Monday, February 9, 2015

ወያኔ አንዳርጋቸው ጽጌን ለመጎብኘት ለጠየቁ የእንግሊዝ ፓርላማ አባላትን ፈቃድ ከለከለ::

February9,2015

- የወያኔ ባለስልጣናት የእንግሊዝ የፓርላማ ቡድን ልኡካን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን እንዳይጎበኙ ፈቃድ መከልከላቸውን ከሎንዶን ተሰማ::አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በወያኔ ከየመን ሰንአ አየር መንገድ ታፍነው በአዲስ አበባ የተለያዩ የማሰቃያ ቦታዎች ከፍተኛ ቶርች ሲፈጸምባቸው ቆይቶ በዚህ ሳምንት ወደ ቃሊቲ እስር ቤት እንደተዘዋወሩ ተጠቁሞ ነበር::
በጀርሚ ኮርቢን የሚመራው የእንግሊዝ የፓርላማ ቡድን ልኡካን ወደ ኢትዮጵያ በመሄድ አቶ አንዳርጋቸው የሚለቀቅበትን ጉዳይ ለመነጋገር እቅድ አድርገው የነበረ ቢሆንም በእንግሊዝ የወያኔ ኤምባሲ አምባሳደር ብርሃኑ ከበደ ከሎንዶን ከልኡኩ ጋር ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ ጉዞው እንደተሰረዘ ታውቋል::
ወደ አዲስ አበባ ሄደን አንዲን ለመጎብኘት በሚቀጥለው ሳምንት ያሰብነው ጉዞ በባለስልጣናት እውቅናና ፍቃድ ባለማግኘቱ ልንሰርዘው ተገደናል ሲሉ የልኡኩ መሪ ተናግረዋል::ሎርድ ዶላኪያ በእንግሊዝ ፓርላማ የፓርቲዎች ሕብረት የኢትዮጵያ ጉዳይ ምክትል ሊቀመንበር ከሚስተር ኮርቢን ጋር ሊያደርጉት ያሰቡት ጉዞን አስመልክቶ አለመፈቀዱን ተቃውመውት ግልጽ የሆነ ሂደት እንዲኖር የጠየቁ ሲሆን የአቶ አንዳርጋቸው ጠበቃ ክሊቭ ስታፎርድ ስሚዝ አንዳርጋቸውን እንዲጎበኙ እንዲፈቀድ አጥብቀው የጠየኡ ሲሆን በዚህ ሳምንት ጉዳዩን በፓርላማ እንደሚያነሱት ገልጸዋል::
የአቶ አንዳርጋቸው ባለቤት ወይዘሮ የምስራች ሃይለማርያም በእንግሊዝ የሚገኘውን የወያኔ ኤምባሲ እና አምባሳደር በሰብአዊ መብት ገፈፋ የሚያደርጉ አለቆቻቸው የገደል ማሚቱ ሆነው ያገለግላሉ ሲሉ ተችተዋል::በለንደን ዳውን ስትሬት የሚከበረው የአቶ አንዳርጋቸው የ60ኛ አመት የልደት በአል ለማክበር እና አቶ አንዳርጋቸው እንዲፈቱ የተሰበሰበውን ፊርማ ለጠቅላይ ሚኒስትር ካሜሮን ይሰጠሉ::ከዚሁ ጋር በተያያዘ የእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቶብሊስ ኢልውድ የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ ንዝህላል መሆናቸውና በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ላይ አለማንሳታቸው ቃላቸውን በማጠፋቸው ተጠያቂ እንዲሆኑ ያደረጋቸው ሲሆን ባለፈው ወር በእንግሊዝ ውጪ ጉዳይ ዲፕሎማቶች መካከል ከፍተኛ አተካሮ ፈጥሮ እንደነበር ይታወሳል::የእንግሊዝ ውጪ ጉዳይ ቃል አቀባይ እንዳሉት የኢትዮጵያ ባለስልጣኖች የፓርላማ አባላቱን የጠበቃውን እና የአማካሪእን ጉብኝት መከልከላቸው አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን አስምረውበታል::
ሚኒሊክ ሳልሳዊ

No comments: