Saturday, February 14, 2015

ወያኔ ከትግራይ ተወላጆች ተቃዉሞ ገጠመዉ፡፡

February 14,2015
Supporters of the ruling EPRDF party and PM Zenawi chant slogans after he addressed them at the Meskel Square in Addis Ababa
በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ካድሬዎች ለትግራይ ተወላጆች ብቻ ባካሄዱት ስብሰባ ላይ ተቃውሞ እንዳጋጠማቸው ምንጮቻችን አስረድተዋል፣ ጥር 24 /2007 ዓ/ም በአራዳ ክፍለ ከተማ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ… ካድሬዎች ተላላኪ የሆነው ይርጋ የተባለ የትግራይ ተወላጅ የትግራይ ተወላጆችን ብቻ በመስብሰብ ለምን ተቃዋሚ ድርጅቶችን ትደግፋላችሁ፥
ተቃዋሚ ድርጅቶች ከፀረ ሰላም ሃይሎች ጋር ግንኙነት አላቸው በቅርቡ እንኳን የሰማያዊና የአንድነት ድርጅቶች አምስት ፖሊሶችን ደብድበውብናል ስለዚህ አትደግፏቸው እያለ መናገር በጀመረበት ጊዜ ህዝቡ በበኩሉ ፖሊሶቻችን ተደብድበውብን ከማለት ይልቅ ለምን በፖሊስ የተደበደቡትን ወገኖቻችን የማትናገሩላቸው አይደለም አንተ ሃላፊህ እንኳን አይፈታውም ሊፈታው አይችልም ይሄ ደግሞ ያንተ አቅም ስላልሆነ ከአቅምህ በላይ አትናገር እንዳሉት ታውቋል፣ 
ተሰብሳቢዎች ጨምረውም ቅንና ቢኖርህ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው በሆስፒታል ስለሚታከሙት ከ11 በላይ ንፁሃን ሲቪል ዜጎች እና አፍናችሁ ስለወስድዋቸው በተናገርህ ነበር ያለአቅምህ መልዕክት ይዘህ ልታታልለን አትሞክር የሚል ሃይለኛ ተቃውሞ እንዳጋጠመው ለማወቅ ተችሏል::

No comments: