Tuesday, January 19, 2016

ኢህአዴግ/ህወሓት ለኢትዮጵያ ድንበር በሞቱት አባቶቻችን ደም ውስጥ እጁን ነከረ!

January 19,2016

በገንዘብ፣በጎጥ እና በደም ጥማት የሚንቀለቀል ልቦና የተሸከሙት የአራት ኪሎ ባለስልጣናት አፄ ቴዎድሮስ ከነገሱበት እስከ አፄ ዮሐንስ የተሰዉበትን መሬት ለሱዳን ለመሸጥ ተስማምተዋል።የሱዳን ትሪቡን ጋዜጣ ትርጉም ይዘናል።


ኢህአዴግ/ህወሓት ለኢትዮጵያ ድንበር በሞቱት አባቶቻችን ደም ውስጥ እጁን ነከረ! አፄ ቴዎድሮስ ከነገሱበት እስከ አፄ ዮሐንስ የተሰዉበትን መሬት ለሱዳን ለመሸጥ ተስማምቷል። ኢትዮጵያ የተዳከመች ሲመስላቸው ጠላቶቿ ስነሱባት መስማት አዲስ ነገር አይደለም። አዲስ ነገር የሚሆነው በቤተ መንግስቷ በኢትዮጵያ ስም መንግስት ነኝ የሚሉ ስብስቦች የኢትዮጵያን ጥቅም ከባዕዳን ጋር ሲዶልቱ፣ሲሸጡ እና ሲያስማሙ መመልከት ነው።በገንዘብ፣በጎጥ እና በደም ጥማት የሚንቀለቀል ልቦና የተሸከሙት የአራት ኪሎ ባለስልጣናት አፄ ቴዎድሮስ ከነገሱበት እስከ አፄ ዮሐንስ የተሰዉበትን መሬት ለሱዳን ለመሸጥ ተስማምተዋል።ይህ ሕሊናን የሚያደማ ብቻ ሳይሆን የመኖር እና ያለመኖር ህልውና ጉዳይ ነው።''ዳሩ ሲነካ መሃሉ ዳር ይሆናል'' የሚለው አባባል እዚህ ላይ ማሰቡ ተገቢ ነው።ይህ ሥራ በመንግሥትነት እራሳቸውን የሾሙ ስብስቦች ኢትዮጵያን የማፈራረስ ልክ የት ድረስ እንደሚሄድ ብቻ ሳይሆን የከሃዲነት ደረጃቸው እና ህዝብን የመናቃቸው መጠን ምን ያክል እንደሆነ ማሳያ ነው።

አቶ ኃይለማርያም በድንበሩ አካባቢ የሚያርሱ ገበሬ ኢትዮጵያውያንን የህዝብ ተወካይ ነኝ ባሉ ምክር ቤት ስም ''ሽፍቶች'' እያሉ የተሳደቡትን ስድብ የሱዳኑ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እብራሂም ጋንዱር ለአልጀዝራ በሰጡት መግለጫ ላይም ደግመውታል።ኢትዮጵያውያንን እርሳቸው ብቻ ሳይሆኑ በስልጣን ላይ የተቀመጠው የኢትዮጵያ መንግስትም እንደሚገልላቸው ሲገልጡ ''ኢትዮጵያ እና ሱዳን በሱዳን ግዛት ላይ የሰፈሩትን ሽፍቶች  (gangs) በመግታት የድንበር ማካለሉን ሥራ በአንድነት እየሰሩ ነው'' ነበር ያሉት።አሁን የንግግር እና የወሬ ጊዜ አይደለም።ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል በሙሉ መለየት አለበት።ኢትዮጵያን ከሸጡ ጋር ነህ ወይንስ አይደለህም? ጥያቄው ይህ ነው።ኢትዮጵያን የከዳ በሙሉ ተገቢውን ቅጣት ማግኘት አለበት።

ኢህአዴግ/ህወሓት ለኢትዮጵያ ድንበር በሞቱት አባቶቻችን ደም ውስጥ እጁን ነክሯል።የኢትዮጵያ የቀደሙት መሪዎች ማናቸውም የኢትዮጵያን ድንበር ጉዳይ ላይ ሲደራደሩ አልታዩም።አፄ ዮሐንስ ከደርቡሽ ጋር ተዋግተው መተማ ላይ አንገታቸው የተቀላው ለአገራቸው ክብር ነው።አፄ ቴዎድሮስ መቅደላ ላይ እራሳቸውን የገደሉት ለኢትዮጵያ ክብር ነው።ዛሬ ሚልዮኖች ያፈሰሱትን ደም እረግጦ የኢትዮጵያን መሬት ለባዕዳን አሳልፎ ለመስጠት የተነሳው የህወሓት ቡድን የሕዝብ ፍርድ ያስፈልገዋል።

ወቅቱ እያንዳንዱ ሰው ለድንበሩ ዘብ የሚቆምበት ጊዜ ነው።ባዕዳን ዳር ድንበሩን ሲፈልጉ ከመሃል በጎሳ እንድንቧደን እና እንድንጋጭ በማድረግ ጭምር ነው።ለእዚህም የሚረዳቸው የአራት ኪሎ መንግስት አለ።ሱዳን የኢትዮጵያን መሬት ስትወስድ ብቻዋን አትሆንም ኢትዮጵያን ለዘመናት ለማዳከም የሚማስኑ የአረብ ሊግ አባላት እና የሩቅ መሰሪዎችንም ይዘው ነው።ጉዳዩ የተቀናበረ ነው።ለኢትዮጵያውያን ቀዳሚውን ሥራ ለመግለፅ የሚያጠቃልለው ሁነኛ አባባል ''ጠላትማ ምን ጊዜም ጠላት ነው።አስቀድሞ መምታት አሾክሿኪውን ነው'' የሚለው ነው።ቀዳሚው ጠላት እኛነታችንን የሸጠን ለ24 ዓመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተንሰራፋው ስርዓት ነው።ቅድምያ ስልጣኑን መልቀቅ ያለበት ህወሓት ነው።የሱዳኑ ጉዳይ 'እዳው ገብስ ነው'።

ከእዚህ በታች የሱዳን ትሪቡን ጋዜጣ እኤአ ጥር 17/2016 ዓም ድንበሩ በእዚህ ዓመት እንደሚሰጥ የገለጠበትን ዘገባ ትርጉም ያንብቡ።(ትርጉም ጉዳያችን)

ሱዳን እና ኢትዮጵያ የድንበር ማካለል ስራቸውን በእዚህ ዓመት ያጠናቅቃሉ

ጥር 17/2016 (ካርቱም)
በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል የድንበር ማካለሉን ሥራ ኃላፊነት የወሰደው የቴክኒክ ኮሚቴ በመሬት ላይ ድንበሩን የማካለሉን ሥራ በእዚህ ዓመት እንደሚያጠናቅቅ ገልጧል።ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በኃላ ቆሞ የነበረው የድንበር ማካለሉ ሥራ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሃይለማርያም እና የሱዳኑ ፕሬዝዳንት  አልበሽር ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸው በሰጡት መመርያ መሰረት ስራውን በህዳር ወር 2014 ዓም ቀጥሏል።የቴክኒክ ኮሚቴው ሰብሳቢ አብደላ አል-ሳዲግ ለሱዳን ሚድያ ሴንተር (SMC) እንደገለጡት ኮሚቴው እዚህ ግባ የሚባል ምንም ችግር በስራው አልገጠመውም ነበር።
አብደላ አል-ሳዲግ አክለው እንደገለጡት በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል ያለው  የሚካለለው የድንበር ርዝመት 725ኪሜ በሁለቱ አገሮች መካከል ያሉ ገበሬዎች በባለቤትነት ግጭት የተፈጠረበት አል-ፋሻጋ አካባቢ እና ደቡብ ምስራቅ ግዛት ገዳረፍን ያጠቃልላል።

አል-ፋሻጋ 250 ስኩኤር ኪሎ ሜትር እና 600 ሺህ ጋሻ ለም መሬት ይዟል።ከእዚህ በተጨማሪ ቦታው በወንዝ የበለፀገ ሲሆን አትባራ፣ሰቲት እና ባስላም የተባሉ ወንዞች ይገኙበታል።ባሳለፍነው ቅዳሜ እና ዕሁድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢብራህም ጋንዱር መቀመጫውን ኩአታር ላደረገው አልጀዚራ ቴሌቭዥን እንደገለፁት ''ኢትዮጵያ እና ሱዳን በሱዳን ግዛት ላይ የሰፈሩትን ሽፍቶች  (gangs) በመግታት የድንበር ማካለሉን ሥራ በአንድነት እየሰሩ ነው'' ከማለታቸውም በላይ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በመቀጠል አፅንኦት ሰጥተው እንደተናገሩት ''አል-ፋሻጋ የሱዳን ግዛት ነው።የሱዳን መንግስት የኢትዮጵያ ገበሬዎች እንዲያርሱት ፈቃድ የሰጠውም በሁለቱ አገራት መካከል ባለው ትብብር ሳብያ ነው።ኢትዮጵያም አልፋሻጋ የሱዳን ግዛት መሆኑን አምናለች'' ብለዋል።

ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋንዱር በሁለቱ አገራት መካከል በፕሬዝዳንት ደረጃ በድንበሩ ጉዳይ ውይይት መደረጉን ጠቁመው ውይይቱ በሱዳን ጋዳርፍ እና ብሉ ናይል ግዛት እና በኢትዮጵያ በአማራ ክልል ደረጃም መደረጉን ገልጠዋል።በኢትዮጵያ እና ሱዳን መካከል የተሰመረው በእንግሊዝ እና ጣልያን ቅኝ ግዛት ወቅት በ1908 ዓም ነው።ሁለቱ መንግሥታት ድንበሩን እንደገና በማካለል የአካባቢው ሕዝብ መጥቀሙ ላይ ተስማምተዋል።ሆኖም ግን የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ገዢውን ፓርቲ የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን አሳልፎ በመስጠቱ ይከሱታል።

 ====የሱዳን ትሪቡን ጋዜጣ ትርጉም መጨረሻ===

Sudan, Ethiopia to complete border demarcation this year
January 17, 2016 (KHARTOUM) - The technical committee tasked with redrawing the border between Sudan and Ethiopia said it would complete its work on the ground during this year.
JPEG - 45.1 kb
A road leading to Ethiopia-Sudan border (Photo Jamminglobal.com)
In November 2014, Ethiopia’s Prime Minister Hailemariam Desalegn and Sudan’s President Omer al-Bashir instructed their foreign ministers to set up a date for resuming borders demarcation after it had stopped following the death of Ethiopia’s former Prime Minister, Meles Zenawi.
The head of the technical committee Abdalla al-Sadig told the semi-official Sudan Media Center (SMC) that the border demarcation between Sudan and Ethiopia doesn’t face any problems.
He pointed out that the length of the border with Ethiopia is about 725 km, saying the process of demarcation is proceeding properly.
Farmers from two sides of the border between Sudan and Ethiopia used to dispute the ownership of land in the Al-Fashaga area located in the south-eastern part of Sudan’s eastern state of Gedaref.
Al-Fashaga covers an area of about 250 square kilometers and it has about 600.000 acres of fertile lands. Also there are river systems flowing across the area including Atbara, Setait and Baslam rivers.
On Saturday, Sudan’s foreign minister Ibrahim Ghandour told the Qatar-based Aljazeera TV that Sudan and Ethiopia are working together to curb the activities of Ethiopian gangs inside Sudanese territory.
He stressed that Al-Fashaga is a Sudanese territory, saying the government allowed Ethiopia farmers to cultivate its land as part of the cooperation between the two countries.
“However, Ethiopia is committed and acknowledges that [Al-Fashaga] is a Sudanese territory,” he said.
Ghandour pointed to joint meetings between the two countries at the level of the presidency to discuss borders issues.
Sudan’s Gadarif and Blue Nile states border Ethiopia’s Amhara region. The borders between Sudan and Ethiopia were drawn by the British and Italian colonisers in 1908.
The two governments have agreed in the past to redraw the borders, and to promote joint projects between people from both sides for the benefit of local population.
However, the Ethiopian opposition accuses the ruling party of abandoning Ethiopian territory to Sudan.

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com
ጥር 10/2008 ዓም (ጃኗሪ 19/2016)

የትግራይ ነጋዴዎችን ለመጥቀም አዲስ የበርበሬ አዋጅ በጎጃም

January 19,2016
berbere
ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በተለይ በምዕራብ ጎጃም አካባቢ የደነገገው አዲስ የበርበሬ አዋጅ ችግር እያስከተለ መሆኑን የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) በላኩልን መረጃ አስታውቀዋል፡፡ እንደ እማኝ ዘጋቢው ከሆነ አዋጁ የወጣው በ2002ዓም ሲሆን በሥራ ላይ መዋል የጀመረው በዚህ ዓመት እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ ይህ በበርበሬ ላይ ብቻ የተደነገገው አዋጅ ዋና ምክንያቱን በውል ለማወቅ የሚያዳግት ቢሆንም እንደ እማኝ ዘጋቢው አስተያየት በርበሬው ወደ ትግራይና አዲስ አበባ የሚላክ በመሆኑ በተለይ የትግራይ ነጋዴዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ለመጥቀም ታስቦ እንደሆነ ከሚሰጡት ግምቶች የላቀው መሆኑን ያስረዳሉ፡፡
እማኝ ዘጋቢያችን የላኩልን መረጃ እንዲህ ይነበባል፡-
“በአማራ ክልል በምዕራብ ጎጃም ዞን በቡሬ በፍኖተ ሰላም በሺንዲ ወረዳዎችና አካባቢዎች በበርበሬ ንግድ ላይ አዲስ አዋጅ አውጥተው ህዝቡን ለችግር ነጋዴውን ደግሞ ለኪሳራ እየዳረጉት ነው። አዲስ ያወጡት አዋጅ ለጎጃም ብቻ ሲሆን፡-
1ኛ. ሁሉም ነጋዴዎች በሚሸጡበት ቦታ ሁሉ ቅርንጫፍ እንዲኖራቸው ያስገድዳል። ለምሳሌ የቡሬ ነዋሪ የሆነ ነጋዴ መቀሌ መሸጥ ቢፈልግ ቅርንጫፍ ሊኖረው ግድ ነው፤ አዲስ አበባ ቢሆን ሌላ ተጨማሪ ቅርንጫፍ ሊኖረው ያስፈልጋል፤ ሽሬም ቢፈልግ እንዲሁ፤
2ኛ. ማንኛውም ነጋዴ ከነጋዴ ላይ መግዛት አይችልም፤ ለምሳሌ 90 ኩንታል መጫን የፈለገ 85 ኩንታል ኖሮት 5 ቢጎለው 5 ከነጋዴ ላይ ገዝቶ መሙላት አይችልም፤
3ኛ. ቫት እንዲጀምሩ ማለትም በቫት እንዲገዙ፤
4ኛ. ከ6 ወር በላይ መከዘን ወይም ማስቀመጥ አይቻልም።
ለምሳሌ 1 ኪሎ 60 ብር ቢገዛና በቀጣይ ጊዜ ቢቀንስ 50 ብር ቢሆን ከስሮም ቢሆን መሸጥ ግዴታው ነው።”
በማለት የአካባቢው ነጋዴና ሕዝብ እየተጋፈጠ ያለውን ችግር እንድናሰማላቸው ልከውልናል፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)

Sunday, January 17, 2016

ይድረስ ለጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለማሪያም ደሳለኝ

January 16, 2016
በዛልኝ ፀጋው ከአዲስ አበባ
ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለማሪያም ደሳለኝ፣
ይህን ደብዳቤ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ዋናው ምክንያት በአሁን ጊዜ በብዙ ኢትዮጲያዊያን ላይ የሚፈጸመውን ግድያ፣ ግፍ፣ መከራና ሰቆቃ በመመልከት ከምንም ነገር በላይ የአገራችን የኢትዮጲያ ቀጣይ  ሁኔታ ስላስጨነቀኝ ነው።
Hailemariam-PM1-300x282አቶ ኃይለማሪያም፣ እርስዎ ወደስልጣን  ሲወጡ አገራችን የተሻለ አስተዳደር ታገኛለች ብለው ብዙ ተስፋ አድርገው ከነበሩት ኢትዮጲያዊያን መካከል አንዱ ነኝ። ለዚህም ምክንያቶች ነበሩኝ። አንደኛ እርሰዎ እግዚአብሄርን የሚፈሩ ሰው ነዎት ሲባል በመስማቴ፣ ሁለተኛ በትምህርት ባገኙት ችሎታዎ በራሰዎ የሚተማመኑና የሚያምኑበትን ለመናገር ወደኋላ አይሉም ብየ በማሰቤ፣ ሶስተኛ በትምህርት ቤት በነበሩበት ዘመንዎ ያዩት የነበረው የተማሪወች እንቅስቃሴ ለአጠቃላይ ህዝብ መብት መከበር እንጅ በዘር ላይ ያልተመሰረተ ስለነበር፣ እርሰወም የዘር ፖለቲካን እንደዋና መርህ አይቀበሉም ብየ መገመቴ፣ አራተኛ እነ አቶ መለስ የሚቃወሟቸውን ሁሉ፣ የረሳቸውን ጓደኞች ሳይቀር፣ እያጠፉ ለሰው ህይወት ብዙም ሳይጨነቁ ወደ ስልጣን ሲመጡ፣ እርሰዎ ግን ወደ ስልጣን አመጣጠዎ የተለየ ነው ብየ በመገመቴ ነው። ይህ አመለካከቴ ከመጠን በላይ በጎ ነገር ከመጠበቅ የተነሳ መሆኑን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተረዳሁ መጣሁ።
እኔ ተስፋ ሳደርግ፤ ብዙ ኢትዮጲያዊያን ግን የእርሰዎ ጠቅላይ ሚንስቴር መሆን፣ ስልጣኑንና፣ ጦሩን፣ የስለላ ድርጅቱንና  ኢኮኖሚውን ህውሃት እስከተቆጣጠረው ድረስ፣ ለውጥ እንደማያመጡ ሲናገሩ ነበር። በትክክልም እርሰዎ አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ እንዳሉ መገንዘብ ቻልኩ። ሆኖም ግን አሁንም አገሪቱን ወደ ከፋና የማትወጣበት ችግር ወስጥ ከመግባቷ በፊት፣ በታሪክም ተወቃሽ እንዳይሆኑ፣ ህዝቡን ይዘው ማድረግ የሚችሉትን መጠቆም እወዳለሁ።
የወያኔ መንግስት ባመጣው በዘር ከፋፍሎ አስተዳደር፣ በገዥው መንግስት መሪነት፣  በህዝቡ መካከል ይዘራ የነበረው የዘርና የጥላቻ ፖለቲካ፣  ከሃያ አራት አመታት በላይ በዘለቀው ገደብ የሌሌው የመብት ረገጣና የንጹሃን ግድያ ጋር ባንድ ላይ ሆኖ  በፈጠረው ብሶት፣ የህዝብ አመጽ ገንፍሎ እየመጣ ነው። ይህም የአገራችንን የወደፊት እጣ ምን ሊሆን እንደሚችል ማወቅ አስቸጋሪ አድርጎታል። እርስወ በዘር ፖለቲካና ትእቢት በተሞሉና፣ የህዝብ ሃብት በሚዘርፉ ወያኔወች ተተብትበው በመታሰርዎ ኢትዮጲያን በዲሞክራሲያዊ መንገድ መምራት እንደማይችሉ ኢትዮጲያዊ ሁሉ ያውቃል። ሆኖም ግን አገራችንን ከከፋ ጥፋት ለማዳን አሁንም ማድረግ የሚችሏቸው ነገሮች አሉ፣
  1. የህዝቡን ስቃይና መከራ ለማየት ህሊናዎን ይክፈቱ፣
  2. የመብት ጥያቄ የሚያነሱትን ኢትዮጲያዊያን ጠላት አድርጎ መመልከትዎን አቁመው ለአገራቸው እንደሚያሰቡና በአገራቸው ጉዳይ እኩል ባለድርሻ መሆናቸውን ይቀበሉ፣
  3. የመንግስት ሃይል በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የሚያደርገውን ዘግናኝ ግድያ ባስቸኳይ ያስቁሙ፣
  4. የታሰሩትን የፖለቲካ እስረኞችና ጋዜጠኞች በመፍታት፣ ሁሉንም ለአገሪቱ ባለድርሻ የሆኑትን የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የሃይማኖት መሪወች፣ የዜጎች ወይም ማህበራዊ ድርጅቶች መሪዎችና ያአገር ሽማግሌወች የሚካፈሉበት አገር አቀፍ ጉባኤ በመጥራት፣ ጉልበት ሳይሆን የህግ የበላይነት የሚመራበት ሁሉን ኢትዮጲያዊ የሚወክል መንግስት እንዲቋቋም ይርዱ፣
  5. ይህን ማድረግ የማያስችለወት ሁኔታ ካለ ግን፣ ለኢትዮጲያ ህዝብ ችግረዎን በግልጽ አሳውቀው ስልጣንወን ይልቀቁ። ይህን በማድረግ ለእግዚአብሄር፣ ለኢትዮጲያና ለኢትዮጲያ ህዝብ መታመነዎን ያሳያሉ።
ይህን መልዕክቴን በቀና ልቦና እንደሚያዩልኝ ተስፋ አደርጋለሁ።

በዛልኝ ፀጋው
አዲስ አበባ

Friday, January 8, 2016

Food crisis looming in Ethiopia after worst drought in 50 years

January 8,2016

Tekle Birhan clutched her malnourished infant son as she waited to get a food supplement and treatment at an Ethiopian health clinic in early December. It was their third trip in as many months to the facility, located about an hour's walk from her family farm that has seen almost no rain since July.
The worst drought in 50 years is eroding harvests of everything from corn to sorghum across Ethiopia, compounding a food shortage for a country where 30 percent of the population subsists on less than $1.25 a day. Already sub-Saharan Africa's biggest wheat consumer, Ethiopia will need $1.1 billion to buy food for more than 18 million people this year, according to a report by the government and humanitarian partners including theUnited Nations.
"Because of the drought there is crop failure, so we don't have any food," Tekle, 30, said in an interview at a packed clinic in the Hintalo Wejerat district of the Tigray region. As her 18-month-old son nibbled on a cookie, Tekle said that the pulse, barley and wheat crops on her family farm got almost no moisture in July, and the normally wet month of August was dry.
Ethiopian droughts have become more frequent and severe in the past decade, and a lack of rain from El Nino weather patterns is fast becoming a problem in many parts of Africa. Zimbabwe, Zambia and South Africa have reported failed corn crops. Ethiopia, among the world's poorest countries, will see the number of people that need food aid almost double this year. The nation has historically struggled with hunger, including in the 1980s, when famine and civil war left hundreds of thousands of people dead.
Ethiopia, which is the continent's most-populous nation after Nigeria, is already buying more grain, purchasing 1 million metric tons of wheat in a tender announced in October. That's about the same as it usually procures in an entire season. The country will need about another 500,000 tons in the next few months to replenish stockpiles, said Qaiser Khan, program leader for the nation at the World Bank, which is helping fund the grain purchases.
Farmers in Ethiopia usually harvest two grain crops a year, and problems started during the smaller "belg" season, when rains were about half the average from March to May. Erratic precipitation throughout the summer mean that the main "meher" harvest in most eastern areas also will be well-below average, according to the U.S. Agency for International Development's Famine Early Warning Systems Network. The country is normally Africa's third-largest grain producer, after Nigeria and Egypt.
"It's a really scary situation," Mario Zappacosta, an economist at the U.N.'s Food & Agriculture Organization, said in an interview from Juba, South Sudan. "In part of the country, there were two bad seasons in a row."
Ethiopia, with almost 97 million people, is just finishing up the harvest in some drought-hit areas, so shortages will probably be most severe from March or April, when stockpiles are depleted, Zappacosta said. Wheat imports into the nation will more than double to a record 2 million tons this season, the U.S. Department of Agriculture forecasts.
Near the border of Ethiopia's low-lying, arid Afar region, Abraha Haftu, 39, said he is facing a dry rainy season for a fourth year, and water shortages are adding to a lack of food supplies. Faced with crop failure, his family will once again have to count on the Productive Safety Net Program, an aid project run by the World Food Programme, he said.
"Water is very critical, as well as food," he said, waiting in line at a government food-distribution warehouse in Hintalo Wejerat. "The government is trying, but some of the water sources are dry."
Dried-out pastures have also killed off livestock, with 200,000 animals estimated to die in 2015 and an additional 450,000 this year, according to the U.N. That's helping push up the food-import bill, putting more strain on the country's already depleted foreign currency reserves, said Clare Allenson, an Africa-focused analyst at Eurasia Group, a Washington-based research and consulting firm.
"There's already a lack of dollars available to the private sector," Allenson said. "The livestock sector is really suffering, the same for milk and vegetables. This has led to major food-price inflation."
Ethiopia has improved its defenses after previous famines. Better infrastructure, a growing economy, access to international aid and years of peace mean the country is more prepared to cope with crop failures than in the 1980s, FAO's Zappacosta said.
The amount of international aid dollars available this year is likely to be stretched, with many crises cropping up around the world. The U.N. and humanitarian agencies released an appeal last month for a record $20.1 billion in funding, citing crisis situations in 27 countries.
"There are so many other emergencies in the world, and donors will have to decide where to put their money," Zappacosta said. "There is some doubt that Ethiopia can pop up as a priority when you have Syria, South Sudan, Central African Republic and many other places in the world in bad situations."

Saturday, January 2, 2016

“መፍትሄ ያጣው የቡዳ ፖለቲካችን” – ዶ/ር መረራ ጉዲና

January 2,2016
gudina zehabesha
 (“የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ህልሞች” በሚል ርዕስ አንጋፋው ፖለቲከኛና የፖለቲካ ሣይንስ ምሁር ዶ/ር መረራ ጉዲና ሰሞኑን ለንባብ ካበቁት ሁለተኛ መጽሐፋቸው የተቀነጨበ

… የቡዳ ጉዳይ በሀገራችን ባሕል ውስጥ የታወቀ ስለሆነ ለማስረዳት ዝርዝር ውስጥ አልገባም፡፡ ቡዳና ፖለቲካችንን ምን አገናኛቸው ለሚለው ጥያቄ ግን ተገቢ መልስ መስጠት ስለአለብኝ አንዳንድ ጭብጦችን ላስቀምጥ፡፡ ተረቱ እንደሚለው፣ አንድ ቡዶችን ለይቶ የማያውቅ ሰው፣ የቡዶች መንደር ይደርስና፣ “እዚህ አካባቢ የቡዶች መንደር አለ ይባላል፣ የትኛው ነው” ብሎ ራሱን፤ ቡዳውን ይጠይቀዋል፡፡ ቡዳው ሰው፣ “ቡዶች የምንባለው እኛው ነን” ለማለት ድፍረት ስላጣ፣ “እኛ እዛ ማዶ ያሉት ናቸው እንላለን፣ እነሱ ደግሞ እኛን ይሉናል” አለ ይባላል፡፡

ላለፉት አርባ ዓመታት ለውጥ ለመምጣት ከአንድ ትውልድ በላይ ቀላል ያልሆነ መስዋእትነት ተከፍሎዋል። የሀገራችን ፖለቲካ ባለህበት እርገጥ ከመሆን፣ አንዳንዴ ደግሞ የኋሊት ከመሄድ አላለፈም፡፡ ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ለፀረ – ቅኝ አገዛዝ ትግል ከከፈሉት በላይ ሀገራችን ውድ ዋጋ ከፍላለች፣ የታሰበው ለውጥ ግን አልመጣም፡፡ እዚህ ላይ ዋናው ጥያቄ ለሀገራችን ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞ ኃላፊነቱን የሚወስደው ማነው? የሚለው ነው። ቢያንስ አንዱ በሌላው ላይ ጣት ከመቀሰር አልፎ የየድርሻችንን እንኳ እንውሰድ ሲባል አይታይም፡፡ እንደቡዳው፤ ስህተት የሠራሁት እኔ ነኝ ከማለት ይልቅ፤ አጥፊዎች እነዛ ናቸው ማለት ይቀላል፡፡ የአንድ ትውልድ ምርጦችን ያለርህራሄ የጨፈጨፈው መንግሥቱ ኃይለማርያም እንኳ “ሰው ይቅርና ዝንብ አልገደልኩም” ነበር ያለው፡፡ ተባባሪዎቹ የነበሩ የደርግ ባለሥልጣናትም ያንን አስከፊ ግፍ የፈጸምነው “የሀገር ፍቅር ያንገበገበን ወታደሮች ነበርን” እያሉ መጽሐፍ እየጻፉ ነው፡፡ የጥፋት ኃላፊነቱንም በሌሎች ላይ እየደፈደፉ ነው፡፡

ቢያንስ ብዙዎቹ በድንቁርና ለጨፈጨፉዋቸው ዜጐች ኃላፊነቱን ለመውሰድ አልተዘጋጁም፡፡ እውነቱን ለመናገር እኔም ባለፈው ጊዜ በጻፍኩት መጽሐፌ ላይ የነገሮችን ሚዛን ለመጠበቅ በጣም አስቸግሮኝ እንደነበረ አስታውሳለሁ። ለአብነት፤ የቀድሞ የመኢሶን ጓዶቼ ከኢሕአፓ ጋር አመሳሰልከን የሚል ቅሬታ እንዳላቸው ነግረውኛል። ታሪክ ፀሐፊዎች ስለ አንድ ድርጊት እርግጠኛ ሆነው መጻፍ ያለባቸው የድርጊቱ ተሳታፊዎች ሲሞቱ ነው የሚሉት የገባኝ አሁን ነው፡፡ አንድ ቀን ከቀድሞ የሕወሓት አመራር አባል ጋር ስለዚህ ጉዳይ አንስተን ስናወራ ለተሠሩት ስህተቶች የኃላፊነት ደረጃ ለድርጅቶች ስጥ ብትለኝ ደርግ አንደኛ፣ ሕወሓት ሁለተኛ፣ ኢሕአፓ ያንተ ድርጅት ስለሆነ ነው ወንጀሉን ያስነሳከው” አለኝ፡፡ የቀልድም ይሁን፤ የምር አስተያየቱ ቢያናድደኝም፣ ገርሞኛል፡፡ በእኛ ትውልድ ስላየናቸው የአፄ ኃይለሥላሴ፣ የደርግና የኢሕአዴግ መንግሥታት የትኛውን ትመርጣለህ ቢባል፣ የየዘመኑ ተጠቃሚ ያለምንም ጭንቀት እራሱ ተጠቃሚ የነበረበትን ሊመርጥ እንደሚችል ይገመታል። በሕዝብ ደረጃ ሲታሰብ ግን፤ እንደጊዜው ሁኔታ ሊታይ እንደሚችል አያጠራጥርም፡፡

ከቀይ ሽብር በኋላ፣ አብዮቱ የደርግ መንግሥት ጭፍጨፋ እየመረረው ሲመጣ ብዙ ወጣቶች፤ “ተፈሪ ማረኝ፣ የደርጉ ነገር ምንም አላማረኝ” ሲሉ መስማቴን አስታውሳለሁ፡፡ ይህ ምርጫ እንደየ ማህበረሰቡም ሊለያይ ይችላል፡፡ ኦሮሚያና ደቡብ ውስጥ፣ ከዝንጀሮ ቆንጆ…ቢሆንም የደርግ መንግሥት ሊመረጥ ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ውለታ ይሁን፣ የደርግ መንግሥት፣ የመሬት አዋጅ በእነዚህ አካባቢዎች እስከ ዛሬም ድረስ እጅግ በጣም ሰፊ ድጋፍ አለው፡፡ የቡዳ ፖለቲካችንን ከሁሉም በላይ አስቸጋሪ የሚያደርገው ሁሌም ጥፋተኞች እኛ ሳንሆን እነዛ ናቸው ብለን ስለምንደርቅ ነው፡፡ እዚህ ላይ ፈረንጆች የሚበልጡን በሁለት መሠረታዊ ጉዳዮች ነው፡፡

አንደኛው፣ ለነሱ ዛሬ ለደረሱበት ደረጃ ጥፋት መቀበልን እንደሞት አያዩትም፡፡ ሁለተኛ፤ ሥልጣንን የሙጥኝ በማለት አጥፍቶ መጥፋትን ከባህላቸው አስወግደዋል ወይም የኋላቀሮች አስተሳሰብ አድርገውታል፡፡ ቢያንስ ከሂትለር ወዲህ የአብዛኞቹ ጉዞ በዚህ አቅጣጫ ነው፡፡ ሦስተኛው፣ ፖለቲካቸው ሰጥቶ መቀበል ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ሁሉንም አግኝ ወይንም ሁሉንም እጣ (Zero –sum-game) የሚባለውን ፖለቲካ ከልብ እየተው መጥተዋል፡፡ ይበልጥ ደግሞ ከሥልጣን በኋላ፣ ጥሩ ኑሮ መኖርም፣ ክብር ማግኘትም እንደሚቻል አውቀዋል፡፡ እንደውም ከሥልጣን በኋላ ያለጭንቀት የተደላደለ ኑሮ መኖር እንደሚቻል ያውቃሉ፡፡
ኦባማ በአፍሪካ ኅብረት ንግግሩ የአፍሪካ መሪዎችን ለማስተማር የሞከረው ይህንኑ ነው፡፡ ትምህርቱ ገብቶት ይሁን፤ በተለመደው የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት የማስመሰል ፖለቲካ፤ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትርም ሲያጨበጭብ አይቻለሁ፡፡

“ከአገዛዝ ወደ ነፃነት የምንሸጋገርበት ትግል ላይ ነን”

January 2,2016
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፤ የሰማያዊ ፓርቲ ሊ/መንበር
yilkal
አለማየሁ አንበሴ
የሰማያዊና ኦፌኮ ፓርቲ አባላትና አመራሮች መታሰራቸውን ሰማያዊ ፓርቲ ያወገዘ ሲሆን፤ “አሁን የፓርቲ ፖለቲካ የምናደርግበት ጊዜ ላይ አይደለንም፤ ከአገዛዝ ወደ ነፃነት የምንሸጋገርበት ትግል ላይ ነን” ብለዋል የፓርቲው ሊ/መንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት፡፡
የሰማያዊ አመራሮች ባለፈው ረቡዕ በፅ/ቤታቸው በሰጡት መግለጫ፤ በኦሮሚያ ክልል የተፈጠረውን ተቃውሞ ተከትሎ ዜጎች መገደላቸውንና በርካቶች መታሰራቸውን በመጥቀስ “መንግስት ፋና ወጊ የሆኑትን ተራ በተራ እየለቀመ የእሳት እራት እያደረጋቸው ነው” ሲሉ ወቅሰዋል፡፡
የፓርቲው ልሳን የሆነው የ“ነገረ ኢትዮጵያ” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ፣ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው፣ የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው ዮናታን ተስፋዬ፣ የፓርቲው አባላት፡- ቴዎድሮስ አስፋው፣ ዳንኤል ተስፋዬ፣ ኤርሚያስ ፀጋዬና ፍሬው ተክሌ መታሰራቸውን የጠቆመው ሰማያዊ፤ የታሰሩት አባላት ፍ/ቤት ቀርበው፣ ፖሊስ በሽብር ወንጀል እንደጠረጠራቸው በመግለፅ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቆባቸዋል ብሏል፡፡
በቅርቡ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ፤ በኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር ዙሪያ ለፓርላማ ያደረጉትን ንግግር የተቹት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል፤ “ጠ/ሚኒስትሩ  ለፓርላማ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያውያን የሱዳንን ድንበር የደፈሩ አስመስለው ዜጎችን “ሽፍቶች” በማለት የማይረሳ ታሪካዊ የክህደት ምስክርነት ሰጥተዋል” ሲል ብለዋል፡፡
ምንጭ – አዲስ አድማስ

Friday, December 25, 2015

የ11ኛው ሰዓት ጥሪ እያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ይመለከታል!

December 25, 2015
def-thumbየንቅናቄያችን መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ህዝብ ባደረጉት የትግል ጥሪ በ11ኛው ሰዓት ላይ እንደምንገኝ ገልጸዋል ። የ 11ኛው ሰዓት መልዕክት፣ አንደኛ፣ ወደ 12ኛው ሰዓት ወይም ወደ ፍጻሜው እየተቃረብን መሆኑን የሚነገረን ነው። የ11ኛው ሰዓት የትግል ጥሪ የአንድን የትግል ምዕራፍ ለመዝጋት እና አዲስ የትግል ምዕራፍ ለመጀመር የመጨረሻ የሞት ሽረት ትግል የምናደርግበት ጊዜ ላይ መድረሳችንን የሚገልጽ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ጥሪው ከትግሉ ፍጻሜ በሁዋላ ስለሚፈጠረው አዲስ ስርዓት ከአሁኑ ማሰብ መጀመር እንዳለብን የሚያነቃን ደወል ነው። 11ኛው ሰዓት ላይ ቆመን ከ12ኛው ሰዓት በሁዋላ ስለሚፈጠረው ነገር መጨነቅ ካልቻልንና በጊዜ ቤታችንን ካላሰናዳን ፣ ከትግሉ ፍጻሜ በሁዋላ ሊገጥሙን የሚችሉትን ተግዳሮቶች በጊዜና ብቃት ባለው መልኩ ለመፍታት መቸገራችን አይቀርም ። አንድ በእድሜ የገፋ ሰው 11ኛው ሰዓት ላይ መሆኑን ሲያውቅ ከህይወቱ ፍጻሜ በሁዋላ ስለሚኖረው ህይወት ማሰላሰሉ ተፈጥሯዊ ነው። የ11ኛው ሰዓት ጥሪም የአንድን አገዛዝ እርጅናና ፍጻሜ የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን፣ በቦታው የሚወለደውን አዲስ ስርዓት ምንነትም የሚያሳይ ነው።
የ11ኛው ሰዓት ጥሪ ተደራሾች እነማን ናቸው? የጥሪው ተደራሾች በኢህአዴግ ዙሪያ የተሰባሰቡት እና እነዚህን ስብስቦች በማፍረስ አዲስ ስርዓት ለመገንባት የሚታገሉት የነጻነት ሃይሎች ሁሉ ናቸው። የ11ኛው ስዓት ጥሪ ለወያኔ ገዢዎች መገርጀፋቸውን የሚያረዳ የሞት ጥሪ ደወል ነው፤ ወደማትመለሱበት መቃብር ከመወርወራችሁ በፊት በቀራችሁ የአንድ ሰአት እድሜ አሟሟታችሁን አሳምሩ ብሎ የሚመክር ነው። በተለይ በጣት የሚቆጠሩ የሻገቱ ገዢዎችን ደግፋችሁ የቆማችሁ የመከላከያ፣የፖሊስና የደህነት አባላት አሰላለፋችሁን በጊዜ አስተካክሉ የሚል አርቆ ከማሰብ የመነጨ ምክር ነው ። የ11ኛው ሰዓት ጥሪ የሚመክር ብቻ ሳይሆን የሚያስጠነቅቅም ነው። ይህን የገረጀፈ አገዛዝ ደግፈው የቆሙ ሁሉ በጊዜ ከህዝብ ጋር እንዲታረቁ ይህ ካልሆነ ግን በመጨረሻው ሰዓት ከፍርድ እንደማያመልጡ የሚያስጠነቅቅ ነው። ካለፈው የሚመጣው ይበልጣል፤ ወያኔን ደግፋችሁ የቆማችሁ ሁሉ ያለፈ ጥፋታችሁን ለወደፊት በምትስሩት ስራ እንድትክሱ መልእክት ተላልፎላችሁዋል።
የ1ኛው ሰዓት ጥሪ የነጻነት ሃይሎች በአንድነት እንዲሰባሰቡና ትግሉን እንዲያቀጣጥሉም ያሳስባል። አገዛዙ 11ኛው ሰዓት ላይ ነው ማለት በራሱ ጊዜ ይወድቃል ማለት አይደለም። አገዛዙ ከደሃው በዘረፈው ገንዘብ ኪኒኖችን እየዋጠና ምርኩዞችን እየገዛ እድሜውን ሊያራዝም ይችላል። ከገፋነው በቀላሉ ተሰባብሮ ይወድቃል፤ ዝም ካልነው ግን ድዱ ረግፎም በህይወት መቆየቱና ስቃያችን ማራዘሙ አይቀርም። እኛ በዘር፣ በጾታ፣ በትምህርት ወይም በሌሎች ጥቃቅን ነገሮች ሳንለያይ አንድ ሆነን ይህን የሻገተ አገዛዝ እንድናስወግድ ግልጽ ጥሪ ተላልፏል።
የ11ኛው ሰዓት ጥሪ ያረጀውን ስርዓት ወደ መቃብሩ ከከተትነው በሁዋላ ስለሚፈጠረው አዲስ ስርዓት እንድናስብ የሚመክርም ነው። ዛሬ በመሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበን እንድንነጋገርና የነገውን ትልም እንድንተልም የሚጠይቅ ነው። አስቀድሞ በጋራ መተለሙ ነገ ሊፈጠር የሚችለውን ችግር ከመቀነሱም በላይ፣ የሻገተውን አገዛዝ በህብበረት ለመጣል ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል። በጭሩ የ11ኛው ሰዓት ጥሪ ወያኔን ተባብሮ ለመቅበር ብቻ ሳይሆን፣ በመቃብሩ ላይ ስለሚተከለው አዲስ ችግኝ ለመነጋገር ጥሪ የሚያቀርብ ነው።
ሁላችንም የ11ኛውን ሰዓት ጥሪ ተቀብለን ተግባራዊ ልናደርገው ይገባል። ድሉ የሁላችንም ነው!
አርበኞች ግንቦት7!

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን የመሰጠቱን ጉዳይ ዳግም አረጋገጡ።

December25,2015
ንግግራቸው የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አስመስሏቸዋል።

''በታሪካችን ያላየነው ረሃብ ላይ ነን'' አቶ ኃይለ ማርያም

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ዛሬ ታህሳስ 15/2008 ዓም በኢትዮጵያ ፓርላማ ቀርበው በሰጡት ማብራሪያ ላይ በተለይ በኦሮምያ ክልል ለተነሳው ሕዝባዊ አመፅ እና በሱዳን እና በኢትዮጵያ መካከል ስላለው የድንበር ጉዳይ ላይ  የተለመደ አወዛጋቢ እና የበለጠ አወሳሳቢ ንግግሮችን ተናግረዋል።

በኦሮምያ የተነሳውን ሕዝባዊ አመፅ ችግሩን፣መነሻውን እና መፍትሄውን የጠቆሙበት አገላለፅ የእራሳቸውን እና የመንግስታቸውን መፍትሄ ቢስነት በአደባባይ በድጋሚ ያጋለጠ ነው።ችግሩ ገበሬው መረጃ አለማግኘቱ ነው ማለታቸው እና በውጭ ኃይሎች ቅስቀሳ ነው የሚለው እርስ በርሱ የተቃረነ አነጋገር በእራሱ ለእራሳቸውም በአግባቡ የገባቸው አይመስልም።ችግሩን መንግስት ስለ ፕላኑ አለመንገሩ ነው ያሉት እና አሁን መንግስታቸው እያናገረ ያለው በጥይት መሆኑን ለሚያስተውለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ንግግራቸው በሕዝቡ ላይ ከመዘባበት ያለፈ አንዳች የሚሰጠው ፋይዳ የለም።በመፍትሄነት ያስቀመጡትም ምንም አዲስ ነገር የሌለው እና አሁንም መልሰን እንነግረዋለን የሚለው አባባል ንግግሩ በጥይት እንደሆነ አመላካች ነው።ሕዝብ የሚባለው እና የሚደረገው ስላልገባው ነው የሚለው አባባል በእራሱ ለሕዝብ ያለን የንቀት ደረጃ አመላካች ነው።በሰላማዊ ሰልፍ እጆቻቸውን ወደ ሰማይ እየሰቀሉ ድምፃቸውን ያሰሙ ታዳጊዎችን በጥይት አረር ከመቱ (እንደ አቶ ኃይለማርያም አነጋገር 'ካናገሩ') በኃላ አሁንም እናናግራለን እያሉ መዘባበት በእራሱ ህዝብን የአላዋቂነት ጥግ ነው።

በሌላ በኩል የሱዳን እና የኢትዮጵያን የድንበር ማካለል ጉዳይ ላይ የጀመሩበት አረፍተ ነገር እና በመካከል እና በመጨረሻ ላይ የደመደሙበት ንግግር ኢትዮጵያ በእዚህ አይነት ደረጃ የባዕዳንን ጉዳይ የሚያስፈፅም መንግስት ኖሯት እንደማያውቅ በግልፅ የሚያሳይ ነው።

''በመሬት ጉዳይ ላይ የተደረገ ድርድር የለም። በኢትዮጵያ እና በሱዳን መሃል ያለው ድንበር በደንብ ስላልተስተካከለ በእርሱ ላይ ነው እየሰራን ያለነው'' ካሉ በኃላ የሱዳን ጠቅላይ ሚንስትር የሚናገሩ እስኪመስል ድረስ የኢትዮጵያን ክብር በሚነካ መልኩ ሱዳንን እየረበሽን ያለነው የእኛ ገበሬዎች ናቸው።አሁን የሚያርሱት መሬት የሱዳን መሬት ነው ብለው ለመከራከር ሞክረዋል።ይህ ማለት ባጭሩ ኢትዮጵያውያን ለዘመናት ሲያርሱት የነበረው መሬት በእራሳቸው አገር ጠቅላይ ሚኒስትር መሬቱ የሱዳን ነው እየተባሉ ነው ማለት ነው።በተለይ የሱዳን ወታደሮች ለስራ በወሰዷቸው ኢትዮጵያውያን ላይ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ ብቻ እጅግ አሰቃቂ በሆነ መንገድ ስለመገደላቸው አንዳች ያልተነፈሱት አቶ ኃይለማርያም ይልቁንም የኢትዮጵያን ገበሬዎች በሱዳን ተገብተው ሲወቅሱ እንዲህ ብለዋል-
''ከእኛ አካባቢ እየሄዱ ሱዳናውያንን እየገደሉ የሚመለሱ'' እንደሳቸው አገላለጥ ''ሽፍቶች''ናቸው ሲሉ ተደምጠዋል።በመቀጠል አቶ ኃይለማርያም እንዲህ አሉ: ''በርካታ ኪሎ ሜትሮች ሱዳን ውስጥ ገብተው የሚያርሱ እኛ የምናውቃቸው ኢትዮጵያውያን አርሶ አደሮች እና ባለሀብቶች አሉ''  በማለት እነኝህ መሬቶች ለጊዜው ለሱዳን አይሰጡ እንጂ የሱዳን መሆናቸውን ባረጋገጡበት ንግግራቸው በቀጣዩ የድንበር ማካለልም መንግስታቸው የሱዳን መሆናቸውን እንደሚያውቅ አሁንም እንደ ኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሳይሆን እንደ ሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትርነት ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ባጠቃላይ ድንበሩን በተመለከተ ከተናገሩት መረዳት የሚቻለው ሁለት ጉዳይ ነው።አንዱ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የድንበር ማካለል ሂደት ላይ ናቸው የሚለው ዜና ትክክል መሆኑን።በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ አሁንም እንደ ኢትዮጵያዊ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳይሆን በሱዳን ወገን ተገብተው የኢትዮጵያን ገበሬዎች እና ባለ ሀብቶች የሱዳንን መሬት አረሱ እያሉ ይህ መሬት ለሱዳን እንደሚገባ በአንደበታቸው ሲናገሩ ተሰምቷል።በሌላ አነጋገር ለብዙ ትውልዶች መሬቱን ሲያርሱ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከመሬታችን አንነቀልም ካሉ ከሱዳን ወታደሮች ጋር ተባብረው ገበሬዎቹን እና ባለ ሀብቶቹን የማባረር ሥራ እንደሚሰራ እየገለጡ ነው ማለት ነው።ምክንያቱም በአደባባይ መሬቱ የኢትዮጵያን አይደለም።ለጊዜው ነው ሱዳኖች የፈቀዱልን ካሉ በኃላ ይህንንም የሱዳን ውለታ መሆኑን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስረዳት ሲውተረተሩ ተሰምተዋል።

በመጨረሻም አቶ ኃይለማርያም ''በምግብ እራሳችንን ችለናል'' ብለው በተናገሩ በወራት ውስጥ በዛሬው እለት ደግሞ ካለ አንዳች እረፍት ''የገጠመን ድርቅ በታሪካችን ምናልባትም ባለፉት ሃምሳ ዓመታት ውስጥ አይተነው የማናውቅ በእኔ አመለካከት እጅግ የከፋ ድርቅ ነው'' ሲሉ ተደምጠዋል።ለድርቁ የሰጡት መፍትሄ ግን የበለጠ አስቂኝ ነው።መፍትሄዎቹ የሚመጡ እርዳታዎችን መቀበል እና የውሃ ጉድጓድ በመቆፈር ነው ይላሉ አቶ ኃይለማርያም።ጥያቄው ግን  ከእሩብ ክ/ዘመን አምባገነናዊ እና የከፋፍለህ ግዛ የኢህአዴግ/ህወሓት አገዛዝ በኃላ ኢትዮጵያ በታሪክ ያላየችው ርሃብ ላይ ነች ማለት እና የውሃ እጥረት ችግር ለሆንባት አገር የውሃ ጉድጓድ መቆፈር መፍትሄ ነው ማለት ምን አይነት የአስተሳሰብ ድህነት ነው? የሚል ነው።ባጭሩ አቶ ኃይለማርያም ህወሃቶች ስልጣን እንዲለቁ እና የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት ሿሚዎቻቸውን ቢመክሩ እና የመሸበት ቢያድሩ የተሻለ ነው።

ጉዳያችን GUDAYACHN

Friday, December 18, 2015

የህወሓት የደንነት ቢሮ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝን አስጠነቀቀ፡ መፈንቅለ መንግስት ሊደረግ እንደሚችል የቅርብ አዋቂዎች ተንብየዋል

December 18,2015
tigrai

የደንነት መስሪያ ቤቱ በሚንስትሮች ምክር ቤት በኩል ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያ የሰባት ቀን የጌዜ ገደብ የተሰጠው ማስጠንቀቂያ ማስተላለፉ ታውቆአል። የደህንነት መስሪያ ቤቱ በሀገሪቱ ውስጥ ሳይታሰብ የፈነዳውን አመፅ ለመቆጣጠር ምን አይነት እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ሙሉ ስምምነት ላይ መድረስ አልችል ብሎ ሲወዛገብ መሰንበቱ ሲታወቅ ዛሪ ከጥዋት ጁምሮ ሲአካሂድ በዋለው ውይይት ላይ ግን ማንኛውንም አይነት ሀይል ተጠቅሞ አመፁን ለመቆጣጠር ወስኖአል። የውሳኔውን ቅጅ ከ አንድ ሳምንት ማስጠንቀቂያ ጋር በአቶ ካሳ ተክለብርሀን በኩል ለጠቅላይ ሚንስትሩ ልዃል።

የአቶ ሀይለማርያም አስተዳደር አመፁን ለመቆጣጠር መመሪያ ከአሜሪካ መንግስት መቀበሉን በአስቸዃይ አቁሞ የተነሳውን መጠነ ሰፊ አመፅ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ መቆጣጠር የሚያስችል የኦፕሪሽን መርሀ ግብር አውጥቶ ለፊደራል ፓሊስና መከላከያ ማስረከብና ለተግባራዊነቱም ካልተንቀሳቀሰ ሙሉ ሰላም የማስከበሩን ስራ መከላከያ ይረከባል ይላል። በአጭሩ መፈንቅለ መንግስት ይደረጋል ማለት እንደሆነ ምንጮቸ አረጋግጠዋለል።

Thursday, December 17, 2015

ትግላችንን ተጠናክሮ በአንድነት ይቀጥል!

December 17, 2015
def-thumbየኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ በያቅጣጫው መነሳቱ የሚያኮራ ነው። ባለፉት 3 ዓመታት ብቻ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ያደረጉትን የመብት ትግል ጨምሮ በደቡብ፣ አማራ፣ አፋር፣ ጋምቤላና በሌሎችም አካባቢዎች በርካታ የነጻነት ትግሎች ተካሂደዋል። አሁን በኦሮምያ እና በአማራ በተለይም በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች እየተካሄዱ ያሉት የነጻነት ትግሎች የአጠቃላዩ የነጻነት ትግል አካሎች ናቸው። በእነዚህ የነጻነት ትግሎች ገዢው ፓርቲ ከህዝብ ጋር ለምንጊዜውም መለያየቱን ለማየት ችለናል። ስልጣኑን ለማስጠበቅ ሲልም፣ አቅሙ ቢፈቅድለትና ማግኘት ቢችል በምድር ላይ ያሉትን ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎችን ሁሉ በገዛ ህዝቡ ላይ ለመጠቀም ወደ ሁዋላ የማይል የአረመኔዎች ስብስብ መሆኑን አረጋግጠናል። በጭካኔውና በፍርሃቱ ብዛት የተነሳ በርካታ ሙስሊሞች፣ ክርስቲያኖች፣ መብታቸውን በሰላም ለመጠየቅ ወደ አደባባይ የወጡ ወጣቶች ተገድለዋል፤ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ጋዜጠኞች በእስር ተንገላተዋል፤ በእስር ቤትም ማንነታቸውን ከማዋረድ ጀምሮ የተለያዩ አካላዊ ጥቃቶች ተፈጽሞባቸዋል።
የኦሮሞ ህዝብ መብቴ ይከበርልኝ ብሎ መነሳቱን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ከያቅጣጫው ድጋፋቸውን እየገለጹ ነው። ይህ ለነጻነት ሃይሎች ብስራት ሲሆን ዘርን ከዘር በማጋጨት የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ለሚፈልገው የሽፍታ አገዛዝ ደግሞ ትልቅ መርዶ ነው። ባለፉት 25 ዓመታት ወያኔ አንዱን ዘር ከሌላው ዘር እያጋጨ፣ በወንድማማቾችና እህትማማቾች መካከል መተማመን እንዳይፈጥር መርዙን ሲረጭ ቆይቷል፤ ያሰበው አልሰምርለት ሲል ደግሞ በአገሪቱ አንጡራ ሃብት በሸመተው ጠመንጃ ለመብቱ የተነሳውን ህዝብ ደረት ደረቱን እየመታ ፈጅቶታል። በተለይም የአማራው ህዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድነት ተሰልፎ በህወሃት አገዛዝ ላይ የነጻነት ክንዱን ለማሳረፍ እንዳይችል ሌት ተቀን የጥላቻ መርዙን በመርጨት ከሌላው ህዝብ ጋር እንዲጋጭ ለማድረግ በእጅጉ ደክሟል። ወያኔ የረጨውን የጥላቻ መርዝ የኦሮሞ እና የአማራ ልጆች በጋራ እያረከሱት መገኘታቸው፣ የሌሎች ብሄሮችና ብሄረሰቦች ህዝቦችም እንዲሁ ” አንለያይም” በማለት በጋራ ለመሰለፍና ትግሉን ለማቀጣጠል ዝግጁነታቸውን መግለጻቸውና በተግባር እያሳዩ መምጣታቸው የ25 አመታት የወያኔ የአፈናና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ እያከተመ መምጣቱን የሚያመላክት ነው። ወያኔ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲው በመላው ኢትዮጵያውያን ትብብር እንደረከሰበት ሲያውቅ ደግሞ የግድያ አዋጅ አውጥቶ በ-ኢትዮጵያውያኑ ላይ ጥይት አርከፍክፎ ጸጥ ሊያሰኛው መዘጋጀቱን በአዋጅ አስነግሯል። ከታሪክ መማር የማይችለው ጠባቡ ወያኔ፣ ህዝባቸውን አዋጅ አስነግረው የገደሉ ጨቋኝ መንግስታት መጨረሻቸው ምን እንደነበረ እንኳን ቆም ብሎ ማሰብ አልቻለም። ዛሬ የእሳት ላንቃ በሚተፋ ጠመንጃቸው ሊጨፈልቀው የሚያስበው ህዝብ ነገ መልሶ ራሱን እንደሚጨፈልቀው ለአፍታም ቢሆን ለማሰላሰል አልቻለም። የዘረፈው ሃብትና የታጠቀው መሳሪያ አእምሮውን ደፍኖት፣ እየመጣ ያለውን ህዝባዊ ሱናሚ ለማየት ተስኖታል። በጦር መሳሪያ ጋጋታና ድንፋታ ቢሆን ኖሮ ወራሪዋ ጣሊያን እስከዛሬ ድረስ ከአገራችን ለቃ ባልወጣች ነበር፣ በጦር መሳሪያ ጋጋታ ቢሆን ኖሮ እነ ጋዳፊን ዛሬ ቤተመንግስት እንጅ መቃብር ውስጥ አናገኛቸውም ነበር።
የአገራችን ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለነጻነቱ የሚያደርገውን ትግል በጥንቃቄ የሚመራበት ጊዜ ላይ ነን ። የገጠመን ጠላት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ፣ የገዛ ህዝቡን በጠላትነት ፈርጆ ሊያጠፋው የተነሳ በመሆኑ፣ አገዛዙ እስከዛሬ ካደረሰው ጥፋት ሌላ ተጨማሪ ጥፋት ሳያጠፋ፣ ከአገራችን መሬት ለመንቀል እንድንችል እርምጃችን ሁሉ ጥንቃቄ የተሞላበት ሊሆን ይገባል። ጠላታችን ህዝብን ከህዝብ ለማፋጀት ያለ የሌለ ሃይሉን የሚጠቀም መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ አቅሙ በፈቀደለት መጠን ሁሉ ህዝቡን በጅምላ ለመፍጀት ወደ ሁዋላ የማይል ነው። ህዝቡ የጠላቱን አውሬነት ተገንዝቦ እሱ በሚከፍተው ቀዳዳ ዘው ብሎ ላለመግባት መጠንቀቅ አለበት። ሊገድሉን ሲመጡ ዘወር ብሎ በማሳለፍ፣ እንደገና ደግሞ ወደ አደባባይ በመውጣት፣ እንዲሁም የተቃውሞውን አድማስ በማስፋትና የሃይል መከፋፈል እንዲፈጠር በማድረግ ወያኔን አዳክሞና ተስፋ አስቆርጦ ካለሙት ግብ መድረስ ይቻላል። አሁን እየታየ ያለው አንድነት ይበልጥ እየተጠናከረ፣ ከኦሮሞው ጎን አማራው፣ ከአማራው ጎን ጉራጌው፣ ከጉራጌው ጎን ትግሬው፣ ከትግሬው ጎን አፋሩ፣ ከአፋሩ ጎን ጋምቤላው፣ ከጋምቤላው ጎን ሀረሪው፣ ከሃረሪው ጎን ጉሙዙ፣ ከጉሙዙ ጎን አዲስ አበቤው፣ ከአዲስ አበቤው ጎን ጋሞው በአጠቃላይ መላው ህዝብ እጅ ለእጅ እየተያያዘ የነጻነት ባበሩ ወደፊት እንዲሮጥ ማድረግ አለበት። ወጣቱ ራሱን ባለበት ቦታ እያደራጀና አመራር እየሰጠ በያቅጣጫው የጀመረውን የነጻነት ትግል አጠናክሮ ይቀጥል።
አርበኞች ግንቦት7 ትግሉን በተለያዩ አቅጣጫዎች አጠናክሮ ቀጥሎአል፤ የአርበኛው ሰራዊት የወያኔን ጀሌዎች በቀኝና በግራ መውጫና መግቢያ እያሳጣቸው ነው። የንቅናቄው አባላት በዳር አገር በአፈሙዝ፣ በመሃል አገር ደግሞ ወጣቱን እያደራጁ ለትግል እንዲሰልፍ እያደረጉት ነው። የንቅናቄያችን መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ “ከነጻነት ትግሎች ጎን አለን” እንዳሉት የአርበኛው ልጆች ፊት ለፊት ተሰልፈው አመራር በመስጠት የነጻነት ትግሉን ለማቀጣጠል እና መከፈል ያለበትን የህይወት መስዋትነት ለመክፈል ተዘጋጅተው በያቅጣጫው እየተንቀሳቀሱ ነው።
ተደጋግሞ እንደተነገረው የአርበኞች ግንቦት7 አላማ በአገራችን የዲሞክራሲያዊ የሽግግር ስርዓት ማስጀመር ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ አላማ ዙሪያ ተሰልፎ ትግሉን ይቀጥል። ይህን አላማ የሚደግፉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ዛሬውኑ ከጎናችን ተሰልፈው ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው የሞት ሽረት ትግል ይሰለፉ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
አገራችን በልጆቿ ነጻ ትወጣለች!
አርበኞች ግንቦት7

“ፕሮፌሰር፣ ጄኔራል” ሳሞራ

December 17,2015
የቻይና ደም-መላሽ!
samoray
ረቡዕ በተሰማው ዜና መሠረት የቻይናው ቲያንጂን የቴክኖሎጂና ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለሳሞራ የኑስ የክብር ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡
ሚያዚያ 1999 የዖጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግምባር በክልሉ በሚገኝ የነዳጅ ፍለጋ ቦታ ላይ ባደረሰው ጥቃት ከ70 በላይ ንጹሃንን በገደለበት ወቅት ዘጠኝ ቻይናውያን ከሞቱት መካከል ነበሩ፡፡
በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር አዛዥነት በየጊዜው በዖጋዴን ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ሲቃወም የነበረው ኦብነግ ለወሰደው ድንገተኛ እርምጃ በሟቹ መለስ የሚመራው ህወሃት በክልሉ አምስት ቦታዎች ማለትም በፊቅ፣ ቆራሄ፣ ጎዴ፣ ዋርድሄር እና ደጋሃቡር ዘግናኝ የሆነ የመልሶ ማጥቃት ጭፍጨፋ በነዋሪው ሕዝብ ላይ አድርሷል፡፡
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት (ሂውማን ራይትስ ዎች) ባወጣው ዘገባ መሠረት ኦብነግ ላደረሰው የአጸፋ መልስ እና ታጣቂዎችን ለመደምሰስ በሚል ህወሃት ያዘመተው ጦር በተደጋጋሚ በሰላማዊው ሕዝብ ላይ ፍጹም ጨካኝና ዘግናኝ ዕልቂት ፈጽሟል፡፡
samorayየመልሶ ማጥቃቱን ዘመቻ ለማካሄድ ጂጂጋ ላይ የክልሉ የደኅንነት ኃላፊዎች ስብሰባ ባደረጉበት ወቅት የመለስ የጸጥታ አማካሪ አባይ ጸሃዬ እና ሳሞራ የኑስ በጥቃቱ ዕቅድ አወጣጥ ላይ ተገኝተው እንደነበር ታማኝ ምንጮቹን ጠቅሶ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ ያስረዳል፡፡
ከዚያም በ1999 ሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ አቶ መለስ መጠነ ሰፊ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻ እንዲካሄድ ትዕዛዝ አስተላለፉ፡፡ የዖጋዴን ሕዝብ ፍዳውን በላ፤ እንደ ቅጠል ረገፈ፤ ዕድሜያቸው ለአካለ መጠን ያልደረሱ ልጃገረዶች፣ ሴቶች አዛውንቶችንም ጨምሮ ተደፈሩ፡፡ ህጻናት ወንዶችም ሳይቀሩ የዚህ ሰለባ ሆነዋል፡፡
የቀድሞው የቻይና መሪ ማዖ ሴቱንግ ሽምቅ ተዋጊዎችን ስለማጥፋት የተናገሩት ቃል በመለስ ፊት አውራሪነት ተፈጸመ፡፡ “ዓሣ በባህር እንደሚዋኝ ሽምቅ ተዋጊም በሕዝቡ መካከል መንቀሳቀስ አለበት፤ (ሽምቅ ተዋጊን ለማጥፋት ካስፈለገ ዓሣው ያለበትን ባህር ማድረቅ ነው)” ያሉት የማዖ ቃል በመለስ ትዕዛዝ በሳሞራ የኑስና ሌሎች የህወሃት አጋፋሪዎች ተፈጸመ፡፡
ውለታ የማይረሱት ቻይናውያን የትምህርት ደረጃው በውል የማይታወቀውን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አሉ ከሚባሉት የጦር አካዳሚዎች ሥልጠና ስለመውሰዱ ምንም ማስረጃ ላልተገኘለት “ቻይናዊ ጄኔራል ደምመላሽ” ባቋራጭ “የላቀ ምሁርነት” አጎናጸፉት፡፡
ውለታን መመለስ ከሆነ አይቀር እንዲህ ነው፡፡
ማዖ ነኝ ከቲያንጂን

“እኛ አማራ ነን እንጂ ትግሬ አይደለንም” የወልቃይት ሕዝብ

December 17,2015

Annexation_Tigray

* “(ችግራችን) ትግሪኛ መናገር፤ ትግሪኛ መጻፍ፤ በትግሪኛ መዝፈን፤ አለብህ የሚል ነው፤ እኛ መሽከርከር አንችልም” የወልቃይት ሕዝብ
“እኛ አሁን የምናቀርበው ምንድነው ማንነት ነው፤ አማራነት በማመልከቻ ለማምጣት አይደለም የተነሳነው፤ አማራ ነን፤ ትላንት አማራ ነን፤ ነገ አማራ ነን፤ ለዘላለም አማራ ነን፤ ይኼ አያሳፍረንም፤ እኛ ስንዘፍን፣ ስናለቅስ፣ ስንፎክር፣ ስንሸልል፣ ለቅሶ ስንደርስ፤ ስናመሰግን ለማንኛውም የምንገልጸው በአማርኛ ነው፡፡ ይህ አማርኛችን ከአያት ቅድመ አያቶቻችን የገኘነው ነው፤ አያሳፍረንም፡፡
“የወልቃይት ሕዝብ አንዲት ጎጆ ተከዜ ተሻግሮ አልቀለሰም፤ ስለዚህ ይህ ምን ማለት ነው፤ የምን ስሜት ነው፤ ሠርጋችንን፤ ሃዘናችንን፤ ደስታችንን የምናወሳውም እንዲሁ ነው፡፡ ለቅሷችንን የሚያውቅ፤ ደስታችንን የሚያውቅ፤ እንጂ በእኛ ላይ አናታችን ላይ መጥቶ አይደለህም፤ አባትህ ሌላ ነው ሊለን አይችልም፤ ማንነት እንደዚሁ ነው የሚገለጸው፤ ማንነት ለቅሶ የምገልጽበት ቋንቋ ነው፤ ማንነት ሳዝን የምገልጽበት ቋንቋ ነው፤ በተለያዩ መልኮ የሚገለጽ ነው፤ እኛ በተለያዩ ሁኔታዎች ከአማራ የሚለየን ምንነት የለም፡፡ ዛሬ ታሪክን የመቶ ዓመት ያደረጉ ሰዎች ሌላ ቋንቋ ሊያወሩ ይችላሉ፤ ታሪክን በትክክለኛ ሁኔታ የገለጹ ምሁራን ግን አማራነታችንን በትክክል ይገልጻሉ፡፡
“24 ዓመት ሙሉ ሕዝባችን እያለቀሰ፤ እንዳይናገር አጎንብሶ እየሄደ ቀና ብሎ እንዳይናገር ያሳፈረው አንድ ኃይል ብቻ ነው፡፡ ይህም ትግሪኛ መናገር፤ ትግሪኛ መጻፍ፤ በትግሪኛ መዝፈን አለብህ የሚል ነው፤ እኛ መሽከርከር አንችልም፤ … አማርኛችን ጥርት ያለ አማርኛ ነው፤ እንደማንኛውም ተናግረን፤ ጽፈን የምንገልጸው ነው፤ … ስለዚህ ዛሬ አማራ መሆናችንን በማመልከቻ ዕርዱን እያልን አይደለም፤ በደማችንና በሥጋችን፣ በማንነታችን፣ በዘራችን የመጣ አማርኛ ነው፤ (ትግሬ አይደለንም) … ይህ የወልቃይት ሕዝብ ድምጽ ነው፡፡”
ሙሉውን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡

Saturday, December 12, 2015

የአርበኞች ግንቦት 7 የመጀመሪያ ምክር ቤት ስብሰባ መግለጫ

December 12,2015
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከህዳር 26 ቀን 2008 ዓ.ም እስከ ህዳር 30 ቀን 2008 ዓም ድረስ ሰራዊቱ በሚገኝበት የትግል ቦታ የመጀመሪያውን የምክር ቤት ስብሰባ አድርጎ በስኬት አጠናቋል::
ይህ ስብሰባ የቀድሞዎቹ የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባርና ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ተዋህደው አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ከተሰኘ ወዲህ የተደረገ የመጀመሪያው የምክር ቤት ስብሰባ ነው::
ይህ ስብሰባ፦
1. ውህደት ከተደረገበት ከጥር 2 2007 ዓ.ም ወዲህ የስራ አስፈፃሚውን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አድምጧል፤
2. ከውህደት ወዲህ ንቅናቄው የፈጸማቸውን ተግባራት በጥልቀት መርምሯል፤
3. የንቅናቄውን ህገ-ደንብና አሰራሮችን መርምሮ ማሻሻያዎችን አድርጓል፤
4. የምክር ቤቱ ልዩ ልዩ ኮሚቴዎችን አቋቁሟል
5. ተተኪና ወጣት የአመራር አባላት ምክር ቤቱ ውስጥ እንዲካተቱ አደርጓል፤
6. የሃገራችንን የወቅቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ሁኔታዎች በጥልቀት መርምሯል፤
7. በወቅቱ ሁኔታዎች ጥናት ላይ ተመርኩዞ የወደፊት የትግል አቅጣጫውን ቀይሷል፣ ግልጽ የሆነ የትግል ስትራቴጅ በሙሉ ድምጽ አጽድቋል፤
8. ከስብሰባው በኋላ መከናወን የሚገባቸውን ተግባራት ቅደም ተከተል አውጥቶ ለስራ አስፈጻሚው መመሪያዎችን አስተላልፏል፡፡
የአርበኞች ግንቦት 7 ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የህወሓትን አምባገነን አገዛዝ አስወግዶ በምትኩ ፍትህ የነገሰባት፣ የዜጎች እኩልነት የተረጋገጠባት፣ ዴሞክራሲያዊት አገር ለመገንባት የሚያደርገውን ትግል በግንባር ቀደምትነት ለማስተባበርና ለመምራት ከመቸውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት መነሳቱን ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ይገልጻል::
አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ወደ አዲስ ደረጃ ተሸጋግሯል ብሎ ያምናል:: ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን ዜጎችና ድርጅቶች በሙሉ በሚያመቻቸው መንገዶች እየተደራጁ ከንቅናቄያችን ጋር ግንኙነት በመፍጠር በጋራ ትግል አምባገነኑን ወያኔ ከስልጣን እንድናስወግድና በምትኩ ፍትህ፣እኩልነትና የሃገርን አንድነት የሚያረጋግጥ የፖለቲካ ስርዓት እንድናቋቁም ጥሪ ያደርጋል::
ድል ለ ኢትዮጵያ ህዝብ!

ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በህወሓት አገዛዝ የጦር ኃይል ላይ ጥቃት በመሰንዘር ከፍተኛ ድልን ተቀዳጀ!!

December 12.2015
የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ተደጋጋሚ የሽምቅ ውጊያዎችን በማድረግ የህወሓትን መከላከያ ሰራዊት፣ ልዩ ኃይልና ሚሊሻ ጦር አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የህዝብ አለኝታነቱን እያስመሰከረ ይገኛል፡፡
ባለፈው ሳምንት ህዳር 21/2008 ዓ.ም ጀግናው ሰራዊታችን በዋልድባ በጠላት ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን አሁን ደግሞ ከዋልድባ ወደ አዲ-አርቃይ በመወርወር ማክሰኞ ህዳር 28/2008 ዓ.ም አዲ-አርቃይ ላይ ከወያኔ መከላከያ ሰራዊትና የሚሊሻ ታጣቂ ኃይል ጋር ከቀኑ 10፡00 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 1፡00 ለሶስት ተከታታይ ሰዓታት የዘለቀ ከባድ ውጊያ በማድረግ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የጠላት ጦር በመግደልና በማቁሰል ድልን ተጎናፅፏል፡፡
ሰራዊታችን በጦር ሜዳ ውሎው፣ ከጥልቅ የሀገር ፍቅር ስሜት በተቀዳ ወኔ፣ እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የህወሓትን መከላከያ ሰራዊትና የሚሊሻ ታጣቂ ኃይል በጦር ሜዳው ላይ በጥይት ቆልቶና አሳሮ አስቀርቶታል፡፡
ፍልሚየው በማግስቱ ረቡዕ ህዳር 29/2008 ዓ.ም ከጥዋቱ 1፡00 ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ሰዓታት ማለትም እስከ ረፋዱ አራት ሰአት በዚያው አዲ-አርቃይ ላይ የቀጠለ ሲሆን ፣ ወያኔ ከሌላ ቦታ አጓጉዞ ለጦርነት ያሰለፈውን ተጨማሪ የመከላከያ ሰራዊት ጀግኞቹ የአርበኞች ግንቦት ሰባት የነፃነት ፋኖዎች የጠላትን ጦር ድባቅ መትተውታል፡፡
ለነፃነት የሚደረገው ጦርነት አሁንም ቀጥሏል፡፡የወያኔ ባለስልጣናት የሚይዙት የሚጨብጡት አጥተው በተለይ በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል የሚገኘውን ድንበር የበለጠ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ሰራዊት ለመዝጋት ቢሯሯጡም ድንበር ላይ የተመደበው ወታደር ከወያኔ እየከዳ የነፃነት ትግሉን ከነትጥቁ እየተቀላቀለ ይገኛል፡፡ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሰራዊት በተቀዳጀው ድል የአካባቢው ህዝብ ጮቤ እየረገጠ እደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡ጀግናው የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሰራዊት ህዝቡን ከጎኑ በማሰለፍ፣ በህዝብ ድጋፍ ታጅቦ ወደ መሃል አገር እየገሰገሰ ነው፡፡

Wednesday, December 9, 2015

በረሃብ የተጎዳው ወገን ቁጥር በእርዳታ ድርጅቶች ዳታ 13 ሚሊዮን ደረሰ:: ቀየውን ጥሎ የሚሰደደው በርክቷል::

December 12,2015
ተለያዩ የሰሜን እና ምስራቅ ኢትዮጵያ ክፍላተሃገራት የተሰማሩ ከተለያዩ የአለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች የተገኙ ዳታዎች እንደሚያመለክቱት በድርቅ የተጎዳው እና በረሃብ አለንጋ እየተገረፈ ያለው ሕዝብ ቁጥር 13 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሪፖርት መሰረት በጥር 2016 አስረ አምስት (15 )ሚሊዮን እንደሚገባ ተረጋግጧል::የእርዳታ ድርጅቶቹ ሰራተኞች እንደጠቆሙት በምስራቅ ኢትዮጵያ ሃረርጌ ውስጥ ብቻ ካለፈው ወር ከነበረው የረሃብ ተጎጂ ወገን ቀር በዚህ ዲሴምበር 2015 65% ከፍ ብሌል::የተረጂዎች ቁጥር እና የምግብ አቅርቦቱ እንዳይጨምር የመንግስት ባለስልጣናት ጫና ይፈጥራሉ ያሉት ሰራተኞቹ ሕዝቡ ቀየውን ትቶ ወደ ከተሞች እየዘለቀ መሆኑን ይናገራሉ::
በሰሜን ኢትዮጵያ በትግራይ እና በአገው ልዩ ዞን እንዲሁም በአዲስ ዘመን አከባቢ ያለው ሁኔታ ከሌሎች የባሰ ሲሆን ከምስራቅ በለሳ እና ከአገው ምድር ሰቆጣ ቀያቸውን ጥልው በረሃብ ምክንያት የተሰደዱ በጎንደር አዲስ ዘመን ተሰፈሩ መሆኑ ሲታወቅ በትግራይ እንዲሁ እስካሁን እርዳታ ያላገኙ አከባቢዎች እንዳሉ ተጠቁሟል:: በአዲስ ዘመን ያሉ የብኣዴን ባለስልጣናት ከሰቆጣ እና በለሳ ተሰደው የሄዱትን ወገኖች መንግስት በያላችሁበት በጀት እየመደበ ስለሆነ በሚል ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ በማስገደድ ላይ መሆናቸው ታውቋል::ባለፈው ሳምንት በትግራይ በእንደርታ ወረዳ ለሚገኙ በድርቅ ለተጎዱ ተብሎ የመጣው ኣንድ እስካንያ መከኒ ከነተጎታቹ የእርዳታ እህል በወረዳው ባለስልጣናትና ነገዴዎች በመመሳጠር የተራገፈ ኣስመስለው በሌላ መኪና ገልብጠው ጭነው ሲወስዱ የኲሓ ህዝብ እጀ ከፈንጅ ይዞ ለፖሊስ ማስረከባቸው ይታወሳል::

Friday, December 4, 2015

ፈረንሳይ እስከ 160 የሚሆኑ መስጊዶችን ልትዘጋ ነው!

December 4,2015

“ጥላቻ የሚሰብኩ ፈቃድ የሌላቸው መስጊዶች ይዘጋሉ” ኢማም ሃሰን
mosque Paris France
በመጪው ጥቂት ወራቶች ፈረንሳይ እስከ 160 የሚጠጉ መስጊዶችን ለመዝጋት መወሰኗ ተሰማ፡፡ የአገሪቱ ከፍተኛ ኢማም እንዳሉት በሥራ ላይ በዋለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መሠረት ጽንፈኛ አመለካከት የሚያራምዱ የእምነት ቦታዎች መዘጋትአለባቸው፡፡
በኅዳር ወር መጀመሪያ አካባቢ በፓሪስ የተከሰተውን ጥቃት ተከትሎ እስካሁን ጽንፈኛ አቋም አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ ሦስት መስጊዶች መዘጋታቸውን የአገር አቀፍና የአካባቢ ኢማሞች ለመምረጥ ኃላፊነት የተሰጣቸው ኢማም ሃሰን ኤል-አላዊ ለአልጃዚራ መናገራቸው ተዘግቧል፡፡ እርሳቸው እንደሚሉት በቀጣይ ወራቶች በርካታ መስጊዶች እንደሚዘጉ አስረድተዋል፡፡
“ከአገር ውስጥ ሚኒስቴር ጋር በምናደርገው ውይይት እና ይፋ በሆኑት መረጃዎች መሠረት ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸው፣ ጥላቻን የሚሰብኩ፣ ታክፊሪ ንግግር የሚደረግባቸው ከ100 እስከ 160 መስጊዶች ይዘጋሉ” በማለት ኢማም ሃሰን ተናግረዋል፡፡ ታክፊሪ ንግግር ማለት በእምነቱ ውስጥ ያሉትን ሌሎች ሙስሊሞችን በከሃዲነት የሚነቅፍ ንግግር ነው፡፡ “እንዲህ ዓይነቱ ንግግር ዓለማዊ በሆነችው ፈረንሣይ ብቻ ሳይሆን በእስላማዊ አገራትም ቢሆን መፈቀድ የለበትም” በማለት የመጀመሪያው የእስርቤት ኢማም (ቻፕሊን) ለመሆን የበቁት ሃሰን ኤል አላዊ ተናግረዋል፡፡
franceይህ በፈረንሳይ አገር በቤተ እምነት ላይ የተወሰደ የመጀመሪያው የተባለለት እርምጃ የተወሰደው “አንዳንድ ሕገወጥ ነገሮች በመገኘታቸው” መሆኑን የጠቀሱት ኢማም ድርጊቱ ባለሥልጣናት ማድረግ የሚገባቸው ሕጋዊ እርምጃ ነው ማለታቸውን አልጃዚራ ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
ለ130 ሰዎች መሞት ምክንያት የሆኑትን “አሸባሪዎች” በማለት የጠቀሷቸው ኢማም ሃሰን “እነዚህ የሃይማኖት ልብስ የተጎናጸፉ ሌቦችና አደንዛዥ ዕጽ አዘዋዋሪዎች ናቸው፤ ነገሩ የአሸባሪዎች ጉዳይ ነው እንጂ ከሙስሊሞች ጋር ምንም ግንኑነት የለውም፤ የሁሉንም ሰው ደኅንነት ማስፈን የመለከተ ነው” በማለት ኢማም ሃሰን በጥቃት አድራሾቹ ላይ ያላቸውን አስተያየት ሰጥተዋል፡፡
ሌላው ለአልጃዚራ አስተያየታቸውን የሰጡት የአል-ካዋኪቢ ድርጅት ተባባሪ መሥራች የሆኑት የፋርሱ ሙስሊም ፊሊክስ ማርቃርት የመስጊዶቹ መዘጋት እንዳላስደነቃቸው ተናግረዋል፡፡ ይልቁንም በተለያዩ የፈረንሳይ ከተሞች በተካሄዱ እስላማዊ የጸሎት ሥነ ሥርዓቶች ላይ የሰሙት ነገር በእጅጉ እንዳስደነገጣቸው ተናግረዋል፡፡ “እስልምናን ከፖለቲካ ጋር በማያያዝ እስልምናን አስፈሪ የማስደረግ ሥራ በፈረንሳይ መንግሥት እንደሚሠራ አንዳንድ ቦታዎች በይፋ ሲነገር ሰምቻለሁ” ብለዋል፡፡
ሆኖም ግን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ከጥቃቱ በኋላ ፈረንሳይ ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠረ የመብት ጥሰት እየፈጸመች መሆኗን ይናገራሉ፡፡ የቤት አሰሳ፣ እስራት፣ ሙስሊሞች ባለቤት የሆኑባቸው ድርጅቶችን የመዝጋት፣ ወዘተ የመብት ጥሰት ተከስቶባቸዋል የተባለባቸው ናቸው፡፡
“በአሁኑ ጊዜ በፈረንሳይ ሙስሊም ሆኖ መኖር ቀላል አይደለም” ያሉት ማርቃርት “በተለይ የፊት መሸፈኛ የሚያደርጉ ሴቶች የመድልዖ ሰለባ ሲሆኑ ለወንዶች ደግሞ ሥራ ማግኘት እጅግ ከባድ ነው” በማለት አስረድተዋል፡፡
በፈረንሳይ ውስጥ በድምሩ 2,600 መስጊዶች ይገኛሉ፡፡

የወገኖቻችን ስቃይ፣ ችግርና ብሶት በያለንበት ይሰማን፤ ለመፍትሔውም በጋራ እንነሳ!- የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

December 3, 2015
def-thumbበአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሰበብ በከተማዋ ዙርያ ያሉ ወገኖቻችንን ማፈናቀል በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተፈፀመ ጥቃት ነው። በማስተር ፕላኑ ሰበብ የሚፈናቀሉ ገበሬዎች የሁላችን ወላጆች፣ ወንድሞችና እህቶች ናቸው። በማስተር ፕላኑ ሰበብ የምንፈናቀለው ሁላችንም ነን። ይህን መሰሪ ፕላን በመቃወም ላይ ያሉት የኦሮሞ ተወላጅ ወገኖቻችን ትግል ፍትሀዊ በመሆኑ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከጎናቸው ይቆማል።
በዚሁ ወቅት በጎንደር ሌላ አሳዛኝ ጉዳይ ተከስቷል። ህወሓት ከሶስት ሺህ በላይ ዜጎቻችንን ያጎረበት እስር ቤት በእሳት ሲጋይ ዜጎች ተቆልፎባቸው እንዲነዱ ተደርጓል። ከእሳቱ በእድል ያመለጡት በጥይት ታድነዋል። ኢትዮጵያዊያን እንዲህ ዓይነቱን ጭካኔ የሚያውቁት በፋሺስት ጣሊያን ወረራ ጊዜ ነው። ይህን ጥቃት በመቃወም ላይ ያሉ የአማራ ተወላጅ ወገኖቻችን ትግል ፍትሀዊ በመሆኑ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ከጎናቸው ይቆማል።
ግፍ ያልተፈፀመበት የኢትዮጵያ ክፍል ባይኖርም ሰሞኑን በአማራና በኦሮሚያ ላይ በርክቷል። በሁለቱም የአገራችን ክፍሎች የንፁሀን ደም እየፈሰሰ ነው፤ በሁለቱም ቦታዎች የእናቶች ዋይታና እሪታ ጎልቶ እየተሰማ ነው። የህወሓት አገዛዝ የትውልድ ቦታ፣ ቋንቋና ዘር ሳይለይ በኢትዮጵያዊያን ሁሉ ላይ የተደቀነ አደጋ መሆኑ ከምንጊዜውም በላይ ዛሬ ግልጽ ሆኗል።
ለዚህ የምንሰጠው ምላሽ ምንድነው? ዛሬም ኦሮሚያ ውስጥ የሚፈፀመው በደል የኦሮሞ፤ አማራ ውስጥ የሚፈፀመው በደል የአማራ ጉዳይ አድርገን እንወስዳለን? መቸ ነው ኦሮሚያ ላይ ለደረሰው ጥቃት አማራዉ፤ አማራ ላይ ለደረሰው ጥቃት ኦሮሞው የሚቆረቆረው?
የሁላችን የጋራ ጠላት የሆነው ህወሓት መኖሩ በዘውግ የተከፋፈለውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ አንድነት የሚያመጣ ታላቅ ኃይል ሊሆን ይገባል። ይህ የመከራና የመጠቃት ወቅት የምንቀራረብበት ወቅት ሊሆን ይገባል። ይህ የመከራ ወቅት በህወሓት ላይ በጋራ የምንነሳበት ወቅት ሊሆን ይገባል። ዛሬ በኢትዮጵያ ያሉ የተለያዩ ማኅበረሰቦች በሙሉ በፀረ-ህወሓት ትግል መቀናጀት ይኖርባቸዋል። ይህ ማድረግ ግዴታችን ነው።
ለችግሮቻችን መፍትሄ የምናገኘው ችግሮቹ ከተፈጠሩበት እርከን በላይ ሆነን ስናስብ እንጂ ችግሮቹ በፈጠሩበት ደረጃ ላይ ቆመን መሆን አይችልም። ችግሮቹ ከተፈጠሩበት እርከን በላይ ለመሆን አገር አቀፍ እይታ መኖሩ እጅግ ተፈላጊ ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያን ሁሉ በተለይም የአማራና የኦሮሞ ልሂቃን ይህንን ጉዳይ አበክረው እንዲያስቡበት አርበኞች ግንቦት 7 በጽኑ ያሳስባል።
ግፍ ሞልቶ የፈሰሰበት ወቅት ላይ እንገኛለን። የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች የሆኑት ሕፃናት በፌዴራል ፓሊስ ጥይት የሚገደሉበት አሳዛኝ ወቅት ላይ ነን፤ ዜጎች በር ተዘግቶባቸው በእሳት እየጋዩ ነው። ሰፊ እና ለም የእርሻ መሬት ለሱዳን በስጦታነት ለመስጠት ዝግጁቱ የተጠናቀቀበት ወቅት ላይ ነን። ከአስር ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ተርቧል። በፍትህ እጦት እስር ቤቶች በንፁሃን ዜጎች ተሞልተዋል። ውሀ፣ መብራትና የቴሌፎን አገልግሎት ብርቅ ሊሆኑ ነው። ይህ ሁሉ እየሆነ ግን የሥርዓቱ አገልጋዮችና ደጋፊዎች በህንፃ ላይ ህንፃ እየገነቡ በድሀው ላይ ይሳለቃሉ። የህወሓት አገዛዝ ድህነትን፣ ችጋርን፣ ስደትን፣ የእርስበርስ ግጭቶችን እያባባሰ ኢትዮጵያን እየጋጠ የሚኖር አገዛዝ ነው። አገዛዙ በቀደደልን ቦይ ከተጓዝን ችግሮችን ማባባስ እንጂ ማርገብ እንኳን አንችልም። ይህንን ሥርዓት በቃህ ማለት የአማራ ወይም የኦሮሞ አጀንዳ አይደለም፤ ይህ የሁላችንም – የኢትዮጵያዊያን – ጉዳይ ነው።
ለቀምት፣ ሀረር፣ ሱልልታ እና ሌሎች በርካታ የኦሮሚያ ከተሞች ውስጥ ለደረሱ ጥቃቶች ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደሴ፣ ሀዋሳ፣ መቀሌ፣ አሶሳ፣ ሁመራ፣ ጋምቤላ ውስጥ ተቃውሞ መሰማት አለበት። በጎንደርና ባህርዳር ለደረሰውም ጥቃት አዳማ፣ ጅማ፣ ሆሳዕና፣ ጅግጅጋ፣ አክሱም ላይ ተቃውሞ መሰማት አለበት። በማንኛውም የኢትዮጵያ ክፍል ለሚደርሰው በደል መላዋን ኢትዮጵያ ሊያሳምም ይገባል። መከፋፈላችን መከራችን አብዝቶታል፤ የህወሓት እድሜን አርዝሟል፤ ይብቃ!
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የመከራ ጊዜዓችን እንዲያጥር በዘውግ ሀረግ፣ በብሔርና እና በሀይማኖትና ሳንታጠር የወገናችን ህመም ይሰማን፤ ተሰምቶንም ለጋራ ትግል እንነሳ ይላል።


ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Thursday, December 3, 2015

ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የቀረበውን ይግባኝ ውድቅ አደረገ

December 3,2015
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክር ሆነው እንዳይቀርቡ ያቀረበውን ይግባኝ ዛሬ ህዳር 23/2008 ዓ.ም በዋለው ችሎት ውድቅ አደርጎታል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ተጠይቆ የነበር ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ በተደጋጋሚ ሳያቀርባቸው ቀርቷል፡፡
አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክርነት በተጠሩበት ወቅት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቦባቸው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባቸው የህዝባዊ መብታቸው የተሻረ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ እንደማይችሉ መቃወሚያ አቅርቦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ይሁንና ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት የተባለውን ጉዳይ ለመናገር በመሆኑ ለምስክርነት ሊቀርቡ ይገባል በሚል የፌደራል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ተቃውሞ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
የልደታ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሀምሌ 13/2007 ዓ.ም ቀርበው ምስክርነት እንዲሰጡ ከወሰነ በኋላ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ‹‹ትዕዛዝ አልደረሰኝም፣ የተፃፈው ለቃሊቲ ሳይሆን ለአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት የሚል ነው›› እና ሌሎችም ምክንያቶች በማቅረብ በተደጋጋሚ አቶ አንዳርጋቸውን ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡ በስተመጨረሻም ጥቅምት 12/2008 ዓ.ም ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ቃሊቲ እንደሌሉ በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ከተከሰሱት መካከል አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) ውጭ ያሉት የፍትህ ሂደቱ እየተጓተተባባቸው በመሆኑ የአንዳርጋቸው ፅጌ ምስክርነት ቀርቶ በሌሎች መረጃዎች ውሳኔ እንዲሰጥላቸው ሲጠይቁ ሁለቱ ተከሳሾች ግን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሊመሰክሩላቸው እንደሚገባ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ነበር፡፡
በዚህም መሰረት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለፀረ ሽብር ግብረ ኃይልና አቶ አንዳርጋቸውን ጠይቀውታል ለተባሉት የብሪታኒያ አምባሳደር ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወቃል፡፡ ይሁንና ተከሳሾቹ ለሶስቱ አካላት ደብዳቤውን በፃፉበት ማግስት የፌደራል አቃቤ ህግ ከወራት በፊት ለልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ መመስከር አይገባቸውም ብሎ አቅርቦት የነበረውን መከራከሪያ መሰረት በማድረግ አቶ አንዳርጋቸው ምስክር እንዳይሆኑ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠይቆ ነበር፡፡
የአቃቤ ህግን ይግባኝ ያየው ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ዛሬ ህዳር 23/2008 ዓ.ም በዋለው ችሎት ‹‹አንድ ሰው ለምስክርነት ይቅረብ አይቅረብ በሚል ይግባኝ ሊጠየቅበት አይገባም፡፡ ካስፈለገ ግለሰቡ የሰጡት ምስክረነት መረጃው ተመዝኖ የሚሰጠው ፍርድ ላይ ይግባኝ ሊባል ይችላል፡፡ እኛም ጉዳዩን ለማጣራት ምስክርነቱ እንዲቋረጥ አድርገን የነበር ቢሆንም አሁን ግን እንዲቀጥል ወስነናል፡፡ የአቃቤ ህግን ይግባኝም አልተቀበልነውም›› ሲል ይግባኙን ውድቅ አድርጓል፡፡ አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክር መሆን የለባቸውም ብሎ ያቀረበው ክርክር በፍርድ ቤት ውድቅ ሲሆንበት ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከተከሰሱት በተጨማሪ በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል 1ኛ ተከሳሽ አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በመከላከያ ምስክርነት ጠርቷቸዋል፡፡ በሌሎች የክስ መዝገቦች ከአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር ተገናኝታችኋል የተባሉ ተከሳሾችም አቶ አንዳርጋቸውን የመከላከያ ምስክር አድርገው ሊጠሯቸው እንደሚችሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልፀዋል፡፡

የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት መገኘት ለኢትዮጵያ ዲሞከራሲ ሀይሎች የጋራ ዲፕሎማሲያዊ ድል ነው

December 3,2015

ከዚህ ወዲያ አፍ እንዳመጣ “ሽብርተኛ” ማለት የህወሃት መሩ መንግስት እብደት ሆነ!

የፕ/ር ብርሃኑ ነጋን የአውሮፓ ፓርላማ ንግግር በተመለከተ የኢሳት ዘገባን ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ – የቪኦኤ ዘገባ ለማዳመጥ ደግሞ እዚህ ይጫኑ
ቢላል አበጋዝ – ዋሽግተን ዲሲ
ዛሬ ኢትዮጵያ ለህወሃት መሩ መንግስት ተንፈራጦ መግዛት የምትመች አለመሆንዋን ማንም ዜና መከታተል ለሚፈልግ ግልጽ ነው።የህወሃት ባለስልጣናትም ከወትሮው በተለየ መልኩ እርስ በርስ እየተናቆሩ ነው።ተስፋ የቆረጡት ደግሞ ንብረት እያሸሹ ይገኛሉ።በቀይ ባህር አካባቢ አፍሪካ ቀንድን ሊያምስ የሚችል ደመናም ጥሏል ማለት ይቻላል።ሀብታም አረቦችም ልክ እንደ ህወሃት በስጋት ተወጥረዋል።ኢትዮጵያን ማተራመስ ቅር ሳይላቸው ማንኛውንም ድርጊት የሚፈጽሙ ለመሆናቸው የቅርብ ጊዜ ታሪካችን ይመሰክራል።Professor Berhanu Nega in Eritrea
ከላይ የጠቀስኩት አደጋ ማንጃበቡ ሳያንስ ዛሬ አስራ አምስት ሚሊዮን ወገናችን ለራብ ተዳርጓል።ይህን መከራ በመካድ የጀመረው ህወሃት ህይወት ለማትረፍ የሚጥር አይደለም።በኢትዮጵያ በያለበት እስራትና ግድያው በርትቷል።የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት ስለ ኢትዮጵያ እንዲናገር መጋበዙ ያቀረብኩትን የኢትዮጵያ ሁኔታ ለመንግስታቱ ተወካዮች መግለጽ ብቻ ሳይሆን አጣዳፊ ሁኔታ መፈጠሩንም የማስስጨበጥ ሁኗል። ኢትዮጵያን የፋሺት ኢጣሊያ መንጋጋ ሲያኝካት የተሰደዱ አርበኞች በዓለም መድረክ ጮሆውላት ነበር። ዛሬም በህወሃት መንጋጋ ስትታኘክ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከኢትዮጵያውያ ወገኖቹ ጋር ሆኖ ድምጹን ከፍ አድርጎ አሰምቶላታል።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይህን የፈጸመው በግንባር ሆነው ህወሃት መሩን መንግስት ብርክ እያስያዙ ያሉትን የኢትዮጵያን ጀግኖች ከበረሃ ተለይቶ ነው።
የኢትዮጵያ ሁኔታ ጊዜ የማይሰጥ ነው።ህወሃት መሩ መንግስት በመለስ ዜናዊና ጀሌዎቹ አማካይነት ያፈላው የጥላቻ ጥንስስ ድንገት ሳይፈነዳ አደጋውን ሊገታ የሚችል ዝግጅት ማድረግን ይጠይቃል።ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ሁሉም የሚወከልበት ጊዜያዊ መንግስት ካልቆመ ወያኔ ፈጽሞ የመግዛት ሀይሉን ሊያጣ የሚችልበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም።ህዝቡ በቃኝ ለማለቱ ምልክቶቹ መበራከታቸው ይህን አመላካች ነው።የኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ሃይማኖትን ተቋማት ጣልቃ በመግባት አዳክሟል።የእስልምና ሃይማኖት ተቋማትን ደፍሮ መሪዎችን ለእስር ዳርጓል።ነጻነትና ዜግነት በየፈጁ ተደፍሯል።
የዓለም መንግስታት በተለይ ሃያላን የኢትዮጵያን ጉዳይ ወደጎን በመተው ህወሃት መሩን መንግስት መወንጀል ሳይሆን በስመ ሽብርተኝነትን መቋቋም አብረውት እየሰሩ ነው።በታሪካችንም የፋሺት ኢጣሊያውን ሙሶሊኒንም አይዞህ ያሉት ነበሩ።ሁሉም ለየራሱ ጥቅም በዓለም ዲፕሎማሲ ሰልፉን ያስተካክላል።በየጊዜውም ይለውጣል።ኢትዮጵያን የምንል አንድ መሆን የግድ የሚለን ጊዜ አሁን ነው።ህወሃት መሩ መንግስትማ ለሙግት፡ለመልስ እንኳን ያቆመው ቅጥረኛ የውጭ አገር ተላላኪን ነው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዋለበት መድረክ።የህወሃት ድንቁርና አንድ መገለጫ ምልክት ነው።የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአውሮፓ ህብረት መግለጫ መስጠት ህወሃት መሩን መንግስት ለሚቃወሙና ለተራበው ከተሜ ገጠሬ ወገናችን ትልቅ ግምት የሚሰጠው ዲፕሎማሲያዊ ድል ነው።ኢትዮጵያ በዚህ የመከራ ዘመን ለታደጓትን አላህ ለነሱም ይመስክርላቸው።
ድል ለዲሞክራሲያዊ ሀይሎች ሁሉ!
ኢትዮጵያ በአንድነትዋ በነጻነት ለዘለዓለም ትኑር!
አላህ ኢትዮጵያ ይጠብቃት!