Saturday, June 15, 2013

የአባይ ፍጥጫን በተመለከተ ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

እነሱ ከአባቶቻቸው አይበልጡም እኛም ከአባቶቻችን አናንስም!

ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ ወረራና ደባ መፈፀም የጀመረችው ኢትዮጵያ ዛሬ በአባይ ላይ ግድብ ለመስራት ከመነሳቷ እጅግ በርካታ አመታት በፊት ጀምሮ ነው፡፡ ሀገራችን ከግብፅም ሆነ ከሌሎች የተቃጣባትን ተደጋጋሚ ወረራዎች በመመከትና ጠላቶቿንም ድባቅ በመምታት ነፃነቷን ጠብቃ መኖሯ ለጠላቶቿ መራር የሆነ እውነት ነው፡፡ በተለይም ከጥንት ጀምሮ የአባይን ምንጭ ለመቆጣጠር ጥልቅ ምኞት የነበራት ግብፅ በሃገራችን ላይ የፈፀመችውን ግልፅና ድብቅ ወረራ በመመከት ተደጋጋሚ ሽንፈትን አከናንበን መልሰናታል፡፡

ሀገራችንን በጦር አውድማዎች ማሸነፍ እንደማትችል በቂ ትምህርት የወሰደችው ግብፅ ከቅርብና ሩቅ ታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በማበር ዛሬ በኤርትራና በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ የተቀመጡ አማፅያንን በማስታጠቅና ሁለንተናዊ ድጋፍ በመስጠት ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትገነጠልና ኢትዮጵያም እንድትዳከም ከፍተኛ ደባ ፈፅማለች ፡፡ ግብፅ ይህን ሁሉ ግልፅ እና ስውር ደባ የምትፈፅመው ኢትዮጵያ በወንዞቿ መጠቀም የማትችል ደካማ ሐገር እንድትሆን ለማድረግ ነው፡፡ ይህ ጥረቷ ግን ደካማ ኢትዮጵያን ለመፍጠር ከመሞከሯ ውጭ የምኞቷን ያህል አልተሳካላትም፡፡ ቢሆንም እኛን ኢትዮጵውያንን እርስ በእርሳችን በማናከስ በጦርነትና በክፍፍል ተጠምደን ወንዞቻችንን የመጠቀም አቅም በማሳጣት ለዘለዓለም ብቸኛ ተጠቃሚ ሆና መኖር ትፈልጋለች፡፡ ይህ ካልተሳካላት ቀጥተኛ ወረራ በመፈፀም የወንዞቻችን ምንጮች ለመቆጣጠር እንደምትመኝ የየዘመናት ሙከራዎቿ ያረጋግጣሉ፡፡
...
ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ የጀመረችውን ግድብ አስመልክቶ ሰሞኑን ከግብፅ በኩል የሚሰማው ዛቻና ማስፈራሪያም ከላይ የተገለፁት እውነታዎች ነፀብራቅ ነው፡፡ በመሠረቱ በአባይ ወንዝ ላይ የተጀመረው ግድብ ከሐገራዊ ጠቀሜታው ይልቅ የገዥውን ፓርቲ የስልጣን እድሜ ለማራዘም የታለመና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚደለቅ ከበሮ መሆኑን ፓርቲያችን ይገነዘባል፡፡ የግድቡ ሥራ የገዥውን ፓርቲ የተለየ አሣቢነትና ተቆርቋሪነት የሚያሳይ አድርጎ ለማቅረብ የሚደረገው ልፈፋ ከተራ ጩኸት በዘለለ የዜጎችን ልብ የሚያማልል አይደለም፡፡ በአንፃሩ ከገዥው ፓርቲ አመለካከት ውጭ ያሉ ዜጎችን የግድቡ ሥራ የማይመለከታቸው አድርጎ ለማቅረብ የሚደረገው የወሬ ክምር ልብን የሚሰብር ርካሽ ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ በመሆኑም ለኢትዮጵያ ክብርና ኩራት መሠዋት ለዜጎችም ጥቅም መጠበቅ እነማን ምን እንደከፈሉና እንደሚያስቡ ለታሪክ በመተው ሃገርን መክዳትና መጥላትን በሌሎች ላይ ለመለጠፍ የሚደረገው ሩጫ ግን እንዲታሰብበት እንመክራለን፡፡

የግድቡ ሥራ ከስም አወጣጥ ጀምሮ የፕሮጀክቱ አነዳደፍ፤ የፋይናንስ አሰባሰብ፣ ግንባታውን የሚያካሂዱ ድርጅቶች አመራረጥና ሌሎችም ጉዳዮች እጅግ ግልፅነት የጎደላቸውና ባለቤትነታቸውም ከኢትዮጵያ ህዝብ ተነጥቆ ለተወሰኑ ቡድኖች በተለይም ለገዥው ፓርቲ ፍላጎት ማሳኪያ እየዋለ መሆኑ ቀርቶ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን በሚያስማማ ሁኔታ እንዲካሄድ ፓርቲያችን አጥብቆ ይጠይቃል፡፡

ሐገራችን ለሚያስፈልጋት ዓላማ ሁሉ በወንዞቿ መጠቀሟን በመቃወም በግብፅም ሆነ በሌላ በማንኛውም አካል የሚፈፀሙ ዛቻም ሆነ ሌሎች አሉታዊ ድርጊቶችን ፓርቲያችን አጥብቆ ያወግዛል፡፡ የሃገራችንን ጥቅም ለማስጠበቅም ማንኛውንም መሰዋዕትነት መክፈልን ከጀግኖች አባቶቻችን የወረስነው አኩሪ ታሪካችን በመሆኑ ይህን ቃል ኪዳን ማክበርና መጠበቅ የፓርቲያችን የፀና አቋም ነው፡፡

በመጨረሻም አሁን የተፈጠረው ውጥረት በውይይት እንዲፈታ የኢትዮጵያ መንግስት ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እንዲያደርግ እያሳሰብን ነገር ግን ግብፅ ይህን አልቀበልም በማለት ፍላጎቷን በሃይል ለማስፈፀም የምትፈልግ ከሆነ የአባቶቻችንን ታሪካዊ አሸናፊነት የምንደግመው መሆኑን ከታሪክ እንድትማር ለማስታወስ እንገደዳለን፡፡

ሰኔ 7 ቀን 2005 ዓ.ም

Friday, June 14, 2013

በደቡብ ጎንደር ዞን መምህራን በደንነት ሀይሎች ታፍነው ተወስደዋል

ሰኔ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በደብረ ታቦር ከተማ ከአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ እና ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ የተባሉ መምህራን ትናንት ማታ እና ዛሬ ጠዋት በደህንነት ሐይሎች ታፍሰው ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውን ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል።

... መምህር ታደሰ መንግስቴና መምህር ፈቃዱ ጌትነት የሚባሉ በ ፈቀደ እግዚ ኮሌጅ ውስጥ አስተማሪዎች ሲሆኑ መምህር አሸናፊ አለሙ ደግሞ የሁለተኛ ደረጃ መምህር ነው። አብይ ሃይሌ እና ማስረሻ የተባሉ ወጣቶችም እንዲሁ ታፍነው ተወስደዋል።

 ታፍነው ከተወሰዱት መካከል የሁለቱ የቅርብ ጓደኛ የሆነ ወጣት እንደገለጸው ቤተሰቦቻቸው የአካባቢውን ፖሊሶች ሲጠይቁ ” የት እንደተወሰዱ አናውቅም” የሚል መልስ ተሰጥቷቸዋል። በጉዳዩ ዙሪያ የፌደራል ፖሊስ አዛዦችን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
 

Thursday, June 13, 2013

ኢሕአፓ በአዲስ አበባ በርካታ ቦታዎች በህቡዕ ወረቀት በተንኩ አለ


Imageበስውር የሚንቀሳቀሱ የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)አባላት በአዲስ አበባ በርካታ ቦታዎች ረቡዕ ሌሊት ሰኔ 5/2005 ዓ.ም. /June 12, 2013/  ተነሥ በሚል ርዕስ የተዘጋጁ ቀስቃሽ ፅሑፎችን የበተኑ ሲሆን በዋናነት በቦሌ፣በካዛንቺስ፣በአራት ኪሎ፣በሽሮ ሜዳ፣በቄራ፣በፈረንሳይ ለጋሲዪን፣በሜክሲኮ፣በፒያሳ፣በመገናኛ፣በኮልፌ፣በመርካቶ፣በጎፋ እና በመሳሰሉት ዋና ዋና የከተማዋ ክፍል በሚገኙ የማስታወቂ ቦርዶች ላይ ተለጥፈው የታዩ ሲሆን በተለይ ሐሙስ ሰኔ 6/2005 ዓ.ም. በርካታ ነዋሪዎች ጽሑፉን ማንበብ ችለዋል።ይሁን እንጂ ይህ ዜና የደረሳቸው የገዢው ፓርቲ አመራሮች ወዲያው የፌደራል ፖሊሶችን እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላትን በማሰማራት በዋና ዋና ቦታዎች ላይ የሚገኙትን ያነሱ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢ ግን ጽሑፎቹ እስከ ቀትር ሳይነሱ በበርካታ ሰዎች መነበብ ችለዋል።
 
የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በ5ለ1 አደረጃጀት ጠርንፎ እንደያዘ የሚነገርለት ኢህአዴግ ይህ አይነቱ ድንገተኛ ክስተት ዛሬም ድረስ ከህዝብ ጋር ሆድ እና ጀርባ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ሲሉ አንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ትዝብታቸውን የገለፁ ሲሆን የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ የአዲስ አበባ ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ የወጣቶች ሊግ አመራሮች አስቸኳይ ስብሰባ ሐሙስ ዕለት እንደተቀመጡ ከስፍራው መረዳት ተችሏል።
 
ተነሥ  በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የዚህ ጽሑፍ ይዘት የሚከተለው ነው፦ “እጅግ የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፦ የአኩሪ ታሪክ ባለቤት፤ይልቁንም ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ጮራን የፈነጠቅህ ፋና ወጊ የነፃነት አርበኛ መሆንህ የአደባባይ ምስጢር ነው።
 
Imageይሁን እንጂ የዚህ ሁሉ ጥንካሬህ መሠረት የሆነው አንድነትህ በጎጠኛው የወያኔ ቡድን የዘውጌ አስተዳደር ተሸርሽሮ ዛሬ በሀገርህ ተንቀሳቅሰህ የመስራት መብትህ ተገድቦ፣ከችሎታህና ከግለሰባዊ ክህሎትህ ይልቅ በዘር ማንነትህ እየተመዘንክ የኢኮኖሚ መገለል እየደረሰብህ ህይወት ብርቱ ሠልፍ ሆናብህ ሀገርህን ጥለህ እንድትሰደድ በተሰላ ስሌት በመኖርና ባለመኖር ቅርቃር ውስጥ እንድትባዝን ተደርገህ፣ሰብዓዊና ዴሞክራሲዊ መብትህ ተገፎ የመናገርና ሃሳብህን በነፃነት የማራመድ መብትህን ከመነጠቅህ ባሻገር በአጠቃላይ ህልውናህ በወያኔ የግፍ መዳፍ ውስጥ ወድቋል።

ስለሆነም እንደመዥገር በላይህ ላይ ተጣብቆ በደምህ የሰባውን ይህን ዘረኛ ቡድን ከጫንቃህ ላይ አራግፈህ በፍትህ አደባባይ የምታቆምበት ጊዜው አሁን ነው።ሀገርህንና ራስህን ለማዳን ተነሥ!!!”

8ኛውን አመት የሰኔ 1997 ሰማዕታት የምናስታውሰው የተሰውለትን ክቡር አላማ ለማሳካት ዝግጁነታችንን እየገለጽን ነው


የምርጫ 1997 ውጤት በወያኔ/ኢህአደግ መሰረቁን ተከትሎ ተቃውሞአቸውን ለማሰማት አደባባይ የወጡት ዜጎቻችን ላይ በመለስ ዜናዊ ይመራ የነበረው አጋአዚ ጦር ፋሽስታዊ እርምጃ መውሰድ የጀመረበት ሰኔ 1 1997 8ኛ አመቱን ባለፈው ቅዳሜ አገባዷል።

በግፍ የተጨፈጨፉትን የሰኔ 97 ሰማዕታቶቻችንን ባሰብን ቁጥር ሁሌም በአይነ ህሊናችን የሚመላለሰው፣ አገርን ከወራሪ ጠላት ለመከላከል በሚያስችል ወታደራዊ አቅምና ዝግጅት እስከ አፍንጫው ድረስ ታጥቆ የነበረውና; በመላው አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ እየተርመሰመሰ በወገኖቻችን ላይ ያን ሁሉ የተኩስ ናዳ ሲያዘንብ የሰነበተው የአጋአዚ ጦርና በአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የቴሌቪዥን መስኮቶች የተመለከትናቸው በደም የተጨመላለቁ አካላት ምስል ፤ በአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ከተስተጋባው የሟቾች ቤተሰቦች የድረሱልን ለቅሶና ዋይታ ጋር ተደበላልቆ ነው። “መሪያችሁን ወጥታችሁ በሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ምረጡ” ብሎ የፈቀደ ሃይል ሲሸነፍ: ታንክና መተረየስ የታጠቁ አልሞ ተኳሾችን ያዘምትብናል ብሎ ያሰበ አልነበረምና ፍትህ፤ እኩልነትና ነጻነት የሰፈነበት አገር ባለቤት ለመሆን ተስፋ ሰንገው ጥያቄያቸውን በሰላማዊ መንገድ ለማሰማት ከቤታቸው የወጡ ዳግም ላይመለሱ እስከወዲያኛው ተለዩን።
        
ፋሽስት ጣሊያን አገራችንን በቅኝ ግዛትነት የራሷ ለማድረግ በነበራት ህልም ለነፃነቱ ቀናዕ የሆነውን ህዝባችንን በፍርሃት ለማሽመድመድ የሩዶልፍ ግራዚያኒ ጦር የካቲት 12 ቀን 1928 በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ላይ ከፈጸመው የጭካኔ እርምጃ ፈጽሞ ባልተናነሰ አረመኔያዊነት ሰኔ 1 ቀን 1997 ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው ያ አሰቃቂ ጭፍጨፋ፡ ታዳጊዎችን ከአዋቂ ፤ አዛውንትን ከጎልማሳ፤ አካለ ስንኩላንን ከጤነኛ ፤ ሴቶችን ከወንዶች መለየት ሳያስፈልግ አደባባይ የወጣውን ሁሉ “ የትግሬ ጠላትና የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂዎች ናቸውና በሉዋቸው” የሚል ትዕዛዝ ባስተላለፉ የዘር ጥላቻ ሂሊናቸውን ባናወዛቸው ጥቂት “ከትግራይ ህዝብ አብራክ የተገኘን እንቁዎች ነን” በሚሉ ዘረኞች የተቀነባበረ እንደሆነ ታወቃአል።

መለስ ዜናዊ ፤ በረከት ስሞን ፤ ሳሞራ ይኑስና ታደሰ ወረደ ከነዚህ ቀንደኛ ዘረኞች ዋንኞቹ እንደሆኑ ሲታወቅ “የተጭበረበረው የምርጫ ድምጻችን ይመለስልን!! ፤ እንዲመሩን የመረጥናቸው ሰዎች ያስተዳድሩን !!” በማለት ጥያቄ ያነሳውን ህዝብ ለመቅጣት ሲባል የአገሪቱ የጸጥታ ሃይሎች በሙሉ በአንድ ዕዝ ሰንሰለት ሥር ገብቶ ተጠሪነቱ በቀጥታ ለመለስ ዜናዊ እንዲሆን ምርጫው በተካሄደበት የግንቦት 7/ 1997 ምሽት መመሪያና አዋጅ በሬዲዮና በቴሌቭዥን በራሱ በመለስ ዜናዊ ካስነገሩ ቦኋላ: እስከዛሬ ወደ አፎቱ ያለተመለሰ የጥቃት ሳንጃቸውን በህዝባችን ላይ መዘዋል።

ዘረኝነት ምን ያህል ጭካኔ ሊያመነጭ እንደሚችል ትምህረት ሰጥቶ ባለፈው የሰኔ 97 ጭፍጨፋ ሰለባ ከሆኑት መቶዎች ውስጥ፡ መርካቶ አካባቢ ይጫወትበት የነበረውን የጨርቅ ኳስ አንስቶ ለመሸሽ ጎንበስ ባለበት ተደፍቶ የቀረው የ10 አመቱ ታዳጊ ህጻን እንዲሪስ፤ ደብተሩን ተሸክሞ ከትምህረት ቤት ሲመለስ ፍልውሃ አካባቢ የተገደለው የ14 አመቱ ነብዩ አለማየሁ፤ ኮተቤ መምህራን ኮሌጅ ፊት ለፊት ግንባሯን በጥይት ተመታ የተገደለቺው የ18 አመቷ ወጣት ሽብሬ ደሳለኝ፤ ባሌን አትውሰዱብኝ በማለታቸው ደረታቸውን በጥይት ተደብድበው የተገደሉት የ8 ልጆች እናት ወ/ሮ እቴነሽና ቀድሞ በተተኮሰ ጥይት የወደቀውን ወንድሙን አብረሃም ይልማን አስከሬን ቀና ለማድረግ ሲሞክር ጀርባውን በጥይት ተበሳስቶ የተገደለው የፈቃዱ ይልማ ወላጅ ቤተሰቦች በአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ያሰሙት የድረሱልን እሮሮና ለቅሶ ዛሬም ድረስ ሂሊናችን ውስጥ እያንቃጨለ እረፍት ይነሳናል።
በተለይም ደግሞ ድንገተኛ ሞት ከረጂሙ የጥፋት አላማው ከቀጨው መለስ ዜናዊ በስተቀር የዚህ ሰቆቃ ፈጻሚዎች ዛሬም ድረስ በሰሩት ወንጀል ፍትህ ፊት ሳይቀርቡና ተገቢውን ቅጣታቸውን ሳያገኙ መቅረታቸው ያንገበግበናል፤ ይቆጨናል፤ እስከመጨረሻው የድል ቀን ድረስ ፀንተን እንድንታገላቸው ሞራላችንንና ወኔያችንን በየደቂቃው ይሰቀሰቃል።

 ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በምርጫ 97 የተነጠቅነውን የህዝብ ድል ለማስመለስና ወያኔ በአገዛዝ ዘመኑ በህዝባችን ላይ ለፈጸመው ሰቆቃና አገራችን ላይ ለፈጸማቸው ወንጀሎች ህግ ፊት ቀርቦ ተጠያቂ እንዲሆን ለማድረግ ተግቶ እየታገለና እያታገለ ያለው ለነጻነት ሲሉ ውድ ህይወታቸውን መሰዋዕት የከፈሉ ወገኖቻችን አደራና የህዝባችን የነጻነት ጥማት ከሁሉም በላይ ስለሚያሳስበው እንደሆነ ደጋግሞ ገልጾአል።

ወያኔ ሥልጣን ከተቆጣጠረ ጊዜ ጀምሮ የአገራችንን ሉአላዊነት ለማፍረስና የህዝባችንን አንድነት ለመናድ የሚያደርገውን እኩይነት ተቃውሞ ሲታገሉ የታሰሩ፤ የተደበደቡ፤ የተገደሉና ለአካለ ጎዶሎነት የተዳረጉት ዜጎቻችን መስዋዕትነት መና ሆኖ እንዳይቀር እንዲሁም ከሰኔ 1997 እስከ ህዳር 1998 በአጋአዚ ጦር የተጨፈጨፉ የዲሞክራሲ ለውጥ አርበኞች አጥንትና ደም እንዳይፋረደን እያንዳንዱ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ትግሉን ከዳር ለማድረስ እየተካሄደ ያለውን የነፃነት ትግል ለማገዝ ዛሬውኑ እንዲቀላቀለን ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪዉን ለያንዳንዱ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ያቀርባል። አውራው እንደሞተበት ንብ እየተበታተነ ያለው የወያኔ ኢህአደግ አባላትና ደጋፊዎችም በጭፍጨፋ ወንጀል ተሳታፊ እስካልነበሩ ድረስ የሚመጣው ለውጥ ለነርሱም የተስፋና የነፃነት ዋስትና የሚሰጥ በመሆኑ ምንም ሳያቅማሙ የትግሉን ጎራ ዛሬውኑ እንዲቀላቀሉ ወገናዊ ጥሪውን ያስተላለፋል።

ወያኔ ላለፉት 22 አመታት በአገራችንና በህዝባችን ላይ እየፈጸመ ያለውን ሰቆቃ ማስቆም የሚቻለው ወያኔን በማስወገድ ብቻ እንደሆነ አቋም የያዘው የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራርና መላው አባላቱ ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት ሁሉ ለመክፈል ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ መሆናቸውን የሚገልጹት በታላቅ ብሄራዊ ስሜትና ኩራት ነው። ለሰኔ 97 ሰማዕታትና ለቤተሰቦቻቸው ከዚህ የበለጠ ቃልኪዳን የለምና።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ወደሶማሌ ክልል ተጉዞ የነበረው የአርቲስቶችና የጋዜጠኞች ቡድን በክልሉ አስተማማኝ ሰላም እንዳለ ምስክርነቱን በመስጠት የአንድ ሳምንት ጉዞውን ሰኞ ዕለት አጠናቀቀ

ሰኔ ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ቡድኑ ከጎዴ ተነስቶ በቀብሪደህር፣ በደገሃቡር፣ በቀብሪበይህ፣ በጂጂጋ አድርጎ ወደሐረር በመግባት የሳምንት ጉዞውን በድሬዳዋ ከተማ ባለፈው እሁድ አጠናቋል፡፡

በጉዞው ወቅት በአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገለት የተጓዘው የዚሁ ቡድን አባላት ከሆኑት መካከል፤ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፣ደበሽ ተመስገን፣ጥላሁን ጉግሳ፣ችሮታው ከልካይ፣አብራር አብዶ፣ አበበ ባልቻና የመሳሰሉ አርቲስቶችና ጸሐፊዎች “በሶማሌ ክልል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም አለ” በሚል   ምስክርነት የሰጡ ሲሆን  ይህም  ብዙዎችን አስገርሟል፡፡
አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ በአንድ መድረክ ላይ ባደረገው ንግግር “መጀመሪያ ከቤተሰቦቼ በቀን ለአምስት ጊዜያት ያህል ሰላም ነህ ወይ እየተባለ ይደወልልኝ ነበር፡፡ ቀስ እያለ በቀን ወደሶስቴ፣ ወደሁለቴ ወረደ፡፡ በአሁኑ ወቅት እኛ እንምጣ ወይ ሳይሉ አይቀሩም” በማለት  ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡

በጉዞው ወቅት የመከላከያ ሰራዊት ቡድኑን ከማጀቡም በተጨማሪ በየበረሃው ከወትሮው በተለየ መልኩ የሰራዊቱ አባላት በከፍተኛ ቁጥር ተሰማርተው መታየታቸው፤ በአካባቢው የጸጥታ ችግር መኖሩን ጠቋሚ ኧንደሆነ በቡድኑ ውስጥ የተሳተፉ ወገኖች ተናግረዋል፡፡

በአንዳንድ አካባቢዎችም ጉዞው ለደቂቃዎች እንዲቆም ኧየተደርገ ሰራዊቱ ቦታ ቦታውን ከያዘ በሃላ  እንዲቀጥል መደረጉታውቋል፡፡ ይህ በሆነበት ሁኔታ አንዳንድ አርቲስቶች የሰጡት  ምስክርነት እውነታውን የማይገልጽ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ራሳቸውንም ያስገመተ እንደሆነ ለመረዳት ተችሎአል፡፡

በግልጽ ንግግራቸው የሚታወቁት የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሀመድ ባለፈው ዓርብ ዕለት ለአርቲስቶችና ጋዜጠኞች ባደረጉት ንግግር በክልሉ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው ኦብነግ የተባለው ቡድን ጠንካራ እንደነበር አረጋግጠዋል፡፡

ኦብነግ ታላቋ ሶማሊያን ለመገንባት በእነኳታርና ግብጽ እየተደገፈ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን፣ በዚህ ምክንያት የክልሉ ሰላም አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ወድቆ እንደነበር በንግግራቸው ያስታወሱት ፕሬዝዳንቱ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ሳይቀር የኦብነግን እንቅስቃሴ በመደገፍ በሁለት ቢላዋ ይበሉ እንደነበር አረጋግጠዋል፡፡

በአንድ ወቅት በውጪ አገር ለኦብነግ ድጋፍ አልሰጥም ያለ የክልሉ ተወላጅ ወደሶማሌ ክልል ቤተሰቦቹን ለመጠየቅ በሄደበት ጊዜ በክልሉ ፖሊስ ተይዞ ያለአንዳች ምክንያት እንዲታሰር መደረጉን ያወሱት ፕሬዝዳንቱ   ኦብነግን ለምንድነው የማትደግፈው ተብሎ ሲጠየቅም፤ ሰውየው ጥፋተኛ መሆኑን፣ ከእንግዲህ ለመደገፍና ያለፈውንም ለመካስ ቃል በመግባቱ ከእስር መለቀቁን በመግለፅ ግንባሩ የቱን ያህል የመንግስት መዋቅርን ጭምር ተቆጣጥሮት እንደነበር ተናግረዋል፡፡

አቶ አብዲ በአሁኑ ሰዓት_ ኦብነግን ጨምሮ የሌሎች የጠላት ሃይሎች እንቅስቃሴ በመከላከያ ሰራዊት፣ በክልሉ ልዩ ሃይልና በሕዝቡ ትብብር ተረጋግጦአል ቢሉም አንዳንድ በጅጅጋ ያነጋገርናቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ግን ዋና ከተማዋ ጅጅጋ እንኩዋን በከፍተኛ ጥበቃ ስር በመሆንዋ እንደልብ ወጥቶ ለመግባት እንደማይቻል ተናግረዋል:: አክለውም  ይህ የሰላም ምልክት እንዴት ሊሆን ይችላል ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ለ አርቲስቶችና ለጋዜጠኞች ቡድን በሶማሌ እና በሐረሪ ክልሎች ከፍተኛ አቀባበልና የጫት ግብዣ ተደርጎላቸዋል:: በቆይታቸው ደረጃውን ለጠበቀ የጫት ግብዝ ብቻ   ከ100ሺ ብር በላይ እንደወጣ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች አረጋግጠዋል፡፡
ጉዞውን የፌዴሬሽን ም/ቤት ከክልሎቹ ጋር በመቀናጀት ያዘጋጀው ነበር፡፡

Ethiopia and Egypt on “war of words”

ESAT News   June 12, 2013 

Following Ethiopia’s declaration that it has successfully “diverted the Abay River”, the bicker between Ethiopia and Egypt has intensified.  Video clips showing the discussion of Egyptian President Mohammed Morsi with opposition political parties was transmitted live when some opposition leaders suggested Egypt should back rebels in Ethiopia or attack the Dam that Ethiopia is building on the River.

Morsi two days ago, then, warned Ethiopia saying “all options are open” if the Ethiopian project to build a dam on the Blue Nile diminishes a drop of Egypt’s water share.

Although Ethiopia has been consistently stating that the water will continue to flow in the same direction upon the building of the Dam and will have no effect on Egypt’s share, Morsi said “Egypt’s water security shouldn’t be compromised”.

“If Egypt is ‘the gift of the Nile,’ then the Nile is God’s gift to Egypt,”  Morsi said. “We will defend each drop of Nile water with our blood if necessary,” he warned.

The Ethiopian Ministry of Foreign Affairs said on its part that Ethiopia will not stop even for a second the construction of the Dam alarmed by Egypt’s rhetoric. “Ethiopia was deeply frustrated to see further unconstructive propaganda aired about the GERD in the presence of the President, Mohamed Morsi, the Prime Minister, Hisham Qandil, and other high ranking Egyptian officials at the Popular Conference on Egypt’s Rights to Nile Water.” The Ministry said.

The statement added that proposed suggestions of any resort to war or other forms of sabotage are unacceptable and have no place in the 21st century. In this context, Ethiopia would like to make it clear that it expects the Government of Egypt to refrain from all such unacceptable forms of behavior or engagement and work towards greater cooperation between the two countries.

Political analysts, who are following the situation closely, say both countries are using the Dam issue and the “war of words” to divert the attention of local opposition from their internal political and economic crises.

Wednesday, June 12, 2013

ኢትዮጵያና ግብጽ የቃላት ጦርነት መወራወር ጀምረዋል።

<<ማናቸውንም እርምጃ ለመውሰድ በሩ ክፍት ነው>>ግብጽ

<<በቀረርቶ ተደናግጠን ለሰከንድ የግድብ ግንባታውን አናቆምም>>-ኢትዮጵያ

በሁለቱ አገሮች መካከል መተነኳኮሱ እየባሰ የመጣው ዘንድሮ ግንቦት 20 ቀን የተከበረውን የገዥውን ፓርቲ በኣል ምክንያት በማድረግ ኢትዮጵያ ፦” የአባይ ወንዝን የተፋሰስ አቅጣጫ አስቀየስኩ” ብላ ማወጇን ተከትሎ ነው።
ይህን ተከትሎ በተለይ የግብጽ መንግስት -ከተቃዋሚዎቹ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ላይ እስከ ወታደራዊ ጥቃት ድረስ የሚደርስ እርምጃ ለመውሰድ የመከሩበት ስብሰባ በይፋ ታየ፤

 ይሁንና የግብጽ መንግስት-ከተቃዋሚዎቹ ጋር በመሆን ኢትዮጵያ ላይ ለመውሰድ ስለታሰበው እርምጃ ሲመክሩበት የነበረው ስብሰባ በቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት መተላለፉ፤ግብጽ -ኢትዮጵያን ለማስፈራራት መፈለጓን የሚያሳይ ተራ ጨዋታ ነው በሚል ብዙዎች ትኩረት ሳይሰጡት ቆይተዋል
ይህ በ እንዲህ እንዳለ ትናንት የግብጹ ፕሬዚዳንት መሀመድ ሙርሲ ፦ኢትዮጵያ በምትሠራው ግድብ ሳቢያ ወደ ግብጽ ከሚፈሰው የ አባይ ወንዝ የጠብታ ያህል ከቀነሰ አገራቸው ግብጽ ማናቸውንም እርምጃዎች ኢትዮጵያ ላይ ለመውሰድ ዝግጁነቱ እንዳላት አስታውቀዋል።

 ከ ኢትዮጵያ ጋር ጦርነት እንደማይፈልጉ፤ ግድቡን ለማስቆም የሚያደርጉት ጥረት ካልተሳካ ግን ሁሉንም አማራጭ እርምጃዎች ለመውሰድ እንደሚገደዱ ነው ፕሬዚዳንቱ የተናገሩት።
ኢትዮጵያ - አቅጣጫውን የቀየረው የወንዙ ፍሰት ሀይል ካመነጨ በሁዋላ ተመልሶ በመደበኛው መስመር እንደሚፈስ እና በግብጽም ሆነ በሱዳን ላይ የሚፈጥረው ነገር እንደማይኖር ደጋግማ ብታሳውቅም፤ፕሬዚዳንት ሙርሲ ፈጽሞ የግብጽ የውሀ ደህንነት ሊነካ አይገባም! በማለት የ ኢትዮጵያን ምላሽ እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል።
“የ አገሪቱ ፕሬዚዳንት እንደመሆኔ መጠን ሁሉንም እርምጃዎች ለመውሰዱ በሩ ክፍት መሆኑን አሳውቃለሁ” ነው ያሉት -ፕሬዚዳንት ሙርሲ።
በማያያዝም፦”ግብጽ የዓባይ ስጦታ ከሆነች፤ዓባይ የግብጽ ስጦታ ነው”ብለዋል-በስሜት ውስጥ ሆነው በቴሌቪዥን ባደረጉት ንግግር።
እንደ አንድ ታላቅ ህዝብ የግብፃውያን ህይወትና ኑሮ ከ ዓባይ ጋር የተያያዘ ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ሙርሲ፤ ፍሰቱ በ አንዲት ጠብታ ከቀነሰ ያለን ቀሪ አማራጭ ደማችን ነው”ብለዋል።
የግብጽን ተደጋጋሚ ዛቻ ተከትሎ የ ትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፦<<ኢትዮጵያ በቀረርቶ ተደናግጣ ለሰከንድ የግድብ ግንባታዋን አታቆምም>>ብሏል።

ኢትዮጵያ ከምንም በላይ ለትብብር ፣ ለወዳጅነትና ለጋራ ጥቅም ያላትንም ፅኑ እምነት በወቅቱ ግልፅ አድርጋለች ያለው የሚኒስቴሩ መግለጫ ፥ ይህ በእንዲህ እንዳለ ትናንት ብሄራዊ የናይል ጉባኤ በተሰኘው ስብሰባ ላይ የግብጽ ፕሬዚዳንት ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ ሚኒስትሮችና ሌሎችም በተገኙበት ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አስመልክቶ አፍራሽ መልዕክቶች ተላልፈዋል ብላል ።
በዚህ ረገድ በግብፅም ሆነ በሌላ ማንኛውም ወገን የሚቀርብ የግድቡን ግንባታ የማዘግየት ወይም ከነአካቴው የማቋረጥ ነገር ፈፅሞ ተቀባይነት እንደማይኖረው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል ።

 ጦርነትና ሌሎች አፍራሽ ስልቶችን ስለመጠቀም የሚቀርቡት ሀሳቦች ያረጁና ያፈጁ ፣ የ21ኛውን ክፍለ ዘመን አስተሳሰብ የማይሸከሙ ፣ እና ጤናማ ያልሆኑ አስተሳሰቦች እንደሆኑ የገለጸው የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ኢትዮጵያ በዚህ ቀረርቶ ተደናግጣ ግንባታውን ለሰኮንድም አታቆምም ብላል።

 ጉዳዩን በትኩረት እየተከታተሉ ያሉ የፖለቲካ ተንታኞች ግን ሁለቱ መንግስታት የቃላት ጦርነት ውስጥ የገቡት በውስጣዊ አስተዳደራቸው የተፈጠረባቸውን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ለመጠምዘዝ እንደሆነ በስፋት አስተያየት ሢሰጡ ይደመጣሉ።

Federal police clash with residents in Afar

ESAT News

June 11, 2013

Following the assassination of Muhammad Kayeb, 20, by the Issa clan in the presence of Federal Police yesterday, the Afar people have been fighting with the Federal Police near Gewane Wlegeli, Afar, in Eastern Ethiopia. The shot out has continued until we entered the Studio.

The residents began the shooting because they believed that the Police were trying to generate conflict between the two people. ESAT had reported last week that the pastoralists of this same area were asked to give their weapons to the police but the police left the area and the clash was calmed. Residents state that the current clash is also linked to clashes of the previous week.

The extent of causality and death has not been established yet. ESAT’s attempt to speak with the officials of Afar has been unsuccessful.

Tuesday, June 11, 2013

‹መድረክ›| ያለፈው ሰልፍ ድራማ ሊሆን ይችላል – እኛም አቅደናል

ተቃዋሚዎች ሰላማዊ ሰልፉ “የኢህአዴግ ድራማ” ሊሆን ይችላል አሉ
Beyene Petros

ባለፈው እሁድ በሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪነት የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ፣ ከ97 ምርጫ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የተደረገ መሆኑን የሚናገሩት ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ ላለፉት ስምንት ዓመታት እንኳን ሰልፍ ስብሰባም ማካሄድ እንዳልቻሉ በመግለጽ፤ የእሁዱም ሰልፍ “የኢህአዴግ ድራማ ሊሆን ይችላል” በማለት እንደሚጠራጠሩ ገለፁ ፡፡ የኢህአዴግ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን በበኩላቸው፣ ህገመንግስቱን መሰረት ባደረገ መልኩ የሚፈፀሙ ሰላማዊ ሰልፎች እንደማይከለከሉና ድሮም የነበረ አሰራር መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የመድረክ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፤ እስከአሁን ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ይቅርና አዳራሽ ለመከራየት እንኳን ሆቴሎች የመስተዳድሩን ፈቃድ አምጡ እያሉ ሲያስቸግሯቸው እንደነበር ገልፀው፤ የሰሞኑ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍም ምናልባትም ከአፍሪካ ህብረት ጋር በተያያዘ ኢህአዴግ ያደረገው ጨዋታ ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡

“ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት እኛም ዕቅድ ይዘን እየተነጋገርን ነው” የሚሉት ፕ/ር በየነ፤ ኢቴቪ ሰልፉን መዘገቡን ብቻ በማየት መሻሻሉን ለማወቅ እንደማይቻል ገልፀዋል፡፡ “ኢቴቪም ቢሆን ድራማውን እየሰራ ይሆናል” በማለት ዘገባውን የሰራው አንዳንድ የሚያስወነጅሉ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ነው ብለዋል፡፡ “አላማቸውና መሻሻላቸው የሚታወቀው ወደፊት መቀጠሉ ሲታይ ነው” ብለዋል – ፕሮፌሰሩ፡፡ የመድረክ ምክትል ሊቀመንበርና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ዶ/ር መረራ ጉዲና በበኩላቸው፤ ሰላማዊ ሰልፉ መካሄዱ ችግሮችን ካልፈታ ልክ በአረብ አገራት ላይ እንደታየው አይነት ችግሮች ሊከሰት እንደሚችል ይናገራሉ፡፡ “የህዝብ ችግር እስካልተፈታ ድረስ ህዝብ አንድ ቀን በቃኝ ሊል ይችላል – መብቱ ካልተከበረለትና የሚበላው ካጣ ችሎ የሚቀመጥበት መንገድ የለም፡፡ ይሄ ህዝብ መብቱ እንዲከበርለት፣ ነፃነት እንዲያገኝ፣ በልቶ እንዲያድር ይፈልጋል፡፡ ኢህአዴግ ይህንን ችግር መፍታት ካልቻለ፣ ህዝቡ አሁንም “መሪውን ይበላል” የሚባለውን ሊተገብር ይችላል፡፡” የሚሉት ዶ/ር መራራ፤ እኛን አዳራሽ እየከለከሉ ለሌላው ሰላማዊ ሰልፍ የሚፈቅዱት የህዝብ ሙቀት ለመፍጠር በማሰብ ሊሆን ይችላል ብለዋል፡፡

“ምናልባትም የኢህአዴግ አዲስ አሰራር ከሆነ ይበል የሚያሰኝ በመሆኑ፣ በነካ እጁ ለመድረክና ለሌሎች ፓርቲዎችም እንዲፈቅድ ጥያቄያችን ነው” ብለዋል፡፡ አቶ ሬድዋን በበኩላቸው፤ ተቃዋሚዎች ሰልፍ ተከለከልን ማለታቸውን አይቀበሉትም፡፡ “በራሳቸው ምክንያት ሳይካሄዱ የቀሩ ካልሆኑ በስተቀር፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ በፊትም ነበር፤ አሁንም ተካሂዷል፡፡ ሃሳብን በነፃነት በአደባባይ ወጥቶ የመግለጽ መብት አዲስ አሠራር ነው ብለን አናስብም” ብለዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አዳራሽ ተከለከልን፣ ሰልፍ አልተፈቀደልንም የሚል ቅሬታ ያነሳሉ የሚሉት አቶ ሬድዋን፤ የአዳራሽ ጉዳይ የባለ አዳራሾች እንጂ የመንግስት አለመሆኑን ጠቅሰው፣ “መንግስት አዳራሽ አያከራይም፡፡ ለዚህኛው ፓርቲ አከራይ፣ ለዚህኛው አታከራይ የሚል ነገርም የለም” ይላሉ፡፡

በአደባባይ ሃሳብን በነፃነት የመግለጽና ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግን በተመለከተም፤ “ነፃና ክፍት በሆነ ሰዓትና ቦታ፣ ህጉን ጠብቀውና ፎርማሊቲውን አሟልተው እስካካሄዱ ድረስ የሚከለከሉበት ሁኔታ የለም፡፡ ከዚህ በኋላም አይኖርም” ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን በአዘጋገብ ላይ ያሳየውን ለውጥ በተመለከተ የተጠየቁት አቶ ሬድዋን፤ “ከዚህ በፊትም የማውቀው ኢቴቪ፤ ሁሉንም ወገን ለማናገር ጥረት ሲያደርግ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ሲያጋጥም የነበረው ግን ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ ኢቴቪ እንዳይመጣና እንዳይዘግብብን፣ ከዘገበም ሙሉውን እንዳይቀርጽብን የሚል አቋም እንደነበራቸው ነው፡፡ ተቋሙ የሚሰጣቸውን እድል ያለመጠቀም፣ አትግቡብን የሚል የራሳቸው የሆነ ችግር እንዳለባቸው ነው የማውቀው፡፡ የሆኖ ሆኖ ፕሮግራሙን የሚያየው ተመልካች የራሱን ፍርድ መስጠት ይችላል” በማለትም መልሰዋል፡፡

“መድረክ” ለሰኔ 17 ህዝባዊ ስብሰባ ሊጠራ ነው

ዋና ኦዲተርና የስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሰሞኑን ለፓርላማ ያቀረቡትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ በነገው ዕለት በመድረክ፣ በመኢአድ፣ በአንድነትና በሰማያዊ ፓርቲ ቢሮዎች የፓርቲዎቹ አመራሮች ውይይት እንደሚያደርጉና መድረክ ለሰኔ 17 ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚጠራ ተገለፀ፡፡

የመድረክ ስራ አስፈፃሚ አቶ አስራት ጣሴ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ የፓርቲዎቹ አመራሮች በነገው ውይይት የሚደርሱበትን የጋራ መግባባት በመያዝ፣ መድረክ ለሰኔ 17 ህዝባዊ ስብሰባ ለመጥራትና በአዲስ አበባ ከተማ በመዘዋወር የመኪና ቅስቀሳ ለማድረግ ተዘጋጅቷል፡፡ ሙስና የስርአቱ መገለጫ በሆነበት፣ የህዝብ ሃብት እየባከነና የዲሞክራሲ መብቶች እየተጣሱ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ መንግስት እምቢተኝነቱን ትቶ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ውይይት እንዲያደርግ ጥሪ እንደሚተላለፍለት ገልፀዋል፡፡ ገዢው ፓርቲ የሚቀርብለትን የውይይት ሃሳብ ተቀብሎ ወደ ውይይት ካልመጣ፣ 33ቱ ፖርቲዎች ሰላማዊ ትግሉን ተጠቅመው አገራዊ ንቅናቄ በማድረግ፣ እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዳቸውንም አስረድተዋል፡፡

Monday, June 10, 2013

በአፋር ፌደራል ፖሊሶች ከህዝቡ ጋር ሲታኮሱ ዋሉ

ሰኔ ፫ (ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በትናንትናው እለት የ20 አመቱ ወጣት የሆነው ሙሀመድ ካይብ የፌደራል ፖሊስ አባላት በቅርበት ባሉበት በኢሳዎች መገደሉን ተከትሎ፣ አፋሮች ገዋኔ ወለጌሊ እየተባለ በሚጠራ ስፍራ ከፌደራል ፖሊስ ጋር ዛሬ ሲታኮሱ ውለዋል። ስቱዲዮ እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ተኩሱ አለመቆሙን ለማወቅ ተችሎአል።

ነዋሪዎች በፌደራል ፖሊስ አባላት ላይ ተኩስ የከፈቱት ፣ ፖሊሶቹ ሆን ብለው ሁለቱን ብሄረሰቦች ለማጋጨት እየጣሩ ነው በሚል ምክንያት ነው። ከሳምንት በፊት በዚሁ አካባቢ የሚኖሩ አርብቶ አደሮች መሳሪያቸውን እንዲያስረክቡ በተጠየቁበት ጊዜ ተኩስ በመክፈታቸው ፖሊሶቹ አካባቢውን ለቀው መሄዳቸውንና ግጭቱ መብረዱን መዘገባችን ይታወሳል። ዛሬ የተፈጠረው ግጭት ባለፈው ሳምንት ከተካሄደው ግጭት ጋር እንደሚያያዝ ነዋሪዎች ይናገራሉ።

በግጭቱ ምን ያክል ሰዎች እንደቆሰሉ ወይም እንደሞቱ ለማወቅ አልተቻለም። በጉዳዩ ዙሪያ የአፋር ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

Sunday, June 9, 2013

አንድነት ፓርቲ የሰኔ 1 ሰማዕታትን በልዩልዩ ዝግጅቶች ዘከረ

ሰኔ 1 ቀን 1997 ዓ.ም በመንግስት ሀይሎች በግፍ የተጨፈጨፉ የሰላማዊ ትግል ሰማዕታትን ለመዘከር አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ዞን ያዘጋጀው መርሀግብር ትላንት ተካሄደ፡፡

 ቀበና አካባቢ በሚገኘው አንድነት ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት ሰማዕታቱን ለማሰብ በህሊና ፀሎት በተጀመረው በዚሁ መርሀ ግብር ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ሲሆኑ ከሳቸው በመቀጠል የአንድነት ፓርቲ አዲስ አበባ ዞን ሰብሳቢ አቶ ትዕግስቱ አወሉ ዕለቱን የሚመለከት ንግግር አድርገዋል፡፡

ከ300 በላይ ታዳሚዎች በተሳተፉነት በዚህ መርሀግብር ላይዕለቱን የተመለከቱ ግጥሞች በገጣሚ መላኩ ጌታቸው ቀርበዋል፡፡ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ነብዩ ኃይሉ ዕለቱን አስመልክቶ የነበረውን ትዕውስታ ለታዳሚው አካፍሏል:: የመርሀግብሩ አዘጋጆች ሰኔ አንድ በግፍ ከተገደሉ ዜጎች መካከል 42 የሚሆኑትን ስምና የአገዳደል ሁኔታ በመቀንጨብ አቅርበዋል፡፡ የታሳሪዋ ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ አባት አቶ አለሙ ጌቤቦ የመዝጊያ ንግግር ካደረጉ በኋላ በቅርቡ በማዕከላዊ ታስሮ ድብባና እስር ሲፈፀምበት በነበረው ወጣት ብርሀኑ ተክለያሬድ የተመራ የጧፍ ማብራት ስነስርአት ተካሂዶ መርሀግብሩ ተጠናቋል፡፡ 

Saturday, June 8, 2013

መድረክ ለሰኔ 17 ህዝባዊ ስብሰባ ሊጠራ ነው

መንግስት ለውይይት ካልተዘጋጀ 33ቱ ፓርቲዎች ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ አቅደዋል ዋና ኦዲተርና የስነምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሰሞኑን ለፓርላማ ያቀረቡትን ሪፖርት መነሻ በማድረግ በነገው ዕለት በመድረክ፣ በመኢአድ፣ በአንድነትና በሰማያዊ ፓርቲ ቢሮዎች የፓርቲዎቹ አመራሮች ውይይት እንደሚያደርጉና መድረክ ለሰኔ 17 ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚጠራ ተገለፀ፡፡

የመድረክ ስራ አስፈፃሚ አቶ አስራት ጣሴ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ የፓርቲዎቹ አመራሮች በነገው ውይይት የሚደርሱበትን የጋራ መግባባት በመያዝ፣ መድረክ ለሰኔ 17 ህዝባዊ ስብሰባ ለመጥራትና በአዲስ አበባ ከተማ በመዘዋወር የመኪና ቅስቀሳ ለማድረግ ተዘጋጅቷል፡፡ ሙስና የስርአቱ መገለጫ በሆነበት፣ የህዝብ ሃብት እየባከነና የዲሞክራሲ መብቶች እየተጣሱ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ መንግስት እምቢተኝነቱን ትቶ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ውይይት እንዲያደርግ ጥሪ እንደሚተላለፍለት ገልፀዋል፡፡ ገዢው ፓርቲ የሚቀርብለትን የውይይት ሃሳብ ተቀብሎ ወደ ውይይት ካልመጣ፣ 33ቱ ፖርቲዎች ሰላማዊ ትግሉን ተጠቅመው አገራዊ ንቅናቄ በማድረግ፣ እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማቀዳቸውንም አስረድተዋል፡፡
ምንጭ አዲስ አድማስ

Thursday, June 6, 2013

ወያኔ የፈጠረዉ የፍርሀት ድባብ ሲሰበር . . .

         
በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚደርሰዉ በደልና መከራ ወለደን ብለዉ ለትግል ጫካ የገቡት ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባ ገብተዉ ከተደላደሉ በኋላ በህዝብ መብትና ነጻነት፤ በአገር አንድነትና በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ህዝብ ብሄራዊ ጥቆሞች ላይ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችልና ከእነሱ በፊት ከነበሩት መንግስታት ጋር ሲተያይ እጅግ በጣም የከፋ በደል ፈጽመዋል እየፈጸሙም ይገኛሉ። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባ ገብተዉ የኢትዮጵያን መንበረ ስልጣን ከመቆጣጠራቸዉ በፊት ዕቅድ አዉጥተዉና ተዘጋጅተዉ የመጡት የኢትዮጵያን ህዝብ በዘር፤ በሐይማኖትና በክልል በመከፋፈል በጠመንጃ ኃይል የያዙት ስልጣን በግዜና በህገመንግስት ያልተገደበ መሆኑን ለማረጋገጥና የእኛ ነዉ ለሚሉት የህብረሰተብ ክፍልና ለሚተባበሯቸዉ ሆዳሞች ተቆጥሮ የማያልቅ ሀብት ማጋበስ የሚችሉበትን መንገድ ለመፍጠር ነዉ። የወያኔ መሪዎች ይህንን አገራዊ በደል ያለምንም ተቃዉሞ መፈጸም እንዲችሉ ከአገሩ ይልቅ የተወለደበትን ክልል ብቻ፤ ከብሔራዊ አንድነቱና አጋራዊ ጥቅሙ ይልቅ የራሱን ጥቅም ብቻ የሚመለከትና የእነሱን ኃይለኝነትና የተለየ ጀግንነት እየሰበከ የሚኖር በፍርሀት የተሸበበ ፈሪ ትዉልድ ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።

የወያኔ ክፋት፤ ዘረኝነትና “ልማት” በሚል ሽፋን የተደበቀ አገር የማፍረስ ሴራ ከወዲሁ የገባቸዉ የኢትዮጵያ የቁርጥ ልጆች ከ1997ቱ ምርጫ በፊትም ሆነ በኋላ የወያኔን ገመና ለማጋለጥና የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ፤ ለነጻነቱና ለእኩልነቱ እንዲታገል ለማድረግ እንደሻማ እየቀለጡ ብርሀን ሆነዉ አልፈዋል። ይህ የዕልፍ አዕላፋት የትግል መስዋእትነትና ምሳሌነት ፍሬ እያፈራ መጥቶ በላፈዉ እሁድ ግንቦት 25 ቀን የተካሄደዉንና ወያኔ ከሃያ አመታት በላይ ሲቋጥር የከረመዉን የፍርሀት መቀነት የበጠሰ እጅግ በጣም የሚያበረታታ ትዕይንተ ህዝብ እንዲደረግ አስተዋጽኦ እድርጓል፡፡ ይህ ባለፈዉ እሁድ የተካሄደዉ ሰላማዊ ሰልፍ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያስተባብሩት፤ አቅጣጫ የሚያሳዩትና ጉያዉ ዉስጥ ገብተዉ እያበረታቱ የሚመሩት መሪዎችን ካገኘ እንኳን ምንም አይነት ህዝባዊ መሠረት የሌለዉን ወያኔን የመሰለ ፀረ ህዝብ ሃይል ቀርቶ ለማንም የማይበገር ህዝብ መሆኑን ያስመሰከረ ሰልፍ ነዉ።

በሰማያዊ ፓርቲ የተጠራዉና የብዙ ኢትዮጵያዉያንን ይሁንታ ያገኘዉ የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ወያኔ ያስረናል ወይም ይገድለናል እየተባለ አላግባብ እየተፈራ በቀጠሮ ሲተላለፍ የቆየዉን ህዝባዊ ትግል ከፍርሀትና እንደ ገመድ ከረዘመ ቀጠሮ ዉስጥ በጣጥሶ ያወጣና የህዝብን የትግል መንፈስ ያነቃቃ ሰላማዊ ሰልፍ እንደነበር በሰልፉ ላይ የታየዉ የህዝብ ስሜትና ለኢትዮጵያ ህዝብ የተላለፉት መልዕክቶች በግልጽ ይናገራሉ። ባለፈዉ እሁድ በተደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የታየዉ ህዝብዊ መነሳሳት ሊበረታታ የሚገባዉና እንዲሁም በአገር ዉስጥና በዉጭ አገር የሚገኙ ኢትዮጵየዉያን የመብትና የነጻነት ትግላቸዉ አካል አድርገዉ ሊቀላቀሉት፤ ሊረዱት፤ሊተባሩትና ህዝባዊ ትግሉ የሚጠይቁዉን አመራር ሊሰጡት የሚገባ እጅግ በጣም አበራታች ጅምር ነዉ። ለትግልና ለመስዋዕትነት ዝግጁ የሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ያጣዉ መሪ ነዉ እያልን አግባብ የሌለዉ ጩከት ከመጮህ ይልቅ አገራችንን የምንወድ የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ መሪዎችን በትግል ሂደት ዉስጥ የምንፈጥረዉ እኛዉ እራሳችን መሆናችንን ተረድተን ይህንን የሚያበረታታ ተስፋ የሰጠንን ሰላማዊ ሰልፍ የምናጠናክርበትንና ተከታታይነት ኖሮት ብዙ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚያካትትበትን መንገድ ልንቀይስ ይገባል።

የኢትዮጵያ ህዝብ አሁንም ቢሆን ለመብቱ፤ለነጻነቱና ለአንድነቱ ማናቸውንም አይነት መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ባለፈዉ እሁድ በግልጽ አሳይቷል። አሁን የሚቀረዉ ህዝባዊ ትግሉን የመምራት ታሪካዊ ሀላፊነት የወደቀበት የህብረተሰብ ክፍል ጨርቄን ማቄን ማለቱን ትቶ ወቅቱ የሚፈልገዉን የትግል አመራር መስጠት ብቻ ነዉ።

ዘረኛዉ የወያኔ አገዛዝ አንዴ የታጠቀዉን ጠመንጃ በመጠቀም ሌላ ግዜ ደግሞ ፓርላማዉንና የህግ ተቋሞችን ተጠቅሞ ተቃዋሚ ኃይሎችን የሚያጠፋ ህግ በማዉጣት የኢትዮጵያን ህዝብ የፍትህና የነጻነት ፍላጎት ለማፈን ብዙ ጥሯል፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ እራሱን “ተራሮችን ያንቀጠቀጠ” ትዉልድ ብሎ በመጥራት ህዘብ በፍርሃት ጨለማ ዉስጥ እንዲኖር ለማድረግ ብዙ ታግሏል።
ቆራጡ የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ስድቡን፤ ንቀቱን፤ እስራቱን፤ግድያዉንና ስደቱን እንዳመጣጡ መክቶ በፍርሀት ዉስጥ የማይኖር ህዝብ መሆኑን ባለፈዉ እሁድ ለወዳጁም ለጠላቱም በግልጽ አሳይቷል። ይህ እሁድ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓም አዲስ አበባ ዉስጥ የታየዉ የትግል መነሳሳት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች በማቀፍ ወያኔና በጠመንጃ ኃይል የመሰረተዉ ዘረኛ ስርአቱ እስከተወገዱና ኢትዮጵያ ፍትህ፤ ነጻነትን ዲሞክራሲ የነገሱባት ምድር እስክትሆን ድረስ መቀጠል ይኖርበታል፤ ይህንን ለማድረግ ደግሞ በአገር ዉስጥና በዉጭ አገር የሚኖረዉ ኢትዮጵያዊ እንደ አንድ ሰዉ ቆሞ መታገል ይኖርበታል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ (መንግስት ለሕዝብ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሰጥ አሁንም እንጠይቃለን!)

Blue Party Ethiopia
ሰማያዊ ፓርቲ

ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ታላቅ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም በርካታ ሕዝብ በተገኘበት ደማቅ ሆኖ ተካሂዷል፡፡ ለዚህ ሰልፍ መሳካት ከፍተኛ ድጋፍና አስተዋፅኦ ላደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የመገናኛ ብዙኃንና በሰልፉ ለተሳተፉ ዜጎች እንዲሁም ሰልፉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለረዱ የፀጥታ ኃይሎች ፓርቲያችን ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

ከዚህ በተቃራኒ ግን ይህንን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ ተከትሎ የገዥው ፓርቲ ባለስልጣናትና የመንግስት ተወካዮች የተለመደውን ተልካሻ አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ የገዥው ፓርቲ ተወካይ ሰልፉን አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት “የሐይማኖት አክራሪነት አጀንዳው አድርጎ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ድብቅ አጀንዳው ገሃድ ወጣ” በማለት በሰጡት አስተያየት ፓርቲውን ለማንቋሸሽና ለማራከስ ሞክረዋል፡፡

 ይህም ፓርቲውን በእጅጉ ያስቆጣ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ መሰረተ ቢስ ፍረጃ የገዥው ቡድን አባላት ለንግግራቸውና ለሚሰጡት አስተያየት ሚዛን የሌላቸው ከመሆኑ ውጭ በፓርቲው ፕሮግራምም ሆነ እንቅስቃሴ ከአሸባሪነት ጋር የሚያገናኘውን አንዳችም ነገር አልጠቀሱም፡፡ ፓርቲው በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ እና በሕገ መንግስቱ በተሰጠው መብት ተጠቅሞ በሕጋዊ ሥነስርዓት ያደራጀውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በእንዲህ አይነት መንገድ መፈረጅ ሰልፉ ከተጠራበት ዓላማና መንፈስ በእጅጉ የራቀ አስተያየት ሆኖ አግኝቶታል፡፡

ፓርቲው ከዚህ በፊትም በተደጋጋሚ በሰጣቸው መግለጫዎች በእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ የሚደረገውን ጣልቃ ገብነት መቃወሙ ይታወሳል፡፡ ይህንኑ ጥያቄ በተቃውሞ ሰልፉ ላይ ወደ አደባባይ ይዞ መውጣቱ ሕገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄ መሆኑን ይገነዘባል፡፡ ከባለሥልጣኑ የተሰጠው አስተያየት ግን የእስልምና ሐይማኖት ተከታይ ዜጎች በሰላማዊ መንገድ የተቃውሞ ጥያቄ ማቅረባቸውን ገዥው ፓርቲ በበጎ ጎን አለማየቱንና የመብት ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ሁሉ ወደ ሽብርተኝነት ፍረጃ ለመክተት የሚያደርገውን ጥረት የሚያመላክት ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ በተጨማሪም ገዥው ፓርቲ የእስልምና እምነት ተከታዮችን ኢትዮጵያውያን ዜጎች እንደሆኑ አድርጎ እንደማያያቸውም ሰማያዊ ፓርቲ ተገንዝቧል፡፡

የመንግስት ተወካይ የሆኑት ባለስልጣን በበኩላቸው በሰጡት አስተያየት በሰላማዊ መንገድ ተጠይቆና ታውቆ መንግስት ራሱ ያመነውና እጅግ ሰላማዊ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ እንዲካሄድ ያደረገን ፓርቲ ውጭ የሚገኙ ኃይሎች ተላላኪ አድርጎ ማቅረብ የአብዬን ወደእምዬ እንደሚባለው መሆኑን እየገለፅን ይልቁንም በሕጋዊ መንገድ ተመዝግቦ የሚንቀሳቀሰውን ፓርቲያችንን መንግስት ከልቡ ሊቀበለው እንዳልቻለ አስገንዝቦናል፡፡ በተጨማሪም ይህ አባባል ሰማያዊ ፓርቲን የማይመጥን፤ ፓርቲውም በተግባር እያሳየ ያለውን ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚጥስ በመሆኑ አጥብቀን እናወግዘዋለን፡፡ እኝሁ የመንግስት ባለስልጣን በሰላማዊ ሰልፉ የተላለፉት መልዕክቶች ህገ መንግስቱን የሚንዱ ናቸው በማለት በደፈናው ህዝብን ለማታለል ከመሞከራቸው በተለየ የትኛው ሃሳብ የትኛውን የሕገ መንግስት ድንጋጌ እንደሚፃረር ካለማመልከታቸውም በላይ ፓርቲው በፍርድ ቤት ጉዳይ ጣልቃ እንደገባ አድርጎ ለማሳየት መሞከር የመንግስትን ግብር ለሰማያዊ ፓርቲ መስጠት ከመሆኑም ሌላ ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ያደርገዋል፡፡

በመጨረሻም የእስልምና እምነት ተከታይ ዜጎቻችን ማንኛውንም የመብት ጥያቄ ከሌሎች ወገኖቻቸው ጋር በሰላማዊ መንገድ የማቅረብ ሕገ መንግስታዊ መብታቸው መሆኑን መንግስትም ሆነ ገዥው ፓርቲ እንዲያውቀው እያሳሰብን፤ ሰማያዊ ፓርቲ ከመንግስትም ሆነ ከገዥው ፓርቲ በሚሰጥ ማንኛውም ማስፈራሪያ ከጀመረው የሰላማዊ ትግል ጉዞ ፍፁም ወደ ኋላ እንደማይል፤ ይልቁንም የተነሱትን የሕዝብ ጥያቄዎች መንግስት በሦስት ወራት ውስጥ ምላሽ እንዲሰጥ አሁንም በድጋሚ ማሳሰብ እንፈልጋለን፡፡
ግንቦት 29 ቀን 2005 ዓ.ም
አዲስ አበባ

በግብጽ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው

በዛሬው እለት ለማለዳ ታይምስ ቅርበት ያላቸውን ወገኖች እንዳነጋገርናቸው ከሆነ በግብጽ መንግስት ክፉኛ የሆነ ክትትል እየተደረገብን ነው
እኛ ምንም አቅም የለንም በስራም በኩል ሆነ በጎዳናዎች ላይ ህብረተሰቡ ጥላቻውን አድርቶብናል ፣በተለያዩ ካፍቴሪያዎች ወንድሞቻችን እና
እህቶቻችን ተደብድበዋል በማለት ስሜታቸውን የገለጹት በተለይም በአሁኑ የኢትዮ-ግብጽ አጣብቂኝ ሁኔታ ሁላችንንም ውስጥ በመከራ
ከቶናል ሲሉ ተናግረዋል ።
በግብጽ የሚገኘውም የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ማናቸውንም ዜጎች ለጊዜው ኢትዮጵያዊ ነኝ ብለው እራሳቸውን ለአደጋ
እንዳያጋልጡ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ጠቁመዋል ።
በአባይ ግድብ ምክንያት እና መስመሩን በመቀየሱ ምክንያት ውጥረቱን ማየሉን
አስመልክቶ የተለያዩ የውጭ ዜጎችም ለውጭ ዜጎች ለግብጽ ማስጠንቀቂያ እሰጡ ቢሆንም ፣ በሌላም በኩል ደግሞ የኢትዮጵያ ኤምባሴ
በግብጽ ሰራዊት መከበቡን ከስፍራው የደረሰን ዘገባ አረጋግጦአል ። ይህ በእንዲህ እንዳለ ዜጎችን የማዳን እና ካሉበት ስፍራ ወደ ተሻለ ሁኔታ
ለማኖር የሚያስችለውን ተግባር የማድረግ ጥረት እንዲደረግ ርብርቦሹ እንዲጠናከር የማለዳ ታይምስ መረጃ ማእከል ይመክራል።

Wednesday, June 5, 2013

በጦርነቱ ሰበብ በተዘረፈ ሐብት የሕወሃት ጄነራሎች ሚሊየነር ሆነዋል፡፡

ማን ያውራ የነበረ…….ማን ያርዳ የቀበረ……”

 “….የጦር መኮንን ሆነህ እንደባለሙያ ስታየው ውጊያው በጥቅሉ የሙያ ብቃት ያልታየበት አሳፋሪ ጦርነት ነበር ማለት ይቻላል፡፡በጃንሆይ እና በደርግ ዘመን ኤርትራ ላይ ውጊያ ተደርጎ የተሰዋው ዜጋችን ቁጥር ከ250 ሺ እስከ 300 ሺ ይደርሳል፡ከዚህ አንፃር ወያኔ በአንድ ዓመት ውስጥ ኤርትራ ላይ ያስፈጀው የወታደር ቁጥር በጣም አሳፋሪ ነው፡፡ከመከላከያ የሰው ኃይል አስተዳደርና ልማት መምሪያ ሰነዶች ያገኘሁት መረጃ እንደሚያሳየው በጠቅላላ በኢትዮ ኤርትራ ውጊያ 98,700 ወታደር ሲሞትብን 194¸300 ቁስለኛ ተረክበናል፡፡

ከኦርዲናንስ እዝ ያገኘሁት መረጃ ደግሞ መጀመሪያ ለውጊያ ከተዘጋጀው ከባድ መሳሪያ 2ሐ3ኛው መውደሙን ነግረውኛል፡፡ ይህንን ትርጉም አልባጦርነት የመሩት መሪዎች ሰዓረ መኮንን፣ ሳሞራ የኑስ፣ዮሀንስ ገብረመስቀል፣ታደሰ ወረደ፣ኳርተር /አብርሃ ወልደማርያም/፣ ብርሃነ ነጋሽ የተባሉት ጄነራሎች ናቸው፡፡ የጦርነቱ ማዕከላዊ እዝ አባላት ደግሞ መለስ ዜናዊ፣ ስዬ አብርሃ፣ ተወልደ ወልደማርያም፣ አለምሰገድ ገብረአምላክ፣ ተፈራ ዋልዋ፣ ፃድቃን ገብረትንሳኤ እና ክንፈ ገብረመድሕን ነበሩ፡፡

 ያ ሁሉ ዜጋ ያለቀበትና ያ ሁሉ የሀገር ሀብት የወደመበት ጦርነት ከጦርነት አመራር ችግር መሆኑ በግልፅ እየታወቀ አንድም የጦርነቱ መሪ ተጠያቂ ሳይሆን እንዲሁ መቅረቱ በጣም ያሳዝናል፡፡…….”
ኮሎኔል አለበል አማረ

 የአጋዚ ኮማንዶ አመራር አባል የነበሩ እና በግንቦት 7 መፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተጠርጥረው ዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት የተፈረደባቸው

 ሌላኛው ኮሎኔል ደግሞ እንዲህ ይሉናል፡

“……የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ለጦርነቱ መሪዎች የሐብት ምንጭ ሆኖ ማገልገሉን ማየት ችያለሁ፡፡ በጦርነቱ ሰበብ በተዘረፈ ሐብት የሕወሃት ጄነራሎች ሚሊየነር ሆነዋል፡፡ ፃድቃን፣ ጀቤ፣ ብርሃነ ነጋሽ፣ ገዛኢ አበራ፣ አባዱላ ገመዳ፣ አበባው ታደሰ፣ ባጫ ደበሌ፣ ታደሰ ወረደ፣ ሰዓረ መኮንን፣ እና ሌሎችም ጄነራሎች በአዲስ አበባ በባህርዳርና በመቀሌ ያስገነቡት ቪላና ፎቅ ውበቱ አይንን ያፈዛል፡፡ የቤት እቃዎቻቸው፣ ምንጣፎቹ፣ መብራቶቻቸውና ኮርኒሶቻቸው በውድ ዋጋ ከአውሮፓ እየተጫኑ የመጡ ናቸው፡፡ የመጨረሻውን ቴክኖሎጂ እየተጠቀሙ ለቪላዎቻቸው ማሞቂያና ማቀዝቀዣ ተክለውላቸዋል፡፡ ከዚያ ሁሉ እልቂት በኋላ ጄነራሎቹ በቀጥታ ወደ ሃብት ፉክክር ነው የገቡት፡፡ የሚፈሰው ገንዘብ በጦርነቱ ወቅት የተዘረፈ ነው፡፡ …..”
ኮሎኔል አበበ ገረሱ
ጎበዝ የአበበችን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም ይባላል፡፡ በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ለሀገራቸው ዳር ድንበር መከበር ሲሉ በኢትዮጵያዊነት የሀገር ፍቅር ስሜት ግን ደግሞ የወያኔን መሰሪ ባህርይ ባለመረዳት ውድ ሕይወታቸውን መስዋዕት ያደረጉት የነ በረከት፣ አባዱላ፣ ስዩም፣ አዲሱ እና ከላይ ያየናቸው ጄነራሎች እና የወያኔ ባለስልጣናት ልጆች አልነበሩም፡፡ የምስኪኑ ደሃ ኢትዮጵያዊ ልጆች እንጂ፡፡ ለዚያውም እኮ ያ ሁሉ ጀግና ወታደር ያለቀበት መሬት በጀርባ በተደረገ ስምምነት የኢዮጵያን ሕዝብ አጭበርብሮ ለወራሪው ሃገር እንዲመለስ አድርጓል፡፡ እነዚህ መስዋዕት የሆኑ ልጆቻችን ግን ለቤተሰባቸው መርዶ ማድረስ ቀርቶ ለአንድ ደቂቃ እንኳን የሕሊና ፀሎት እንዲደረግላቸው ያስታወሰ አንድም የወያኔ ባለስልጣን የለም፡፡ ባጭሩ ወያኔ ድሃውን ኢትዮጵያዊ የሚያየው ልክ እንደ ኮንደም ነው፡፡ በአፀያፊ ሁኔታ ይጠቀምባቸውና እንደ ቆሻሻ ይጥላቸዋል፡፡

 ይኸው አሁን ደግሞ ግብፅ፤ ልትወረን ነው በማለት የጦርነት ነጋሪት እንደለመደው እያስጎሰመ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በታሪኳ ከግብፅ ጋር ባደረገችው ጦርነት አንድም ጊዜ ተሸንፋ አታውቅም፡፡ ይኸውም የአባቶቻችን ወኔ እንዳለ ሆኖ በዋናነት የጦር መሪዎቹ አመራር ወሳኝ ነበር፡፡ ዘንድሮ ግን የዚህ ዓይነት ጄነራሎችን ይዘን ወደ ጦርነት ብንገባ ዳግም ድሃውን ኢትዮጵያዊ ማስጨረስና ለወያኔ ጄኔራሎች የሐብት ዝርፊያ መመቻቸት መስሎ ይታየኛል፡፡ በዋናነትም የወያኔ የሰሞኑ ልፍለፋ እንደለመደው የሀገር ውስጥ ችግርን ለማስቀየስ የሸረበው አዲስ ተንኮል እንጂ ከልቡ ለአባይና ሀገር ተቆርቋሪ ሆኖ በማሰብ ነው ብዬ በግሌ አምናለሁ፡፡ ከዚህ በኋ በወያኔ ቆስቋሽት በሚነሳ ጦርነት የአንድም ኢትዮጵያዊ ደም መሬት ላይ ይፈስ ዘንድ ፈፅሞ አልሻም፡፡

አባይ ቢገደብ በጣም ደስ ይለኛል ከሁሉም በላይ ደግሞ ወደ ውጭ ሀገር በመሰደድ ላይ ያለው የሀገሬ የተማረ ሰው ፍልሰት ቢገደብ እንዲሁም ከአባይ የበለጠ ሀገርን ሊያሳድግ የሚችል ፈጠራና ግኝቶችን ማውጣት የሚችለው የሰው ልጅ ሕይወትና ሕሊና በአባይ ሰበብ መስዋዕት ይሆን ዘንድ ተገቢ ነው ብዬ አላምንም፡፡

 ደብተራው ፀጋዬ

Breaking News: Armoured Vehicles Surround Ethiopian Embassy In Cairo

Awramba Times – The Ethiopian embassy in Cairo is surrounded by heavily armed personnel and armoured vehicles. Ethiopian citizens, both refugees and Ethiopian-passport holders, are savagely harassed and beaten by ordinary Egyptians and the police everywhere they move.

According to our sources, it is very difficult for Ethiopians to move around and many people are starving as they fear for their life to go out and buy foodstuff and drinking water. Egyptians are preparing a massive demonstration against Ethiopia to be held next Friday.

On the other hand, Ethiopian Ambassador to Egypt Mohamed Dirrir met with Egyptian opposition leader and former Secretary General of the Arab League, Amr Moussa in Cairo today. Ambassador Mohamed Drirr has a two hours meeting with Amr Moussa on the recent developments on the Nile and has made clear that Ethiopia has no any intention of harming egypt or affecting its access to the Nile waters.

source: awrambatimes.com

EPRDF going bankrupt due to few readerships: Document

ESAT News    June 3, 2013
  
The ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) has said that it was going bankrupt due to lack of readership of its Party Organ newspapers and magazines.

 Although the Front attempted to change the contents of its Abiyotawi Democracy newspaper and Addis Raeye magazine, both the leadership and members are not willing to read. Abiyotawi Democracy is mainly produced for farmers and those with primary education while Addis Raeye is prepared for members with advanced education.

This was revealed in a document that ANDM, member party of the EPRDF, prepared for its senior and mid level leadership titled “the evaluations of the 10th Organizational Congress: Decisions and Future Directions”. The 43 page document explains the problems that both ANDM and EPRDF have faced.

The document states that many members join the ruling party with the aim of finding jobs and other benefits but as they fail to succeed in that, they leave the party. Although many members have been recruited in the rural areas, they are only good at helping themselves than leading, supporting and empowering others. In cities, the document states, very few people working in small and micro business, the civil service and educational institutions have been recruited and those few have many limitations in their allegiances.

It stated that although Abiyotawi Democracy offers analytical articles few members pay attention to it, feel unhappy to purchase copies and deliberate on them. Similarly, the report said little attention has been given to the biannual magazine, Addis Raeye. The main problem, the report said, is within “the leadership”. Problems in distribution, participation and quality were mentioned as the shortcomings of the magazine.

The document said that the leadership and members of the Front seriously lack theoretical, reading culture, political and ideological knowledge.

According to the report, poor leadership is the basic cause of poverty, bad governance and social problems in the Amhara region particularly

ESAT Daily News Amsterdam June 04, 2013 Ethiopia