Wednesday, February 18, 2015

የግዳጅ ሰልፍ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ( በፎቶ ግራፎች የተደገፈ )

ቢንያም ግዛው ( ኖርዌይ ኦስሎ)

ምርጫው በተቃረበበት በዚህ ወቅት ገዢው ብድን ወያኔ በተለያዩ መንግስታዊና የግል ተቋማት እንዲሁም የእምነት ቤቶች ውስጥ እጁን በማስገባት ያለ ህዝብ ፈቃድ ዜጎችን ማስፈረም እና በግዳጅ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲወጡ ማድረጉን በይበልጥ አፋፍሞታል።

ትላንት መቀሌ ከተማ በሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ተማሪውን ያለፍላጎቱ በማስገደድ እንዲሰለፍ በተሰጠው መመርያ መሰረት ሁሉም የተሰጠውን ችቦ በመያዝ ቀኑን ሁሉ ከትምህርት ገበታቸው ላይ ተስታጉለው ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት ያለፍላጎታቸው በማስገደድ በሚደረገው ሰልፍ ላይ የህ ወ ሀ ትን የምስረታ 40 ኛ ዐመት በዐል በሚል አላማ ተማሪዎቹ የሚተባበሩ እና የሚያከብሩ በማስመሰል ድራማ ሲያሰሩዋቸው ቆይተዋል።

          በትላንትናው ውሎ በተለምዶ የተማሪዎቹ የካፌው አሰራር የቁርስ ግዜያችውን የሚያስተናግደው በኢትዮጵያ ሰዐት አቆጣጠር ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 2፡30 ሲሆን ይህን አሰራር በመቀየር እና በማን አለብኝነት ለሊቱ ወደማብቂያው ገደማ 9፡30 ተጅምሮ 10፡30 ድረስ ለቁርስ ያልተገኘ ተማሪ መመገብ ሳይችል እንደሚቀር ለህዳሴ ካፌው ከባለስልጣናቱ በተላለፈው ማስጠንቀቂያ መሰረት በለሊት ቁርሳቸውን እንዲበሉ ተገደዋል።
           ይህም ተማሪዋች ወደ ግዳጅ ሰልፉ ማልደው በቶሎ እንዲዘጋጁ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን ሁሉም በዚህ ጥሪ ላይ የመሳተፍ ግዴታው እንደሆነ በማስጠንቀቂያ መልዕክቱ ተላልፏል። ተማሪው ሳይፈልግ እና የራስ ተነሳሽነት በጎደለው መልኩ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ ወያኔዎቹ ይህንን የማን አለብኝነት ትዕዛዝ ሲያስተላልፉ ሀገሬውን እንደፈለጉ በጠመንጃ አፈሙዝ ግድ እንደሚሉት ሁሉም ሊይውቀው ይገባል ።

            እንዲህ የሚመሳስሉ መረን የለሽ ግፍ እየተፈጽመበት በአይነ ቁራኛ የሚጠበቀው የኢትዮጵያ ህዝብ በረዥም የጭቆና ሰንሰለት ተሸምቅቆ ከወያኔ ፍላጎት ውጪ በሚያደረገው እንቅስቃሴ ታላቅ አፈና እና ግድያ ፊትለፊቱ ተጋርጦበት የተባለውን ብቻ የሚፈጽም ተደርጓል ።

ስለዚህም በግፍ አገዛዙ በአለም ሁሉ የሚታወቀው አምባገነኑ ወያኔ በሃገራችን ላይ እያደረሰ ያለውን ግፋዊ ስርዐት እና ሃብትን ያለአግባብ መዝረፉን፣ ማስገደዱንም ፣ ግድያውንም በቃኝ ጠግቢያለሁ ስልማይል በተባበረ ህዝባዊ አመጽ በቃህ ሊባል ይገባዋል።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
biniamgizaw@gmail.com























       



No comments: