Wednesday, December 10, 2014

መልዕክት ጨርቆስ ፖፖላሬ ከሚገኙ እስረኞች

December 10,2014
ትግላችን በመደገፍ በተለይም በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት የደረሰብንን የህወሓት/ኢህአዴግ ጭካኔያዊ እርምጃ በመቃውም ከጎናችን ለቆማችሁ በዓለም ዙሪያ የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ምስጋናችን እናቀርባለን፡፡ በሰልፉ ወቅት ድብደባን ጨምሮ የደረሰብን በደል በመቃወም በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ሰላማዊ ሰልፍ መውጣታችሁን ሰምተናል፡፡ ትግላችን በመደገፍና ከጎናችን በመቆማችሁ ምስጋናችን ላይ ያለ ነው፡፡ ወደፊትም ከጎናችን እንደምትቆሙ እንተማመናለን፡፡ 

በእኛም ላይ ሆነ በየ እስር ቤቱ የሚገኙት የትግል ጓዶቻችን ላይ የሚደርሰው ግፍና ጭካኔ ያሳስበናል፡፡ በተለይ አዲስ አበባ ፖሊስ ወይንም ሶስተኛ እየተባለ የሚጠራው እስር ቤት ውስጥ ታስረው የሚገኙት የትግል ጓዶቻችንና አጋሮቻችን ላይ ከፍተኛ ደብደባ ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ለየ ብቻቸው ጨለማ ቤት ውስጥ እንደታሰሩም ሰምተናል፡፡ ከዚህም ባሻገር ኮተቤ አካባቢ የሚገኙት የትግል አጋሮቻችን ሽንት ቤት ውስጥ መታሰራቸውን ሰምተናል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ (ሶስተኛ) ታስረው የሚገኙት የትግል ጓዶቻችን የሚደርስባቸውን በደልና ጭካኔ አስመልክቶ ከዛሬ ታህሳስ 1/2007 ዓ.ም ጀምረው የርሃብ አድማ ሊያደርጉ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ ይህ የትግሉ አንድ አካል ነው፡፡ በተለያዩ እስር ቤቶች የሚገኙት ጓዶቻችን ላይ የሚፈጸመው በደልና ግፍ ምክንያት እኛም ጨርቆስ ፖፖላሬ እስር ቤት ውስጥ ሆነን ትግላችን እየቀጠልን ነው፡፡ በትግል ጓዶቻችን ላይ የሰብአዊ መብት ጥሰት በአስቸኳይ ካላቆመ እኛ ፖፖላሬ እስር ቤት የምንገኝ ታሳሪዎች አንድ ነገር ለማድረግ እየተዘጋጀን ነው፡፡

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!

Tuesday, December 9, 2014

በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ጥቃት እናወግዛለን !!!

December 8,2014

በአብዛኛው በወጣት ወንዶችና ሴቶች የተገነባው ሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነበት የዘጠኝ ፓርቲዎች ኅበረት፣ “ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የተሰኘ የአንድ ወር መርሀ ግብር አውጥቶ፤ ችግሮችን ተጋፍጦ አብዛኛውን ተግባራዊ አድርጓል። የመርሀ ግብሩ አቢይ አካል የነበረውና በህዳር 27 እና 28 ሊከናወን ታድቆ የነበረው የ24 ሰዓት የአደባባይ ተቃውሞ ግን በአገዛዙ የኃይል እርምጃ ምክንያት በታቀደው መንገድ ሊከናውን አልቻለም። የህወሓት ቅልብ የሆኑት ሲቪል የለበሱ ሰላዮችና የፌደራል ፓሊስ በተቃውሞው ተሳታፊዎች ላይ ኢሰብዓዊ የሆነ ጥቃት ፈጽመዋል።
ከጅምሩ፣ የፓርቲዎቹ ኅበረት የተቃውሞ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለማስገባት የገጠመው ችግር የህወሓት አገዛዝ የመንግሥትን መዋቅር ለፓርቲ ሥራ፤ የመንግሥት ተቀጣሪዎችን ደግሞ እንደ ህወሓት አገልጋዮች የሚጠቀምባቸው መሆኑ አንዱ ማሳያ ሆኗል። ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ማሳወቅ የፈለጉት ፓርቲዎች ህወሓት የዘረጋውን አፋኝ ሥርዓት የሚታገሉ በመሆናቸው ብቻ ደብዳቤዓቸውን የሚቀበል እንኳን አጥተው ተጉላልተዋል። ለሰልፉ ቅስቀሳ ማድረግም በራሱ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ ወጣቶች ተንገላተዋል፣ ተደብድበዋል፣ ታስረዋል። ያም ሆኖ ውጣ ውረዶች ታልፈው ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ. ም. ደረሰ።
የኅበረቱ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ጥሪውን የሰማ ሕዝብ ወደ መስቀል አደባባይ ማምራት ሲጀምር ሲቪል የለበሱ የአገዛዙ ታጣቂዎች እና ፌደራል ፓሊሶች ከሰንደቅ ዓላማዎችና መፈክሮች ባለፈ አንዳች ነገር ያልያዙትን እድሜያቸው ከሃያዎች ያልዘለሉ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችን ደብድበዋል፤ ብዙዎቹም አፍነው በአሰቃቂ ሁኔታ እያንገላቱ ወደ እስር ቤቶች ወስደዋል። ወጣቶች ተወልደው ባደጉበት አገር፤ ስሜታቸውን በነፃነት ለመግለጽ በመድፈራቸው ብቻ በጭካኔ ተረግጠዋል፤ ተፈንክተዋል፤ እጅና እግሮቻቸው ተሰብሯል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህ የህወሓትን ፋሺስታዊ እርምጃ አጥብቆ ይቃወማል። ግንቦት 7፣ ህወሓት ከስልጣን እስካልተወገደ ድረስ እንዲህ ዓይነቱን ፋሺስታዊ ተግባር መፈፀሙን የማይተው እኩይ ኃይል እንደሆነ ያውቃል፤ በዚህም ምክንያት የትግላችን ግብ ህወሓትን ማስወገድና በምትኩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መመሥረት መሆን ይኖርበታል ብሎ ያምናል፤ ለዚህም ይታገላል።
ግንቦት 7፣ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ.ም. “መብቶቻችንን በህወሓት ዘረኛ አምባገነኖች አናስነጥቅም” በማለት አደባባይ የወጡ ወጣቶችን ጽናት ያደንቃል። ህወሓት የሚለውን ሳይሆን የይስሙላ ህጉ የፈቀደላቸውን ለማድረግ በመድፈራቸው በህወሓት የህግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ የሚደረገውን ትግል አንድ እርምጃ ወደፊት አራምደውታል።
እያንዳንዱ የፓለቲካ ድርጅት ከዚህ ኩነት የሚወስዳቸው ተጨማሪ ትምህርቶች ቢኖሩም የሚከተሉትን ነጥቦች ብዙዎችን ያስማማሉ ብለን እናምናለን።
1. ህወሓት በምንም ዓይነት ቢሆን የያዘውን ስልጣን ለሕዝብ ፈቃድ ማስገዛት አይፈልግም፤
2. ህወሓት አገራችን ወደ ትርምስ እየገፋት እንደሆነ ግልጽ እየሆነ መጥቷል፤
3. ስልጣኑን የሚያሳጣው ከመሰለው እና አቅሙ እስካለው ድረስ ዘግናኝ እርምጃዎችን ከመውሰድ አይመለስም፤
ከህወሓት አገዛዝ መገላገል የሚቻለው ተገዶ ሲወገድ ብቻ ነው። ህወሓት እንዲወገድ ደግሞ የመጨቆኛ አቅሙ መዳከም ይኖርበታል። ህወሓትን የማስወገጃ አማራጭ መንገዶች ብዙ ሲሆኑ ተቀናጅተው ቢሠሩ የበለጠ ውጤታማ ይሆናሉ ብለን እናምናለን፤ “ሁለገብ ትግል” የምንለው የትግል ስልት ጭብጥ ይህ ነው። “እምቢ ለነፃነቴ” ብሎ የተነሳ ሕዝብ ህወሓትን ምን ያህል እንደሚያስደነግጥ በተደጋጋሚ ታይቷል። ህዳር 27ን መንደርደሪያ አድርገን በመውሰድ ከዚህ በተሻለ ለተደራጀ ሕዝባዊ እምቢተኝነትና አመጽ ራሳችን እናዘጋጅ።
በዚህ አጋጣሚ ግንቦት 7፣ ለመከላከያ ሠራዊት እና ፓሊስ አባላት ተደጋጋሚ ጥሪዎችን ማድረግ ይሻል። የመከላከያ ሠራዊት እና ፓሊስ አባላት እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ በህወሓት ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ የተበደላችሁ መሆኑን እናውቃለን። የህወሓት ሹማምንት ከሆኑ አዛዦቻችሁ መላቀቅና ራሳችሁን ነፃ የማውጣት ኃላፊነት የወደቀው በእናንተው በራሳችሁ ላይ ነው። ሠራዊቱ ራሱን በራሱ ነፃ ማውጣት ይኖርበታል። የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ህወሓት መወገዱ የማይቀር በመሆኑ ሠራዊቱ ራሱን ነፃ አውጥቶ ከሕዝብ ጋር ካልወገደ እጣ ፈንታው የተሸነፈ ሠራዊት መሆን ነው። ከዚህ በላይ የሠራዊቱ አባል እየደበደበ ያለው የራሱን ልጅ፣ ወንድሙን ወይም እህቱን እንደሆነ ይወቅ። ይህ ወሳኝ ጊዜ ነው እያንዳንዱ የሠራዊቱ አባል በግል ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ሊሰማው ይገባል።
በሁሉም ዓይነት የትግል ዘርፎች የኢትዮጵያ ወጣቶች በስፋት እየተቀላቀሉ መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው። ጊዜው የለውጥ ነው። የተለያዩ ስትራቴጂዎች ተደጋግፈው እንዲሄዱ መደረግ ያለበት ወቅት ላይ ነን። በህዳር 27 ቀን በህወሓት ቅልብ ሰላዮችና የፌደራል ፓሊሶች አማካይነት የደረሰው ጉዳትና የፈሰሰው ደም ለፍትህና ለነፃነት የተከፈለ ዋጋ ነው። ህመማችሁ ህመማችን፤ ትግላችሁ ትግላችን ነው። የተለያዩ መንገዶች ወደ ነፃነት አደባባይ እያመሩ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Monday, December 8, 2014

እነ ግርማ በቀለና ጌታነህ ባልቻ መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውድመዋል ተብለው ተከሰሱ

December 8,2014
ለአዳር ሰላማዊ ሰልፉ መስቀል አደባባይ ተይዘው ጨርቆስ ፖፖላሬ ታስረው የሚገኙት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፀኃፊ አቶ ግርማ በቀለ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የጥናትና እስትራቴጅ ክፍል ኃላፊ ጌታነህ ባልቻን ጨምሮ 27 ያህል የትብብሩ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ዛሬ ህዳር 29/2007 ዓ.ም ጨርቆስ አካባቢ የሚገኝ ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውድመዋል፡፡›› በሚል ተከሰዋል፡፡

ፖሊስ ‹‹ታሳሪዎቹ መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውድመዋል፣ የጠፉ ንብረቶችና ያልተያዙ ግብረአበሮቻቻው ስላሉ ለምርመራ 14 ቀን ይሰጠኝ›› ሲል ጠይቋል፡፡ ታሳሪዎቹ በበኩላቸው ‹‹እኛ መስቀል አደባባይ ላይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ሳንጀምር ነው የታሰርነው፣ ምንም ያወደምነውም ሆነ የወሰድነው ንብረት የለም፡፡›› ሲሉ የፖሊስን ክስ አጣጥለዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በህጋዊ መንገድ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በሚዘጋጁበት ወቅት መያዛቸውን በመግለጽ የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡ ሆኖም ዳኛው የ7 ቀን ቀጠሮ አስተላልፈውባቸዋል፡፡

በተመሳሳይ በዛሬው ዕለት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው የ14 ቀን ቀነ ቀጠሮ የተሰጠባቸውና በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት ታሳሪዎች በደረሰባቸው ድብደባ ምክንያት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ ወደ ሆስፒታል ከተወሰዱት መካከል ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ እየሩስ ተስፋው፣ ጋዜጠናኛ በላይ፣ አቤል ኤፍሬም፣ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ ስሟ ያልተጠቀሰች አንዲት ሴትና ሌሎች በርካታ ወንዶች እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡ ሶስተኛ ከሚገኙት ታሳሪዎች መካከል ከሴቶቹ ንግስት ወንዲፍራውና ምኞቴ መኮንን ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰባቸው እና አብዛኛዎቹ ወንዶች ለየብቻቸው ጨለማና ቀዝቃዛ ቤት ውስጥ እንደታሰሩ ተገልጾአል፡፡

የህወሃት ምርጫ የህዝብ መከራ!

December 8,2014
ህወሃቶች እኛ ከሌለን ይህችን አገር እንበትናታለን፤ ይህችን አገር የምንሰብር እኛ የምንጠግን እኛ እያሉ እንደሚያሟርቱ ሰምተናል። እኛ የቀረፅነው ፖሊስ ከሚቀየር ሞታችንን እንመርጣለን እያሉ ማቅራራታቸውም ከህዝብ የተሰወረ ነገር አይደለም። የህወሃት ፖሊሲ የሚቀየረው በመቃብርችን ላይ ነው የሚል የማይናወፅ አቋማቸው መቼም ቢሆን በሠለጠነ መንገድ በውይይትና በድርድር እንደማይቀየር ደጋግመው አሳይተውናል። ህወሃቶችን በሠለጠነ መንገድ ተደራድሮ እና ሰጥቶ በመቀበል መርህ ለለውጥ አዘጋጃለሁ ማለት ከእባብ የእርግብ እንቁላል እንደመመኘት ያህል ነው። ከእባብ የእርግብን ዘር የሚጠብቅ ማን ነው?
እንግዲህ ህወሃቶች ይህን የመሰለ የከረረ አቋም ይዘው ምርጫ ለምን ያደርጋሉ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ይሆናል። ይሄ ህወሃቶች ለኢትዮጵያና ለህዝቧ ራዕይ የሌላቸው ከመሆን የሚመነጭ ነው። ድርጅቱ ራዕይ አልባ የሆነው ደግሞ በህወሃት ውስጥ የተሰባሰቡ ግለሰቦች ራዕይ አልባ በመሆናቸው ነው። ህወሃቶች የሚኖሩለትም ሆነ የሚሞቱለት ቁም ነገር ከመብልና መጠጥ የዘለለ አይደለም። ህወሃቶች ራዕይ ቢኖራቸው ኑሮ በታሪክ የሚያስወቅሳቸውንና የህዝቡን ፍቅር የሚያሳጣቸውን እኩይ ተግባራት ባልፈፀሙ ነበር። ራዕይ የሌላቸው በመሆኑ ለሚፈፅሙት ወንጀል ሁሉ ገደብ እንዳይኖራቸው ሆኑ። ራዕይ ያለው ሰውም ሆነ ድርጅት እኔ ብቻ አይልም። ራዕይ የሰነቀ ድርጅትም ሆነ ሰው ከራሱ ክበብ አልፎ ሌላው እንደምን ሁኖ በሠላም እና በደስታ እንደሚኖር ያስባል እንጂ ዕለት ዕለት ደም በማፍሰስ አይኖርም።
ህወሃት በምርጫ ስልጣኑን እንደማይለቅ ለራሱ የማለ ድርጅት ነው። እዚህ መሃላ ላይ ያደረሰው ደግሞ እስከ ዛሬ የፈፀማቸው ወንጀሎቹ ናቸው።የጨበጠውን ስልጣን በምርጫ ቢለቅ ነገ የሚከተለውን ጠንቅቆ ያውቃል። ትላንት ያፈሰሱት የንፁሃን ደም ከኢትዮጵያ ምድር ላይ እየጮኸ ነው። ዘርፈው የገነቡት ህንፃ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ቆመው ሌብነታቸውን እየመሰከሩባቸው ነው። በልማት ሥም ከኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ተዘርፎ የተደራጀው የንግድ ተቋም በኢትዮጵያ ህዝብ ወዝና ደም ታጥኖ እንዳማረበት አለ። ህወሃት የኢትዮጵያ የህዝብ ጠላት ሆኖ ራሱን ያቆመ ቡድን በመሆኑ በሰላማዊ እና በሰለጠን መንገድ የያዘውን ሥልጣን ለህዝብ አይለቅም።
እንግዲህ ምን ይሻላል ?
ህወሃቶች ኑና እንወዳደር ብለዋል። እነዚህ ቡድኖች ኑና እንወዳደር ሲሉ እነርሱ የብረት ቦክስ ጨብጠው፤ ሌሎቹ ደግሞ ሌጣቸውን ሁነው ያለ በቂ ታዛቢ እንዲፎካከሯቸው ወስነው ነው። እንዲህ ባለ ሁኔታ ውስጥ ሁነንም ቢሆን የምንወዳደረው ለነፃነት መሆን ይኖርበታል። ከነፃነት በመለስ ያለው ማንኛውም ዓይነት የምርጫ ውጤት በአገራችን እየተካሄደ ያለውን ዝሪፊያ፤ ዘረኝነት፤ እሥራት እና ግድያ ያስቆማል የሚል ዕምነት በማንም ዘንድ ያለ አይመስለንም። በምርጫ ውድድር የምናተርፈው የህግ የበላይነት፤ እኩልነት እና ነፃነት ካልሆነ ተጎጂው ሰፊው ህዝብ ይሆናል።
ህወሃት የብረት ቦክስ ጨብጦ እኛ ደግሞ ሌጣችንን ሁነን መወዳደር ፍትሃዊ አይደለም በማለት ድምፃቸውን እያሰሙ ያሉት ወገኖችም የህዝብን መሠረታዊ ፍላጎት ለሟሟላት አስፈላጊ የሆነው ነፃነት ዋነኛው ግባቸው መሆን ስለሚኖርበት ይመስለናል። ወደ ውድድር ከመግባታችን በፊት ህወሃት የብረት ቦክሱን ያውልቅ፤ የመወዳደሪያ መድረኩም እኩል ይሁን ማለታቸው የሚሰማ ቢኖር ፍትሃዊ ጥያቄ ነው።የህወሃትን የብረት ቦክስ ለማስወለቅ መሥዋዕትነት ለመክፈል መዘጋጀታቸውም ለነፃነት የሚከፈል ዋጋ ይሆናል። ከህወሃት ጭካኔና ድንቁርና ስንነሳ በዚህ መንገድ የሚሄዱት የሚከፍሉት መሥዋዕትነት ከባድ እንደሚሆን እንጠብቃለን። ግን ደግሞ ነፃነት ያለ መሥዋዕትነት እንደማይገኝ ሌላው ቀርቶ ነፃነትን የማያውቁት ህወሃቶች ያውቃሉ። በማንኛውም መልኩ ከህወሃቶች ጋር አገት ለአንገት ተናንቀው በአገር ቤት ውስጥ እየተንቀሳቀሱ ያሉት ድርጅቶች ልበ ሙሉነታቸውን እጅግ አድርገን እናደንቃለን። እምቢ ለነፃነቴ፤ እምቢ ለክብሬ፤ እምቢ ለህወሃቶች ቀይ መስመር ማለት ይሄ እንጂ ሌላ አይደለም። እንግዲህ ዘረኞቹና ዘራፊዎቹ ቡድኖች ሊያደርሱ የሚችሉትን ጉዳት መቀነስ የሚቻልበትን መንገድ ማሰብ ተገቢ ይሆናል። ህዝቡ በልዩ ልዩ ሰንሰለት የታሠረ በመሆኑም በሚፈለገው መጠን ወጥቶ የትግሉ አካል ካልሆነም ተስፋ መቁረጥ አይገባም።በተጀመረው ላይ ይበልጥ እያጠናከሩና እየጨመሩ እየተካሄደ ያለውን ትግል መቀጠል ምርጫ የሌለው ሥራ ነው።
ግንቦት ሰባት የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አገር ቤት ሁነው ከጭካኔ በቀር ሌላ ዕውቀት ከሌላቸው ህወሃቶች ጋር በትግል ላይ ያሉ ድርጅቶችን ያደንቃል። ያመስግንማል። በርቱ ከማለት በቀር የምንለው ሌላ የለንም።
እኛ የጀመርነውን ሁለ ግብ ትግል እያጠናከርነው ነው። የአገራችንን ውርደት፤ የወገኖቻችንን ጉስቁልና እያየን ዝም ብንል እርግማን ይሁንብን ያሉ ወጣቶች የአያቶቻቸውን ጋሻና ጦር አንስተዋል። እናቶችም ልጆቻቸውን መርቀው ፋኖ ተሠማራ ብለዋል። ሌሎች ደግሞ የኋላ ደጀን ሁነው ሳያቅማሙ ቁመዋል። ብዙ ባለሙያዎች ለአገራቸው የሚከፈልውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጀተዋል።
እንግዲህ የጀመርነውን ትግል የሚያስቆመን ምድራዊ ኃይል የለም። የህወሃት የመረጃ መረብ ይበጣጠሳል። የጦር ኃይሉ ከጥቂት ዘረኞችና ሌቦች ይልቅ ወገኑን እንደሚመርጥ በየቀኑ የሚደርሱን መረጃዎች ያሳዩናል። የከተማው ህዝብ ህወሃቶችን አክ እንትፍ ካላቸው ብዙ ዘመን ሁኖታል። የገጠሩም ህዝብ የህወሃት ዋሻ የመሆኑ ነገር አብቅቷል። ይሄ ሁሉ የእኛ አቅማችን ነው። ይሄን አቅም አደራጅተንና ሥራ አሲይዘን አገራችንን ነፃ የምናወጣበት ግዜ ሩቅ አይደለም።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

እነ ፍቅረማሪያም የሽንት ቤትና ሌሎች ቆሻሻዎች የሚፈስበት ጋራዥ ውስጥ ታስረዋል

December 8,2014
እነ ወይንሸት ንጉሴ 7 ቀን ተቀጠረባቸው
በሰላማዊ ሰልፍ ዝግጅት ወቅት ታፍና ቤላ 18 ተብሎ በሚጠራው ፖሊስ ጣቢያ ታስራ የምትገኘው ወይንሸት ንጉሴና ሌሎች 6 ወጣቶች ሾላ አካባቢ በሚገኘው ፍርድ ቤት ቀርበው 7 ቀን ተቀጠረባቸው፡፡ ወይንሸት ‹‹ባልፈተቀደ ሰላማዊ ሰልፍ በመሳተፍና ሁከት መፍጠር›› የሚል ክስ የቀረበባት ሲሆን እሷ በበኩሏ ሰልፍ ማሳወቅ እንጅ ማስፈቀድ እንደማያስፈልግ በመጥቀስ የዋስትና መብቷ ተረጋግጦላት እንድትፈታ ጠይቃለች፡፡
‹‹የያዝናቸው በቅርብ ቀን ነው፣ ያልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው አሉ፣ መረጃም እናሰባስባለን›› ያለው ፖሊስ 14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ተጠይቆ 7 ቀን ተሰጥቶለታል፡፡
በሌላ በኩል ኮተቤ አካባቢ የታሰሩት እነ ፍቅረማሪያም አስማማው፣ ተስፋሁን አለምነህ፣ ሺፈራው ዋለና ሌሎች 8 ታሳሪዎች የሽንት ቤት ፍሳሽ በሚልፍበት ጋራጅ ቤት ውስጥ መታሰራቸውን ገልጸዋል፡፡ እነ ፍቅረማሪያም የታሰሩት ፖሊስ ከግለሰብ የተከራው ህንጻ ውስጥ ሲሆን የታሰሩበት ጋራዥም ከህንጻዎቹ ላይ የሚገኙት ሽንት ቤቶችና ሌሎች ቆሻሻዎች የሚያልፉበት ነው ተብሏል፡፡ እነ ፍቅረማሪያም ከ2 ቀን በፊት ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹በሽብርተኝነት›› ክስ 10 ቀን እንደተቀጠረባቸው ይታወቃል፡፡

Sunday, December 7, 2014

Security Message for U.S. Citizens in Ethiopia

December 7, 2014
U.S. Embassy Addis Ababa, Ethiopia | December 5, 2014
The U.S. Embassy informs U.S. citizens that political rallies or demonstrations may occur without significant notice throughout Ethiopia, particularly in the lead up to Ethiopian national elections in May 2015. Such rallies and demonstrations may be organized by any party or group and can occur in any open space throughout the country. In Addis Ababa, applications for permits to conduct rallies are often requested for Meskel Square or Bel Air Field. Please remember that even public rallies or demonstrations intended to be peaceful have the potential to turn confrontational and escalate into violence. You should, therefore, stay alert and avoid areas of demonstrations, and exercise caution if in the vicinity of any large gatherings, protests, or demonstrations.U.S. Embassy Addis Ababa, Ethiopia
The U.S. Embassy reminds U.S. citizens of the on-going threat of terrorist attacks in Ethiopia. U.S. citizens are reminded and encouraged to maintain heightened personal security awareness. Be especially vigilant in areas that are potential targets for attacks, particularly areas where U.S. and western citizens congregate, including restaurants, hotels, bars, places of worship, supermarkets, and shopping malls. Al-Shabaab may have plans for a potential attack targeting Westerners and the Ethiopian government, particularly in Jijiga and Dolo Odo in the Somali Region of Ethiopia, and Addis Ababa. Attacks may occur without warning.
Due to serious safety and security concerns, U.S. government personnel and their families are presently restricted from traveling to the following areas except as permitted on a case-by-case basis:
Ethiopian/Kenyan Border (Southern Ethiopia): In southern Ethiopia along the Kenyan border, banditry and incidents involving ethnic conflicts are common. Security around the town of Moyale is unpredictable, and clashes between Ethiopian forces and the Oromia Liberation Front (OLF) have been reported.
Ethiopia/Eritrea Border (Northern Ethiopia): Ethiopia and Eritrea signed a peace agreement in December 2000 that ended their border war. However, the border remains disputed. The border area is a militarized zone where there is the possibility of armed conflict between Ethiopian and Eritrean forces. U.S. government personnel are restricted from travel north of the Shire (Inda Silassie)-Axum-Adigrat road in the Tigray region of Ethiopia. Personnel are further restricted from travel north of the road from Dessie through Semera to the Galafi border crossing with Djibouti, including the Danakil Depression and the Erta Ale volcano. In January 2012, a group of foreign tourists were attacked near the Erta Ale volcano in the Afar region near the Eritrean border, approximately 100 miles southeast of Adigrat in the Danakil Depression. The attack resulted in five deaths, three wounded, and four people kidnapped. The victims were European and Ethiopian citizens. The two Europeans who were kidnapped were subsequently released. On February 15, 2012, Ethiopia, which blamed Eritrea for the attack, retaliated by striking military camps in Eritrea where the attackers were allegedly trained. This episode illustrates the continuing volatility of the border area.
Somali Region (Eastern Ethiopia): Travel to Ethiopia’s Somali regional state is restricted for U.S. government employees, although essential travel to the region is permitted on a case-by-case basis. Since the mid-1990’s, members of the Ogaden National Liberation Front (ONLF) have conducted attacks on civilian targets in parts of the Somali regional state, particularly in predominantly Ogadeni zones. Expatriates have been killed in these attacks. In 2010, the Government of Ethiopia initiated peace talks with the ONLF, which are ongoing. Despite these talks, incidents of violence continue to occur. Throughout 2013, skirmishes between the ONLF and regional government security forces took place. Some of these incidents involved local civilians. Al-Shabaab maintains a presence in Somali towns near the Ethiopian border, presenting a risk of cross-border attacks targeting foreigners.
Gambella Region (Western Ethiopia): Sporadic inter-ethnic clashes are a concern throughout the Gambella region of western Ethiopia. While the security situation in the town of Gambella is generally calm, it remains unpredictable throughout the rest of the region. Intensified conflict between Sudan and the Republic of South Sudan (RSS) has significantly increased refugee flows into Western Ethiopia. Travel to the border areas in the Beneshangul-Gumuz Region (Asosa) is restricted to major towns north of the area where the Great Ethiopian Renaissance Dam (GERD) is being constructed due to political sensitivity.
We strongly recommend that U.S. citizens traveling to or residing in Ethiopia enroll in the Department of State’s Smart Traveler Enrollment Program (STEP). STEP enrollment gives you the latest security updates, and makes it easier for the U.S. embassy or nearest U.S. consulate to contact you in an emergency. If you don’t have Internet access, enroll directly with the nearest U.S. embassy or consulate.
Regularly monitor the State Department’s website, where you can find current Travel Warnings, Travel Alerts, and the Worldwide Caution. Read the Country Specific Information for Ethiopia. For additional information, refer to the “Traveler’s Checklist” n the State Department’s website.
Contact the U.S. embassy or consulate for up-to-date information on travel restrictions. You can also call 1-888-407-4747 toll-free in the United States and Canada or 1-202-501-4444 from other countries. These numbers are available from 8:00 a.m. to 8:00 p.m. Eastern Time, Monday through Friday (except U.S. federal holidays). Follow us on Twitter and Facebook to have travel information at your fingertips.
The U.S. Embassy in Addis Ababa is located at Entoto Street, P.O. Box 1014. The Consular Section of the Embassy may be reached by telephone: +251-111-306000 or e-mail at consacs@state.gov, and is open Monday-Thursday, 7:30 a.m.-5:00 p.m. For after-hours emergencies, U.S. citizens should call +251-111-306911 or 011-130-6000 and ask to speak with the duty officer.

የ72 አመቱ አዛውንት በወያኔ መንግስት በአሸባሪነት ተከሰሱ

December 7,2014

ነገረ ኢትዮጵያ
የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ውስጥ የጥበቃ ሰራተኛ ናቸው፡፡ የሚኖሩት ከ10 አመት ልቻቸው ጋር ነው፡፡ ይህን ልጅ እሳቸው ብቻ ነው የሚያሳድጉት፡፡ ትናንት ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከታፈሱ ከሰዓታት በኋላ ስራ ውለው ወደ ቤታቸው ሲሄዱ በደህንነቶች ታፈኑ፡፡ አቶ ቀኖ የጥበቃ ስራ ከመስራት ውጭ ሰልፉ አስተባባሪም ተሳታፊም አልነበሩም፡፡ ግን ታጥሮ ከሰነበተው የሰማያዊ ቢሮ የወጣ ሁሉ ሲለቀም ነበርና እሳቸውንም አፈኗቸው፡፡ ምን አልባትም ተደብድበው ይሆናል፡፡
ይህ ስርዓት እነ ይልቃልን፣ ብርሃኑን፣ አቤልን፣ በላይን፣ ጣይቱዎቹን....ሰማያዊን ብቻ አይደለም የሚፈራው፣ የሚያፍነው፣ የሚያፍሰው፣ የሚደበድበው፡፡ አቶ ቀኖንም የሆነ ነገር ያደርጋሉ ወይንም አድርገዋል በሚል (በራሱ ትርጉም) አፍኖ አስሯቸዋል፡፡ አሁን አቶ ቀኖ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ ይገኛሉ፡፡ አይጠየቁም፡፡ ምን አልባትም ጨለማ ቤት ውስጥ ከታሰሩት መካከል ሳይሆኑ አይቀሩም፡፡
ኢቲቪ ትናንት ታፍሰው የታሰሩትንም ሆነ የታፈኑትን ‹‹ከአሸባሪ ድርጅት ጋር በመስራት›› ሲል የተለመደ ፍረጃውን አሽጎድጉዷል፡፡ እንግዲህ ለስርዓቱ የ72 አመቱ አቶ ቀኖም ከ‹‹አሸባሪዎች›› ጋር አሲረዋል ማለት ነው፡፡
የአቶ ቀኖ መታፈን የስርዓቱን ቅጥ ያጣ ፍርሃት ደግሞም አረመኔነት የሚያሳይ ነው፡፡ ቀጣዩን ትውልድ ብቻ ሳይሆን አዛውንቶችንም ለማጥፋት እንደቆመ፣ ጥላውንም ማመን እንዳቃተው የሚያመለክት የእውር ድንበር እርምጃ ነው፡፡ ፍትህ፣ ሞራል፣ ምክንያታዊነት፣ ህግ፣ ኢትዮጵያዊነት፣ ሰብአዊነት ጨርሶ ከስርዓቱ ጋር እንደሌለ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡
ትናንት ሴቶች፣ እናቶች፣ ወጣቶች፣ እንደ አቶ ቀኖ ያሉ አዛውንቶች ታፍነዋል፣ ተደብድበዋል፣ ታስረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ይህን የሚመስል፣ ለሰሚው ግራ የሚያጋባ፣ ደግሞም የሚያሳፍር፣ የሚያበግን ጭቆና ውስጥ ነች፡፡ እህቶቻችን፣ ወንድሞቻችን፣ እናቶቻችንና አባቶቻችን እያነቡ ነው፡፡ ይህን የህዝብ እንባ ልናብስ የምንችለው በቆራጥነት ደግሞም ተባብረን ስንታገል ነው፡፡
ያለ መስዋዕትነት ድል የለም!

አመራሮቹ ጨለማ ቤት ታስረዋል

December 7,2014
• ኢ/ር ይልቃልን ከመኪና ገፍትረው ሊጥሏቸው ነበር

ህዳር 27/2007 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ታፍሰው ከታሰሩት መካከል አብዛኛዎቹ ጨለማ ቤት መታሰራቸው ታወቀ፡፡ ከሰማያዊ ጽ/ቤት አካባቢ በጀመረው ሰልፍ ላይ ታፍሰው አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) ታስረው የሚገኙት መካከል ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬና ሌሎቹም ለየ ብቻቸው ጨለማ ቤት መታሰራቸው ታውቋል፡፡ ታሳሪዎቹ ትናንት ህዳር 27/2997 ዓ.ም ምሽት ላይ ከጨርቆስ ፖፖላሬ እስር ቤት ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ (ሶስተኛ) የተዛወሩ ሲሆን ‹‹ምርመራ ላይ ናቸው፡፡›› በሚል እንዳይጠየቁ ተደርገዋል፡፡ 

በሌላ በኩል ከሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት አካባቢ የተነሳው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ተሳታፊ ከነበሩት መካከል አብዛኛዎቹ እግርና እጃቸውን እንደተሰበሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህም ባሻገር የታፈሱት አመራሮች በፒክ አፕ መኪና ተጭነው በሚወሰዱበት ወቅት ደህንነቶች ኢንጅነር ይልቃል ጌትነትን ከመኪናው ላይ ገፍተው ለመጣር ሙከራ አድርገው እንደነበርና አብረው የተጫኑት ታሳሪዎች ይዘው እንዳስቀሯቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከትብብሩ የተሰጠ መግለጫ – በአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ትግላችን አይቆምም!

December 7, 2014

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ባለፈው አንድ ወር ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚል መርሃ ግብር ቀርጸን ስንቀሳቀስ ዋናው አላማችን የስርዓቱን አረመኔያዊነት ለህዝብ በማጋለጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በትግሉ እንዲሳተፍ ማድረግ ነው፡፡ እንደጠበቅነው ገና ከጅምሩ የህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ትግላችንን በጭካኔ ለማስቆም ጥሯል፡፡ ህዳር 7/2007 ዓ.ም የመጀመሪውን የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በጠራንበት ወቅት ስብሰባውን በኃይል በትኗል፡፡

ትብብራችን ከመቸውም ጊዜ በላይ ያሰጋው ህወሓት/ኢህአዴግ በተለይ የህዳር 27/28 2007 ዓ.ም የአደባባይ አዳር ሰልፍን እንዳይካሄድ የትብብሩን አመራሮችና አባላቶቻችን በማዋከብ፣ በመደብደብና በማሰር ተጠምዶ ሰንብቷል፡፡ በተለይ በትናንትናው ዕለት ሰልፍ በወጣንበት ወቅት ስርዓቱ አመራሮችንን፣ አባላቶቻችንን፣ ተሳታፊዎችንን እንዲሁም አልፎ ተርፎ መንገደኛውን ህዝብ በጭካኔ ደብድቧል፡፡ አፍሶ አስሯል፡፡ ሙስሊም እህትና ወንድሞቻችን በየጎዳናው ታፍሰው የአገዛዙ አረመኔያዊ እርምጃ ሰለባዎች ሆነዋል፡፡ በርካቶችም በ እስር ቤቶቹ ታጉረዋል፡፡ እስካሁን ባለን መረጃ ከ300 በላይ የትብብሩ አመራሮችና አባላት የታሰሩ ሲሆን የትብብሩና የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበርን ጨምሮ በርካታ አመራሮች ከፍተኛ የአካል ጉዳት ድርሶባቸዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል የሆነው አቤል ኤፍሬም ራሱን እስኪስት ተደብድቧል፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ የተገኙ ሴት አመራርና አባላት አንድ አገርን እየመራሁ ነው ከሚል አካል በማይጠበቅ መንገድ በጭካኔ ተደብድዋል፡፡ እነዚህ በጭካኔ የተደበደቡ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ህክምና እንዳያገኙ ተከልክለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በጥበቃ ሰራተኝነት የሚሰሩ የ72 አመቱ አቶ ቀኖ አባጆቢር ከስራ ሲወጡ በደህንነት ኃይሎች ታፍነው የተወሰዱና እስካሁን የት እንደደረሱ ያልታወቀ ሲሆን ይህም አገዛዙ የመጨረሻው የአረመኔነት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ይህን የስርዓቱ ውንብድና ለማስቆም ጊዜ የማይሰጠው ተግባር መሆኑን በግልጽ የተገነዘብንበት ነው፡፡

አገዛዙ በትናንትናው ዕለት በፍጹም ሰላማዊ ሰዎች ላይ የወሰደው የውንብድና እና አረመኔያዊ እርምጃ በትግሉ ውስጥ የምንጠብቀውና ስርዓቱ ለኢትዮጵያ የማይበጅ መሆኑን ዳግመኛ ያያ ረጋገጠበት ነው፡፡ የትናንትናው ትላችን አገዛዙ ለይስሙላ እከተለዋለሁ ከሚለው ‹‹ህጋዊ ሰርዓት›› ይልቅ ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ቆርጦ መነሳቱን እና በህገ መንግስት ስም ህዝብን የሚበድልበትን የአረመኔያዊነት ጭንብል ገልጠን ለዓለም ያሳየንበት የትግላችን ውጤት ነው፡፡

አገዛዙ ላላፉት 24 አመታት ስልጣኑን በኃይል ለማስጠበቅ ሲጥር ቆይቷል፡፡ በትናንትናው ዕለት የፈጸመው ፍጹም አረመኔያዊ እርምጃም እንደተለመደው ሰላማዊ ታጋዮችን ያሸማቅቃል ብሎ አስቦ እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የአገዛዙ አረመኔያዊነት ከሰላማዊነታችን ፍጹም ወደኋላ ሊያንሸራትተን አይችልም፡፡ ወደ ትግል ስንገባ የስርዓቱን ጭካኔና ለኢትዮጵያ የ ማይመጥን መሆኑን አውቀንና የሚያስከፍለውን መስዋዕትነት ለመክፈል ተዘጋጅተንም ነው፡፡ አሁንም አገዛዙ የህዝብን ድምጽ በማፈን ስልጣኑን ለማስጠበቅ ተመሳሳይ እርምጃ እንደሚወስድ እንጠብቃለን፡፡ ነገር ግን መጀመሪያውንም ትግሉን ስንቀላቀል አስበን የገባነው እየቆሰልን፣ እየታሰርንም፣ እየሞትንም ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ ለመሆን ነውና ከትግላችን ቅንጣት ሊያደናቅፈን አይችልም፡፡ ስለሆነም ወደፊትም ይህን የአገዛዙን አረመኔያዊነት በማጋለጥና ህዝቡን በትግሉ በማሳተፍ ለኢትዮጵያ የሚገባት ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመመስረት በቀጣይነትም ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ነን፡፡

በዚህ አጋጣሚ ሰላማዊ ሰልፉን ለማሳካት እንዲሁም የህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን የፈጸመውን ጭካኔ በማውገዝ ከጎናችን ለቆማችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡ ከህወሓት/ ኢህአዴግ አገዛዝ ጋር የሚደረገው ትግል እልህ አስጨራሽ፣ ከፍተኛ መስዋዕትነት የሚያስከፍልና የእያንንዳንዳችን ትብብር የሚጠይቅ መሆኑን ተገንዝበን ሁላችንም በጋራ እንድንቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን

ያለ መስዋዕትነት ድል የለም፡፡

Saturday, December 6, 2014

ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት?

December 6,2014
ከክንፈ አሰፋ
teddy-afro1
ወደ አውሮፓ የሚያስገባውን ቪዛ እና ትኬት ይዞ ከወዳጆቹ ጋር ጉዞውን ለመጀመር ወደ ቦሌ አለም-ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ አቀና። እዚያው እንደደረሰ የተለመደው የፓስፖርትና ትኬት ቁጥጥር ተደረገ። ሁሉም የተሟላ ነበር። ቴዲ ሸኚዎቹን ተሰናብቶ ወደ ውስጥ ጋባ። እለተ ሐሙስ፣ ህዳር 28 ቀን 2007 ዓ.ም.።
የአውሮፓው ኮንሰርት በፊንላንድ፣ ሄልሲንኪ ቅዳሜ፤ ህዳር 28 ቀን ይጀምራል። ፊንላንድና አካባቢው ያሉ የቴዲ አድናቂዎች ትኬት ቆርጠው አርቲስቱን በጉጉት እየተጠባበቁት ነው። የቴዲ አፍሮ ማናጀርም አቡጊዳ ባንድን ይዞ ሄልሲንኪ ላይ ለቅዳሜው ስራ በልምምድ ላይ ይገኛል።
ቴዲን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተሰናብተው የተመለሱ ወዳጆቹ አውሮፓ ደውለው አርቲስቱን ሄልሲንኪ ላይ እንዲቀበሉት ተናግረው ነበር። ነገሩ እነሱ እንዳሰቡት ግን አልነበረም። ዘግየት ብሎ ሌላ ነገር መጣ። ሰዎቹ ቦሌ ላይ አገቱት። በውድቅት ሌሊት ፓስፖርቱን ነጥቀው ወደ ቤቱ አሰናበቱትም። ይህንን ያደረጉበትን ምክንያትም አልነገሩትም።  አስቀድመው ገና ከበሩ ላይ መከልከል ይችሉ ነበር።… ግን ማንገላታት ነበረባቸው። ስሜቱን ለመጉዳት መሞከር ነበረባቸው። ጉልበት እንዳላቸው ማሳየት ነበረባቸው። ፈላጭ፤ ቆራጭ መሆናቸውን ማሳወቅ ነበረባቸው። ቂመኞችና ተበቃዮችም መሆናቸውን መናገር ነበረባቸው። ….
ነገሩ ያልተጠበቀ ባይሆንም፤ ለቴዲ ጠበቆች ግራ ማጋባቱ አልቀረም።  በነጋታው ጠበቆቹ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ፍርድ ቤት መሄድ ነበረባቸው። ከፍርድ ቤት ያገኙት ምላሽ በቴዲ አፍሮ ላይ ምንም አይነት የማገጃ ትዕዛዝ ያለመኖሩን ነው። ከዚያም ወደ ኢሚግሬሽን ጉምሩክ እና ሌሎች ጉዳዩን የሚመለከቱ ቢሮዎች ሁሉ አመሩ። እዚያም የጉዞ ማገጃ አልተገኘም። ታዲያ ማን ይሆን ያዘዘው? የካዛንችዙ ስውር መንግስት ስራውን እንደገና ጀምሮ ይሆን?
ጉዳዩ ግራ ያጋባል። እርግጥ ነው። የዛሬይቱ ኢትዮጵያ አንድ ተራ ካድሬ እንዲህ አይነት ተራ ወንጀል የሚፈጽምባት ሃገር ሆናለች። አንዳንድ ቦታዎች ላይ “መንግስት የለም እንዴ?” የሚያስብሉ ወንጀሎች እንደሚፈጽሙ ይሰማል።  የቀድሞው የኮሚኒኬሽን ሚንስትር ዴዔታ የነበረው ኤርምያስ ለገሰ፤ በቅርቡ ባሳተመው “የመለስ ትሩፋቶች” የተሰኘ መጽሃፉ አዲስ አበባን ባለቤት አልባ ከተማ ብሏታል።
በልማታዊ አርቲስቶች እለት-ተለት የሚወደሰው ጸሃዩ መንግስት፤ ለልማት የተጋው መንግስት፣ ጭቆናን ያቆመው መንግስት፤ ለዜጎች መብትና ነጻነት የቆመ መንግስት፣ ሃገሪቱን ወደ እድገት እና ትራንስፎርሜሽን ጎዳና ላይ ያስኬደ መንግስት፣ የመቻቻል ባህልን ያመጣ መንግስት…. እንዴት ሆኖ የጥላቻ፣ የቂም እና የበቀል እርምጃ ሊወስድ ቻለ?
ልማታዊ አርቲስቶቻችን ይቅርታ አድርጉልኝና የአስተሳሰብና የአመለካከት ለውጥ ሳይኖር ቁሳዊ ለውጥ ይመጣል ብሎ የነገራችሁ ማን ይሆን? አመለካከታችን ካላደገ፣ እድገት ይታሰብ ይሆን?
ወደ ጉዳዩ ስንመለስ፣ ከፊንላንድ በኋላ ሌሎች ስድስት የአውሮፓ ከተሞች ላይ ኮንሰርቶች ተዘጋጅተዋል። ፕሮሞተሮች ለመሰናዶው ብዙ ወጪ አውጥተዋል። የአርቲስቱ አድናቂዎችም አስቀድመው ትኬት ቆርጠዋል። ይህንን ካድሬዎቹ ጠንቅቀው ስለሚያውቁ ሁሉንም ማጉላላቱ፤ ከተቻለም ማደናቀፉ ደስታን ይሰጣቸዋል። እንዲህ አይነት የድፍረት ስሜት የሚመነጨው አርቲስቱን ሳይሆን ይልቁንም ሕዝብን በጅምላ ከማናቅ ነው። ሕዝብን ከመጥላት። እየገዙት ያሉትን ህዝብ መናቅና መጥላት የት ድረስ ሊያደርሳቸው እንደሚችል የምናየው ይሆናል። እንደ ሰብአዊ ፍጡር ሳይሆን እንደ እንስሳ የሚያስቡ እነዚህ የዘመናችን ጉዶች ሕዝብ የሚወደውን ነገር በሙሉ በመጥላት፤ የህዝብ አካል እንዳልሆኑ እይረጋገጡልን ነው። ከጫካ ከወጡ 21 አመታትን አስቆጥረዋል። አካላቸው ከጫካ ወጣ እንጂ አመለካከታቸው ግን እዛው እንደሆነ ድርጊታቸው ይነግረናል።  ከሁለት ዓስርተ-ዓመት በኋላም ጥንት ከሚያስቡበት ከጫካው ህግ አልተላቀቁም።
ይህንን ትልቅ ሃገር እና ይህንን ትልቅ ሕዝብ እየመሩ ለምን እንደመንገስት ሊያስቡ እንደማይችሉ አይገባኝም። መንግስት ሆነው እንደግለሰብ ቂም ይይዛሉ። ቂም ይዘው እንደ ክፉ ሰው ይበቀላሉ። ሀገር ደግሞ በጥበብ እና በማስተዋል እንጂ፤ ከቶውንም በቂም እና በበቀል አትመራም። ይህንን የሚያደርጉ ሁሉ መጨረሻቸው ውድቀት፤ አወዳደቃቸውም የውርደት እንደሆነ ለደቂቃ አስተውለውት የሚያውቁ አይመስለኝም።
እንግዲህ ይህ ተራ ወንጀል በዚህ ድንቅ አርቲስት ላይ ሲፈጸም የመጀመርያ አይደለም። ከወራት በፊትም ወደ አሜሪካ ሊጓዝ ሲል የአየር መንገዱ ካድሬዎች ይዘው ብዙ አጉላልተውት ነበር። እርግጥ ነው ቴዲ አፍሮ ላይ ጥርሳቸውን ነክሰውበታል። ኤርምያስ ለገሰ፤ በ”መለስ ትሩፋቶች” መጽሃፉ ላይ የቴዲን ጉዳይ አንስቶ የገዢው ፓርቲ ሰዎች ይህንን አርቲስት እንዴት በክፉ አይን እንደሚመለከቱት ዳስሷል። ይህ አርቲስት ምናልባት በአንዲት ዜማ ተችቷቸው ይሆናል። እነሱም አላለፉትም። በፍትህ ስም የበቀል ዱላቸውን አሳርፈውበታል። ወህኒ ወርዷል። እስኪበቃቸውም ቀጥተውታል።
ቴዲ አፍሮ ግን ቂም አልቋጠረባቸውም። አሁንም የሚያቀነቅነው ስለ ፍቅር ነው። አሁንም የሚለው እንዲህ ነው። “ፍቅር ያሸንፋል!”
እነዚህ ሰዎች ሃያ ሁለት አመታት ሙሉ ከጥፋት አለመማራቸው ብቻ አይደለም የሚደንቀው። በአንድ ግለሰብ ምክንያት ከሚሊዮኖች ጋር እንደሚላተሙ አለማሰተዋላቸውም የሚገርም ነው።  ለሟቹ ፓትሪያርክ ሲሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኦርቶዶክስ ምዕመናን ጋር ተቃርነው ነበር። አንድ የሙስሊም መጅሊስ መሪን ለመያዝ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሙስሊም ምዕመናን ጋር ጠፋጥተዋል።
ዛሬ አንድ ቴዲን ቢያንገላትቱት፣ ቢያግቱትም ሆነ ፓስፖርቱን ቢነጥቁት ለግዜውም ቢሆን የአድናቂዎቹን ስሜት ሊጎዱት ይችሉ ይሆናል። ይህ ድርጊታቸው ቴዲ አፍሮን ቅንጣት ያህል አይጎዳውም።  ይልቁንም የበለጠ ተወዳጅ እና የበለጠ ጀግና ያደርገዋል።  ከዚህ የፖለቲካ ንግድ እነሱ የሚያተርፉት ነገር ቢኖር የህዝብ ጥላቻን ነው። የቴዲን መታገት የሰሙ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ሳይቀሩ እንዲህ ሲሉ ተደመጡ፤ “አሁንስ አበዙት… ሃገራችንን እንድንጠላ አደረጉን….” ካድሬዎቹ ማህበራዊ ድረ-ገጾችን ቢጎበኙ የህዝቡን ስሜት ያነብቡ ነበር።
በሕዝብ አመኔታ ሳይሆን ይልቁንም በጆሮ ጠቢዎችና በመሳርያ በመተማመን እስካሁን ስልጣን ላይ ላላችሁት ገዢዎች ግን አንድ የምለው አለኝ።  የፈረንሳዩ አንባገነን ናፖሊዮን ቦናፓርት የነበረውን ሰራዊት እስተውሉ። ይህ ግዙፍ እና የሰለጠነ ሰራዊት በህዝብ እንደ አሸዋ ተበተነ። የግብጹ ሆስኒ ሙባረክ ያልታሰበ እና ያልታለመ ውድቀት የመጣው እንዲሁ በመሳርያ ከመተማመን እና ህዝብን ከመናቅ ነበር። ይህ አስደንጋጭ ትዕይንት ለእናንተ ትምህርት ካልሰጣቸሁ የሱ እጣ ፈንታ ይጠብቃችኋል። መቶ አመት የቆየ አንባገነን ገዢ በታሪክ አላየንም።
Breaking News from Helsinki: 

‹‹የከተማ ጦርነት አውጃችኋል!የተዘጋጀ ኃይል አለን ልካችሁን ያሳያችኋል›› ኮሎኔል ዘውዴ የየካ/ክ/ከ/ፖ/መ/ኃ

December 6, 2014
ሳሙኤል አበበ (በፖሊስ ታግቶ የነበረ)

ትናንት ከቀኑ 10 ሰአት አካባቢ ልክ እንደ ሰሞኑ ሌሎች ጓዶቻችን ላይ ይደረግ እንደነበረው የፖሊስና የደህንነት አፈና ሁሉ ፍቅረማርያም አስማማውን የህወሓት ቅልብ ደህንነትና ፖሊሶች አፍነው ወሰዱት፡፡ እኛም ቢያንስ ያለበትን ቦታ ለማወቅ ከትንታጉ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ ጋር በመሆን ፖሊስ ጣቢያዎችን ማሰስ ጀመርን፡፡ የመጀመሪያ መዳረሻ የሆነን የየካ ክ/ከተማ አድዋ ድልድይ ፖሊስ ጣቢያ ሆነ፡፡ እንደደረስንም በር ላይ የነበሩትን ሁለት ፖሊሶች ጓደኛችን በፖሊስ ተይዞ ወዳልታወቀ ቦታ ስለተወሰደ እዚህ መኖሩን ለማረጋገጥ ነው ስንላቸው ‹‹ልጁ እዚህ ገብቷል፡፡ ግን ምርመራ ላይ በመሆኑ ትንሽ ቆይታችሁ ኑ!›› ተባልን፡፡

እኛም ‹‹ምን አልባት ሊያድር ስለሚችል እራት እናስገባለት›› አልናቸው፡፡ አሁን እኛን አላናገረንም፡፡ በቀጥታ ውስጥ የቆሙት ሁለት ፖሊሶች ጋር ሄዶ አነጋገራቸውና ተመለሰ፡፡ ‹‹አሁን አይቻልም፡፡ ሂዱና ቆይታችሁ ተመለሱ፡፡›› የሚል ትዕዛዝም ሰጠን፡፡ በትዕዛዙ መሰረት ፊታችንን ከማዞራች ሰከንድ እንኳ ሳይሞላ ከውስጥ በጎርናና ድምጽ ‹‹ኑ ተመለሱ! እናንተም ትፈለጋላችሁ፡፡›› በማለት አምባረቀብን፡፡ እኛም ሳናቅማማ ገባን፡፡ ሁለቱም ፊታቸው ላይ ከፍተኛ ጥላቻና ንቀት ይነበብባቸዋል፡፡ የማስፈራሪያና ማሸማቀቂያ ቃላትን በተደጋጋሚ ይናገራሉ፡፡

እኛ ደገሞ ውስጣችን ያለው እውነት ነውና እንዳሰቡት ልንደናገጥላቸው አልቻልንም፡፡ ጓደኛዬ በላይ ማናዬን ‹‹ስትገባ ስቀሃልና ምን እንዳሳቀህ ንገረን!›› አለው አንደኛው ፖሊስ! በላይም ‹‹ይህ የአኔ የግል ጉዳይ ነውና ልትጠይቀኝም፣ ልነግርህም አልችልም›› ብሎ በልበ­ሙሉነት መለሰለት፡፡ ቀጥሎም‹‹ተፈተሹ!›› ተባልን፡፡ እኛም ‹‹ፍ/ቤት ትዕዛዝ ካልተሰጠ በስተቀር ምንም ሰው ሊፈተሸ አይገባምና እኛም አንፈተሸም›› አልን፡፡ እነሱም አስገድደው ፈተሹን! እንዲያውም ‹‹እኛምኮ ህግ እናውቃለን፡፡ እንድፈትሽም የለበስነው የፖሊስ ልብስ መብት ሰጥቶናል፡፡.ወዘተ..›› በማለት ህጉን ሳይሆን ፍላጎታቸውን ነገሩን፡፡

በዚህም ንትርክ መሃል የክፍለ ከተማው ኃላፊ ኮሎኔል ዘውዴ የተባሉ ሰው ግቢውን ዘልቀው እኛ ጋር ደረሱ፡፡ እንደደረሱም ‹‹እነኚህን ልጆች አውቃቸዋለሁ፡፡ ከአንተ ጋር በተደጋጋሚ ቁጭ ብለን አውርተናል፡፡ ግን ሁሌም ያው ናችሁ፡፡ ሊገባችሁ አልቻለም፡፡›› አሉን፡፡ በእርግጥ እኚህ ሰውዬ ጋር ለሚያዚያ 19/06 ዓ.ም የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ የወጡትን የፓርቲውን አባላት ከመንገድ ለቅመው ያሰሯቸውን ልጆች ለመጠየቅ በሄድኩ ጊዜ ከሁለት ሰዓት በላይ የፈጀ እልህ አስጨራሽ ክርክር አይሉት ውይይት ብቻ ቅጥ የሌለው ንግግር እንዳደረግን አስታውሳለሁ፡፡ ያኔ ያሉኝ ‹‹እናንተ ምን ፈልጋችሁ ነው? ልማቱ ተፋጥኗል፡፡ መንገዱ ኮንዶሚኒየሙ፣ ግድቡ፣ ዩኒቨርሲቲዎች ወዘተ ተገንብተዋል›› በማለት የተሞሉትን ዘከዘኩልኝ፡፡

እኔም ባይሰሙኝም ‹‹እዚህ አገር ያለው ስርዓት የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካ እና የማህበራዊ ቀውስ መውጣት ወደማንችልበት አዘቅት ውስጥ እየከተተን እንደሆነ ስነግራቸው etv እንደሚለው ጸረ­ልማት ብለው ከመፈረጅ አልተቆጠቡም፡፡ ዛሬም ከ8 ወር በኋላ ስንገናኝ በአቋማቸው ጸንተው እንዲያውም ከሬድዋን ሁሴን በልጠው አገኘኋቸው፡፡ ከላይ እስከታች እየገላመጡ ‹‹ከእናንተ ጋር እንተዋወቃለን፡፡ የከተማ ጦርነት አውጃችኋል፡፡ ይህ ደግሞ አይቻልም፡፡ ጫካ ግቡና ጦርነት ክፈቱ፡፡ ያኔ የተዘጋጀ ኃይል አለን፡፡ ልካችሁን ያሳያችኋል፡፡›› በማለት የህወሓት/ኢህአዴግን ፍላጎት ነገሩን፡፡ እነሱም እንዳሰቡት ልንሸማቀቅና ልንሰግድላቸው አልቻልንም፡፡ ረዥም ጊዜ ካቆዩን በኋላ ተጠራን፡፡ ስልካችንና መታወቂያችን መንግስቱ የተባለ መጀመሪያ ያገተን ፖሊሲ ይዞት መጣ፡፡ በማዝተዛዘንም ‹‹የያዝናችሁ በአመለካከታችሁ ወይንም እኛ ለአንድ ወገን በመቆም አይደለም፡፡ የያዝናችሁ ለሁላችንም ደህንነት ስንል ነው፡፡ ግን ላንግባባ እንችላለን፡፡›› በማለት አስረዳን፡፡ እኛም መጀመሪያ ዱላ ቀረሽ ንግግር፣ ክብር የሚነኩ ቃላትን ሲተፋ የነበረ ሰው አሁን ይህን ቢለን እንዴትስ ሊገባን ይችላል? ግቢውንም በእኩለ­ሌሊት ለቀን ወጣን፡፡ በመጨረሻም እንዲህ ልላቸው ወደድኩ፤ በእያንዳንዷ ቀን የምትፈጽሙብን ግፍ ለእኛ ብርታት፣ ትግላችንም አስፈላጊ መሆኑን የበለጠ ያስረዳናል እንጅ እናንተ እንደምታስቡት ይህ ግፍ መቀጣጫ ሆኖን ወደየ ቤታችን ፈጽሞ ልንመለስ አንችልም፡፡ ትግላችን እስከ መስዋዕትነት ደረስ ነው!!

Friday, December 5, 2014

ከመተባበርና አንድ ከመሆን በላይ ታላቅነት የለም – የሰማያዊ ከፍተኛ አመራር

December 5,2014
ፍኖተ ነፃነት
“አምናለሁ። አንድ ሆኖ ለአንድ ሀገር መቆም ብንችል እውነት ይሄ ታላቅነት ነው። ከዚህ በላይ ታላቅነት አለ ብዬ አላስብጭ፡፡”
“በፍቅር በሰላማዊ መንገድ በመነጋገር የማንንም ሰው ሀሳብ ማሸነፍ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።”
ወ/ሮ ሃና ዋልለልኝ ይባላሉ። የሰማያዊ ፓርቲ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልና የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ናቸው። ፍኖተ ነጻነት ባወጣው 86ኛ እትሙ ቃለ መጠይቃ ካደረገላቸው የተወሰደ ነበር። ከቅአለ መጠይቅቁ የተወሰነዉን እንደሚከተለው አቅርበናል።
ፍኖተ ነፃነት፡- በመጪው ምርጫ ላይ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ምንድን ነው የሚጠበቀው?
10344785_738568506228086_275256779448546603_n

ወይዘሮ ሀና፡ – ከተቃዋሚዎች የሚጠበቀው እርስበርሳችን በመስማማትና ትንንሽ ልዩነቶቻችንን በማስተካከል ባለችው ቀዳዳ፣ ጠባብ ቀዳዳ ማለት እችላለሁ ሾልከን ለውጥ ለማምጣት መትጋት ነው፡፡ የረጅም ጊዜ ልምድ አለ፤ ከዛ ውስጥ ደግሞ ነጥረው የሚወጡ ሰዎች ይኖራሉ፤ የሚታዩም አሉ። ጥሩ ጥሩ ወጣቶችም እያደጉና እያበቡ ነው። እነዚህን ነገሮች ወደ ተግባር ወይም ወደ ውጤት በመቀየር ለምርጫ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል። ምክንያቱም ሀገሪቷ ላይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በምርጫ የሚመጣ ስልጣን ብናገኝ በእውነት ይህቺ ሀገር ታላቅ ትሆናለች። ጥሩ ነገርም ይታይባታል፡፡ስለዚህም እርስ በእርሳችን በብዙ ፍትጊያ ውስጥ አልፈን በብዙ ዘረኝነት ውስጥ አልፈን እዚህ ደረጃ መድረስ ራሱ ትልቅነት ስለሆነ ይሄን ብናደርግ ደግሞ የተሻለ ትልቅ ሰው እንሆናለን ብዬ አምናለሁ። እርስ በርሳችንም እንከባበራለን፤ እንቻቻላለን፤ መቻቻሉ ግን በመተማመን ውስጥ መሆን አለበት ብዬም አምናለሁ።
ፍኖተ ነፃነት፡- በፖለቲካ ፓርቲዎች አብሮ በመስራት ላይ ሁለት አይነት አስተሳሰቦች በአደባባይ ሲራመዱ እናስተውላለን። ፓርቲዎች አንድ ላይ ተባብረው መስራት አለባቸው የሚል ወገን አለ፡፡ አንዳንዱ ደግሞ ብቻቸውን ነጥረው መውጣት አለባቸው ይላል፡፡ባንቺ አመለካከት አሁን ካለው የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አውድ አንጻር የትኛው ያዋጣል
ወይዘሮ ሀና፡- ፓርቲዎች ነጥረው ይወጣሉ የሚለው ነገር የእኔም ሀሳብ ነበረ። ጥረቱ ጥሩ ነው። ባልተሄደበት መንገድ መሄድ የአስተዋይነት ምልክት ነው። ባለንበት እንቁምና ባለንበት እንርገጥ የሚል አስተሳሰብ መኖር የለበትም። ሁልጊዜ የሰው ልጅ አዲስ ነገርን ይፈልጋል። አዳዲስ ነገሮችን ማምጣት ይፈልጋል። ስለዚህ ያልተደረጉ ነገሮችን መሞከርና ማድረግ ጤናማነት ነው። ያ ደግሞ የማይሳካበትን ሁኔታ ካወቅን ወይም ደግሞ በፊት አብሮ መስራቱ አይጠቅምም ብለን ከነበረ አሁን ይጠቅማል ወደሚለው ነገር ላይ አስተሳሰባችን ከመጣ ደግሞ ያንን ተቀብሎ ማራመድ ምንም የሚጎዳ ነገር አይደለም።
ሁለቱም ሀገርን ለመጥቀም ለውጥን ለማየት ከመፈለግ የመነጨ እስከሆነ ድረስ ጤናማ ናቸው፡፡ ለየብቻ መስራት የሚያዋጣ ነው ብለን እርግጠኛ ስንሆን ብቻችንን መስራት ይኖርብናል። እኔ አሁን ያለኝ እምነት አብሮ መስራት ታላቅ ያደርጋል ነው። ሁለተኛው ነገር ደግሞ ከአንድ ብርቱ ሁለት መድሃኒቱ የሚለው ተረት ቀላል አይደለም። በሶስት የተገመደ ገመድም ምን ያህል ጠንካራ እንደሆነ እናውቃለን። ከዚህ በፊት ለብቻችን ነጥረን እንውጣ የሚለውን ሀሳብ ከሚያራምዱት ውስጥ ነበርኩኝ። ያም የተደረገበት ምክንያትም ከመገፋት ወይም ደግሞ አቅምንና ያለንን እውቀት ለማውጣትእንዳንችል ከመደረግ አንፃር ነው።ሆኖም ግን ያንን ነገር ለውጠን የአብሮመስራታችንን ብቃታችንን ክህሎታችንን አሳድገን አብሮ በመስራት ለውጥ ማምጣት፣ ራሱን የቻለ ስኬት ነው ብዬ አምናለሁ። አንድ ሆኖ ለአንድ ሀገር መቆም ብንችል እውነት ይሄ ታላቅነት ነው። ከዚህ በላይ ታላቅነት አለ ብዬ አላስብም፡፡ ራስን ለሀገር መሰዋት ማድረግ ያስፈልጋል። በነገራችን ላይ እኔ መስዋዕት የምለው የመሞት የመታሰርን ብቻ አይደለም፡፡ ትልቁ መስዋዕትነት ማለት ፍላጎትን ሁላ ማሸነፍ መቻልን ራስ ወዳድነትን ማሸነፍ መቻልንና ለሌሎች መኖር መቻልን ነው፡፡ ለሌሎች መኖርን መልመድ መቻል አለብን። በአፍ ሳይሆን በተግባር ይሄን ካደረግን የማይፈነቅል ድንጋይ አይኖርም።
ፍኖተ ነፃነት፡- የፓርቲዎች የውስጥ ዴሞክራሲ ምን መሆን አለበት ትያለሽ? በየፓርቲዎቹ ውስጥ ያሉ አስቸጋሪ ባህርያቶችስ ምንድን ናቸው?
ወይዘሮ ሀና፡- ብዙ ጊዜ ችግራችን መደማመጥ አለመቻል ነው ብዬ አስባለሁ። እንደገና ደግሞ እኔ አውቃለሁ የሚሉ ሰዎች ካሉ የሌላውን ሀሳብ የሚገፉ ከሆነ የመናገር መብትን የሚገድቡ ከሆነ ሁልጊዜ ችግር መፈጠሩ አይቀርም፡፡ ከዛ ይልቅ ግን መደማመጥ ቢኖር በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር ቢኖር ስህተት ያለበትም ሰው ስህተቱን እንዲያምን በሀይል በጠብና በቁጣ ሳይሆን በፍቅር በሰላማዊ መንገድ በመነጋገር የማንንም ሰው ሀሳብ ማሸነፍ ይቻላል ብዬ አምናለሁ።
በሀሳብ ላይ መፋጨት በጣም ጠቃሚ ነው። የተሻለና የነጠረ ሀሳብ እንድናመጣም ያደርጋል። ያ ሰው ምንም ቢሆን ሀሳቡንም ማዳመጥ ማክበር ያስፈልጋል። እንደዚህ አይነት ነገሮችን አዳብረን ብንሄድ አሁንም ደግመዋለሁ የማንፈነቅለው ድንጋይ ይኖራል ብዬ አላምንም።
ፍኖተ ነፃነት፡- በመጨረሻ ማስተላለፍ የምትፈልጊው መልዕክት ካለ
ወይዘሮ ሀና፡- ማስተላለፍ የምፈልገው አንደኛ ለፓርቲዬ ማለትም ለሰማያዊ ፓርቲ ነው። ሰማያዊ ፓርቲ በውስጡ ምርጥ ምርጥ ወጣቶች አሉ፡፡ ብዛትም ባይሆን አንድ ሰው ለውጥ ያመጣል ብዬ አስባለሁ። ያንን ሰው ግን በአግባቡ መጠቀም መቻል አለብን ጓደኞቼን በጣም አከብራቸዋለሁ እወዳቸዋለሁ የአስተሳሰብ ልዩነታችንን በጣም አደንቃለሁ፤ በአስተሳሰብ ልዮነታችን ውስጥ ብዙ የተደበቁ ነገሮች ይወጣሉ ብዬ ስለማምን ስላየሁም ማለት ነው። ጥሩ ነገሮች ብቻ ሳይሆን የተደበቁ ስህተቶችም ይወጣሉ። ይህንን በደንብ አይቻለሁ፡፡ ይሄንን ነገር በደንብ አከብራለሁ። በውስጥ የሚሰራውንም ስራ በርቱ ግፉበት እላለሁ፡፡በተለይ በማንም ፓርቲ ውስጥ ያላየነውን የኦዲትና የኢንስፔክሽን ስራ አከብራለሁ ለዚህም በእውነት አድናቆቴን ማስተላለፍ እፈልጋለሁ። ጥሩ እየሰራ ነው። ፓርቲ ውስጥ ላሉ ችግሮች እስከ ቅጣት ድረስ በመሄድ ለማስተካከል የተሞከረውን ነገር ሳላደንቅ አላልፍም።
በሁለተኛ ደረጃ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎችንም አከብራለሁ አደንቃለሁ ብዙ ትምህርቶችን እንድማር አድርገውኛል አሁን ለደረስኩበት ብስለት እንድደርስ የእነዚህ ፓርቲዎች መፈጠር ጥሩ አጋጣሚና እድል ፈጥሮልኛል። ሀቀኛ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የጭቆናውን አመት ለመቀነስና በጭንቅ ላይ ያለችን ሀገር ለመታደግ መፍጠን አለባቸው። አሁን የዕንቅልፍ ጊዜ አይደለም፡፡የምንፈጥንበትን የሩጫ ሂደትና ቀስ የምንልበትን እንደገና ደግሞ አሯሯጭ የምንሆንበትን መለየት መቻል አለብን።
የኢትዮጲያ ህዝብንም የምለው ነገር ይኖራል፡፡ የኢትዮጲያ ህዝብ ሆይ! ተስፋ አትቁረጥ፤ ተስፋ የሚቆርጥ የሞተ ብቻ ነው። በቁም ያለ ሰው የሚፈልገውን ነገር እጁ ውስጥ እስካላስገባ ድረስ ተስፋ አይቆርጥም። እስከ መጨረሻ ህልፈተ ህይወቱ ድረስ ማድረግ ያለበትን በሙላ ያደርጋል። ሰው እንሁን፤ ስብእናችንን እንጠብቅ፤ እርስ በእርሳችን እንከባበር፤ እንተማመን፤ መተማመን አንድነትን ያመጣል፤ አንድ ከሆንን ደግሞ የማንሰራው ነገር አይኖርም። ከዓለም በታች ጭራ የሆነችውን ሀገር ከፍ እናደርጋታለን፡፡ለዚህ ደግሞ እግዚአብሔር
ይርዳን ማለት እፈልጋለሁ። አመሰግናለሁ።

በአዳር ሰልፉ ኢህአዴግ “ተሸብሯል”

December 5,2014
በስውርና በግልጽ አፈናው ተጧጡፏል
police 11
* የከምባታ ጠንባሮ ዞን ህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉ ተገለጸ
* የሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ በፖሊስ ተከብቦ አደረ
የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በፖሊስ ተከብቦ ማደሩንና አባላት ከውጭ እንዳይገቡ መደረጋቸውን ለአዳር ሰልፉ ቅስቀሳ ዝግጅት ቢሮ ያደሩ የፓርቲው አመራሮችና አባላት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ አመራሮችና አባላቱ እራት በልተው ወደ ፓርቲው ጽ/ቤት ሲመለሱ ቢሮው በፖሊስ ተከብቦ እንዳገኙትና ወደ ውስጥ እንዳይገቡ እንደተከለከሉ በቦታው የነበሩት የፓርቲው አመራሮችና አባላት ገልጸዋል፡፡
police 14አመራሮችና አባላቱ ፖሊስ ከ200 ሜትር ርቀት ውጭ ወደ ፖለቲካ ፓርቲ ጽ/ቤት መጠጋት እንደማይችል ቢከራከሩም ፖሊሶቹ “መመሪያ ተሰጥቶናል፤ አንሄድም!” ማለታቸው ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ከፖሊስ ጋር ሲከራከሩ የአካባቢው ህዝብ በመውጣቱ ፖሊሶቹ ፓርቲው ጽ/ቤት እንደራቁ ታውቋል፡፡
በሌላ በኩል ከውጭ ወደ ቢሮ ከሚመጡበት ወቅት የፓርቲው ቢሮ አካባቢ ምንነቱ ያልታወቀ ወረቀት ተበትኖ እንዳገኙና እነሱ ሲደርሱ ፖሊሶቹ እንዳነሱት የፓርቲው የምክር ቤት አባል ወጣት እየሩስ ተስፋው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻለች፡፡
*********************
በነገረ ኢትዮጵያ የፌስቡክ ገጽ ላይ የታተመው መረጃ እንደሚያመለክተው ፖሊስና ደህንነቶች ወደ ሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት የሚገቡና የሚወጡ አባላትንና አመራሮችን እያዋከቡ ይገኛሉ፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንና አባላትን “እንፈልጋችኋለን!” በሚል እየያዙ ሲሆን በተለይ ደህንነቶቹ መታወቂያ አሳዩ ሲባሉ ፈቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡
ሰማያዊ ቢሮ ጽ/ቤት የሚገኙ ደህንነቶች የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን እያፈኑ እየወሰዱ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ የሆነውን ፍቅረ ማሪያም አስማማውን አፍነው ወስደውታል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የገዥው ፓርቲ ደህንነቶች ተጨማሪ ሰዎችን አፍነዋል፡፡ የነገረ ኢትዮጵያ ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ በላይ ማናዬ እና የሰማያዊ ፓርቲ የወጣቶች ጉዳይ ምክትል ኃላፊ እንዲሁም የብሄራዊ ምክር ቤት ፀኃፊ ወጣት ሳሙኤል አበበ በደህንነቶች ታፍነው መወሰዳቸውን ነገረ ኢትዮጵያ በዚሁ የፌስቡክ ገጹ ዘግቧል፡፡volunteers of 9 parties
ከጥቂት ሰዓታት በፊት የተሰራጨው መረጃ እንደሚያመለክተው የአዳር ሰልፉን የጠሩት የ9ኙ ፓርቲዎች ቢሮ በፌደራል ፖሊስ ተከብቧል፡፡ እንዲሁም የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር አባል የሆነው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ቸርቺል የሚገኘው ጽ/ቤት በፌደራል ፖሊስ ተከቧል፡፡ ከሰማያዊ ጽ/ቤት መውጣትም ሆነ መግባት የማይቻል ሲሆን በርካታ አመራርና አባላት ታፍነው ታስረዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የትብብሩ አመራሮች ስልክ እንዳይሰራ እየተደረገ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር የኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ስልክ እንዳይሰራ ተደርጓል፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በተሰራጨ መረጃ መሠረት የሰማያዊ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት ስራ አስፈጻሚ ፀኃፊ የሆነው ወጣት አወቀ ተዘራ ወደ ቤቱ በሚገባበት ወቅት በስርዓቱ የደህንነት ኃይሎች ተይዞ ታስሯል፡፡ ፍቅረማሪያም አስማማው፣ አወቀ ተዘራና ተስፋሁን አለምነህን ጨምሮ በደህንነቶች የታፈኑት ወጣቶች የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡
በተያያዘ ዜና የከምባታ ጠንባሮ ዞን ህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉ ተገለጸ፡፡ በገዥው ፓርቲ አድሏዊ አሰራር ምክንያት ልማትና መልካም አስተዳደር ባለመኖሩ የከንባታ ጠንባሮ ነዋሪዎች ዛሬ ህዳር 26/2007 ዓ.ም ዱራሜ ከተማ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጋቸውን የከምባታ ህዝብ ኮንግረንስ ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርዲሎ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ህዝብ ያለ ማንም ቀስቃሽና አስተባባሪ ሰላማዊ ሰልፍ መውጣቱን የገለጹት አቶ ኤርጫፎ የብሄር ብሄረሰቦችን መብት አከብራለሁ በሚል ለፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ ከማድረጉ ውጭ በተግባር ግን በህዝብ ላይ ከፍተኛ በደል እየፈጸመ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡
የከንባታና ጠንባሮ ህዝብ ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ ተቃዋሚዎችን በተለይም የከምባታ ህዝብ ኮንግረንስን ትደግፋላችሁ በሚል በደል እንደሚደርስበት የገለጹት አቶ ኤርጫፎ “ህዝቡ በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት በደል እየደረሰበት ነው፡፡ ምርጫ ሲደርስ መንገድ፣ ዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ይሰራልሃል ይባላል፡፡ ምርጫው ሲያልፍ ለማታለያነት ይሰራሉ የተባሉ ነገሮች ተግባራዊ አይሆኑም፡፡ እስካሁን ከ1993 ዓ.ም አንስቶ ይሰራል የተባለ መንገድ አልተሰራም፡፡ በምርጫ ወቅት አርሶ አደሮችን እያፈናቀሉ ኮሌጅና ዩኒቨርሲቲ እንሰራለን ይላሉ፡፡ ከምርጫ በኋላ ግን ይህ መሬት የሚሰጠው ለሹመኞች ነው፡፡ ሁለቱም ጠቅላይ ሚኒስትሮች የምርጫ ሰሞን በየቦታው የመሰረት ድንጋይ ተክለዋል፡፡ ከምርጫ በኋላ ግን ለሹመኞች ይሰጣል፡፡ ዛሬ ህዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ የወጣውም ከዚህ አንጻር ነው” ሲሉ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
የከንባታ ጠንባሮ ህዝብ ባለፉት ምርጫዎች ተቃዋሚዎችን በመምረጥ ከገዥው ፓርቲ ጋር ያለውን ልዩነት በግልጽ እንዳሳየ የገለጹት አቶ ኤርጫፎ “ወጣቶች ልማትና የትምህርት እድል ስለማያገኙ ወደ ደቡብ አፍሪካና አረብ አገራት እየተሰደዱ መንገድ ላይ እየሞቱ ነው፡፡ በቀን 11 አስከሬን የመጣበት ጊዜ አለ፡፡ በስርዓቱ አድሏዊ አሰራር ምክንያት ከንባታ ጠንባሮ ወጣቱ ከቀየው እየተፈናቀለ የሚሰደድበት ትልቁ ዞን ነው ማለት ይቻላል” በማለት አስረድተዋል፡፡
በዛሬው እለት አርሶ አደሩ፣ ተማሪውና ነጋዴው የዞኑ ጽፈት ቤት ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ከማድረጉም ባሻገር በቀጣይነት በየወረዳዎቹ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚየደርግ ገልጾአል ሲሉ ሊቀመንበሩ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ (ለመረጃ ጥንቅሩና ለፎቶዎቹ፡ ነገረ ኢትዮጵያ)
ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የተወሰደ

Thursday, December 4, 2014

ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ አመክሮ ተከለከለች

December 4,2014
(ኢ.ኤም.ኤፍ) ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ “ሽብርተኛ” ተብላ በእስር ላይ የምትገኝ ሲሆን እንደማንኛውም እስረኛ ልታገኝ የሚገባውን አመክሮ ሳታገኝ ቀርታለች:: በመሰረቱ አመክሮ የሚሰጠው አንድ እስረኛ በ እስር ቤት ቆይታው ወቅት የሚያሳየው መልካም ባህሪ ተገምግሞ ለአንድ እስረኛ ከተፈረደበት አመት ተቀንሶ እንዲወጣ ይደረጋል:: ከቤተሰብ ያገኘነው መረጃ እንደሚያስረዳው ከሆነ ለርዕዮት አለሙ ሊሰጣት የነበረው የአመክሮ ቅፅ “ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” የሚል ነው::
ከዚህ በፊትም “አጥፍቻለሁ ይቅርታ ይደረግልኝ” ተብሎ በፕሬዘዳንቱ አማካኝነት የሚደረገውን ሂደት ሳትቀበለው ቀርታ የይቅርታ ደብዳቤ አለማገባቷ ይታወሳል:: አሁን በቅርቡ ማድረግ የሚቻለውን “አመክሮ” ተቀብላ ቢሆን ኖሮ አሁን ከ እስር የምትወጣበት ወቅት እንደነበር ከቤተሰብ አካባቢ ያገኘነው ምንጭ አረጋግጧል::ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን በዚህ ጉዳይ ያነጋገራት ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኤጀንሲ የመጣ ሰው ነበር:: በውይይታቸው ወቅት “ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” የሚለውን አባባል ለመቀበል አልቻለችም:: ምክንያቱም ሃሳቧን በጽሁፍ ስለገለጸች ነው “አሸባሪ” ተብላ የታሰረችው:: ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኤጀንሲ የመጣውም ሰው “እንግዲያው አንቺ ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” ብለሽ የማትፈርሚ ከሆነ እኛም አመክሮ አንሰጥሽም ብሏታል::

የሃና ላላንጎ ጉዳይ በዝግ ችሎት ታየ

December 4,2014
ቤተሰቦቿ ሐኪሞችንና ፖሊሶችን ወቀሱ
Hana-lalango

* “አሸባሪዎችን” ለይቶ የመያዝ ልዩ ችሎታና ብቃት ያለው ፖሊስ ያልያዘው ተጠርጣሪ አለ
ሃና ላላንጎ የተባለችውን ተማሪ በሚኒባስ ታክሲ አፍነው በመውሰድ፣ በቡድን በመድፈርና ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙትን አምስት ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ጉዳይ በዝግ ችሎት መታየት ጀመረ፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ለሦስተኛ ጊዜ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት፣ ቂርቆስ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊስ ቀደም ባለው ቀጠሮ እንደሚሠራቸው ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት፣ ለችሎቱ ያስረዳበትና ተጠርጣሪዎቹን ያቀረበበት ሰዓት፣ ከሌሎች ቀናት የተለየ ነበር፡፡
ሟች ሃና ላላንጎ በቡድን ተደፍራ ሕይወቷ ማለፉ በመገናኛ ብዙኃን ከተሰራጨበት ጊዜ አንስቶ እያነጋገረ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየቀጠሮው ፍርድ ቤት የሚገኘው ታዳሚ ቁጥር ጨምሯል፡፡ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. እንደተለመደው ፖሊስ ዘግየት ብሎ ከ4፡30 ሰዓት በኋላ እንደሚመጣ በማሰብ፣ ሕዝቡ ወደ ፍርድ ቤት መድረስ የጀመረው በአብዛኛው ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ጀምሮ ነበር፡፡
የጠዋቱ ጊዜ ወደ እኩለ ቀን እየተቃረበ በመሄዱ፣ ሕዝቡ እርስ በራሱ “አራዳ አቅርበዋቸዋል አሉ፤ አይ አይደለም ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ክስ መሥርተዋልና ፖሊስ እንጂ ተጠርጣሪዎቹ አይቀርቡም፤” የሚሉና ሌሎች መላምቶችን በመነጋገር ላይ እያለ፣ ፖሊስ ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ላይ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ ቀርቦ፣ ማንም ወደ ችሎት ሳይገባ በዝግ ችሎት፣ የሠራውን የምርመራ ሒደት ለፍርድ ቤቱ ካስረዳ በኋላ፣ ለሚቀረው ተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናትን ጠይቆ እንደተፈቀደለት ተሰማ፡፡ ለታኅሣሥ 6 ቀን 2007 ዓ.ም. መቀጠሩም ታወቀ፡፡
የተነገረውን ለማረጋገጥና ተጨማሪ መረጃ ለመስማት ቀጠሮውን ወደሰጡት ዳኛ የሟች ዘመዶችና የመገናኛ ብዙኃን በመሄድ ሲጠይቁ፣ ጠዋት በሥራ ሰዓት ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ በመቅረብ፣ ችሎቱ በዝግ እንዲታይለት ባመለከተው መሠረት ፍርድ ቤቱም ስላመነበት በዝግ ችሎት መታየቱ ተረጋገጠ፡፡
በሕገ መንግሥቱም ሆነ በፍርድ ቤቶች አሠራር በዝግ መታየት ያለባቸው የወንጀል ድርጊቶች መኖራቸው እንዳለ ሆኖ፣ ተማሪ ሃና ላላንጎን ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ጉዳይ፣ ለሁለት ጊዜያት በግልጽ ችሎት ከታየ በኋላ፣ በየትኛው የሕግ መሠረት ሦስተኛው ቀጠሮ በዝግ ሊታይ እንደቻለ ማብራሪያ እንዲሰጡ ዳኛው ተጠይቀው ነበር፡፡
የሃና ጉዳይ በዝግ ችሎት እንዲታይ የተወሰነው፣ ፖሊስ ምርመራውን ሳይጨርስ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃንና ድረ ገጾች፣ የሆነውንና ያልሆነውን ዘገባ በማሰራጨት ለምርመራው እንቅፋት እየፈጠሩበት መሆኑን አስረድቶ፣ ምርመራውን እስከሚያጠናቅቅ ድረስ በዝግ ችሎት እንዲታይለት መጠየቁ አሳማኝ ሆኖ በመገኘቱ በዝግ ችሎት እንዲታይ መፈቀዱን አስረድተዋል፡፡
hana 2ፖሊስ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ተጠርጣሪዎቹን በችሎት አቅርቦ ቀደም ባለው ችሎት ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት ምን ያህሉን እንደሠራና ምን ያህሉ እንደቀረው ማወቅ ባይቻልም፣ ቀደም ባለው ቀጠሮ ተጨማሪ 14 ቀናትን ጠይቆ፣ ፍርድ ቤቱ ‹‹10 ቀናት ይበቃሃል›› በማለት ከጠየቀው ቀናት ላይ አራት ቀናትን የቀነሰ ከመሆኑ አንፃር፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. የጠየቀውን 14 ቀናት ሙሉውን መፍቀዱ፣ ሌላ ተጨማሪ ተጠርጣሪ የመያዝና በርካታ ቀሪ ምርመራ ሳይኖረው እንዳልቀረ ጥርጣሬ አሳድሯል፡፡
የሟች ተማሪ ሃና ወላጅ አባት አቶ ላላንጎ አይሶ ኅዳር 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በየሳምንቱ እሑድ ምሽት ላይ በኢቢኤስ በሚቀርበው “ሰይፉ ፋንታሁን ሾው” ላይ ቀርበው ፖሊስ አንድ ተጠርጣሪን መያዝ እንደሚቀረው በመናገራቸው፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ጉዳዩ በዝግ መታየቱንና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን ተከትሎ ጥርጣሬውን አጠናክሮታል፡፡
አቶ ላላንጎ ሟች ልጃቸው መስከረም 21 ቀን 2007 ዓ.ም. ታፍና መወሰዷንና ለ20 ቀናት አስታመዋት፣ በደረሰባት ከባድ ጉዳት ልትተርፍ አለመቻሏን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ላላንጎ ገለጻ፣ ልጃቸው ጦር ኃይሎች ሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተጥላ ከተገኘች በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ አለርት ሆስፒታል ወስደዋታል፡፡ የአለርት ሆስፒታል ዶክተሮች ተመልክተዋት በስለት በመወጋቷና በደረሰባት የመደፈር አደጋ ሕይወቷን ልታጣ እንደምትችል በመናገር፣ ሕይወቷ ከማለፉ በፊት ቃሏን ለፖሊስ እንድትሰጥ በመናገራቸው ቃሏን እንድትሰጥ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
የሃና ላላንጎ ወላጅ አባት ስለልጃቸው ስቃይ እንዳብራሩት፣ አለርት ሆስፒታል ከአቅሙ በላይ መሆኑን ገልጾ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሪፈር ተብለው ሲወስዷት፣ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ደግሞ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሪፈር እንዲወስዷት እንደነገራቸው አስረድተዋል፡፡ ያለምንም ሕክምና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ መልሶ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሲልካቸው ተስፋ የቆረጡት አቶ ላላንጎ፣ ልጃቸውን በቀጥታ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል መውሰዳቸውን ትተው፣ ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመውሰድ አንድ ቀን አድራና ቤተሰቦቿን ተሰናብታ፣ በማግስቱ ወደ ጋንዲ ሆስፒታል እንደወሰዷት ገልጸዋል፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ጋንዲ ሆስፒታል በሪፈር የሄደችው ሟች ሃና፣ ይኸ ሁሉ ውጣ ውረድ ሲደረግ ደም እየፈሰሳትና ቁስሏም ወደ ሌላ ሕመም እየተቀየረ መሆኑን የገለጹት አባቷ፣ ሙሉቀን በጋንዲ ሆስፒታል ከቆየች በኋላ፣ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል አልጋ ተገኝቶላት መተኛት መቻሏን ተናግረዋል፡፡
የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ሐኪሞች የሃናን ጉዳትና ሕመም ሲመለከቱ፣ በከፍተኛ ሐዘንና እንባ ታጅበው ለማትረፍ የተረባረቡ ቢሆንም፣ ችግሩ ወደ ሌላ ነገር ተቀይሮ የነበረ በመሆኑ ሕይወቷ ሊተርፍ አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡
አቶ ላላንጎ የልጃቸውን ስቃይ በሐዘን ሲገልጹ፣ ሐኪሞችንና ፖሊሶችን ወቅሰዋል፡፡ “ሁሉንም ሐኪምና ሁሉንም ፖሊስ በጅምላ መውቀስ አልፈልግም፤” ብለው፣ መልካምና ሥራቸውን የሚወዱ፣ ኃላፊነታቸውን የሚወጡ ሐኪሞችና ፖሊሶች ስላሉ እነሱን ማመስገን እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ ልጃቸው ደም እየፈሰሳት በሄዱበት ሆስፒታሎች “አልጋ የለም፣ ውጭ አስመርምሯት” ማለትና ችላ ማለት ተገቢና የገቡለትም ቃል ኪዳን ባለመሆኑ፣ ተገቢ አለመሆኑን በመናገር፣ መንግሥትም ሊከታተለው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ፖሊሶችም ቢሆኑ፣ ጉዳዩን በትጋት ተከታትለውና ራሳቸው የሚሆነውን እንደማድረግ “እዚያ ውሰድ እኛ ጋ አይደለም” በማለት እንዲንገላቱ ማድረጋቸው ተገቢ ባለመሆኑ መንግሥትም ሊያየው የሚገባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ ሪፖርተር)

Wednesday, December 3, 2014

TPLF shockingly admits failures in Ethiopia

December 3,2014
By Admasu Belay
TPLFSince it came to power over 20 years ago, the TPLF regime has always declared its achievements in Ethiopia’s political and economic sectors. Everybody knows the state media ETV and its daily nonstop propaganda of how much better Ethiopia has become over the years. Not only that, TPLF has been telling the international community about how it changed and transformed Ethiopia. So much so that it had even deceived some Bush and Obama adminstration officials to believe its lies.
But after over 20 years, the London-based Financial Times (FT) reported today that TPLF has finally admitted its massive failures in Ethiopia.
Shockingly, the TPLF admitted its disasterous policy of landlocking Ethiopia and its economic impact as well as the risk of another famine in Ethiopia.

Lessons for those who harp on TPLF’s non-existing “Economic Growth” and other “achievements”

“The document, seen by the Financial Times, is a sobering reminder of the risk of investing in one of Africa’s less developed nations. With gross domestic product per capita at less than $550 per year, Ethiopia is the poorest country yet to issue global bonds.
In the 108-page prospectus, issued ahead of its expected $1bn bond, Ethiopia tells investors they need to consider the potential resumption of the Eritrea-Ethiopia war, which ended in 2000, although it “does not anticipate future conflict”.
There is also the risk of famine, the “high level of poverty” and strained public finances, as well as the possible, if unlikely, blocking of the country’s only access to the sea through neighbouring Djibouti should relations between the two countries sour.
Addis Ababa, Ethiopia’s capital, also warns that it is ranked close to the bottom of the UN Human Development Index – 173rd out of 187 nations – and cautions about the possibility of political turmoil. “The next general election is due to take place in May 2015 and while the government expects these elections to be peaceful, there is a risk that political tension and unrest?.?.?.?may occur.” “
For the last two decades, this “F word,” was banned by Meles and all his TPLF disciples. In the past, If any foreign officials dared to use the words “famine” and “Ethiopia” in the same sentence, the wrath of TPLF’s “ministry of foreign affairs (mfa)” would attack and humiliate them with endless MFA press releases. Meles himself told Ethiopians to forget about famine and promised that even our poorer people “will eat three times a day very soon.” That promise was made in 1994! Ironically today, the TPLF government sent a document to international investors, admitting another ” risk of famine, the high level of poverty” in Ethiopia, according to the Financial Times.
Not only has Ethiopia lost most of its hard currency reserves but the “steadily depreciating exchange rate may adversely affect Ethiopia’s economy?,” according to the TPLF document
That is not all. TPLF also admitted the chance of “resumption” of the war with Eritrea and more unrest from “political turmoil” as well as bad relations with Djibouti causing the “blocking of the country’s only access to the sea.”
It is about time TPLF accepted its failures!

Regarding the 5th TPLF policy, everybody knows TPLF has failed. Soon it will admit this failure too.
In 1995, TPLF claimed its “ethnic federalism” system will empower tribes without dividing Ethiopians. But today, Ethiopia is the most ethnically divided country in the world. Ethnic hatred, propaganda and tensions today are the highest ever in history. Just like the 1990s Rwanda, tribalism has destroyed Ethiopian nationalism and humanity. Sooner or later, TPLF will be forced to admit its last and final failure.
Regardless, Today will go down in history as the day TPLF admitted that it has achieved almost nothing (other that a few tall buildings) since it removed the DERG regime in 1991. It has failed Ethiopia in every way possible. The only reason TPLF is still in power is because Ethiopians are peaceful people, unlike the warmongering and hate-filled TPLF.
For all those EPRDF ruling party supporters and TPLF footsoldiers worldwide, this must be the most embarasssing day. One single TPLF document has virtually dismissed over 20 years of ETV propaganda

አሶሳ በከፍተኛ የመከላከያ ጥበቃ ስር መውደቁዋ ተሰማ፡፡

December 3,3014

9ነኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል የሚያስተናግደው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ዝግጅት ማጠናቀቁን ቢገልጽም፣ በአካባቢው መንግስትን የሚቃወሙ ኃይሎች በተለያየ ጊዜያት በደፈጣ ውጊያ ጥቃት ማድረሳቸው ያሰጋው መንግስት በአካባቢው ከፍተና ወታደራዊ ሃይል አሰማርቷል።

ህዳር 29 ከሚካሄደውን በዓል ጋር ተያይዞ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል ብዙዎች የሚሰጉ ሲሆን፣ ጥቂት የማይባሉ አመራሮች፣ ባለሃብቶችና ታዋቂ ሰዎች በተለያዪ ሰበቦች የጉዞ እቅዳቸውን የሰረዙ መሆኑ ታውቆአል፡፡

በቤንሻንጉል ክልል የተመሠረተው የአባይ ግድብ ጨምሮ በዋና ከተማዋ አሶሳ ከወትሮው በተለየ መልክ በኮንቮይ የታገዘ ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገ ሲሆን ለጸጥታ ሲባል እንደልብ መዘዋወር መከልከሉ ተሰምቷል፡፡

የፌዴሬሽን ምክርቤት የዘንድሮው በዓል የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ሕገመንግስቱን ያጸደቁበትን 20ኛ ዓመት ጭምር የሚያከብሩበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን በመጥቀስ በተደጋጋሚ መግለጫ የሰጠ ሲሆን ይህንን በዓል ለማክበርም ከ2ሺ500 በላይ እንግዶች ወደስፍራው ይጓዛሉ ተብሎ ይጠበቅ እንደነበር ታውቆአል፡፡


ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን የተውጣጣ ቡድን ነገ ሐሙስ ወደስፍራው የሚያቀና ሲሆን ከኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (የቀድሞ ኢቲቪ) ብቻ ከ100 በላይ ጋዜጠኞችና ባለሙያዎች አሶሳ መግባታቸው ታውቆአል፡፡


በስተሰሜን ምዕራብ ሀገሪቱ ክፍል የሚገኝ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአሁኑ ሰዓት የህዝብ ቁጥሩ 964 ሺ 647 ደርሷል፡፡ በክልሉ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ማለትም በርታ ፤ ጉሙዝ ፤ ሽናሻ ፤ ማኦ፣ ኮሞ ኦሮሞና አማራ የሚገኙ ሲሆን እነዚህ ብሔር ብሔረሰቦች ከዚህ ሥርዓት ቀጥተኛ ተጠቃሚ ካለመሆናቸውም በላይ መሬታቸው ለውጪ ባለሃብቶች ጭምር ያለፈቃዳቸው በገፍ የሚሰጥ በመሆኑ በጅምላ የመፈናቀል አደጋና በሰፈራ ስም ከቀዩአቸው እንዲሰደዱ በመደረጋቸው በሕዝቡ ውስጥ ከፍተኛ ቅሬታ መኖሩን ዘጋቢያችን ገልጻለች።


ምንጭ ኢሳት ዜና

በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ

December 3,2014
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ዛሬ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡

ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡

በጠቦቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ ግልባጭ ሳይደርሰን ተሻሻለ የተባለው ክስ መሰማት የለበትም ብለው የነበር ቢሆንም፣ ክሱን አይታችሁ መቃወሚያ ካላችሁ አስተያየት እንድትሰጡበት እድል እንሰጣለን ያለው ፍርድ ቤቱ ክሱ እንዲሰማ አድርጓል፡፡

ፍርድ ቤቱ ጠበቆቹ ያላቸውን አስተያየት ይዘው እንዲቀርቡ ለታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡
Photo: በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ዛሬ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡

ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡

በጠቦቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ ግልባጭ ሳይደርሰን ተሻሻለ የተባለው ክስ መሰማት የለበትም ብለው የነበር ቢሆንም፣ ክሱን አይታችሁ መቃወሚያ ካላችሁ አስተያየት እንድትሰጡበት እድል እንሰጣለን ያለው ፍርድ ቤቱ ክሱ እንዲሰማ አድርጓል፡፡ 

ፍርድ ቤቱ ጠበቆቹ ያላቸውን አስተያየት ይዘው እንዲቀርቡ ለታህሳስ 7 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል፡፡

Tuesday, December 2, 2014

The Zone9 Defense: Limits of International Law

December 2, 2014
by Ivan Sigal (World Policy Blog)
The international human rights system is broken – or perhaps it never worked at all.An Ethiopian court granted police 10 more days to investigate six bloggers and journalists
In case after case, citizens’ human rights are violated under the national laws of their respective countries, despite the existence of international human rights commitments in the United Nations’ Universal Declaration, and by The Organization for Security and Cooperation in Europe, the Organization of American States, the African Commission, and others. The International Criminal Court has little say concerning any but the most egregious of international human rights violations, and member states have wide latitude to dispense justice as they see fit.
For those who live in countries that fail to provide or enforce their own laws protecting freedom of expression, international principles have rarely provided actual recourse. This is the case, today, with the independent Ethiopian blogger collective known as Zone9.
In April of this year, the government of Ethiopia arrested six members of Zone9 and affiliated journalists in Addis Ababa. They were held for months without a formal charge and were denied the ability to communicate. Testimony from Befeqadu Hailu, one of the accused bloggers who was smuggled out of prison in August, as well as statements in court, allege mistreatment and frequent beatings. Informally, the nine were held on accusations of “working with foreign organizations that claim to be human rights activists and…receiving finance to incite public violence through social media.”
In July, the Zone9 prisoners were charged under Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation of 2009 for receiving support from political opposition organizations, defined formally by the government as terrorists, and receiving training from international activists in email encryption and data security from the Tactical Technology Collective, a group that helps journalists and activists protect themselves from digital surveillance.
The Zone9 bloggers joined other media outlets targeted under similar laws, including Eskinder Nega, who had reported on recent Arab uprisings and the possibility of similar uprisings in Ethiopia. He was arrested and charged with the “planning, preparation, conspiracy, incitement and attempt” of terrorism and sentenced to 18 years in prison.
International appeals from human rights advocacy organizations have had little effect on the case. In May, UN High Commissioner for Human Rights Navi Pillay issued a statementexplaining, “The fight against terrorism cannot serve as an excuse to intimidate and silence journalists, bloggers, human rights activists and members of civil society organizations. And working with foreign human rights organizations cannot be considered a crime.” Additionally, seven international human rights and press freedom organizations pressed the African Commission and the United-Nations in an urgent appeal to intervene in the case against Zone9. The appeal focused on the lack of clear charges and failure to allow the defendants adequate legal representation.
Nani Jansen, a lawyer for the Media Legal Defence Initiative and the lead signatory in the appeal, writes in an email that both the African Commission and the UN “operate under the cover of confidentiality in the early stages of these matters: when they follow up with a Government, this is done without informing the outside world. Only months and months (often over a year) later, these exchanges with a Government get published in the mechanism’s report to its supervisory body.” Thus any intervention joins the rest of those in the cone of silence that is Zone9—hidden from public scrutiny or participation.
Even if these bodies do follow up with the Ethiopian government, their recourse is limited. In an article on the urgent appeal, Jansen notes that the African Commission can condemn the arrests in a resolution, that both organizations’ rapporteurs can request official visits to Ethiopia to investigate, and that Ethiopia, as a member of the UN Human Rights Council, would be obligated to honor such a request. But even should such requests be made, and investigations conducted, there is little chance of enforcement of hypothetical findings on the Ethiopian government.
Since the appeal, the Ethiopian government has proceeded with charges against the accused. The latest details on the trial can be found on the website trialtrackerblog, run by people close to the defendants.
Public attempts to highlight the Ethiopian governments’ transgressions against human rights such as the #Freezone9bloggers social media campaign have an indirect effect. They aim to shame the Ethiopian government to ensure better treatment for the prisoners. They also seek to pressure international organizations and Ethiopia’s allies such as the United States, for whom Ethiopia is a critical military and security partner. The hope is that those organizations will in turn employ political pressure on Ethiopia to free the Zone9 defendants.
The implementation of international commitments seems to rest primarily upon a negotiated process of politics, not a functioning and enforceable system of law. Considering the ease with which national law in Ethiopia is employed or ignored for political ends, it is a grim irony that only political pressure can hope to resolve the case in their favor.
*****
To read more about the Zone9 bloggers, read our Fall 2014 article Joining Zone Nine.
Ivan Sigal is the executive director of Global Voices, a non-profit online global citizen media initiative. He is also a fellow at the Berkman Center for Internet & Society at Harvard University, where he studies digital storytelling and online communities.