አላችሁ?” እየተባልን እንዋረዳለን፤ አያከብሩንም ሲሉ ያማርራሉ።
በሳዑዲ ኢትዮጵያውያን እየደረሰባቸውን ያለው ስቃይ የተረዱ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ዛሬ እዛው አዲስ አበባ የሚገኘው የሳዑዲ አረቢያ ኢምባሲ ደጃፍ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተንቀሳቅሰው በመንግስት ወታደሮች መቀጥቀጣቸውና ብዙ ሰዎች መታሰራቸውም ዘ-ሐበሻ ዛሬ ጠዋት መዘገቧ ይታወሳል።
በሳዑዲ አረቢያ አሁንም ኢትዮጵያውያኑ በስቃይ ላይ እንዳሉ በስልክ የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
አሁንም ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እናቀርባለን።

Friday, November 15, 2013

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ጐን በመቆም ዋና ተባባሪ መሆኑን በዛሬው እለት አስመስክሯል!

November 15/2013

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡

እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡

በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ቢሆኑም እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራችን ድምፃችንን እንኳን እንዳናሰማ ታፍነናል፡፡ በዚህም እንቅስቃሴ ላይ የተሳተፉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡

የመንግሥት ፖሊሶች የራሳቸውን ዜጋ በመደብደብና በማሰቃየት ብሎም በማሰር በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን በደል ሀገር ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ወገኖቻቸው ላይ ደግመውታል፡፡

ይህ በውሸት ዲሞክራሲ ስም የተደበቀው አምባገነን መንግሥት ሕዝብን ለማሸማቀቅ የወሰደውን እርምጃ ወደ ጐን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅድም አያቶቹን በማስታወስ ያስረከቡትን ክብር ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡

ፓርቲያችን እንዲህ አይነቱን የለየለት የመንግሥት ሕገ ወጥ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ የሚመለከተው መሆኑን እየገለፅን፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጐናችን እንዲቆም በአፅንኦት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም


Thursday, November 14, 2013

አንድ አንዳርጋቸውን መግደል የነፃነቱን ትግል ማስቆም አይቻልም

November 14/2013
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ብሔራዊ ደህንነት አማካሪ የጠቅላይ ሚንስትሩን ቢሮ በርግዶ ገባ። ግንቦት ሰባትን በተመለከተ እቅዳችንን ልነግርህ ነው የመጣሁት ሲል ነገሩን ጀመረ።
እሺ ምንድ ነው እቅዱ ?
የአንዳርጋቸውን፤ ጓደኞቹንና አንዳንድ የኤርትራ ባለስልጣኖችን ለመግደል ዝግጅቱ ተጠናቋል። ኤርትራ ድረስ ሂዶ “መስዋዕትነት” ለመክፈል የሚችል አንድ ሰው አግኝተን ልከናል። ግዳጁን ፈፅሞ ሲመጣ አንዳንድ ነገሮች እናደርግለታል። እርሱም ተስማምቷል።ጥቅምት 28 የምስራች እንሰማለን። እስከዛው ግን ፍተሻዎች እንዲጠናከሩ ወጥተህ ተናገር።
ሰውየው “already” ተልኳል ማለት ነው ?
አዎን ከተላከ አምስት ወር ሁኖታል።
የሚሳካ ይምስላችኋል ?
አዎን . . በሚገባ! እኛ ሞክረነዉ ያልተሳካ ምን ነገር አለ? . . . ጌታዬ። በደንብ ነው የሚሳካው። ዛሬ እዚህ መጥቼ የማሳስብዎት ይህ ጉዳይ ሲታቀድም ሲፈጸምም አልሰማሁም ብለዉ እንደ እግር ኳሱ እንዳያሳፍሩን ብዬ ነዉ።
አይዟችሁ እናንተም አታሳፍሩኝም እኔም አላሳፍራችሁም። እሺ ሰምቼያለሁ። አለ “አማኝ ነኝ ባዩ” ደሳለኝ ኃ/ማሪያም ምንም ዓይነት ወንጀል ያልሰሩ የአገሪቷ ምርጥ ልጆች ደማቸው በከንቱ እንዲፈስ እየተስማማ።
“ድሃ በህልሙ ቅቤ ባይጠጣ ንጣት በገደለው “ሲሉ አመሳጠሩ የሃገራችን ሰዎች።
“ቀፎው ነው እንጂ ሲም ካርዱ ከእኛ ነው” የተባለለትና እና በነፍሰ ገዳዮቹ ወንበር የተቀመጠውን የደሳለኝ ኃ/ማሪያምን ጉዳይ በዚህ እናበቃለን።
ህወሃቶች የንጹሃን ዜጎችን ደም በከንቱ ሲያፈሱ የኖሩ ነብሰ ገዳዮች እንደሆኑ የሚታወቅ ነው። አሁንም ክብሬንና ነፃነቴን የሚሉ ዜጎችን ይዘው ደብዛቸውን ለማጥፋት ብዙ ዓይንና ብዙ ጆሮዎችን በየቦታው አቁመናል እያሉ ያቅራራሉ። ይሄን ሁሉ ዓይንና ጆሮ ይዘንስ የሚያሸንፈን ማን ነው ? ሲሉም ይደመጣሉ። እነርሱ እንደሚሉት ዓይኖቻቸው ማየት፤ጆሮዎቻቸውም መስማት የሚችሉ አይደሉም። የህወሃት ዓይኖች ማየት የተሳናቸው እውራን፤ ጆሮዎቻቸውም ማድመጥ የማያውቁ ደናቁርት እንደሆኑ የታወቀ ነው። ህወሃቶች ይህን የማይሰማ ጆሮና ፤ማየት የተሳነውን ዓይን ይዘው እየተደናበሩ፤ ይህን ለመደበቅ ህይዎት ያላቸው መስለው ይታያሉ። አዎን ህወሃቶች ጭው ባለ በርሃ ላይ ብቻችሁን እንደቆማችሁ እወቁ። የሚነገረው እና የሚሆነው በሙሉ ስለተሰወረባችሁ በብዙ ሚሊየኖች መሃከል ብቻችሁን እርቃናችሁን ቀርታችኋል። ብዙ ሚሊዮን ዓይኖች እና ጆሮዎች በእናንተ ላይ መተከላቸውን ልናስታውሳችሁ እንወዳለን።
ግንቦት ሰባት የፍትህ፤የነፃነት እና የእኩልነት ንቅናቄ እንደ ህወሃት-ኢህአዴግ ጆሮዉ የተደፈነና አይኑ የታወረ ድርጅት አይደለም። ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የሚያይ ዓይን፤ የሚሰማ ጆሮና የሚያስተዉል ልቦና ያለው ህያው ንቅናቄ ነው። የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጥያቄ ግልፅ ነው። ነፃነት ! ፍትህ ! እና ዲሞክራሲ ! ናቸው። እነዚህ ጥያቄዎች በአግባቡ መልስ እንዲያገኙ የሚከፈለውን መስዋዕትነት ለመክፈል ተነስተናል ጉዞ ጀምረናል፤ ሺ አንድአርጋቸውን ፈጥረናል። ልብ ይበሉ ነፃነት ፍትህ እና ዴሞክራሲ ለሰው ልጆች የተሰጡ ክቡር ስጦታዎች ናቸው። ህወሃት እነዚህን ክቡር ስጦታዎች ከዜጎች ላይ ነጥቆና ህዝብን ረግጦ መቀጠል የለበትም። ህወሃት የዜጎችን ነፃነት ነጥቆ ፤ ፍትህን አጓድሎና ህዝብን ረግጦ እንደከዚህ በፊቱ በሠላም እኖራለሁ ብሎ የሚያስብ ከሆነ ተሳስቷል። በህወሃት ቅዥት አገራችን ተጎድታለች። ህዝቧም ለማያባራ ጉስቁልናና ውርደት ተዳርጓል። ብዙዎችም አገር አልባ ሁነው በየሰው አገሩ መፃተኛ ሁነው እንዲኖሩ ተገደዋል። በእኛ እምነት በአገራችን ላይ እየደረሰ ላለው ውርደት በዋናነት ተጠያቂው ህወሃት ነው። ህወሃት የኢትዮጵያ ዋነኛው ጠላት ነው የምንለውም ዜጎቻችንን ለጉስቁልናና ለውርደት ስላደረገም ጭምር ነው። እኛ ይህን አገር በቀል ጠላት ከሥሩ ነቅለን ለመጣል ተነስተናል። ከዚህ ትግል የሚያቆመን ምንም ዓይነት ምዳራዊ ኃይል እንደሌለ ህወሃቶች እንዲያውቁት እንፈልጋለን። ህወሃቶች አንገታችንን አስደፍተው አይገዙንም። ጥቁር ደም ያፈራቻቸው የቁርጥ ቀን ውድ ልጆቿ የነጻነት ታሪክ በጥቁር ቀለም ይጻፍ ዘንድ የሚያደርጉትን ሀገርን የማዳን ጥሪ እንዲህ በቀላሉ መግታት ከቶ አይቻልም። ወያኔዎች አትደናበሩ! ጋሬጣውን መለየትን ለእኛ ተውሉን።
ታዲያ ይህን ንቅናቄ አንድ አንዳርጋቸውን በመግደል ማስቆም የሚቻል የሚመስለው ጅላ ጅል ቡድን አገሪቷን እየገዛ በመሆኑ ተቆጭተናል። አንዳርጋቸውን መግደል ሌሎች በርካታ ኢትዮጵያዊ አንዳርጋቸውን መፍጠርና ትግሉንም የሚያጠናክር እና የሚያፋፍም መሆኑን አልተረዱም። የኢትዮጵያ ህዝብ የእምቢተኝነት፣ የአልገዛም፣ የነጻነት ታሪክን ለማስከበር መሰዋእትነትን ለመክፈል ዝግጁ መሆንን ከአንዳርጋቸው ከተማረ ቆይቷል። መቆጨታችን ግን እንዲሁ በቁጭት ብቻ የሚቀር የሚመስለው ካለም ድግሞ ተሳስቷል። ይሄ ቁጭት በየደረሱበት የንፁሃንን ደም በከንቱ ማፍሰስ አገር መምራት የሚመስላቸውን ህውሃቶች ከተንጠለጠሉበት ዙፋን አውርደን በልካቸውና በአቅማቸው እንዲኖሩ ለማድረግ የጀመርነውን ትግል ይበልጥ አጠናክረን እንድንቀጥል ያደርገናል። ህወሃት ውስጥ እንደ ሰው ማሰብ የሚችል ግለሰብ ካለ አሁን ቆም ብሎ እንዲያስብ እናሳስበዋለን። ጀንበር ሳትጠፋባችሁ ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲና ለፍትህ የሚደረገውን ትግል ተቀላቀሉ። እርግጥ ነው ለነፃነት የሚደረገው ትግል በየመስኩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ህወሃትም የእጁን እንደሚያገኝ ምንም ዓይነት ብዥታ እንዳይኖራችሁ ልንነግራችሁ እንወዳለን።
ግንቦት ሰባት የቆመበት መሠረት ፅኑ፤ ዓላማውም ህዝባዊ ነው። በዚህ በፀና መሠረት ላይ ህዝባዊውን ዓላማ አንግበው የተነሱ ሚሊዮኖች አሉ። እነዚህ ሚሊየኖች የሌሉበት ሥፍራ የለም። ከቤተ-መንግስት እስከ እርሻ ማሳ፤ ከስለላ ተቋማት እስከ አገሪቷ መከላከያ ኃይል፤ ከሃይማኖት ተቋማት እስከ መንግስት መሥሪያ ቤቶች፤ ከዘመናዊ ትምህር ተቋማት እስከ ተከበሩ ገዳማት ድርስ ለክብራቸው ዘብ የቆሙ ሚሊየኖች አሉ። እነዚህ ሚሊኖች የቆሙት መረቅ የበዛበትን ወጥ ዓላማ አድርገው ሳይሆን በፀናው መሠረት ላይ ለተተከለው ክቡር ዓላማ ነው። ይህ ክቡር ዓላማ ነፃነት፤ ፍትህ ፤እኩልነት እና የህግ የበላይነት እንጂ ሌላ አይደለም። እነዚህ ሚሊየኖች አትኩረው ማየት የሚችሉ ድንቅ ዓይኖች ያሏቸው፤ አጥርተው ማድመጥ የሚችሉ ክቡራን ጆሮዎች ያሏቸው መሆናቸውን ህወሃቶች እንዲያውቁት እንወዳለን።
ግንቦት ሰባት ማንንም ፍርሃት እና ድንጋጤ ውስጥ መክተት አይፈልግም።እንዲያውም ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የሚታገለው ዜጎች ሁሉ ከፍርሃት ነፃ ሁነው በደስታ እንዲኖሩ ለማስቻል ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ካሁን ወዲያ ከግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዓይንና ጆሮ የሚያመልጥ አንዳችም ነገር እንደማይኖር የሚያሳድደን ቡድን እንዲያውቀው እንፈልጋለን። ዓይንና ጆሯችን በሁሉም ሥፍራ በንቃትና በጥንቃቄ ነገሮችን እየተከታተሉ ይገኛሉ።
ህወሃቶች ከትዕቢታችሁ ብዛት የተነሳ የህዝቡን ምክር መናቃችሁን እናውቃለን።የወገኖቻችንንም ድምፅ ጫጫታ እያላችሁ እንደምትሳለቁም እናውቃለን። ይሄ እንደማይጠቅማችሁ ብዙ ግዜ ነግረናችኋል። የህዝቡን ምክር ስሙ፤ የወገኖቻችሁንም ድምፅ አድምጡ ብንላችሁ በእምቢታችሁ ፀንታችኋል። ልቦናችሁ እንደ ፈርዖን ልብ ደንድኗል።ልብ ማደንደን እንኳን እናንተን ለመሠለ ደካማ ፍጡር ይቅርና በዘመኑ እኔ “እምላክ” ነኝ እሰከ ማለት ለደረሰው ለፈርዖንም አልበጀም። እንዲህ ዓይነት የልብ ድንዛዜ እናንተ በዚያ ጠባብ ዓላማችሁ ጣልነው ለምትሉት ለመንግስቱ ኃ/ማሪያምም አልረባውም። አሁንም የእኛ ምክር አጭርና ግልፅ ነው። የመዘዛችሁትን የበቀል ሰይፍ ወደ ሰገባው መልሱ። የዘጋችሁትን በር ክፈቱ። የነጠቃችሁትን የዜጎች ነፃነት መልሱ። በህዝቡ ላይ ያወረዳችሁትን የፍርሃት ድባብ አስወግዱ። የተከላችሁትን የዘረኝነት እሾህ ንቀሉ። ከእውነት ጋርም ታረቁ። እንዲህ ብታደርጉ የዚያችን አገር በረከት ትበላላችሁ፤ እምቢ ብትሉ ግን የሚበላችሁን እሳት ማጥፋት አይቻላችሁም። መጥተናል!!
እኛም ከምን ግዜውም በላይ ተጠናክረናል። የትግል ዘርፋችን ሰፍቷል። በሁሉም አቅጣጫ መረባችን ተዘርግቷል። ከዚህ መረብ የትም አታመልጡም። ማምለጫ መንገዳችሁ አንድ ብቻ ነው። እርሱም የህዝቡን ድምፅ መስማት፤ እውነተኛ መልስ መስጠት እና ለህግ ተገዢ መሆን። አበቃን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ አሁኑኑ ይቁም!!!

በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው መከራ መስማት ህሊና መሸከም ከሚችለው በላይ ሆኗል። ኢትዮጵያዊን እህቶቻችን ወንድሞቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ፤ አካሎቻቸው በስለት እየተቆራረጠ፤ እየተደበደቡና እየተደፈሩ ነው።
ይህ ሁሉ የሚፈፀው በሪያድ፣ ጂዳና አዲስ አበባ የሚገኙ የወያኔ ዲፕሎማቶች መልካም ፈቃድና ሙሉ ተባባሪነት መሆኑ ደግሞ ይበልጥ የሚያንገበግብ ነው። ወያኔ ለአረብ ሀብታም ሸሪኮቹ ለም መሬቶቻችንን ሰጥቶ ኢትዮጵያዊ በአገሩ ሠርቶ የእለት ጉርሱን መሸፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ አደረገው። ቀጥሎ ደግሞ በሺዎች የሚቆጠሩ ልጃገረዶችና ወጣት ኢትዮጵያንን እየደለለ ከባርነት ላልተሻለ ግርድና አሳልፎ ሰጣቸው። ይህ ሁሉ ግፍ አልበቃ ብሎ “በሏቸው፤ ቀጥቅጧቸው፤ ህገወጦች ናቸው” እያለ በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ በአጋፋሪነት እያስተናገደ ነው።
በኩየት በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ ተመሳሳይ ሰቆቃ ሊደርስ የሚችል መሆኑ ምልክቶች እየታዩ ነው። በኩዌት ያለአንዳች ምክንያት ቁጥራቸው በአንድ ሺህ በላይ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን በድንገት ከሥራ ተባረዋል። እዚህም የወያኔ እኩይ እጆች እንዳሉት መረጃዎች አሉ። በሌሎች የመካከለኛው ምሥራቅ አገሮች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንም ሕይወታቸው በዘወትር ስጋት ላይ ወድቋል።
የኢትዮጵያዊያን እጣ ፈንታ በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም ሰቆቃና እንግልት መሆኑ የሚያሳዝን ብቻ ሳይሆን የሚያስቆጭ፤ ለመራራ ትግል የሚያነሳሳም ነው። ለአገሩ ሕዝብ የሚቆረቆር መንግሥት ኑሮን ቢሆን ኖሮ ሕይታችን እንዲህ የተመሰቃቀሰ ባልሆነም ነበር።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሳውዲ አረቢያ እና ሌሎችም የመካከለኛ ምሥራቅ አገራት መንግሥታት ለኢትዮጵያዊያን እህቶቻንና ወንድሞቻችን ሰብዓዊ ክብር እንዲሰጡ አበክረን እናሳስባለን። ሰብዓዊ መብቶችን መድፈር ዓለም ዓቀፍ ወንጀል መሆኑን ልንነግራቸው እንፈልጋለን። በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ አሁኑኑ ይቁም!!! ሰቆቃ ፈፃሚዎች ለፍርድ ይቅረቡ!!!
በተቻለው ፍጥነትና ባገኘነው እድል ሁሉ ተጠቅመን ሕይወታቸው አደጋ ላይ ላሉት ወገኖቻችን እንድንደርስ ግንቦት 7 ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ያደርጋል።
በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ በዘላቂነት የሚወገደው ወያኔ ከሥልጣን ተባሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የመረጠው መንግሥት ሲያስተዳድር በመሆኑ ለዚህ ታላቅ ግብ በኅብረት እንነሳ።
በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ይቁም!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

መምህር አበበ አካሉ በመንግስት የደህንነት ኃይሎች ስለደረሰባቸው ጉዳት ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ ፡፡ ሙሉ ቃለ-ምልልሱን ያገኙታል

November 14/2013

መምህር አበበ አካሉ የአንድነት ፓርቲ የብሄራዊ ም/ቤት አባልና በተለያዩ ጋዜጦች ላይ ንቁ ተሳታፊ ናቸው፡፡ መምህሩ አንድነት ፓርቲ በሚያደርጋቸው እንቅስቀሴዎች ላይ በመሳተፍ በተለያይ የሀገራችን ክፍሎች ተዟዙረዋል ነው፡፡ ፍኖተ ነፃነት በቅርቡ በፖለቲካ አቋማቸው የተነሳ ስለደረሰባቸው አደጋና  አሳሳቢ ስለሆነው የሀገራችን የትምህርት ጥራት ሁኔታ አነጋግራቸዋለች፤ መልካም ንባብ፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በመጀመሪያ ስለራስዎ ቢያስተዋውቁን?

አቶ አበበ፡- አበበ አካሉ እባላለሁ፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪዬን የያስኩት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ በአማርኛና ስነ ፅሁፍ ነው ፡፡ መምህር ነኝ፡፡ ላለፉት 29 አመታት በመምህርነት ሙያዬ አገልግያለሁ፡፡
 
ፍኖተ ነፃነት፡- በቅርቡ በፖለቲካ አቋምህ የተነሳ በመንግስት ኃይሎች ጉዳት ደርሶብዎ ነበር፤ መነሻ ምክንያቱ ምክንያት ምን ሊሆን ይችላል? አሁንስ በምን ደረጃ ነው የሚገኙት?

አቶ አበበ፡- ማስጠንቀቂያዎች የደረሱኝ ፍኖተ ነፃነት ላይ በጣፎ ጉዳይ ብዙ ነገር ማጋለጥ ከጀመርን በኋላ ነው፡፡ በዚያ የተነሳ የከተማው ወጣቶች ይከተሉኝ ጀመር፡፡ ቤቴ ድረስ እየመጡ የሚያስፈራሩኝ በዚህ ነው፡፡ ተናገርክብን፣ አጋለጥከን ነው የሚሉት፡፡ ዋናው መነሻ ግን በሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ ወቅት በደሴ፣በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በፊቼና በአዳማ ቅስቀሳዎችንና ሰልፎችን በመምራቴ ነው፡፡
የሚገርመው ባህር ዳር ለሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ለመሄድ ስሰናዳ ለባለቤቴ እርምጃ እንደሚወሰድብኝ መረጃ ደረሳት፡፡ ጠዋት ልወጣ ሲል ውዝግብ ውስጥ ገባን፡፡ “ሻንጣዬን ብቻ ስጪኝ፣ ይኸው ቤቱ፣ ደሞዜንም ሙሉ እሰጣዋለሁ እንጂ ማስፈራሪያ መጣ ብዬ በህገ መንግስታዊ መብቴ አልተውም አልኳት፡፡ ትንሹ ልጄም ህገ መንግስት ይዞ መጣ፡፡ በዚህ በዚህ አንቀፅ የተነሳ በማንኛውም ህጋዊ ተቋም ውስጥ የመሳተፍ፣ ሀሳቡን የመፃፍ … መብት አለው ሲል አሳመነ፡፡ በርግጥ “በትግሉ ከገፋ በወጣበት እናስቀረዋለን” ስላሏት እንጂ እሷም መብቴን ታከብራለች፡፡
 
ፍኖተ ነፃነት፡- ስትደበደብ ምን አሉህ?

አቶ አበበ፡- ከፖለቲካ አቋሜ አንስተው በሰላማዊ ሰልፉ ጉዳይ ላይ አተኮሩ ከዚያም ስለ ለገ ጣፎ ጉዳይ አነሱልኝ፡፡ “ጣፎ ላይ የተለየ አብዮት መፍጠር ትመኛለህ” አሉኝ፡፡ “እንዲያውም ጣፎ የሊብያዋ ቤንጋዚ ናት እያላችሁ ነው” ሁሉ ሲሉ ነበር፡፡ በርግጥ ጣፎ ላይ መንግስትን ሳይሆን ሙስናውን ነበር የምንዋጋው፡፡

ስለድብደባው ደግሜ መስታወስ አልፈልግም፡፡ እጄ ሰባራ ነበር፡፡ እንደ ሸንበቆ ሲያንቋቁት ምንም አይሰማቸውም ነበር፡፡ ያጠጡኝ ነገር ዶክተሩ “Absolute” አልኮል ነው ቢሎኛል፡፡ ጨጓራዬ ላይ ከባድ ችግርም አድርሶብኛል፡፡ እሽት አድርገው ከደበደቡኝ በኋላ ነው ያጋቱኝ፡፡ ሽታው አያስጠጋም ነበር፡፡ በዚያ ላይ አልኮል አልጠቀምም፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በኢሳት ላይ “ሌላ የደረሰብኝ ጉዳት አለ እሱን በቅርቡ ይፋ አደርገዋለሁ” ብለው ነበር፤ ምን አይነት ጉዳት ነበር የደረሰባዎት?  

አንዳንዶች ትንሽ ጥግ ድረስ እየወሰዱ ስለፃፉት ልንገርህ፡፡ ያደረጉት በሆነ ጠንካራ ነገር ፍንጢጣዬን ወግተውኛል ፡፡ በዚያ በኩል ሱሪዬም ተቀዷል፡፡ ሁለት ቦታ የመሰንጠቅ ጉዳት ደርሶብኛል፡፡ ዶክተሬ በዛገ ብረት ጉዳቱን እንዳደረሱብኝ ነግሮኛል፡፡ አስቸጋሪ ነው፤ እጅግ ጥንቃቄ የሚጠይቅ ቦታ ስለሆነ ተከታታይ ህክምና እየተከታተልኩ ነው፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- በጉዳትህ ወቅት አብረውህ የነበሩ ልታመሰግናቸው የምትፈልጋቸው ካሉ?

አቶ አበበ፡- በቅድሚያ ቤተሰቦቼን እንዲሁም የአንድነት ፓርቲንና አባላቱን ማመስገን እፈልጋለሁ፤ ከውጪ እስከ ሀገር ውስጥ በየደቂቃው የማስናኛ ስልክ እቀበል ነበር፡፡ እንደጉዳቴ ቢሆን ቆሜ አልሄድም ነበር፡፡ የጣፎ ልጆችንም ከማሳከም ጀምሮ እስካሁን አልተለዩኝም፡፡

ፍኖተ ነፃነት፡- እስኪ አሁን ደግሞ በመያህ ጋር የተያያ ጥያቄዎችን እናንሳ የመምህርነት ስራህን መቼ ጀመርክ?

አቶ አበበ፡- 24 ዓመታት ገጠር ነበርኩ፡፡ በ2000 ዓ.ም ነው ዝውውር አግኝጬ አዲሰ አበባ የገባሁት፡፡ ባለቤቴ እዚህ በመሆኗ ባልና ሚስት ማገናኘት በሚል ነው የተዘዋወርኩት፡፡ ሶስት ሊጆች አሉኝ፡፡
 
ፍኖተ ነፃነት፡- ሀያ ዘጠኝ አመት ያስተማረን ሰው ስለ ትምህርት ጥራት መጠየቅ አግባብ ይመስለኛል፤ ጥራቱ ወዴት  እያመራ ነው?

አቶ አበበ፡- በአፄ ኃይለስላሴ ዘመን ት/ቤት ገብቻለሁ፡፡ ወደ 6፡00 ሰዓት መንገድ ቤተሰቦቼ እያጓጓዙኝ ነው የተማርኩት፡፡ ተለምነንም ነበር የምንማረው፡፡ ወንድሞቼ ሲነግሩኝ ተማሪ ለመሳብ ስኳር፣ ዱቄት ወተት … ይሰጣቸው ነበር፡፡ ትምህርት መበላሸት የጀመረው በደርግ ዘመን ነው፡፡ ከማስፋፋት አንፃር ኢህአዴግ ደርግም ሚና ነበራቸው፡፡በደርግ ዘመን የትምህርት ጥራት መውደቅ የጀመረው “Direct Teaching” በሚል ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍል እየወሰደ እንዲያስተምሩ ሲያደርግ ነው፡፡ አስተማሪነት ስልጠና ያስፈልገዋል፡፡ ሳትሰለጥን ሀኪም እንደማትሆነው ሁሉ፡፡ ያ ትልቅ ጥፋት ነው፡፡ ማስተማር ሙያ ነው፡፡ ያ ግን ኢህአዴግ የሚመፃደቅበትን የማስፋፋት ስራ ለመስራት ሲባል የተሰራ ስህተት ነው፡፡

እኔ ሁለተኛ ደረጃ የተማርኩት በ “TTI” መምህራን ነው፡፡ ነገር ግን ታላቅ ችሎታ ነበራቸው፡፡ አሁን ካለው ዲግሪ ጋርም አይነፃጸሩም፡፡ በክረምት ድግሪ ለመያዝ ከ10 በላይ ክረምት ይማሩ ነበር፡፡ ለረዥም አመት ማስተማር ማስተርስና ፒ.ኤች.ዲ እንደመስራት በለው፡፡ ደርግ የማስተማሪያ መሰላሉንም እያበላሸው መጣ፡፡ በንጉሱ ጊዜ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች በሆነ ርዕስ ላይ ጥሩ ድርሰት የሚፅፉ ነበሩ፡፡ በደርግ ዘመን ለመምህራን የክረምት ትምህርት ዕድል እንኳ አልነበረም፡፡ አሁን የትምህርት ጥራት መዝቀጥ እንጂ እድሉ አለ፡፡ አንድ ዲፕሎም የነበረው የባዮሎጂ መምህሬ 10 ክረምት ከተማረ በኋላ አቋረጠ፡፡ ዛሬም ድግሪውን አልያዘም፡፡ ኢህአዴግ ግን በ4 ክረምት ዲግሪ ይሰጠሃል፡፡ ዕድል ቢሆንም ጥራቱን ገድሏል ነው የምልህ፡፡

በዚህ ላይ ሚዲያው ሁሉ እየጮኸ ነው፡፡ እኔም ፅፌአለሁ፡፡ ችግሩ ኢህአዴግ አይሰማህም፡፡ ፖለቲካውን ካልነካህበት ሀገር በአፍ ጢሟ ብትዘቀዘቅ ምኑም አይደለም፡፡ ትውልዱ ተዘቅዝቋል፡፡ 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብትመጣ ስማቸውን በእንግሊዘኛ የማይፅፉ ተማሪዎች አሉ፡፡

የሚገርምህ ኢህአዴግ ለፓለቲካ በቀል አስተምርበት ከነበረው የመሰናዶ ትምህርት ቤት ወደ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲወሰደኝ የበለጠ የትምህርት ስርአቱ እንዴት እንደዘቀጠ ለማስተዋል ችያለሁ፡፡  የ7ኛ ክፍል ተማሪን እንደ ቄስ ትምህርት ቤት የፊደል ገበታ ዘርግቼ ፊደል እያስቆጠርኩ ነው፤ አስበው፡፡ ያሳፍራሉ፡፡ ነገ ሚኒስትሪ ወስደው “High school” ሊገቡ ነው፡፡
በአለም አቀፍ መለኪያዎች መሰረት 1ኛ ክፍል ያሉ ልጆች ከ1- 50 የ2ኛ ክፍሎች ከ1-100 መፃፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ነገር ግን 60 ተማሪ ካለበት ክፍል አንድ ወይ ሁለት ተማሪ ቢያደርገው ነው፡፡ መንግስት ግን ይሄን አይቀበልም፡፡ ይህ የጠላት ወሬ ነው ይለሃል፡፡ ባለው እውነት ግን 1ኛ ደረጃ የመጀመሪያ ሳይክል ላይ ያሉ ልጆች መፃፍ አይችሉም ፡፡
 
ፍኖተ ነፃነት፡- ችግሩ ምንድነው?

አቶ አበበ፡- መምህሩ በትምህርት ፖሊሲ ቀረፃው ላይ ሚና የለውም ፤ የመምህሩን ገብረ መልስ መንግስት አይቀበልም፡፡ ካሪኩለም ላይ፣ ሲለበስ ላይ መምህሩ አይሳተፍም፤ ባለቤቱ እቤት ተቀምጠህ ፖለቲከኛ ነው የሚቀርፅልህ ፤ ስትነግራቸው ጠላት ነህ፡፡ ለቀህ መውጣት አለብህ ትባላለህ፡፡

በዚያ ላይ ትምህርቱን አድምተህ አትሰራም፡፡ ርዕሰ መምህሩ በምርጫ ጉዳይ ላይ እንዲሰራ የማይሸከመው ጥራዝ ይሰጠዋል፡፡ 40 በመቶ ያስተምራል 60 በመቶው ፖለቲካቸውን እንዲያግዝ ይፈልጋሉ፡፡ በትምህርት ቤት በዚያ ነው የሚገመገመውም፡፡

ዛሬ ትምህርት ቤት ውስጥ የፓርቲ አባላት የሆኑ መምህራን “ግንባር ቀደም” የሚል መለያ ይሰጣቸዋል፡፡ ሌላው ድንጋይ ቢፈልጥ አይመሰገንም፣ አያድግም፡፡ ሙያዊ ፉክክር ሳይሆን፣ በሰራኸው መጠን ሳይሆን፣ ባጎበደድክበት መጠን ነው ከፍ የምትለው፡፡ በርግጥ እኔ የአንድነት ፓርቲ አባልም አመራርም መሆን እስከ ቻልኩ እነሱም መብት አላቸው፡፡ ነገር ግን ፖለቲካ ጓዙን ጠቅልሎ ትምህርት ቤት መግባት የለበትም፡፡

እኔ ስመረቅ “ዲግሪውን ከነሙሉ ክብሩና ጥቅሙ ሰጥቼዋለሁ ብሎ” ነው የኒቨርሲቲው የሸኘን፡፡ ታዲያ ለምንድነው የፖለቲካ አቋሜ ይህንን መብቴን የሚያስነፍገኝ?

አዲስ አበባ ላይ መሰናዶ ትምህርት ቤት መግባት ያልቻሉት ኮተቤ ገብተው መምህራን ሆነው ይወጣሉ፡፡ ከሁለት አመት አገልግሎት በኋላ ሰመር ይገባና ዲግሪ ይይዛል፡፡

ሌላው አሳዛኝ ነገር የመምህሩ ደመወዝ ነው፡፡ ዳቦ የራበው ሰው እንደምን የትምህርት ጥራትን ያረጋግጣል? የተቀደደ ሱሪ፣ የተንሻፈፈ ጫማ አድርጎ በተማሪ ፊት የሚሸማቀቅ መምህር ከሀፍረት የበለጠ ምን ያስተምራል? አሁን ባለው ሁኔታ የደሞዝ ጉዳይ 400 ሺህ ለሚበልጥ መምህር ጫና ነው፡፡

Wednesday, November 13, 2013

በአዲስ አበባ ፍተሻው በአዲስ መልክ ተጀመረ

November 12/2013
ህዳር (ሦስት)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-አልሸባብ የተባለው አሸባሪ ቡድን እና በኤርትራ መንግስት እገዛ የሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድኖች በኢትዮጽያ ውስጥ የተለያዩ ስፍራዎች የሽብር ጥቃት ለመፈፀም እየተዘጋጁ መሆናቸውን የሚያሳይ አስተማማኝ መረጃ ያለው መሆኑን የብሄራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎትና የፌደራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ሃይል ጥቅምት 27 ቀን 2006 ዓ.ም ካስታወቁ በኃላ በአዲስአበባ በመንግስት በግል ተቋማት ከወትሮው የተለየ ፍተሻ በአዲስ መልክ ተጀምሯል፡፡
ግብረኃይሉ በዚሁ መግለጫው በየአካባቢው ሆቴሎች፣ ሕዝባዊ ተቋማት፣ የፍተሻ ኬላዎች ላይ የሚሰሩ የፍተሻ ስራተኞች ተግባራቸውን ከወትሮ በተለየ ጥንቃቄ እና አትኩሮት ማከናወን እንዳለባቸውም መግለጹን ተከትሎ በተለይ በሆቴሎችና በሕዝባዊ መዝናኛዎች ለየት ያሉ ፍተሻዎች እየተካሄዱ ነው፡፡
በካዛንቺስ አካባቢ የሚገኙ ራዲሰን ብሉ እና ጁፒተር ኢንተርናሸናል ሆቴሎች የመፈተሻ ዘመናዊ ማሽኖች ጭምር ገዝተው ለመግጠም የተገደዱ ሲሆን አነስተኛ አገልግሎት መስጫ ተቋማት የሰዎች መፈተሸ ኤሌክትሮኒክስ የደህንነት መፈተሻ መሳሪያዎችን በብዛት በመሸመት በስራ ላይ እያዋሉ ነው፡፡
ይህንን ተከትሎ ፖሊስ ጠርጥሬአቸዋለሁ ባላቸው እንደሳሪስ ባሉ አካባቢዎች ድንገተኛ የቤት ለቤት ፍተሻ ሰሞኑን ያካሄደ ሲሆን በአዲስአበባ ዋና ዋና መንገዶች ላይም ተሸከርካሪዎችን በማቆም ረጅምና አሰልቺ ፍተሻዎችን ሲያካሂድ ታይቶአል፡፡
የጋራ የፀረ ሽብር ግብረ ሃይሉ የተላለፈው ይኸው መግለጫ ባለፈው ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ቦሌ አካባቢ ለሽብር ተግባር ሲሰናዱ በራሳቸው ላይ ባደረሱት አደጋ ህይወታቸው ጠፋ በተባሉ ሁለት ሶማሊያዊያን አሸባሪዎች ጉዳይ ላይ ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱን ያስታውሳል፡፡
እነዚህ ሁለት ግለሰቦች በወቅቱ የኢትዮጵያና የናይጀሪያ ብሄራዊ ቡድኖች የሚያደርጉትን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር በሚከታተሉ የስፖርት አፍቃሪዎች ላይ አደጋ ለማድረስ ዓላማ እንደነበራቸው የሚያሳዩ መረጃዎች መገኘታቸውን መግለጫው በተጨማሪ ያስታውቅ እንጂ ፍንዳታው በእርግጥም በአሸባሪ ቡድኖች ስለመፈጸሙ ለሕዝብ እስካሁን በተጨባጭ የገለጸው ነገር የለም፡፡ በዚህ ምክንያት ብዙ ወገኖች በ1997 ዓ.ም  ገዥው ፓርቲ ራሱ ፈንጂ ቀባሪ፣ ራሱ አምካኝ የሆነበትንና የተጋለጠበትን ክስተት በማስታወስ ነገሩን በጥርጣሬ እየተመለከቱት ይገኛሉ፡፡
በተጨማሪም ሆቴሎቻቸውንና መኖሪያ ቤታቸውን የሚያከራዩ ባለንብረቶችና ባለ ይዞታዎች በተለይ የውጭ ሀገር ዜጎችንና የማያውቋቸውን ኢትዮጵውያንን አድራሻ በአግባቡ መዝግበው በመያዝ መረጃን ለሚመለከተው አካል የማሳወቅ የህግ ግዴታ እንዳለባቸው መግለጫው በጥብቅ አስጠንቅቋል፡፡
በተመሳሳይ መኪናዎቻቸውን የሚያከራዩ ግለሰቦች፣ድርጅቶችና የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባለታክሲዎች የደበኞቻቸውን ማንነት የሚገልጽ ሙሉ መረጃ የመያዝና የማሳወቅ እንዲሁም የሚጭኗቸውን ማናቸውንም ዕቃዎች የማወቅ ግዴታም ያለባቸው መሆኑን የፀረ ሽብር ግብረ ሀይሉ አስታውቋል፡፡ ህብረተሰቡ አጠራጣሪ ሁኔታዎች ሲያጋጥመው ሁኔታውን በአቅራቢያው ላሉ የፖሊስና የፀጥታ ሀይሎች እንዲያሳውቅም አሳስቧል፡፡

Tuesday, November 12, 2013

ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን

November 12/2013
በንቅናቄዓችን ፀሐፊ እና በግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራር አባላት ላይ የተቃጣው ረዥም ጊዜ የወሰደ የግድያ ሴራ መክሸፉ አስደስቶናል። ይህ ሴራ የወያኔ የስለላና የግድያ ኃላፊዎች በሆኑት ጌታቸው አሰፋ እና ጸጋየ በርሄ የቅርብ ክትትል የተመራ፤ የአሻንጉሊቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እውቅናና ይሁንታ የተሰጠው፤ ወያኔ ከፍ ያለ ተስፋ የጣለበት ሴራ ነበር።
“ወያኔ-ኦ-ሚሊኒየም” የተሰኘው ይህ በወያኔ የመጨረሻ ከፍተኛው አመራር የተመራው ሴራ ስለወያኔ ውስጣዊ አደረጃጀት ጠቃሚ መረጃዎችን ሰጥቶናል። ከዚህም በተጨማሪ የወያኔ ሹማምንት ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት፤ ከአመት በኋላ ስለሚደረገው ምርጫ ውጤት፤ ለሰላዮቻቸው ስለሚሰጡት ጉርሻ መጠን፤ እና ሌሎችም በርካታ ጉዳዮች ተስፋ ከጣሉበት ቅጥረኛ ነብሰ ገዳያቸው ጋር ካደረጉት የስልክ ንግግሮች ማድመጥ ይቻላል። ይህ ለበርካታ ጥናቶች በግብዓትነት ሊውል የሚችለውን በድምሩ ከስምንት ሰዓታት በላይ የሚፈጀው የስልክ ንግግር ቅጂ በሕዝባዊ ኃይሉ የመረጃ ክፍል አማካይነት ለሕዝብ በኢንተርኔት በነፃ ተለቋል። በአጋጣሚውም የወያኔ ገበና ተጋልጧል።

በአንፃሩ ደግሞ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተደራጀው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቢሆንም ምን ያህል ወያኔን እንቅልፍ እንደነሳ ተጨባጭ ማስረጃ ሆኗል። ይህ ለነፃነት ታጋዮች ከፍተኛ የስነልቦና ብርታት የሚሰጥ ነገር ሆኖ ተገኝቷል።

በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል የተቃጣበትን ጥቃት ከማክሸፍ በተጨማሪ የወያኔን ገበና ማጋለጥ በመቻሉ የመጀመሪያው ሁነኛ ድል ተቀዳጅቷል።

ግንቦት 7 : የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” አፕሬሽንን ላከሸፉ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል አመራርና አባላት ያለውን አድናቆት ይገልፃል። ለወደፊቱም ተመሳሳይ ጥቃቶች ሊደርሱ የሚችሉ መሆኑን በመገንዘብ የመከላከል ብሎም የማጥቃት ኃይሉን እንዲያጠናክር ይመክራል።
የንቅናቀዓችን እና የሕዝባዊ ኃይሉ አመራርና አባላት ለመስዋዕትነት የተዘጋጁ ናቸው። “ወያኔ ኦ ሚሊኒየም” ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ትግላችን ይገታ ነበር ማለት አይደለም። ትግላችን መስዋዕትነትን የሚጠይቅ መሆኑን እናውቃለን። ጓዶች ሲወድቁ ሌሎች ሺዎች አርማቸውን አንስተው ትግሉን ይቀጥላሉ።
ትግሉ የሚጠይቀንን መስዋትነት ከፍለን ወያኔን ከሥልጣን አስወግደን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት የሆነባት ኢትዮጵያ እንደምትኖረን እርግጠኞች ነኝ።
ትግሉ መሯል፤ እኛም ዝግጁዎች ነን።
ድል ለግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል!!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Assassinating popular leaders will only invigorate the people

November 12/2013

On Thursday November 7, 2013; the Valiant Ginbot 7 Popular Force intelligence unit foiled the assassination plot that targeted the secretary of Ginbot 7: Movement for Justice, Freedom and democracy, and commanders and high ranked officers of Ginbot 7 Popular Force. This futile attempt by the coward TPLF regime that took place in Eritrea territory is yet another sign and proof that this blood-stained regime cannot and does not survive without spilling the blood of innocent Ethiopians. Ginbot 7 and the Ethiopian people at large are outraged by the TPLF regime’s recent assassination attempt, and they strongly denounce this shameful act that does not serve any purpose.

In the last twenty two years, the TPLF leaders assaulted or killed anyone who dare did anything to slightly oppose them, they hated one group of innocent people for no apparent reason, and they even managed to turn one of the most peaceful country in the world into a land of hate politics. All in all, genocide, hate, random killing, mass killing and now targeted killing – the TPLF regime has no shortage of reasons for guilt. Ginbot 7, Movement for Justice, Freedom and Democracy praises the heroic acts of the Ginbot 7 Popular Force in foiling the assassination attempt on its leaders and commanders, and uses this opportunity to pass a clear message to the arrogant TPLF leaders that Ginbot 7 Popular Force is part of the popular struggle that will never and can never be undermined by killing its leaders. In its attempt to perpetuate its power, the TPLF regime has gone to another inglorious dimension of targeted assassination of political leaders. Ginbot 7 wants to remind the TPLF regime and its killing squad that the shame and the sour defeat they were forced to swallow on Thursday November 7 is just the tip of the iceberg.

Once again, Ginbot 7 denounces the recent cowardly act of the Ethiopian regime in its strongest sense, and wants to remind the Ethiopian people that this is a wakeup call that must be answered with due diligence. Torturing and killing popular leaders has always been a worthless coward act that invigorates the people and creates more courageous leaders. We Ethiopians should cheerfully acknowledge that in its futile attempt to harm us, our enemy has wounded itself, now it’s up to us to hit the nail on the coffin.

We shall overcome!

Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy
Public Relation

በሳውዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ላለው ጥቃት ተጠያቂው ወያኔ ብቻ ነው


          
ወያኔ በትረ ሥልጣን ከተቆጣጠረበት 1983 ዓም ጀምሮ በአገራችንና በወገኖቻችን ላይ ከፈጸማቸው በርካታ ወንጀሎች አንዱ በህጋዊ መንገድ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቻችንን ለባርነት ወደ አረብ አገራት በመላክ የአገራችንን መልካም ዝናና የህዝባችንን ክብር ያዋረደበት ተግባር ነው::

በወያኔ ንግድ ድርጅቶች ዋና ተዋናይነት ተመልምለው ለባርነት ሥራ የሚላኩትን ዜጎች በገፍ ስትቀበል የኖረቺው ሳውድ አረቢያ የሥራ ፍቃድ ያለቀባቸውን ከአገሯ ለማባረር ሰሞኑን በወሰደቺው የማዋከብ እርምጃ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቻችን እየተደበደቡና ጎዳና ላይ እየተጎተቱ እሥር ቤት ታጉረዋል፤ ገንዘባቸውን ተዘርፈዋል፤ ከፖሊስ የሚደርስባቸውን ድብደባና እንግልት ለመቋቋም የሞከሩት በግፍ ተገድለው አስከሬናቸው ጎዳና ላይ ተጥሎሏል:: በርካታ ወጣት እህቶቻችን ደግሞ በአምስትና ስድስት የአረብ ጎረምሳ ወሲብ ጥቃት እየተፈጸመባቸው ለአካልና መንፈስ ጉዳት ተዳርገዋል::

ይህ ሁሉ ሲሆን በአባይ ግድብ ግንባታ ሥም ገንዘብ ለመሰብሰብ ቦንድ ግዙ እያለ የሳውዲ ነዋሪ ሲጨቀጭቅ የኖረው በሳውዲ የወያኔ ኤምባሲም ሆነ አዲስ አበባ የሚገኙ ቅምጥል አለቆቹ ጥቃቱን ለማስቆም ድምጻቸውን ለማሰማት አለመፈለጋቸው ብቻ ሳይሆን ጥቃቱን ያደረሰውን የሳውዲ መንግሥት እርምጃ እውቅና የሚሰጥ መግለጫ በውጭ ጉዳይ ሚንስትር ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲህ መሰጠቱ እጅግ የሚያሳዝንና ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው::

ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በመላው አረብ አገር በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለው የባርነት ስቃይ በፋሺስት ጣሊያን ዘመን በወገኖቻችን ላይ ከተፈጸመው የከፋና በተለይ በሴት እህቶቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ግፍና መከራ እንደ አገርና እንደ ህዝብ የገባንበት ውድቀትና ውርደት ማሳያ ነው ብሎ ያምናል::

ስለዚህ ይህንን ውርደት ማስቆም የምንችለው ለዚህ ሁሉ መከራና ውርደት የዳረገንን የወያኔንሥርዓት ታግለን በማስወገድ በምትኩ ለአገሩና ለህዝቡ ፍቅር ያለው፤ በያንዳንዱ ዜጋ ላይ የሚደርሰው መከራና ስቃይ የሚቆረቁረው፤ አገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጥሮ ለባርነት ሥራ ወደ ውጪ የተላኩትን የሚሰበስብ መንግሥት ማቋቋም ስንችል መሆኑ ታውቆ ወያኔን ለማስወገድ የተጀመረውን ትግል በተለይ ወጣቱ የህብረተሰባችን ክፍል በነቂስ እንዲቀላቀል የተቀረውም ህዝባችን አቅም የፈቀደውን ሁሉ እንዲያደርግ ግንቦት 7 የትግል ጥሪውን ያቀርባል::

በመጨረሻም ምንም እንኳ በተለያዩ አረብ አገሮች በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ላለው መከራና ስቃይ ዋና ተጠያቂው ዜጎችን በህጋዊ መንገድ ለባርነት ከላከ ቦኋላ ጥቃት ሲፈጸምባቸው መከላከል ሳይፈልግ ዝም ብሎ እየተመለከተ ያለው የወያኔ አገዛዝ መሆኑ ባያጠያይቅም፣ የሳውዲ አረቢያም ሆነ ሌሎች አገሮች ተቆርቋሪ በለላቸው ዜጎቻችን ላይ የሚፈጽሙትን ወንጀል በአሰቸኳይ እንዲያቆሙና ተጠያቂዎቹንም ለህግ እንዲያቀርቡ ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄን አቅም የፈቀደውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ሁሉ ወያኔን ከማስወገድ ትግል ጋር አጣምሮ እንደሚገፋ ይገልጻል::

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
የግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄን የህዝብ ግንኙነት

Monday, November 11, 2013

በሳኡዲ አረቢያ የሚፈጸመው ግድያ እና የኢትዮጵያ መንግስት ሴራ

November 11/2013

 ባሳለፍነው ወር ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት በሳኡዲ አረቢያ የሚጓዙ ስደተኞችን አግደናል ሲል ለመገናኛ ብዙሃኖች መጠቆሙ የሚታውስ ሲሆን ያንን ተከትሎም ሆነ ከዚህ ቀደም ይደረጉ የነበሩ አንዳንድ ሁኔታዎችን ተመልክቶ አንዳንድ ምልከታዎችን ለመጠቆም ወደድን ።

የኢትዮጵያ መንግስት በሃገር ውስጥ የሚገኙትን ለኡምራ ጉዞ በሚል ፈቃድ በማግኘት እስከ አረብ አገራት ድረስ በመደለል ስራ እናስገባቿለን በማለት ሴት እህቶቻችንን እና ወንድሞቻችንን ጉዞአቸውን ወደዚያው እንዲያመሩ አቅጣጫቸውን እየቀየሩ ህብረተሰቦችን ወደ አልተፈለገ ጉዳት ውስጥ ሲጥሉአቸው እንደነበር በተለያዩ ጊዜያቶች ይነገሩ የነበሩ የረጂም ጊዜ ታሪኮች ናቸው ።ይባስ ብሎ እነዚህ ደላላዎች በሃገር ውስጥ ተቀምጠው ከአሰሪዎቻቸው ጋር በመነጋገር ገንዘብ ወደ ደላላዎቻቸው ብቻ እንዲላክ እንጂ ለሰራተኞቹ በእጃቸው እንዳይደርሳቸው በማድረግ የብዙሃኑን የድሃ ቤተሰብ ልጆች ደም ሲነጥቁ መክረማቸውም ሌላኛው ግልጽ ዘረፋ የተካኑት ግለሰቦች መሆናቸውን ማንም ሰው የሚረዳው ጉዳይ ነበር ።ሆኖም እንዲህ አይነቱ ክስተት ተፈጠረ ሲባል እኛ አናውቅም አሰሪዎቻቸውንም ሆነ በአረብ አገራት የሚገኙትን ደላላዎች አናውቅም በማለት የብዙዎችን ደም ደመ ከልብ ያደረጉት እነዚሁ የግል አስጎብኝ ድርጅት ኖሮአቸው ዜጎቻቸውን በህገወጥ እና በቀላሉ ልጥቅም ብለው በአረብ አገራት ላሉት ባለሃብቶች የሸጡአቸው ዜጎች መሆናቸውን ሳልገልጽ አላልፍም ።ለዚህም ሁሉ ጥፋት ተጠያቂ እነዚህም ወገኖች በህገ ወጥ ስራቸው ብቻ ሊጠየቁበት የሚገባው ዋነኛው ጉዳይ ሆኖ ሊታይ ይገባዋል ።
ከዚህም ባሻገር ለዘመናት እንዲህ ዜጎቻችንን ለርካሽ ባርነት የላኳቸውን ወገኖች ዘወር ብለው ያላዩአቸውን እንዚህን ደላላ ተብዬዎች ከባለፉት ሁለት አመታት ጀምሮ መንግስት እና እንዲሁም ጥቂት የመንግስት ደጋፊ የሆኑ ባለስልጣናት ደጋፊ የሆኑ ሰዎች ይህንን ስራ በህጋዊ መልኩ አድርገን እንሰራለን በማለት በወር ወደ 45.000 የሚጠጉ የቤት ሰራተኞችን እንልካለን በማለት ከባለሃብቱ ሼክ መሃመድ አላህሙዲ ጋር የሚሰራ አንድ ትልቅ የጉዞ አስጎብኝ ወኪል በመፍጠር ለሳኡዲ መንግስት ሴትም ሆነ ወንድ ሰራተኞችን ሊያቀርቡ እንደሚችሉ መፈራረማቸውን በይፋ መግለጻቸውን እና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህገ ወጥ የሚሰሩትን ድርጅቶች ቀስ በቀስ እያመነመኑ እንዲዘጉ ማድረጋቸው የሚታወቅ ሲሆን ..ለህዝባችን በተወሰነ መልኩ እፎይታን ቢሰጥም በእጅ አዙር እራሳቸው ስራውን ሊሰሩት ማሰባቸውን እና ሃሳቡን መቀልበሳቸው በሰፊው የተጋለጠባቸው ግን አሁን መሆኑን ሁሉም ሰው  ተረድቶታል ።መንግስት በህጋዊ መንገድ አቀርባቸዋለሁ ያላቸውን ሰራተኞች እራሱ ጉዳዩን ፈጽሞ እራሱ ልኮ ጠበቃ ነኝ ብሎ በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘው ቆንጽላ በጥቃታቸው ጊዜ ጉዳታቸውን እንዲሰማላቸው አደርጋለሁ ሲልም መናገሩ አይዘነጋም ።
ዛሬ ደግሞ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ  በቃል አቀባይነታቸው መሰረት
በሳዑዲ በመከራና ስቃይ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችንን አስመልክቶ የመንግስት ቃል አቀባይ  የተባሉት የቁጭ በሉ ሰው ዲና ሙፍቲ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ፦”እየተባረሩ ያሉት ህጋዊ ያልሆኑት ናቸው” ብለዋል ተናግረዋል ።ዲና  በሌላም በኩል  ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ ፖሊሶች ስለመገደላቸው የተረጋገጠ ማስረጃ እንደሌላቸው አስረግጠው ገልጸዋል  ሆኖም የሃገሪቱ መንግስት በመገናኛ ብዙሃኑ የተገደሉትን ዜጎች እያሳየ መዋሉን ሲ ኤን ሲ የተባለው የቻይና ቴሌቪዥን ሲያሳይ ቆይቶአል ። ሆኖም የ ዲና ሙፍቲ አነጋገር የሁሉንም ቀልብ ስቦአል ምክንያቱም የሃገሪቱ ተወካይ ሳይሆኑ የሳኡዲ ቃል አቀባይ መስለው መታየታቸው ነው ።
የዲና ሙፍቲ ጉዳይ ወደ ኋላ ተወት እናድርገው እና አቶ ቴዎድሮስ አድሃኖም በሰሞኑ በተጠመዱበት ቲዊተር ስለ ህዝቦቻቸው ሲናግሩ ከአረብ መንግስታቶች ጋር በመምከር ላይ እንዳሉ እና መፍትሄ ሊያመጡ እንደሚችሉ ገልጸዋል ።በትላንትናው እለትም በመንግስት ሃይሎች የሚመራው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንም እንደዚሁ ጅብ ከሄደ ጩኸቱን አስምቶአል ።
ከ16500 በላይ ኢትዮያውያኖች በመካ አቅራቢያ ፣በየመን ዳር ድንበር እና እንዲሁም በሳኡዲ አረቢያ ከተማ በሚገኙ እስርቤት ውስጥ ተጉዘው በእስር ስቃይ ላይ እየማቀቁ ይገኛል ።እንደ ሃገሪቱ ናሽናል ቴሌቪዥን ዘገባ ከሆነ እያንዳንዱ እስረኛ ከ500 እስከ 1000 የአሜሪካን ዶላር የሚደርስ ቅጣት ይጠብቀዋል ይህንን የማይፈጽም ከሆነ ደግሞ እስሩን ጨርሶ ሊፈታ እንደሚችል እና ዳግመኛ ወደዚያች ምድር እንዳይመጣ በሚያደርግ የአሻራ ፊርማ አስወጥተው ሊያባርሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል ። ታዲያ ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው ከኢትዮጵያ መንግስት በተሰጠን  ትእዛዝ ነው ብለው ተናግረዋል የሚሉ መረጃዎች ከወደ ሳኡዲ እየተሰማ ይገኛል ፣ሆኖም ግን ይህ ምን ያህል እውነታ እንደሆነ ማረጋገጫው ባይኖረኝም ይህንን የጻፈውን ብሎግ ግን ማቅረብ መቻሌን ውሸታም አያሰኘኝም ስለዚህ ሙሉውን እንዲህ ይነበባል
ከዚህ ቀጥሎ ከክሊክ ሃበሻ የተዘገበውን ዜና አንዲህ ተቀናብሮ የተቀመጠ ሲሆን እኔም በዚህ መልኩ  ጽሁፉን አስቀምጠው እና ከዚያም ሊንኩን አያይዤ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ ። “ቴዎድሮስ አድሃኖም ህገወጥ ኢትዮጵያውያን እንዲያዙ የተስማማበት ሰነድ አለን”የሳኡዲ ባለስልጣናት
 | 10 בNovember 2013 | 0 Comments
በሪያድ የዛረው ሰልፍየሚመጣውን አደጋ በመፍራትተበትኗል::
999410_10201428110199302_1866404023_n“ቴዎድሮስ አድሃኖም ህገወጥኢትዮጵያውያን እንዲያዙየተስማማበት ሰነድአለን”የሳኡዲ ባለስልጣናት
አምስተኛ ቀኑን የያዘው የሳኡዲጸረ ኢትዮጵያውያን ዘመቻእንደቀጠለ ሲሆን ሁኔታዎችንለመፍታት የተደረጉ ጥረቶችከዚህ
ቀደም የኢትዮጵያመንግስት እና የቆንስላውዲፕሎማቶች በሰርኡት ስህተትመስመር ሊይዝ አልፈለገም::
እንደ ሳኡዲ ባለስልጣናትአነጋገው የውጪ ጉዳይሚኒስትሩ ከዚህ ቀደም ባደረጉት ጉብኝት ሃገራቸው ህገወጥ ኢትዮጵያውያንን እንዲያስወጣ እና በምትኩ40,000 ህጋዊ ስደተኞችን እንደሚልኩ የፈረሙበትን ማስረጃ ይዘዋል::
በሪያድ መንፉሃ ወደ ሃገራችን ስደዱን በሚል መንፉሃ ባንክ አልራጅህ አካባቢ በርካታ ኢትዮጵያውያን መንግስትየወሰደውን እርምጃ ተቃውመው ሰልፍ መውጣታቸው ተሰማ። እንደ አረብ ኒውስ ዘገባ መሰረት በሰልፈኞችበተወረወሩ ድንጋዮች አንድ የሳውዲ ዜጋ መሞቱንም ዘግቧል።
እነዚሁ በነዋሪዎች ድብደባና በደል የደረሰባቸው ኢትዮጲያውያን ወደ ሪያድ ኢምባሲና ኮሚኒቱ መስሪያ ቤትበእግራቸው ያመሩ ሲሆን መንፉሃ አካባቢ የቀሩት ከፖሊስ ጋር ባደረጉት ግጭት አንድ የፖሊስ መኪናእንደተሰበረ የአይን እማኞች ገልጸውልኛል።http://www.clickhabesh.com/?p=103630
ታዲያ እንዲህ ከሆነማ ሴራውን የጠነሰሱት የራሳችን ወገኖች ከሆኑ ለዚህም ተጠያቂው እራሳቸው ስለሆኑ ፣በወጥመድ ውስጥ እራሳቸውን አሾልከው ላለማስገባት ባደረጉት ጥረት ሸፋፍነው ማለፍን ስለፈለጉ የህዝባቸውን ሰቆቃ እያዩ ዝም ማለትን መርጠዋል ፡፤ይህንንም ሰቆቃ እና ግፍ ግድያ እንዲሁም የሴቶችንም ሆነ የወንዶችን አስገድዶ መደፈር እንዲመጣ ያደረጉት እንዚሁ ጨካኝ የሆኑ ገዢ መደቦቻችን ናቸው ማለት ነው። በነገራችን ላይ በመካ መዲና አካባቢ የተወሰዱት እስረኞች በሙሉ ፣የታሰሩት ወገኖች በግብረ ሰዶማውያን በታሰሩበት እስርቤት እንደሆነ ለመጠቆም እወዳለሁ ።
ይህ ቦታ ከፍተኛ ሙቀት ያለው አካባቢ ከመሆኑ የተነሳ የሰው ልጆችን ለመቅጣት ሆን ተብሎ የተዘጋጀ እና ማኛውም ሰው በተፋፈነ ክፍል ውስጥ አይደለም ለቀናት ለሰአታት መቀመጥ የማይችልበት እስርቤት ሲሆን ከዚህም ባሻገር የሚጠጣው ዉሃ ከፍተና ጨዋማ የሆነ ከመሆኑም በላይ ስውነትን ለመላላጥ እና ለተለያዩ ጉዳቶች ሊያደርስ የሚችል መሆኑን ያገኘኋቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ ።ይኅንን ስቃይ እና መከራ ለምን ዜጎቻቸው እንዲጋፈጡት ፈለጉ ፣መንግስት እንዲህ አይነቱን የክፋት ወንጀል ለምን በህዝቦቹ ላይ መፈጸም አስፈለገው ፣ለምንስ በስደት ያሉት ወገኖች ላይ አነጣጠረ የሚለው ምላሽ ።
ዋነኛው ምክንያት በህገወጥ ገቡ የተባሉት ወገኖች በሳኡዲ አረቢያ የሚገኘውን ክፍት የስራ ቦታ ስለሚሸፍኑት መንግስት በህጋዊ መንገድ አቅርባቸዋለሁ ያላቸው ሌሎች ዜጎቹን ስራ አጥተው እንዳይሰቃዩበት ስጋት ስለያዘው እና ፣አዲስ የሚጀምረው የጉዞ ሂደት እንዳይደናቀፍበት ቅድመ ጥንቃቄ ለመውሰድ ያስችለው ዘንድ ህጋዊ አልሆኑም ያላቸውን ህዝቦቹን በግዳጅ ከሳኡዲ መንግስት ጋር በመተባበር እንዲያስወጡ መምከሩ ግድ ሆኖ ስለታየው ያንን ሃላፊነት እራሱ ላይ መሸከምን ችሎአል ።ለዚህ ሲባል የሳኡዲ መንግስት በንጹሃን ህዝቦች ላይ ጥቃትን ፈጽሞአል መንግስትም ይህንን አላየሁም ሲል ድፍን አድርጎ የገለጸ ሲሆን በትላንትናው እለት በቴሌቪዝን የአየር ሰአት ላይ ለማረጋገጥ እንጥራለን ሲል ቃሉን ሲያጥፍ ተሰምቶአል ።
እንደ ማጠቃለያ ...መፍትሄው በሃገር ውስጥም ሆነ ተለያዩ አገራት የምንገኝ ዜጎች የህዝቦቻችንን መብት ለማስከበር በምናደርገው ጥረት ማናችንም በአለን ሃይል ተጠናክረን በመምጣት የህዝቦቻችንን መብት ማስከበሩን ግፊት በማድረግ በአረቡ አለም ላይ ጫና እንዲደረግ መጠየቅ እና መምከር ያስፈልገናል ከዚያም ባሻገር በሳኡዲ አረቢያ ኢምባሲ ቅርንጫፍ ቢሮዎችም ሆነ ቆንጽል ስህፈት ቤቶች በመገኘት ድምጻችንን እናሰማለን ከዚያም ቀጥሎ የዚህን አድሃሪ የሆነ መንግስት ሴራ ማጋለጡም ቢሆን ለጉዳት የሚዳርገን አይመስለኝም እና ሁላችንም ለህዝቦቻችን ቅድሚያ በመስጠት የንጹሃኖችን ህይወት እናትርፍ እያልኩኝ እለያችኋለሁ ።ስለያችሁ በአሜሪካ የሚገኙትን ሴናተሮች እና አገረ ገዢዎችን ኢሜል አድራሻ አያይዤ ሳቅርብላችሁ ሁላችሁም ጩኸታችሁን በኢሜሎቻቸው ላይ ያድርሱአቸው የሚለው የመጨረሻው የልመና ቃሌ ነው ሰላም ያገናኘን ።ዘላለም ገብሬ ከማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል ።
John_McCain@McCain.senate.gov,senator@akaka.senate.gov,senator@biden.senate.govsenator_bingaman@bingaman.senate.gov,senator@breaux.senate.govsenator_byrd@byrd.senate.gov,senator_carnahan@carnahan.senate.govsenator@clinton.senate.gov,senator@conrad.senate.govsenator@dodd.senate.govsenator@dorgan.senate.gov,dick@durbin.senate.govrussell_feingold@feingold.senate.gov,senator@feinstein.senate.govbob_graham@graham.senate.gov,tom_harkin@harkin.senate.govvermont@jeffords.senate.govtim@johnson.senate.gov,senator@kennedy.senate.govjohn_kerry@kerry.senate.gov,senator_kohl@kohl.senate.govsenator_leahy@leahy.senate.gov,senator@levin.senate.govblanche_lincoln@lincoln.senate.gov,senator@mikulski.senate.govsenator_murray@murray.senate.gov,senator@billnelson.senate.gov, jack@reed.senate.govsenator@rockefeller.senate.gov,senator@schumer.senate.govsenator@stabenow.senate.gov,senator_torricelli@torricelli.senate.gov

Sunday, November 10, 2013

Ethiopian woman raped, men killed in Saudi Arabia ሚስት እህቶቻችን አይደፈሩ ነው

የማለዳ ወግ …ከጎደፈው ስም ላይ ሌላ ጉድፍ ! – ነቢዩ ሲራክ

በሪያድ መንፉሃ በተከሰተው ሁከት ግራም ነፈሰ ቀኝ ተጎጅዎች እኛ ነን ! እንኳንስ ሰው ተደብድቦ ፣ ሞቶባቸው ፣ እንኳንስ መኪና ተሰብሮባቸው እንዲያውም እንዲው ናቸው ።

ከማለዳ እስከ ሌሊት የዘለቀውን ሁከት መቆጣጠር ይቻል ዘንድ ገና ሲጀመር አቅጣጫውን አይተው የመንግስት ተወካዮችን የመከሩ በርካታ ነበሩ። የሰማ አካል ግን የለም !

ስልክ ተደውሎ የማይነሳበት ፣ አልፎ አልፎ መስመሩ ሲነሳ ሃላፊዎችን ማግኘት በማይቻልበት ዲፕሎማቲክ መስሪያ ቤት ድክመት ገና ከጅምሩ መላ ሊገኝበት የሚችለው ጉዳይ ወዳልተፈለገ
አቅጣጫ አምርቶ ለዚህ አሳፋሪ አሳዛኝ ቀን በቅተናል …

የቀኑን ሁከት ተከትሎ ትናንት ሌሊት በጸጥታ ሃይሎችና ” ሸባብ ” ተብሎ በሚጠሩት የአረቦች ወጣቶች ኢትዮጵያውያንን በማያዳግም እና ሊሰሙት ሊያዩት በሚሰቀጥጥ ሁኔታ ንብረታቸውን
ዘርፈው ፣ ሴቶች ደፍረው፣ ደብድበው ከመቁሰልና እስከ ሞት ያደረሰ ግፍ ፈጽመውባቸዋል። ሳውዲዎችም ቢሆን በገዛ ሃገራቸው ተንቀው ንብረታቸው ወድሟል ፣ ተደብድበዋል ተገድለዋል ። ( አንድ መሞቱን ሰምቻለሁ) በሁሉም ወገን ትልቅ ጥፋት ተሰርቶ እዚህ ላይ ደርሰናል! በሁሉም ወገን ችግሩን ለመፍታት የተኬደው መንገድ ነባራዊ ሁኔታዎችን ከግምት ያላስገባ ነበረና ጭፍኑ አካሔድ ለዚህ አስከፊ ቀን አድርሶናል! ያም ሆነ ይህ ጥፋቱ እና ጉዳቱ ለእኛ ይከብዳል! ድሮም ከማያምረው ከጎደፈው ስማችን ላይ ሌላ ጉድፍ ጨምረንበት ለዚህ በቅተናል !

የትናንቱ ምሽት ለእኔ ፍጹም አስቀያሚ ነበር ፣ ኢትዮጵያውያን የመንፉሃ ህገ ወጥ ነዋሪዎች ግፍና ዱላው በዝቶባቸው ትናንት ማለዳ ሳውዲ ይሰራልነተብሎ የማይገመር ስራ ሰሩ! ለአመጽ ሻንጣና ቤተሰብ ይዘው በመውጣት “ወደ ሃገራችን በሰላም ስደዱን ፣ አትዝረፉን ሴቶቻችን አትለያዩብን ፣ አትድፈሩብን! ” ብለው አደባባዩን በዋይታ አቀለጡት! እንኳንስ የውጭ ዜጋ ሳውዲው በአመጽ አደባባይ መውጣት በማይታሰብበት ሃገር የኢትዮጵያውያኑ እርምጃ ቢያስገርምና ቢያስደነግጥም ” በሌሊት ቤት እየተሰበረ ከምንዋረድ የመጣው ይምጣ!” በሚል ስሜት ለአመጹ መነሳሳታቸው እውነት ነው ።

የመንፉሃው የትናንት ማለዳው አመጽ በአብዛኛው ብሶትን በመግለጽና ውሰዱን በማለት ያተኮረ ሲሆን የአካባቢው እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ ከመግታት አልፎ ወደ መኪና ማውደም እንቅስቃሴ ያመራ አልነበርም። ከቀትር በኋላ ግን ከሶስት በላይ የፖሊስ መኪና ላይ በድንጋይ ጥቃት ተፈጸመ። ብዙ ሳይቆይ አካባቢው በልዩ ሃይል ተከበበ። መንገድ ዳር የነበረው ሰው ተበተነ ። እንዲህ ሆኖ ቢያልፍ መልካም ነበር። አልሆነም! በፖሊስና በጸጥታ ሃይሎች ከበባ ቀጣይ እርምጃ ፍርሃት በነዋሪው መካከል ስጋትን ጫረ ! ኢትዮጵያውያኑ ወጣቱቶች ተመልሰው በመንፉሃ አውራ መንገድ አደባባዮች ላይ ወጡ… ሁኔታው እየከረረ ሲሄድ የሳውዲ እና የኢትዮጵያ መንግስት ሃላፊዎች ቀደም ባሉ ቀናት መስራት በነበረባቸው ዜጎችን በሰላም የመሸኘት ድርድር ላይ ተቀመጡ … ከፍተኛ የጸጥታ ሃላፊዎችን ጋር ውይይቱ በቀጠለበት ምሽት ግን መንፉሃ በከፋ ቀውስ ውስጥ ወድቃለች ! ሌላ ሁከት … ሌላ አደጋ … ሌላ አደጋ …ሌላ መከራ ተከተለ !


ምሽት ላይ የምህረት አዋጁን ተከትሎ ትምህርት ቤታቸው የተዘጋባቸውን ልጆቸን ለማናፈስ ጭምር ከቤት ስወጣ ከሰአታት በፊት በትምህርት ቤቱ ጉዳይ ካንድ ብርቱ ወዳጀ ጋር ለመመካከር ጭምር ነበር ። በሪያድ የመንፉሃ ሁከት ሲያውክን በጅዳ የኮሚኒቲ የተበለሻሸ አሰራርና በቆንስል ሃላፊዎች ክትትል ጉድለት 3000 ሶስት ሽህ ታዳጊ ትምህርት ለጊዜውም ቢሆን ተሰናክሏል። ወደ 70 ሰባ የሚጠጉ መምህራንና ሰራተኞች ስራቸውን አቁመዋል። እንደ ወላጅ በቻ ሳይሆን እንደ ዜጋ መምከር ግድ ነበርና ተገናኘን… ከወዳጀ ጋር በአንድ ሻሂ ቤት ተቀምጠን ስናወራ በርከት ያሉ ባልንጀሮቻችን ከዚህም ከዚያ መጥተው ክብ ሰርተን ተቀምጠን መጨዋዎት ጀመርን ። በትምህርት ቤቱ ዙሪያ አውርተን መፍትሄው ያው ተጎልቶ ትምህርት ቤቱ እስኪዘጋ የጠበቀው ቆንስል መስሪያ ቤቱን ሃላፊዎች ድክመት ከየአቅጣጫው እያነሳን ቦጫጨቅናቸው።

ወሬው ደርቶ እየተቀባበልን ስንከካው ስልኬ ደጋግሞ ይጮሃል፣ እኔም ደጋግሜ ተነስቸ በመውጣት አውርቸ ስመጣና ከፊስ ቡክ ወዳጆቸ ጋር በወሬው መካከል መልዕክት ስለዋወጥ የተመለከተኝ አንዱ ጠርጣራ ወዳጀ “ለመሆኑ ስለ ሪያድ ባህር ሃይሎች ምን አዲስ ነገር አለ እባክህ? ” በሚለው ጥያቄ ወደ ሪያድ የመንፉሃ ጉዳይ ይዞን ሄደ ። ጨዋታው መድራት ያዘ ከመንፉሃ “ባህር ሃይሎች” እስከ ለፍቶ ግሮ አዳሪው ሰላማዊና ህጋዊ ነዋሪ ሁሉንም እያነሳን ማውራት መወያየት ጀመርን። በየመን ባህር በህገ ወጥ አዘዋዋሪዎች ሪያድ ደርሰው በህንጻ ግንባታ የተሰማሩት “ባህር ሃይል ” በሚል ቅጽል ስም ይታወቃሉ ። “ባህር ኋይሎች” በመንፉሃ ህገ ወጥ እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ በተለይም ጩቤ ይዘው እርስ በርሳቸው ሳይቀር ሲጋደሉ መክረማቸው አንስተን ተወያየን። በመጨረሻም “የሳውዲ መንግስት የምህረት አዋጁ እንዳለቀ በመንፉሃ የወሰደው ከባህር ሃይሎችን የማስወገዱ ዘመቻ ትክክል ነው !” በሚለው ሁላችን ተስማማን ፣ በመካከል ላይ ከአንድ አሜሪካን ሃገር ካለ ወዳጀ ጋር በሳውዲ ጉዳይ ለመነጋገር ቀጠሮ ነበረንና ስለኬ ተንጫረረች … ስልኬን አንስቸ ውይይቱን አደርጌ ስመለስ ከሻሂ ቤቱ መግቢያ የጠበቀኝ ወዳጀ ከመንፉሃ የመጣ ሰው ላገናኝህ ብሎ አንድ ልጅ እግር ወንድም አገናኘኝ። ለ15 ደቂቃ ያህል የሆነውን እና በአይኑ ያየውን ሁሉ አጫወተኝ ። የቤት ሰበራውን ድብደባ፣ ዘረፋውን እና ግድያውን ጨምሮ ሴት እህቶች መደፈራቸውን አጥብቄ ጠየቅኩት ሞተ ላለው ሃገር ቤተሰቦችን ጠቅሶ ፣ ተደፈረች ላለት ቤተሰቦቿን ላገናኝህ ብሎ አስረግጦ ነገረኝ እና ስልኩን ተቀብየው ተለያየን ..

ተመልሸ ክቧን ጠረጴዛ ስቀላቀል ከሪያድ የመጣው እማኙን የሰጠኝን ቃል በአጭሩ አስረድቻች ውይይታችን ቀጠልን ። …የሳውዲ መንግስት የምህረት አዋጁ ሲያልቅ ያወጣው “ቤት ለቤት ፍተሻ አይደረግም! ” የሚለው መመሪያ ተጥሶ የኢትዮጵያውያን ቤት ብቻ እየተሰበረ ንብረት መዘረፉና በዋናነት ሴት እህቶች የመደፈራቸው ጉዳይ በዚህችው ጠረጴዛም ተነሳ … በዚያ የተስማማነው በዚህ ግን በሃሳብ ተለያየን ፣ የትናንቱ የመንፉሃ አመጽ በሳውዲ ለሚንገኝ ነዋሪዎች ትልቅ ጠንቅ እንደሚፈጥር ግን ሁላችንም በአንድ ድምጽ ተስማማን ! “ቀይ መኪና ሰው ገጨ” ከተባለ ቀይ መኪናን ሁሉ የሚያሳድዱት ሳውዲዎች “ሃበሻ አጠፋ ” ተብሎ ሲነገራቸው በገዛ ምድራችን አመጹብን ብለው በቀጣይ ቀናት የሚሆነውን አስቡት … ይህንና ያንን ስጋት ተነጋግረን ተለያየን!
ውጭ በቆየሁበት የሶስት ሰአት ልዩነት ሰላማዊዋ የአለም ቁንጮ ነዳጅ አምራች ሃገር ዋና ከተማ በአንድ የከተማዋ አካል ታይቶ የማይታወቅ መልኩ ተቀውጣለች … በእኛና በእነሱ በተፈጠረ ሸምጋይ የጠፋለት ሁከት መንፉሃ ጸጥ ረጭ ብላ ሰማዩ መከራ አዝሎ ፣ ሃገሬውና ኢትዮጵያዊው ተፈራርቶ ማምሸቱን ወዳጆች በተከታታይ ካደረሱኝ መረጃዎች ተረዳሁ! ሁከቱ ከማለዳ እስከ ምሽት ደምቆ ታይቷልና የነዋሪውን ትኩረት በአያሌው ስቦ መስተዋሉንም ሳውዲ ባልንጀሮቸ “ምን አደረግናችሁ! ” በሚል ቀልድ በጀመሩት ጭውውት የሁኔታውን አሳሳቢነት ገለጹልኝ … እንዲያ እያለ ምሽቱ ምሽት ተብሎ እያመመኝ ተገፋ !
እኩለ ሌሊት ላይ ደግሞ አሳዛኝና አስገራሚውን ትዕይንት ደም እያፋሰሰ ሲቀጥል ሰማሁ ፣ ተጨባጭ መረጃዎችም ደረሱኝ ።
 
አሁንም ገልጋይ ሸምጋይ አልነበረም… በሳውዲ እምብት በሪያድ መንፉሃ ድሮ በህገ ወጥ ስራ እንጠራ ነበር ። ያ ጋብ ሲል ያለ ህጋዊ የሃገራት ሰምምነት እድሜያቸውን እየቆለሉ ወደ ሳውዲ የሚላኩ ታዳጊ እህቶች ተበድለው እያለ በዳይ እየተባሉ የጥቂቶች እርምጃ ብዙሃኑን በከለው ። “እዕምሮ ህሙማን ኢትዮጵያውያን የኮንትራት የቤት ሰራተኞች የአሰሪዎቻቸውን ህጻናት እስከ መግደል ደረሱ! ” በሚል የከፋው ስማችን ዳግም ከፍቶ እንገለል ዘንድ መንፉሃ ላይ ሌላ ጥቁር ታሪክ አስመዘገብን ! ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ ዙሪያ ገቡ በተኩስ ፣ በሰው ጩኽት ፣ በፖሊስ እና የአንቡላንስ መኪናዎች ኡኡታ ሲናጥ በአካባቢው የኢትዮጵያዊ የተባለ ተፈልጎ እየታደነ ነበር …ውክበት ፣ ድብደባ እና ግድያው ጨለማውን ሽፋን ያደረገ ስለነበር ትናነት ሌሊት የሆነውን በትክክል መናገር የሚችል ከቶ ያለ አይመስለኝም !


ከእኩለ ሌሊት በኋላ ሁከቱ ባልበረደበት ሁኔታ የመሳሪያ ጩኸት በሚስተጋጋባት በሪያድ በመንፉሃ ነገሮች በፍጥነት ይቀያየሩ ይዘዋል! በደረሱኝ እና በሚለቀቁ ተንቀሳቃጨሽ ምስሎች ዋይታ ገኖ ይሰማል! ተከበው የሚገኙ ህጋዊ መኖሪያ የሌላቸውን እና ህጋዊ መኖሪያ ያላቸውን ነዋሪዎች አነጋገርኩ ! አንዱ ወዳጀ አረብ መስጊድ ደርሶ ሲመለስ አንድ ሃበሻ በነጭ ለባሽ ተተኩሶ ከተመታ በኋላ በፍጥነት መነሳቱን የአይን ምስክር እንዳረጋገጠለት አጫወተኝ። ሌላው ወዳጀ ከሁለት በላይ መገደላቸውን መስማቱን እና በአይኑ ያየውን በጋዜጣ የተሸፈነ የወገን ሬሳ ምስል ላከልኝ!

በማከታተል የነዋሪውን አስተያየት ማነፍነፍ ያዝኩ ! ከጸጥታ አስከባሪዎች ጋር የተፋጠጡትን በስልክ አግኝች ለምን የምህረት አዋጁ ሳያልቅ እንዳልወጡ እና የአሁኑ አመጽ ምክንያት ምን የሚል ነው በሚል ጠየቅኩ ” ሳውዲዎች ሁሌ ህግ ያወጣሉ፣ ግን አይፈጽሙትም ። ይህ አዘናግቶኛል! ምንም አይፈጠሩም እርምጃ አይወስዱም ብለን እንጅ ከዚህ መከራስ መውጣት ይሻለን ነበር! ሃገራችን አንሂድ አላልንም ፣ ቤት እየሰበሩ ወንዶችን ይወስዳሉ። የእኛን መያዝ የተመለከቱ የሳውዲ ወጣቶች (ሸባቦች) ሚስት እህቶቻችን ይደፍራሉ ፣ ንብረታችን ይዘርፋሉ! ይህ ለሶስት ቀናት ሲቀጥል የደረሰልን የለም ! ኢንባሲ ደወልን ምንም ማድረግ አንችልም ይሉናል ፣ አንተም ድንጻችን ታሰማናለህ ብለን ብንደውልልህ ፈራህ መሰል አታነሳልንም! የት እንድረስ ? ምን እናድርግ? ንብረታችን እየተዘረፍን ሴቶቻችን እየተደፈሩ ዝም ብለን ማየት ነበረብን? ይህን በመቃወም ሻንጣና ቤተሰቦቻቸር ይዘን ወደ ሃገራችን ስደዱን ነው ያልናቸው ” የሚል እየተቆጣና ድምጹን ከፍ እያደረገ መልስ የሰጠኝን አንድ ወንድም መጨረሻችሁ ምን ሊሆን ይችላል ? አልኩት “… ወደ ሃገራችን ከነሚስት እህቶቻችን ይውሰዱን ነው የምንለው! ያለበለዚያ መንፉሃን እና ሚስት እህቶቻችን አንለቅም! ገድለው ያስለቅቁን ” ሲል ክችም ያለ መልሱን ሰጥቶ ስልኩን ጀሮየ ላይ ዘጋው…

“ከኑ ጋር የተገኘህ ሰሊጥ ፣ አብረህ ተወቀጥ !” እንዲሉ ህጋዊ የመኖሪያ ፍቃድ ያላቸውን ኢትዮጵያውያንም የሁከቱ ቀዳሚ ተጠቂዎች ሆነዋል ። አንዳንዶችን አነጋግሬ ነበር ። ነገሩ እየከረረ ሌላ ጦስ እንዳያመጣ ስጋታቸውን በመግለጽ በጭንቀት እያለቀሱ ያሉበትን የከፋ ሁኔታ ገልጸውልኛል። ስለ ችግሩ አነሳስ፣ሴቶች ይደፈራሉ ስለሚባለው እና ስለ መፍትሔው ጠይቄያቸው የመለሱልኝ እህት ” የእኛ ወጣቶች በጩቤ ይዋጋሉ በሚልና በህገ ወጥነት ስለሚታወቁ ስማቸው ከፍቶ እንጅ አሁን የተሰራው ስራ ትክክል አይደለም ። ቤት እየተሰበረ ዝርፊያ አለ ። ሴት ትደፈራለች ። እነሱ እውንት አላቸው ! ሚስት እህቶቻችን አይደፈሩ ነው ። አላህ ምስክሬ ነው ።እኔ ሁለት የተደፈሩ እህቶች አውቃለሁ። ኢትዮጵያ መንግስት ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ ልዩ ልዑካንን በአስቸኳይ በመላክ መፍትሔ ካልተገኘ እዚህ ያሉት የኢንባሲ ሰወችን ተዋቸው! የሚያሳስበኝ የእንግዲሁ ኑሯችን ኑሮ ነው ! አንድ ነገር ካልተደረገ ኑሮው ኑሮ አይባልም”ብለውኛል።

የፊስ ቡክ ወዳጆቸም ጠንክረው መረጃውን ያዥጎደጉዱት ይዘዋል ። አንዳቸውንም ለጥፊ በጭንቀት ያለውን ላስበርገግ አልፈለግኩምና መረጃውን ብቻ በስሱ በጽሁፍ መልክ ማስተላለፉን መረጥኩ … አንድ የፊስ ቡክ ወዳጀ የኢትዮጵያዊ ደም የረከሰበትን ጉድ አየሁ ብለው በላኩልኝ መልዕክት ” ሰላም አመሸህ ነብዪ? የሚፈሰውን ደም እያየህ ነው?ኧረ ምንድ ነው መጨረሻችን ?” ሲሉ አጠይቀዋል ! ጥያቄው እኔ መመለስ የማልችለው ግን የብዙሃኑን የሳውዲ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ነዋሪ ነው … የተፈራው ደረሰ …እኔም መጨረሻው አልገባኝምና መጨረሻችን በማጠየቅ የማለዳ ወግ እያልኩ መብተክተኬን እዚህ ላይ ቆም አደረግኩት …

ከወያኔ ተሿሚ ጄኔራሎች አንዱ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ብር የዘረፈ ሙሰኛ መሆኑ ታወቀ

November 10/2013

ሱዳን ዉስጥ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ሆኖ በማገልገል ላይ የሚገኘዉና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሚመራዉ እንዲሁም በቅርቡ ወያኔ የሌተና ጄኔራልነት ሹመት የሰጠዉ ሌተናንት ጄኔራል ዮሀንስ ገብረመስቀል ተስፋማርያም አዲስ አበባ ዉስጥ በህገወጥ መንገድ የገነባቸዉ የንግድ ህንጻዎች በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዋጋ እንደሚያወጡ ለጄኔራሉ ቅርበት ያላቸዉ ሰዎች ተናገሩ። የጦር ኃይሎች ኤታማጆር ሹሙን ጄኔራል ሳሞራ የኑስን ይተካል ተብሎ የሚነገርነለት ጄኔራል ዮሀንስ ገብረመስቀል ካለፈው አመት መጋቢት ወር ጀምሮ ወይም አዲሱን በተመድ ሰላም ጥበቃ በኩል የተሰጠዉን ሀላፊነት ከተቀበለ በኋላ በወር ከ10ሺ ዶላር በላይ እንደሚከፈለዉ ቢታወቅም አዲስ አበባ ዉስጥ የገነባቸዉን ህንጻዎችን መስራት የጀመረዉ ከአዲሱ ሸመት በፊት በመሆኑ ይህን ያክል ገንዘብ ከዬት አመጣ የሚሉ ጥያቄዎች ከየቦታዉ በመወርወር ላይ መሆኑ ታዉቋል።
ሱዳን አብየ ዉስጥ የሚገኘውን የተባበሩት መንግስታት ሰላም አስከባረ ጦር የሚመራዉና በድክመቱና በምግባረ ብሉሽነቱ ዘወትር የሚወቀሰዉ ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል በቦሌ ክፍለ ከተማ ካልዲስ ኮፊ እየተባለ ከሚጠራው ድርጅት ጀርባ የገነባዉ ግዙፍ ህንጻ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን፣ በዋጋ ደረጃ ከ90 እስከ መቶ ሚሊዮን ብር ያወጣል ተብሎ ይገመታል። ግለሰቡ በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎችን ከመኖሪያ ቤታቸው በተጨማሪ ድርጅቶች አሉዋቸው። ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል እንደማንኛዉም የሰራዊቱ አባል በደሞዝ የሚተዳደር ግለሰብ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ከ17 አመት የጫካ ዉስጥ ኑሮ በኋላ ባዶ እጃቸዉን አዲስ አበባ ከገቡት የወያኔ አባላት ዉስጥ አንዱ ነዉ። ይህ መሆኑ እየታወቀ ጄኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል 90 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ህንጻ ማሰራት መቻሉ የሚያሳየን ህወሀትና ኢህአዴግ ዉስጥ የተሰገሰጉ ሙሰኞች ኢትዮጵያን ምን ያክል ግጠዉ እንደበሏት ነዉ እንጂ አንድ በደሞዝ የሚተዳደር ጄኔራል ከባንክ ተበድሬ ቤት ልስራ ቢል እንኳን አንድ መኖሪያ ቤት ከሚያሰራ ገንዘብ ዉጭ ባንክም ቢሆን 90 ሚሊዮን ብር ብድር አይሰጠዉም።

ወያኔ ዉስጥ “እርቅ አስፈላጊ ነው” ነዉ የሚሉ ድምጾች እያየሉ መምጣታቸዉ ተሰማ

November 9/2013

ሀያ ሁለት አመት ሙሉ ልባቸዉ በትዕቢትና በጥላቻ ተሞልቶ የተቃወማቸዉን እያሰሩና ለሚቀርብላቸዉ የእንተባበር ጥያቄ ሁሉ ጆሮ ዳባ ልብስ ሲሉ የሰነበቱት የህወሀት ጀብደኞች ዛሬ ኢትዮጵያን ግራ የሚያጋባና በአፍ ሊነገር የማይችል የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ መክተታቸዉን አምነዉ የእርቅ ሃሳብ ላይ ማተኮር መጀመራቸዉን ጎልጉል የተባላ ድረ ገጽ ላይ የሚታተም ጋዜጣ የወያኔንና የኢህአዴግን ዉስጥ አዋቂ ምንጮች ጠቅሶ ዘገበ።ህወሀትም ሆነ ኢህአዴግ ዉስጥ አፈና፤ ስለላና አለመተማመን እየተባባሱ መምጣታቸዉንና በእነዚህ ሁለት ድርጅቱ ውስጥ በተፈጠረ አለመተማመን ሳቢያ ስጋት የገባቸው የህወሀት ሰዎች በእርቁ ሃሳብ እየገፉበት መምጣታቸዉን ዉስጥ አዋቂ ምንጮቹ ተናግረዋል።
ቀድሞዉንም ቢሆን በዋና ዋናዎቹ የህወሀት መሪዎች ገመድ ታስሮ የቆየዉ በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ዉስጥ ያለዉ መተባበርና መግባባት ዛሬ ያ ገመድ ተበጥሶ በመካከላቸዉ አለመተማመን መንገሱ በስፋት እየተነገረ ነዉ። ዛሬ በተለይ ከመለስ ሞት በኋላ በህወሃትና ህወሃት በሚያዛቸው በሦስቱ አቻ ፓርቲዎች መካከል ያለው የመከባበርና የመገዛት ስሜት ተበላሽቶ፣ በኢህአዴግም ሆነ በህወሃት ዉስጥ የተፈጠረዉ ከፍተኛ ልዩነትና በሙስና ስም የተጀመረውን ዘመቻ ፓርቲዎቹን መዉጣት የማይችሉበት አዘቅት ዉስጥ እየከተተ መሆኑን ብዙዎች በመናገር ላይ ናቸዉ። አንደ ጎልጉል ጋዜጣ የመረጃ ምንጭች አባባል ህወሀትና ኢህአዴግ ዉስጥ በጣት ከሚቆጠሩ እጅግ በጣም ጥቂት ግለሰቦች ዉጭ የሁሉም ሰዉ እጅ በሙስና የተጨማለቀ በመሆኑ ዛሬ አንዱ ሌላዉ ላይ ጣቱን እየቀሰረ “ማን ንጹህ ሆኖ ማንን ይጠይቃል?” እየተባባሉ የእርስ በርስ ጦርነት ዉስጥ መግባታቸዉ ታዉቋል።
ህወሀት ባለፉት ሀያ ሁለት አመታት በተጓዘባቸዉ መንገዶች በተለይም በሁሉም ነገር ከሁሉም በላይ ሆኖ ሊቀጥል እንደማይችል በራሱ በህወሀት ዉስጥን በየድርጅቶቹ ዉስጥ በቀጥታና በተዘዋዋሪ መንገድ በስፋት እየተነገረ ሲሆን፤ ይህ ከሰሞኑ ይፋ ባልሆነ መንገድ የቀረበው “ታርቀን አገራችንን እንምራ” የሚለዉ የእርቅ ጥያቄ የቀረበዉ በያዝነዉ በኦርቶዶክስ ሃይማኖት የሲኖዶስ ጉባኤ ላይ የተሳመዉን ከፍተኛ የተቃዉሞና አገራችንን አበላሻችኋት የሚለዉን ድምጽ ተከትሎ እንደሆነ ከብዙ የፖለቲካ ተንታኞች አካባቢ እየተደመጠ ነዉ። ከዚህ ቀደም ተደርጎና ተሰምቶ በማይታው መልኩ የሃይማኖት አባቶች ወያኔን በግልጽ ማውገዛቸውና “አገሪቷን ገደላችኋት” ብለዉ መኮነናቸው በወያኔ/ኢህአዴግ ዉስጥ ከፍተኛ መደናገጥ እንደተፈጠረ ለማወቅ ተችሏል። ወያኔ እራሱ በሾማቸዉ በቀድሞው ፓትሪያርክ አማካኝነት የቤተክርሲቲያን ተቋማትን እንደተቆጣጠረ የሚታወቅ ሲሆን ፈቃድና አሁን ግን አንደለመደዉ ቤተክርስቲያኒቱን መቆጣጠርና አመራሮቹን አንደበታቸውን ማፈን የማይችልበት ደረጃ መድረሱን በቅርብ ግዜ ከተደረገዉ የሲኖዶሱ ጉባኤ የተገነዘበ ይመስላል። ከዚህ በጨማሪ ከእስልምና እምነት ተከታዮች አካባቢ ከሁለት አመት በላይ የተካሄደዉን መልስ ያላገኘዉ የድምጻችን ይሰማ ጉዳይ ወያኔን የማይወጣበት አዘቅት ዉስጥ ከትተዉታል።
ባለፉዉ የቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባኤ ላይ የተነሱት ሀሳቦች ወያኔ ነገሮች ቀስ በቀስ ከእጁ እንደወጡበት የሚያሳይ እንደሆነ ያመለከቱት አንድ ከፍተኛ የኢህአዴግ ባለስልጣን ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የኢህአዴግ አባላት እግራቸዉ አንጅ ልባቸዉ ከድርጅቱ ጋር እንዳልሆነ ተናግረዋል ። አብዛኛው የኢህአዴግ አባልና ደጋፊ ድርጅታቸዉ ዉስጥ ሰላማዊ ለውጥ ተካሂዶ ኢህአዴግን ወደ እርቅ ለመገፋፋት ከፍተኛ ፍላጎት አንዳላቸዉ እየተነገረ ነዉ።
እርቅ ከተፈለገ ለምን በግልጽ አይቀርብም በሚል ለቀረበላቸው ሃሳብ ባለስልጣኑ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባይሆኑም “ከማን ጋር ነው የምንታረቀው? እነማንን ነው ለእርቅ የምንጋብዘው? እርቅ ጠያቂ መሆን ያለበትስ ማን ነው?” የሚሉት ጥያቄዎች ዉስጥ ለዉስጥ እንደሚንሸራሸሩ አልሸሸጉም። በቅንጅት ጊዜም በተመሳሳይ የዕርቅ ፍላጎትና “ሥልጣን እናስረክብ” የሚል አቋም ተነስቶ እንደነበር ያስታወሱት እኚሁ ባለስልጣን፤ በወቅቱ ሃሳቡ ተግባራዊ ያልሆነው “ወያኔዎችን ወደመጡበት ጠራርገን እንመልሳቸዋለን” በማለት አንድ የቅንጅት አመራር ለሕዝብ መፈክር ሲያወርዱ ከተሰማ በኋላ ነበር የሚልና ብዙም አመኔታ የሌለዉ አስተያየት ሰንዝረዋል።

Friday, November 8, 2013

ሕወሓት አለማቀፍ አሸባሪ መዝገብ ላይ በአሸባሪነት የሚታወቅበት ፕሮፋይል::

November 8/2013

ምንጭ :- START – UNIVERSITY OF MARYLAND – የአሸባሪዎች አጥኚ ቡድን የአሸባሪ ድርጅቶች መዝገብ በሃገሩ ቋንቛ መጠሪያው .. አልተገለጸም የድርጅቱ ስም …..የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (TPLF) የሚንቀሳቀስበት አከባቢ … ኢትዮጵያ የተቋቋመበት ጊዜ ….. አልተገለጸም የአባላቶቹ ቁጥር/ጥንካሬው … አይታወቅም መለያው ….. ኮሚኒስት/ሶሻሊስት/ብሄርተኛ/ተገንጣይ የገንዘብ ምንጩ …. አይታወቅም የተነሳበት የፖለቲካ ፍልስፍና ራሱን የትግራይ ንቅናቄ ወይንም  ወያኔ በማለት በ1970ዎቹ መጀመሪያ በመንግስቱ ሃይለማርያም አገዛዝ ላይ የተጀመረ ተቃውሞ
በ1975 አከባቢ የትግራይ ነጻ አውጪ በማለት ተመስርቶ በኤርትራ ነጻ አውጪ ስር እየተዳደረ ውጊያ የከፈተ ድርጅት ነው::አላማቸው የአልቤንያን ሞዴል የተከተለ የኮሚኒስት ስርኣት በማስፈን የታለመ...የትግራይን ህዝብ ከደርግ አገዛዝ ነጻ ለማውጣት የተነሳ ነበር::በሜይ 1989 የደርግን ሰራዊት በማሸነፍ ሙሉ ትግራይን መቆጣጠር ችሎ ነበር::በተለያየ ጊዜ ከሻእቢያ ጋር እና በተናጠል በተለያዩ አከባቢዎች የአሸባሪነት ድርጊት ፈጽሟል::
ዝርዝር መረጃውን ከዚህ ድህረገጽ ያገኙታል:- http://www.start.umd.edu/start/data_collections/tops/terrorist_organization_profile.asp?
Terrorist Organization Profile:
Tigray Peoples Liberation Front (TPLF)
Mothertongue Name: n/a
Aliases: Tigrai Peoples Liberation Front
Bases of Operation: Ethiopia
Date Formed: n/a
Strength: Unknown number of members
Classifications: Communist/Socialist, Nationalist/Separatist
Financial Sources: Unknown
Founding Philosophy: The Tigray movement, also known as Weyane, began in the mid 1970's as opposition to the Mengistu dictatorship in Addis Ababa. The Tigray People's Liberation Front (TPLF) was formed in early 1975 by members of a previous organization, the Tigray Liberation Organization that came under the influence of the Eritrean People's Liberation Front (EPLF). The TPLF's goals included the overthrow of the Dergue regime of Mengistu Haile Mariam and the establishment of a more democratic, inclusive government for Ethiopia. Their ideology was communist, following an Albanian model. Although the group was based out of Tigray and was comprised of almost all Tigrayan peoples, they fought in the name of all groups that opposed Menigstu. Their largest offensive against Ethiopian forces was in February 1988, and by May 1989 the Ethiopian Army had completely pulled out of Tigray.
Despite the EPLF's goal of Eritrean independence, contrasted with the TPLF's goal of political change within Ethiopia, the two groups had close contacts throughout the 1970's and 1980's, helped by EPLF raids on Derg bases within Tigray. Differences regarding the territorial boundaries of Tigray and Eritrea, however, eventually led to a split between the two groups.
Current Goals: In 1989 the TPLF formed an alliance with the Ethiopian People's Democratic Movement (EPDM) and formed the Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front (EPRDF), which claimed to fight for the rights of all oppressed nationalities, civil rights, and a genuine people's government. In 1991, the EPRDF succeeded in overthrowing the Menigstu regime, and took control of the Ethiopian government.
A split developed within the TPLF in the early 1990's, based on debates between "moderate" and "hard-line" members of the group. Party leader and Prime Minister Meles Zenawi was a moderate and favored the adoption of market-based economic principles and privatization. Opposition from hard-line communists in the group led to an attempted, yet unsuccessful coup in March 2001. The TPLF-dominated EPRDF continues to hold power in Ethiopia.
Key Leaders
n/a
Related Groups
Ethiopian People's Revolutionary Army -- Rival
U.S. Government Designations
Foreign Terrorist Organization (FTO): No
Terrorist Exclusion List (TEL): No
Learn more about these U.S. Department of State classifications:
Foreign Terrorist Organizations (FTOs)
Terrorist Exclusion List (TEL)
Other Governments' Designations
UK Proscribed Group: No
Australia Specified Group: No
Canada Specified Group: No
EU Specified Group: No
Russia Specified Group: No
Global Terrorism Database
For information compiled by the Global Terrorism Database on terrorist incidents for which this group was responsible click here.
Return to search
top