Tuesday, June 9, 2015

ገዳይና ሟች – አየር ኃይልና ህውሃት

June 9, 2015
አዲስ (ከሲልቨር ስፕሪንግ)
ለኢትዮጵያ አየር ኃይል ቀናዒነት ስላለኝ በቅርብ እርቀት እከታተላለሁ ። ከአባላቱም ጋር በስደት የቅርብ ወዳጅነት መስርቼ ከልብ ትርታቸው ጋ የእኔን አዛምጄ ፣ በአዘኑበት አዝኜ ፣ ሲደሰቱ ተደስቼ ለማንኛውም ጥሪያቸው በግምባር ቀደምትነት ምላሽ በመስጠት በሁሉም ቦታ ታድሜ እነሆ ዘመናት ተቆጠሩ።Ethiopian air force
እማውቀው – እኔ ከብዙዎቹ አንዱ እንደሆንኩ ነው ። የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል በብዙሃኑ ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ በቁጭት አክብሮትና አድናቆትን እንደተጐናፀፈ ከትውልድ ትውልድ እያንፀባረቀ ቢመጣም ፤ የኋላ ኋላ ዕጣ ፋንታው ግን መበተን ፣ መሰደድ ፣ ያለ ፍርድ ለዘመናት መታሰርና ፣ ለሞት ፍርድ ተላልፎ መሰጠት ሆነ ። ይህም እንኳ ሳያግደው ዝናው በጠላቶቹም ጭምር ሳይቀር ከዳር እስከዳር እንደናኘ ዛሬም አለ።
ታድያ ዛሬ የዚህን ታላቅ ወታደራዊ ተቋም ታሪክ በመፅሃፍ ተፅፎ ማየት በህይወት ላሉት ክብር ፣ ለሰፊው ህዝብ ማስታወሻ ፣ ለመጪውም ትውልድ መማሪያ መሆኑ የማንኛውም ቅን ዜጋ ህልም ነው ፤ ለአባላቱና ለቤተሰቦቻቸውም ደግሞ ኩራትና እፎይታ ነው።
ለዚህም ነበር ይህንን ታላቅ አላማ ሰንቀው ለተንቀሳቀሱ የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አንጋፋ አባላት በከፍተኛ ሁኔታ ድጋፍ የተሰጠው ። ድጋፍ በገንዘብ ፣ ድጋፍ በማቴሪያል ፣ ድጋፍ በሞራል …. ወዘተ።
የታሪክ መፅሃፉን እውን ለማድረግ ለዘመናት ሲዳክሩ የነበሩት ፣ በአየር ኃይሉ ውስጥ ቀደምትነት ያላቸው የተከበሩ ፣ ስመጥርና ገናና የመሆናቸውን ያክል ፤ አጨራረሱ ላይ ግን በፊት አውራሪነት በኢትዮጵያችን እየተለመደ የመጣው የገዢው ስርዓት ተዋላጆች ዋነኛ ባለቤት እየሆኑ የብዙሃኑን ቀና ግምት ወደ ትዝብት ፣ ሃዘንና ጥርጣሬ የወሰደ አልነበረም ብሎ መደምደም አይቻልም።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም የመፅሃፉ ይዘት በምን መልኩ ይቀርብ ይሆን የሚለው ከአገር ቤት እስከ ዲያስፖራው የቀድሞው አባላቱ መካከል የተለያየ ሃሳብ ከየአቅጣጫው ተነስቶ በመግባባትም ፣ ባለመግባባትም እንደተናጠ ነበር መፅሃፉ ከመደብር ሳይሆን በውስጥ አወቆች እዚህ ደጃችን የደረሰው።
ስለዚህ የጥያቄውና የውይይቱ መሰረተ ሃሳብ ለምን የአየር ኃይሉ የታሪክ መፅሃፍ ተፃፈ የሚል አይመስለኝም ። በፍፁም አደለምም ። የተወሰኑ ግለሰቦች ግን ለምን የአየር ኃይል ታሪክ ተፃፈ የሚል ጥያቄ እንደተነሳ አስመስለው ለማቅረብ ሲታገሉ በቅርብ አስተውያቸዋለሁ ። ጥያቄው ለምን መፅሃፉን ወደ ጠላት ጉያ ከተቱት (ምክንያቱም የአየር ኃይልን ቁስልና ጥቃት ለመግለፅ አመቺ ቀጠና ስላልመረጡ) ነው እንጂ ለምን ታሪኩ ተፃፈ አይደለም ብዬም ደጋግሜ አስረድቻቸውም ይህንን ይዘሉታል ። ስለዚህ ሆን ተብሎ የሚሰራ ነገር አለ ማለት ነው።
እንደ ግለሰብ ማንኛውም ሰው ፖለቲካዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ወዘተ አመለካከቶች ሊኖሩት ይችላል ። ይህም ሊከበርለትና ሊበረታታም ይገባል ። ሆኖም ግን የዚህ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ታሪክ አካሎች የኢትዮጵያ አየር ኃልይ አባላት ናቸው ። ባለቤቱ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ ነው ። እንግዲያውስ በዚህ መፅሃፍ ዝግጅት ዙርያ የተለያየ ሃሳብ ቢነሳ ሊደመጥና ከግንዛቤ ውስጥ ገብቶ ትኩረት ተሰጥቶት በሃሳብ ተፋጭቶም ነጥሮ ሊወጣ ይገባዋል ፤ ለመፅሃፉም ግብዓት አስተዋፅዖው ቀላል አይሆንም ፤ የታሪኩንም ሙልዓዊነት ሲያዳብረው ተዓማኒነቱንም ከፍተኛ ያደርገዋል ። ይህንንም ስል እንዲያው መቋጠሪያ በሌለው ውዝግብ ውስጥ ገብቶ መቧቸሩ አስፈላጊ ያለመሆኑን እየተረዳሁ ቢያንስ ግልፀኝነትና ታማኝነት በተሞላበት ሁኔታ በተደራጀ መልኩ (በየአካባቢው) በቡድን ኰፒውን የማየትና ሃሳብ የመለዋወጥ ዕድሉ ሊኖር በተገባ ነበር ። አለፍም ሲል በእድሜም ሆነ በልምድ የተከበሩ የሰራዊቱ አባላት እንደዚህ አይነቱን የግራ ቀኝ የሃሳብ ፍጭት ሃላፊነት ወስደው ማወያየትና ሁሉንም በተቀራረበ ግንዛቤ ሸክፎ በአንድነት እንዲጓዝ ማድረግ ታሪክ የጣለባቸው ትልቅ ሃላፊነት መሆን በተገባው ነበር።
ለመሆኑ ችግሩ ምንድነው ? ለምንስ ወደ አላስፈላጊ ጭቅጭቅ በሚል መሸፈኛ እነዚህ ከስርዓቱ ጋር ወስደው ያጣበቁን ሰዎች የፈለጉትን ለማድረግ በር የሚከፍት አካሄድ ተመረጠ ? ትላልቅ የሚባሉት ሰዎችስ ሃላፊነት በሚሰማው መልኩ መሃል ገብተው ማወያየትና መዳኘት ለምን ወኔ ከዳቸው ? ይህ ሃላፊነት ተወስዶ ቢሆን ኖሮ ቢያንስ ዛሬ ላይ ለተነሳው የክህደት ጥያቄ ባልተጋለጠን ነበር።
አገራችን ኢትዮጵያ በረዥም ዘመን ታሪኳ ውስጥ አሁን እንዳለችበት ጊዜ ችግር ገጥሟት አያውቅም ። ለእናት አገራቸው ደከመን ሰለቸን ሳይሉ በሙያቸው እያገለገሉ ሲዋደቁ የነበሩ ፣ ጊዜው በደረሰበት ቴክኖሎጂ የታነፁ ፣ በአፍሪካ ግምባር ቀደሙን አየር ኃይል የአኩሪ ገደል ባለቤት ያደረጉ ፣ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ፣ ለኢትዮጵያ ሲቪል አቬየሽን ጥንስስና መሰረት የጣሉ ፣ ለተለያዩ ሲቪል ተቋማትና አምራች ድርጅቶች አመራር መፍለቂያ የሆኑ ፣ በጤና ፣ በስፖርት የአገሪቷን ስም በዓለም እንዲናኝ ያደረጉ ወዘተ ታላላቅ ሰዎች ሁሉ ሲዋረዱና እንዲሸማቀቁ ሲደረግ በዓይናችን እንድናይ የተገደድንበት ዘመን ላይ ነን ያለነው።
በኢትዮጵያ የአብዮት ዘመንም ተነሳ ተራመድ ብለው በግንባር ቀደምትነት የህዝብን የለውጥ ፍላጐት በመምራት የህዝብ ዕምባ ጠባቂ በመሆን ያገለገሉ ፤ ረዥሙ የእርስ በርስ ጦርነትም ማብቂያ ይበጅለት ብለው በግንቦት 8፣ 1981 ብርቅዬና ውድ አመራሮቻቸውን የገበሩ ፤ ለእናት አገሩ ዘብ በመቆሙና በማገልገሉ ጀግኖቹ አባላቱ ተዋርደው ፣ ታስረው ፣ ተሰደው ፣ ተገልለውና ተሸማቀው እንዲኖሩ የተደረገበት ። የሞት ፍርድ እንኳ ሳይቀር የተበየነበት ዘመን ነው።
ዛሬም እንኳ ይህቺን ፅሁፍ እየጫጫርኩ ባለሁበት አጋጣሚ የግንቦት 20 ድል እየተከበረ ስለ ጨፍጫፊው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሲያላዝኑ ይሰማል ። ሌላው ቢቀር በአንድ ወቅት አየር ኃይሉን እንዲጐበኙ ለተደረጉት አርቲስቶች እንዳሉት የሞተ ፣ የተማረከ ፣ የተንኰታኰተና የተሽመደመደ አየር ኃይል እንደተረከቡና ዛሬ ግን እነሱ አየር ኃይሉን ከፍተኛ ደረጃ እንዳደረሱ ሲገልፁ መስማት ምንኛ ያማል ? እነዚህ የመፅሃፉ አዘጋጆች እንደዚህ አይነቱ የመንግስት ዘለፋ ሊሞቃቸውም ሆነ ሊበርዳቸውም እንዳልቻለ ማስተዋል ገረሜታን መፍጠሩ አልቀረም።
ታድያ ዛሬ መነሻው በተድበሰበሰ ሁኔታ ተጀቡኖ ፣ በአሳዳጆቹ ዳንኪራ ቤት (ሸራተን) በተሰጠ የችሮታ ድግስ የተጀመረው የመፅሃፍ ዝግጅት ፣ የሌላውን ሃሳብ ባለማዳመጥ በድንገት የምረቃው ዜና አሁንም በአሳዳጆቹ አጋፋሪነት መሰማቱ ከፍተኛ ሃዘንና ድንጋጤ ቢፈጥር ምን ይገርማል ? ክህደትስ ነው ቢባል ምን ያጠራጥራል?
ደግሞስ የመፅሃፉ አወጣጥና አካሄድ አላግባብ በማን አለብኝነት ብሎ መተቸት ከመፅሃፉ ይዘት ጋር ምን ያገናኘዋል ? አዎ ወደ አይቀሬው የመፅሃፉ ይዘት ወደድንም ጠላንም እንገባለን! አወጣጡ ግን የተሽመደመደ ፣ በክህደት የተሞላ ፣ ለአፍራሾቹ በበቂ ሁኔታ ምላሽ ሊሰጥ የማይችል መሆኑን በድፍረት እናገራለሁ ። ወደፊት በመፅሃፉ ባህሪና ይዘት ላይ ብዙ ለማለት እንድችል ከወዲሁ ይህንን ሳልጠቁም ማለፍ ስላልፈለኩ ነው።

Monday, June 8, 2015

Ethiopia: Patriotic Ginbot 7 fighters pictures has gone viral

June 8, 2015
Following the Ethiopian sham election which the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) claim 100 percent of 442 parliamentary seats, most Ethiopians are talking about the alternative struggle to bring change.
Currently it looks like the Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy freedom fighters are getting more and more attention.
Below Patriotic Ginbot 7 rebel’s training exercises pictures that has gone viral on social Medias.
Patriotic Ginbot 7 fightersPatriotic Ginbot 7 fighters
Patriotic Ginbot 7 fighters
Patriotic Ginbot 7 fighters
Patriotic Ginbot 7 fighters


በአማራ ክልል የሚገኙት የመንግስት ድርጅቶች በልዩ ሃይል እንዲጠበቁ እያተደረጉ ነው

June 8,2015
bahire
የ2007 ምርጫን የወያኔ መንግስት በሁሉም ክልሎች በከፍተኛ ድምጽ ምርጫውን እነዳሸነፈ ማወጁ ይታወሳል  ይህንንም ተከትሎ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ውጥረት የነገሰ  ሲሆን  የምርጫውን የውጤት ማጭበርበር በመቃወም  ከሌላው ክልል በበለጠ በኦሮሚያና፣ በአማራ ክልሎች የህዝቡ ቋጣ በከፍተኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን፣በዚህም የተነሳ  በአማራ  ክልል የብአዴን/ኢህአዴግ ካድሬዎች በህዝቡ ላይ ያላቸው እምነት እያሽቆለቆለ በመመጣቱ በክልሉ ላይ የሚገኙት የመንግስት ድርጅቶች በልዩ ሃይል እንዲጠበቁ ማድረጋቸውን ተገለፀ::

 ከክልሉ ባገኘነው መረጃ መሰረት ግንቦት 16/2007 ዓ/ም የተካሄደውን የይስሙልና ከምርጫውም በኋላ ወያኔ /ኢህአዴግ መቶ በመቶ እንዳሸነፈ በተለያዩ ሚዲያዎች በተገለፀው ግዜያዊ ውጤት ባለመርካቱ የተነሳ    በአማራ ክልል የሚኖሩ የክልሉ ነዋሪዎች  ድምፃችንን ተሰርቀናል በማለት በተለያየ መንገድ ቁጣቸውን  እየገለፁ ሲሆን ከዚህም የተነሳ  በክልሉ ያሉ የወያኔ ካድሬዎች  ህዝቡ ተቃውሞ ሊያነሳ ይችላል የሚል ትልቅ ስጋት እነደፈጠረባቸውና በፍርሃት ውስጥ እነደሚገኙ ታውቋል ::

 በክልሉ ያለውን የህዝቡን ቋጣ ተከትሉ ለተፈጠረባቸው ስጋት የወያኔ ካድሬዋች እየወሰዱ ያሉት እርምጅ በክልሉ የሚገኙት እንደ ሱር ኮንስትራክሽን፤ ባንኮች፤ ቴሌና የመሳሰሉት ድርጅቶችን ቀደም ሲል በህጋዊ መንገድ ተቀጥረው ሲሰሩ የነበሩ የጥበቃ ሰራተኞችን በማባረር ልዩ ጥበቃ ተብለው በሚታወቁ ታጣቂዎች እንዲጠበቅ እያደረጉ መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፣ ወያኔዎች ይህንን ማድረጋቸው የበለጠ የህዝቡን ቁጣ እንደሚቀሰቅሰው የአካባቢው ነዋሪዎች እየተናገሩ ይገኛሉ::

ይህ አይነቱ በታጣቂ ሓይሎች ተደርጎ ህዝቡ ዓመፅ እንዳያካሂድ ተብሎ የሚደረግ የተጠናከረ የጥበቃ አካሄድ በአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን በመላው ያገራችን አካባቢዎች ውስጥ ለውስጥ እየተሰራበት እንደሆነ።ያገኘነው  መረጃ ያስረዳል::

ሪፖርተር ገዛኸኝ አበበ

Saturday, June 6, 2015

Befeqadu Hailu: An Ethiopian Writer Who Refused to Remain Silent

June 6, 2015
by Nwachukwu Egbunike | Global Voices
Befeqadu Hailu: An Ethiopian Writer
Asmamaw, Befeqadu (middle) and Edom participating in a race organized in Addis Ababa. Photo courtesy of family.
In April 2014, nine bloggers and journalists were arrested in Ethiopia. Several of these men and women had worked with Zone9, a collective blog that covered social and political issues in Ethiopia and promoted human rights and government accountability. And four of them were Global Voices authors. In July 2014, they were charged under the country’s Anti-Terrorism Proclamation. They have been behind bars ever since, their trial postponed time and again.
This marks the third post in our series – “They Have Names” – that seeks to highlight the individual bloggers who are currently in jail. We wish to humanize them, to tell their particular and peculiar stories. This story comes from Nwachukwu Egbunike, a Nigerian poet, writer, and blogger who has worked with Global Voices since 2011.
Befeqadu Hailu is an Ethiopian writer who could not quiet his conscience in the face of brutality and human rights violations in his country. For this, he is currently in behind bars.
His novel, Children of Their Parents won the 2012 Burt Award for African Literature. He also writes poetry. It seemed only natural that his passion found visible expression in blogging, and that he became a co-founder of the Zone9 bloggers collective.
Using the Internet, Befeqadu personified those eternal words of the grandfather of African literature, Chinua Achebe: “an artist, in my understanding of the word, should side with the people against the Emperor that oppresses his or her people.” For doing this, Befequadu was deprived of his freedom.
Befeqadu and eight others have been charged with terrorism and incarcerated since April 2014.  But the real wrongdoers are his jailers: a repressive government that forbids critical dissent. That is indeed the great crime of Befeqadu and his colleagues. They refused to conform to the norm of silence. This trait is obviously innate in any writer, that compulsion not to keep quiet. The poetry in Befequadu’s veins could not be bottled by state intimidation or stifled with the bars in a jail.
Writing from prison, Befeqadu’s strong and unbending will to stand for the truth remains unbroken. In a letter describing his experiences over the first few months of his incarceration, he described repeated interrogations that he underwent in which authorities asked him, “so what do you think is your crime?” He mediated on this question:
“So what do you think is your crime?”
The question is intriguing. It sheds light on our innocence, on our refusal to acknowledge whatever crimes our captors suspect us of committing. Yes, they probed us severely, but each session ended with same question. The investigation was not meant to prove or disprove our offenses. It was meant simply to make us plead guilty.
After two years of writing and working to engage citizens in political debate, we have been apprehended and investigated. Blame is being laid upon us for committing criminal acts, for supposedly being members and “accepting the missions” of [opposition political parties]…
[…]
No matter what, boundaries exist in this country. People who write about Ethiopia’s political reality will face the threat of incarceration as long as they live here.
We believe that everyone who experiences this reality, dreading the consequences of expressing their views, lives in the outer ring of the prison – the nation itself. That is why we call our blog Zone9.
The weight of that question: “so what do you think is your crime?” and the corresponding response shed light on the irony of the jailer (held captive only by fear) and the jailed (who possesses interior freedom). In the words of Wole Soyinka, “books and all forms of writing are terror to those who wish to suppress the truth.”
Befequadu is in jail because he writes.
Weaving stories untold
Befeqadu Hailu is an Ethiopian Writer
Digital drawing of Befeqadu Hailu by Melody Sundberg
Lauding stories unheard 
Shouting for gagged voices
Serving rising voices
From the four compass points
From sun’s rising to its setting
From the Atlantic to the Sahara 
Let a mighty echo arise,#FreeZone9Bloggers!

የህወሓት አምባገነናዊ ስርዓት በመላ አገሪቱ ያሰፈነውን ቅጥያጣ የገበያ ስርዓትና….

June 6, 2015
def-thumb ጭቆና በመቃወም ባለሀብቶችና በሰላማዊ መንገድ ሲታገሉ የቆዩ የተቀናቃኝ ፓርቲዎች አባላት በረሃ እየወረዱ ብረት ማንሳታቸውን ቀጥለዋል፡፡
ሰሞኑን በርካታ ቁጥር ያላቸው ባለሀብቶችና የአንድነት ፓርቲ አባላት በረሃ ወርደው አርበኞች ግንቦት ሰባትን ተቀላቅለዋል፡፡
ህወሓት-ኢህአዴግ የሚያራምደው በጎሰኝነት የተቃኘ የምጣኔ ሀብት ስርዓት አላላውስ ያላቸው ነጋዴዎችና ሰላማዊ ትግል ያበቃለት መሆኑን የተረዱት የአንድነት ፓርቲ አባላት ኢትዮጵያ ውስጥ የስርዓት ለውጥ መጥቶ እውነተኛ ነፃነት እንዲሰፍን ከልብ ከታመነ ብቸኛው መፍትሄ ጠብመንጃ ስለሆነ በአገር ቤት ያሉ ባለሀብቶችና የተቀናቃኝ ፓርቲ አባላት የእነሱን ፈለግ እንዲከተሉ ጠንከር አድርገው አሳስበዋል፡፡
ከሳምንት በፊት የአግአዚ ኮማንዶ ክፍለ ጦር አባላትን ጨምሮ በርካታ የመከላከያ ሰራዊት አባላትና ባለሀብቶች በረሃ ወርደው አርበኞች ግንቦት ሰባትን መቀላቀላቸውን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

Friday, June 5, 2015

በመርካቶ የተቀሰቀሰውን እሳት በቁጥጥር ስር ለማዋል አሁንም ጥረቱ እንደቀጠለ ነው

June 5,2015
ዘጋቢ ገዛኸኝ አበበ
ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ በአዲስ አበባ መርካቶ በተለምዶ ሸራ ተራ በሚባለው ስፍራ ከባድ የሆነ እሳት ተቀስቅሷል። እሳቱ በሸራ ተራና አብዶ በረንዳ ተብሎ በሚጠረው አካባቢ በአደገኛ ሁኔታ እየተያያዘ ሲሆን የእሳት ቃጠሎው መነሻ ለጊዜው ባይታወቅም  በስፍርው የተቀሰቀሰው እሳት ግን በጣም አስፈሪና ከበድ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል ።በአካባቢው የተቀሰቀሰውን እሳት በቁጥጥር ስር ለማዋል  ድረስ ጥረቱ እንደቀጠለ ሲሆን የአሳት ቃጠሎውን ግን  እስከአሁን ድረስ መቆጣጠር እንዳልተቻለ ታውቋል።

 ከሰፍራው  ያገኘነው ዜና እንደሚያስረዳን ከሆነ እሳቱን ለማጥፋት የእሳት አደጋ መኪኖች በስፍራው የነበሩ ሲሆን ነገር ግን  የእሳት አደጋ መኪኖቹ ውሃ ጨርሰው ሲመላለሱ ታይተው ነበር ።

 የአካባቢው ነዋሪና በአካባቢው በንግድ ስራ የተሰማሩት ሰዎች ግን  እሳቱን ለማጥፋት በተቻላቸው  አቅም ሁሉ በመረባረብ ጥረት ያደረጉ ሲሆን የተለያዩ መሳሪያ የታጠቁ ፊደራል ፖሊሶች ግን የእሳት አደጋው በተነሳባቸው ሱቆች ምንም ዓይነት ዝርፊያ እንዳይፈፀም ጥበቃ  በማድረግ በሚል ሰብብ ከተለያዩ የስፍራ በፍጥነት በመምጣት አካባቢውን ወረውታል።

  ህዝቡም በሙሉ አቅሙ እሳቱን ተረባርቡ እንዳያጠፋ በስፍራው የነበሩት የፌዴራል እና የአዲስ አበባ ፖሊሶች ችግር የፈጠሩባቸው ሲሆን እሳቱን ለማጥፋት ሲረባረቡ በነበሩ ወጣቱች ላይም አካባቢውን የወረሩት የወያኔ ፊደራል ፖሊሶች የተለያዩ ወከባ ሲያደርሱባቸው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

ይህ ዜና  እስከ ተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በአካባቢው የሚገኙት የእሳት አደጋ ሰራተኞችም አሁንም እሳቱን ለመቆጣጠር ጥረት በማድረግ ላይ ሲሆኑ። የአዲስ አበባ የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለስልጣን በከተማዋ ካሉት ሁሉም ቅርንጫፎች የእሳት ማጥፊያ ተሽከርካሪዎቹን በማሰማራት ቃጠሎውን ለማስቆም ጥረት እያደረገ ሲሆን ህብረተሰቡና የባለ ሱቆች ባለቤትም በእሳት ከተያያዙ ሱቆች ውስጥ ሸቀጦችን ለማዳን ጥረት እያደረጉ ሲሆን ሌላው እሳቱን ላለመቆጣጠር አስቸጋሪ ያደረገው ነገር

በእሳት በተያያዙ ሱቆች ውስጥ የፕላስቲክ ምርቶች የሚገኙ በመሆናቸው እና አከባቢው ተሽከርካሪን እንደልብ የማያንቀሳቅስ በመሆኑ እሳቱን የማጥፋት ዘመቻውን አስቸጋሪ ማድረጉ ተመልክቷል። ሌላው የእሳቱን ቃጠሎ እየተባባሰ  መምጣት አሳሣቢ ያደረገው ጉዳይ በዛው አካባቢ አንድ ትልቅ የዘይት ማምረቻ መኖሩ ሲሆን እሳቱ ወደዛ ከቀጠላ  በአካባቢው ትልቅ ጥፋትና ውድመት ማስከተሉ እንደማይቀር ተሰግቷል።



ሰማያዊ የG-7 መሪዎች በኢህአዴግ ላይ ጫና እንዲያደርጉ አሳሰበ

June 5,2015
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ሰማያዊ ፓርቲ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ነገ ግንቦት 29/2007 ዓ.ም በሚካሄደው የG-7 ስብሰባ መጋበዛቸውን ተከትሎ የወቅቱ የጉባኤው መሪ ለሆኑት የጀርመን ቻንስለር ለአንጌላ ሜርክል በፃፈው ደብዳቤ መሪዎቹ በኢህአዴግ ላይ ጫና እንዲያደርጉ አሳስቧል፡፡
 
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በስብሰባው ላይ መጋበዛቸው ቅር እንዳሰኘው የገለፀው ፓርቲው 24 አመት በስልጣን ላይ የቆየው የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ፓርቲ አፋኝ ለመሆኑ የ2007 ዓ.ም ጠቅላላ ምርጫን በምሳሌነት ጠቅሷል፡፡ ምርጫው ልምድ ያላቸው የውጭ ታዛቢዎች ያልተገኙበትና የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ ቡድንም ‹‹ነፃና ፍትሓዊ›› ነበር ለማለት ያልደፈረበት፣ ሰማያዊን ጨምሮ ሌሎች ተቃዋሚ ፓርቲዎች የተጭበረበረ መሆኑን ማረጋገጣቸውን በደብዳቤው አስታውሷል፡፡
ምርጫው ገዥው ፓርቲ 100% አሸነፍኩ ያለበት፣ ተቃዋሚዎች ላይ ከፍተኛ ጫናና እስር ከዚህም ሲያልፍ ለሞት የተዳረጉበት ነበር ያለው ሰማያዊ ፓርቲ ገለልተኛ ሲቪክ ማህበራት እንዳይታዘቡ መከልከላቸውን ገልጾአል፡፡ ጋዜጠኞችን፣ ጦማሪያንን፣ የሀይማኖት አባቶችንና ፖለቲከኞችን ለማጥቃት በወጣው የፀረ ሽብር ህግ ምክንያት ኢትዮጵያ በፖለቲካ እስረኞች ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ መሆኗን ፓርቲው አስታውሳል፡፡
የጉባኤው አባላት ከኢትዮጵያ ጋር ባላቸው የንግድ ግንኙነትና በሚያበረክቱት እርዳታ ምክንያት በሰብአዊ መብት፣ ዴሞክራሲና ልማት ላይ አዎንታዊ አስተዋጽኦ ማድረግ የሚችሉ ቢሆንም የኃይለማርያም ደሳለኝ ፓርቲ የሚመራው መንግስት ለሰብአዊ መብት፣ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት እየገደበና ተቃዋሚዎች ላይ ከፍተኛ በደል እያደረሰ ይገኛል ብሏል፡፡
ጉባኤው ሰብአዊ መብትና ዴሞክራዊያዊ መብትን ለልማትና የኢኮኖሚ ግንኙነት በቅድመ ሁኔታነት በመውሰድ ጫና ማድረግ ካልቻለ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ግንባታን እንደሚጎዳም ሰማያዊ ፓርቲ አሳስቧል፡፡ በመሆኑም ጉባኤው የፖለቲካ እስረኞች ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን ማሰርና እንቅስቃሴያቸውን ከመገደብ እንዲቆጠብ እና አፋኝ አዋጆች ላይ ማሻሻያዎች እንዲደረግባቸው በኢህአዴግ መንግስት ላይ ጫና እንዲያደርግና ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ አሳስቧል፡፡

Tuesday, June 2, 2015

የመንግስትና የፖሊስን መልካም ስም አጥፍተዋል የተባሉ ወጣቶች ተፈረደባቸው

June 2,2015
 ኢሳት ዜና :-አይ ኤስ የተባለው አሸባሪ ቡድን በኢትዮጵያውያን ላይ የወሰደውን ዘግናኝ እርምጃ ለማውገዝ በተጠራ ሰልፍ ላይ የመንግስትንና የፖሊስን ስም አጥፍተዋል የተባሉ ወጣቶች በእስርና በገንዘብ ተቀጥተዋል።

አስማማው ወልዴ፣ የማነ ወርቅነህ፣ ስንታየሁ ታሪኩ፣ ያሲን ቃሲምና ይግረማቸው አበበ ሚያዚያ 14 ቀን 2007 ዓም ጠ/.ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ጠ/ሚኒስትሩን መሳደባቸውን በክሱ ላይ ተገልጿል።

አስማማው ወልዴና የማነ ወርቅነህ በመስቀል አደባባይ አድርገው ወደ ቤተመንግስት ሲያልፉ የመንግስትን ስም የሚያጠፉ ቃሎችን በመጠቀም መሳደባቸውን ክሱ በተጨማሪ ያስረዳል።
ፍርድ ቤቱ ወጣቶቹ መንግስትን መሳደባቸውን ማረጋገጡን በመግለጽ፣ ስንታየሁ ታሪኩ፣ ያሲን ቃሲምና ይግረማቸው አበበ በ4 ዓመት ጽኑ እስራት ፣ አስማማው ወልዴና የማነህ ወርቅነህ ደግሞ 500 ብር እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፏል።

በተመሳሳይ ዜናም ናትናኤል ያለምዘውድ በእለቱ ሁከትና ብጥብጥ ፈጥሯል በሚል በ 3 ዓመት ከ3 ወር እስር እንዲቀጣ ፍርድ ቤት ወስኖበታል። ተመሳሳይ ክስ የተመሰረተባቸው ማቲያስ መኩሪያ፣ ብሌን መስፍን፣ ተዋቸው ዳምጤና መሳይ የተባለ ሌላ ወጣት መከላከያ ምስክር ለማቅረብ ለሰኔ 4 መቀጠራቸውን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። እነ ማቲያስ ‹‹ሰልፉ ላይ ሀሰተኛ ወሬ በማውራት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየተናገሩ በነበረበት ወቅት ወደ ፖሊስ ድንጋይ በመወርወር፣ ህዝቡን አትነሳም ወይ በማለት” ለመቀስቀስ ሞክረዋል የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል።

በተመሳሳይ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየተናገሩ በነበረበት ወቅት ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድንጋይ በመወርወር ሰልፉን አውካችኋል›› የተባሉ ሌሎች አምስት ወጣቶች ለሰኔ 4 የመከላከያ ምስክር እንዲያቀርቡ መቀጠራቸውን ጋዜጣው አክሎ ዘግቧል። አይ ኤስን ድርጊት ለማውገዝ የወጡ የአዲስ አበባ ወጣቶች በኢህአዴግ መንግስት ላይ ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ እንደነበር ይታወቃል። በኢትዮጵያ የመንግስትን ስም ማጥፋትና መንግስትን መሳደብ በህግ ያስጠይቃል።

Ethiopia: TPLF’s Deformed Democracy

June 2, 2015

TPLF’s Deformed Democracy: Competing with Themselves and Winning

by Alem Mamo
Ethiopian election 2015: EPRDF election campaign
“If you only have a hammer, you tend to see every problem as a nail.” — Abraham Maslow When you only have a gun in your tool box, you tend to see everyone and everything as a threat to your very existence. The May 24, 2015, “election” was a giant step backward for the development of electoral democracy in Ethiopia. The election drama concocted by the TPLF is nothing more than a fraudulent and futile exercise to legitimize the illegitimate. It was an endeavor marred by gross violations of citizens’ rights and doesn’t even stand the scrutiny of bare minimum benchmark of electoral process. By its very nature, the TPLF stands in stark contradiction with the basic tenants of democracy, which include freedom of assembly, freedom of expression, and respect for the rule of law. How can one expect the political space to be open and fair under such circumstances? Throughout its existence, the TPLF has broken all the sacred tenants of democracy and freedom. Exclusive, extremely violent, and relentlessly committed to dividing and polarizing the public, it has neither the aspiration nor the principled interest to foster democracy in Ethiopia.
The TPLF’s election drama is in the same league with North Korea’s “election” fiasco: one party rule, one candidate, an electoral body created and run by loyal party cadres. When one combines all of these elements, the result is a twisted and deformed version of democracy.
Naturally, authoritarian regimes are no friends of democracy. In fact, they loathe and fear it. Guaranteeing citizens the right to choose their government in a free and fair political competition is against their political agenda and vision. Most importantly, ethnic political parties, like the TPLF, see the emergence of inclusive democracy as an existential threat to the very agenda they promote, which is polarization and division. Their insular and exclusive political consciousness lacks both the intellectual and emotional knowledge to critically understand the nature of broad-based, inclusive democracy, let alone to implement it. In their deformed political world, they develop a narrative that only satisfies their own minimum understanding of freedom and democracy.
Electoral democracy in its actual form is rooted in a competition whereby all competing parties have a level playing field. They have unrestricted and equal access to inform the public about their platform and vision with no harassment or intimidation from anyone. Such transparent political space guarantees, ultimately, that it’s the electorate that decides who should govern. Under the TPLF’s “election”, however, this fundamental principle is non-existent. The TPLF, like many other guerrilla groups who came to power through the barrel of a gun, see their battlefield victory as a permanent and transferable asset that applies to every form of competition, be it political or economic. Admitting defeat in a peaceful and non-violent political competition is considered a denigrating loss to the distant past military victory. The only lens for accessing and evaluating all completion is a through the binary lens of military loss and defeat. It is for this primary reason (mind set) that the TPLF refused to accept the result of the 2005 election, when it was widely defeated. In the end, it declared a state of emergency and deployed a deadly force, killing hundreds and arresting tens of thousands of citizens.
This mindset is clearly demonstrated in the re-enactment of past military victory during the recent election campaign (as reported by Ethiomedia). This enactment has multiple purposes and implicit and explicit messages. First, it is to communicate/remind the public that they are not willing to relinquish power through the electoral process. “Anyone who is thinking otherwise must think again.” Second, for the TPLF and the likes, there is no difference between military victory and electoral victory. The first reinforces the latter. Political psychoanalysts call it “time collapse”: the idea of reactivating and projecting past events into the present such as battlefield or war. In these circumstances the primary objective is not necessarily for the purpose of memorializing or remembrance. Instead the underlying motivation is to blur the time line between the present and the past and to reinstate the past anger and hate against some groups. The other reason for reactivating the past is to play the role of ‘victim’ and ‘hero’ characters. In the reactivation both the ‘victim’ and the hero appear simultaneously. Each side however is exploited for different purposes, the ‘victim’ is played to garner sympathy and support while the ‘hero’ is played to project strength and power. The third objective is to hypnotize the public through the blurred lens of the past and the present so that their woe’s and injustice suffered under TPLF appear in the past.
To embrace electoral democracy, a significant shift in consciousness is required. First and foremost the ability and willingness to play by the rules is a prerequisite. One cannot be a neighborhood bully and embrace a free and fair electoral completion. Accepting a defeat in a peaceful and non-violent arena is the highest form of political maturity and growth. At this stage TPLF doesn’t have either of those qualities. TPLF has grown vertically and horizontally, but it spectacularly failed to grow-up.
The writer can be reached at: alem6711@gmail.com

Monday, June 1, 2015

ከአርበኞች ግንቦት7 ጋር አብራችሁዋል በሚል የተያዙት ክስ ተመሰረተባቸው

June 1,2015
ኢሳት ዜና :-በሰሜን ጎንደር ዞን ማክሰኝት ከተማ ነዋሪ መሆናቸው የተነገረው አቶ ዘመነ ምህረቱ እና ሌሎች የመከላከያ ሰራዊት አባላት የሽብርተኝነት ክስ እንደተመሰረታባቸው ሪፖርተር ዘግቧል። አቶ ዘመነ የመኢአድ ምክትል ፕሬዚዳንት መሆናቸው በክሱ የተመለከተ መሆኑን የዘገበው ጋዜጣው፣ መስከረም 18፣ 2007 ዓም በጎንደር በሚገኘው የመኢአድ ጽ/ቤት ውስጥ አባላትን በመሰብሰብ ” የወያኔ መንግስት መውደቂያው ደርሷል። አንድ የቶር አውሮፕላን፣ 12 የጦር ጄኔራሎች ከድተው ወደ ኤርትራ ገብተዋል። ኢህአዴግ በጦር ካልሆነ በሰላማዊ መንገድ ስልጣን አይለቅም። የህዝብ እምቢተኝነት በመፍጠር የወያኔን መንግስት መጣል አለብን፣ በ2007 ዓ.ም. የሚካሄደው አገራዊ ምርጫ በሰላማዊ መንገድ አይካሄድም፡፡ ወደ ምርጫው አንገባም፡፡ ሌላ አማራጭ መጠቀም አለብን…›› ” የሚል ክስ እንደተሰመረተባቸው ጋዜጣው ዘግቧል።

በዚሁ መዝገብ በአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑት አቶ ጌትነት ደርሶ ተመሳሳይ ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን፣ ወደ ኤርትራ ተሻግረው ከግንቦት7 ከፍተኛ አመራር ከሆኑት ዶ/ር ክፈተው አሰፋ ጋር በመገናኘት ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጠና ወስደዋል ተብሎአል። በዚሁ መዝገብ ተከሰው የቀረቡት ሌላው የአዲስ አበባ ነዋሪ አቶ መለሰ መንገሻ ሲሆኑ ፣ እርሳቸውም የአርበኞች ግንባር አባል ነበሩ ተብሎአል። ተከሳሹ ሰው በመመልመል ስራ ላይ መሳተፉንና በመንግስት ባለስልጣናትላይ ጠቃት ለመፈጸም ሲያጠና ነበር የሚል ክስ እንደተመሰረተበት ጋዜጣው ዘግቧል። የአየር ኃይል ባልደረባ የሆነው ምክትል መቶ አለቃ አንተነህ ታደሰ ዘውዴ ተመሳሳይ ክስ ተመስርቶበታል።


መኮንንኑ ታኅሳስ 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ከደብረ ዘይት አየር ኃይል በመነሳት ወደ ኤርትራ ጉዞ እያደረጉ መንገድ ከሚያሳያቸው ሌላ ሰው ጋር ታኅሳስ 26 ቀን 2007 ዓ.ም. ወሮታ ከተማ ላይ መያዛቸው በክሱ ተመልክቷል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ዞን ቶንጎ ወረዳ ሻንቦላ ከተማ ሻንቦላ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ውስጥ ነዋሪ ናቸው የተባሉት ሼክ መሐመድ አብዱል ቃድር የሚባሉ ተጠርጣሪ የእስልምና ሃይማኖትን እንደ ሽፋን በመጠቀም፣ በኃይል እስላማዊ መንግሥት ለማቋቋም ሲንቀሳቀሱ ነበር በሚል ክስ ተመስርቶባቸዋል።


ከአርበኞች ግንቦት7 ጋር በተያያዘ የሚታሰሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና ወጣቶች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው። በቅርቡ 4 የአየር ሃይል ባልደረቦችና የእግረኛ ሰራዊት አባላት ተመሳሳይ ክስ ተመስርቶባቸዋል። የመኢኢድ፣ የሰማያዊ እና የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አንዳንድ አባላት በተመሳሳይ ወንጀል ተከሰው በማእከላዊና በቃሊቲ እስር ቤቶች ይገኛሉ።


ከአርበኞች ግንቦት 7 ዜና ሳንወጣ በኒዉዚላንድ ኦክላንድ ትላንት ለ አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የገንዘብ ማሰባሰብ በተደረገዉ ዝግጅት በተሳካ ዉጤት መጠናቀቁን አንዱአለም ሃይለማርያም ከኦክላንድ ዘግቧል። የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ የዉጭ ጉዳይ ዘርፍ ተጠሪ የሆኑት አቶ አበበ ቦጋለ በዝግጅቱ ላይ በመገኘት ድርጅቱ በአሁኑ ሰዓት የደረሰበትን እና በማከናወን ላይ ያለዉን ስራ አብራርተዋል።


አቶ አበበ የአርበኞች ግንቦት 7 በኤርትራ በኩል ስለሚያደርገዉ እንቅስቃሴና በተቃዋሚ ሃይሎች በኩል ከተቻለ ተዋሕዶ አለበለዚያም በጥምረት ለመስራት የሚያደርገዉን እንቅስቃሴ በሰፊዉ ገልፀዋል። በአሁኑ ጊዜ ሃላፊነት የጎደለዉ የሕዉሐት መራሹ መንግስት ምርጫዉን አስመልክቶ በሕዝብ ላይ እና በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ እየሰራ ያለዉን ቅጥ ያጣ ግፍ የዘረዘሩት አቶ አበበ፣ አሁን ጊዜዉ ብሶታችንን ብቻ የምናወራበት ባለመሆኑ በምንፈልገዉ መንገድ ሁሉ በመደራጀት አገር አድን ጥሪዉን ተቀብለን ለአገራችን ኢትዮጵያና ሕዝቧ ልንደርስላት ይገባል ብለዋል።
በዝግጅቱ ከ20 ሺ ያላነሰ ዶላር መሰባሰቡንም በዘገባው ተመልክቷል።

"ባለፈው ሰረቁ ነው ሚባለው ያሁኑ ግን ዘረፋ ነው" ዶ/ር መረራ

June1,2015
ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች  የምርጫ ውጤቱን አንቀበለውም አሉ
* “በየ5 ዓመቱ ምርጫ እያሉ ህዝብን ከማሰቃየት፣ እንደነ ሰሜን ኮርያ እና ቻይና የአንድ ፓርቲ አገዛዝ ነው ብሎ ማወጁ ይመረጣል”
* “ኢህአዴግ ያሸነፈው ወደ ዘረፋ ስለገባ ነው እንጂ ተቃዋሚ ስለተዳከመ አይደለም”
* ዋናዎቹ ተቃዋሚዎች የምርጫ ውጤቱን አንቀበለውም አሉ
* ምርጫ ቦርድ የተቃዋሚዎች ውንጀላ መሰረተቢስ ነው ብሏል
ባለፈው እሁድ በተከናወነው 5ኛው አገር አቀፍ ምርጫ የተወዳደሩ ዋና ዋናዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣የምርጫውን ፍትሃዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ ግድፈቶችና የህግ ጥሰቶች መፈጸማቸውን ጠቅሰው የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉ አስታወቁ፡፡ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በ442 የምርጫ ክልሎች ኢህአዴግ ሙሉ በሙሉ እንዳሸነፈ መግለጹን ተክትሎ  መድረክ፣ ሰማያዊ፣ ኢዴፓና መኢአድ የምርጫውን ውጤት አንቀበለውም ብለዋል፡፡
ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግን ተከትሎ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው እጩዎች ለውድድር ያቀረበው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ፣ምርጫውን አስመልክቶ ባለፈው ረቡዕ በሰጠው መግለጫ፤ የምርጫውን ፍትሃዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ ግድፈቶችና የህግ ጥሰቶች በመፈጸማቸው የምርጫውን ውጤት ሙሉ ለሙሉ እንደማይቀበለው ጠቁሟል፡፡
በቅስቀሳ ወቅት በአባላትና ደጋፊዎች ላይ ወከባ መፈፀሙንና በምርጫው ዕለት ታዛቢዎች ከምርጫ ጣቢያዎች መባረራቸውን የጠቀሰው መድረክ፤ ጉድለቶቹንና ግድፈቶቹን ዘርዝሮ ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ማመልከቱንና ምላሹን እየተጠባበቀ እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡
ባለፈው ረቡዕ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ 442 የምርጫ ክልሎችን ውጤት ያስታወቀ ሲሆን ኢህአዴግ ሁሉም ላይ ማሸነፉን ጠቁሞ፣ የተቃዋሚዎች ውንጀላ ሙሉ በሙሉ መሰረተ-ቢስ አሉባልታ ነው ሲል አጣጥሎታል፡፡
የመድረክ ምክትል ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በበኩላቸው፤ “የዘንድሮ ምርጫ ውጤት ከ2002 ምርጫ የባሰ የሃገሪቱን ዲሞክራሲ ያጨለመ ነው” ብለዋል፡፡ “ባለፈው ምርጫ ቢያንስ ሰረቁ ነው የሚባለው፤ አሁን ግን ዘረፋ ነው ያካሄዱት” ያሉት ዶ/ር መረራ፤ ኢህአዴጐች በሪከርድነት የያዙትን 99.6 በመቶ ውጤት ወደ መቶ ለማሳደግ አስበው ያደረጉት ይመስለኛል ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ “ኢህአዴግ ያሸነፈው ወደ ዘረፋ ስለገባ ነው እንጂ ተቃዋሚ ስለተዳከመ አይደለም” ያሉት የመድረክ አመራር፤ “ምርጫ በዚህ ሀገር ላይ በትክክል የማይካሄድ ከሆነ በየ5 ዓመቱ ምርጫ እያሉ ህዝብን ከማሰቃየት፣ እንደነ ሰሜን ኮርያ እና ቻይና የአንድ ፓርቲ አገዛዝ ነው ብሎ ማወጁ ይመረጣል” ብለዋል፡፡ ገዢው ፓርቲ የምርጫ ውጤቱን ተመልክቶ “ስልጣን ወይም ሞት” የሚለውን አመለካከቱን መፈተሽ እንደሚገባው ጠቁመውም መንገዱ ብዙ ርቀት አያስኬድም ብለዋል፡፡ “ኢህአዴጎች በዚህ አካሄዳቸው ከቀጠሉ ማንንም የማትጠቅም ኢትዮጵያን ትተው እንዳይሄዱ ደግመው ደጋግመው ማሰብ አለባቸው” ሲሉ አሳስበዋል – ዶ/ር መረራ፡፡ “ህዝቡ ሰላማዊና ህጋዊ ትግሉን መቀጠል አለበት” ያሉት የፓርቲው አመራር፤ “ምርጫው ተጭበረበረ ብለን እጃችንን አጣጥፈን አንተኛም፤ ህዝቡ ከኛ ጋር ስለሆነ ትግላችንን እንቀጥላለን” ብለዋል፡፡
በምርጫው ከኢህአዴግ ቀጥሎ የተሻለ ድምፅ ያገኘው ሠማያዊ ፓርቲ ትናንት በሰጠው መግለጫ፤ ምርጫው ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ከተካሄዱት ምርጫዎች ጋር እንኳ ሊወዳደር የማይችል እጅግ ኢ-ፍትሃዊ፣ ወገንተኛና ተአማኒነት የሌለው በመሆኑ የምርጫውን ሂደትም ሆነ ውጤት አልቀበለውም ብሏል፡፡
“ነፃነት በሌለባት ኢትዮጵያ ህዝባዊ አስተዳደር መትከል ዘበት ነው” ያለው ፓርቲው፤ “በኃይል በተቀማ ድምፅ የሚመሰረት መንግስትም በህዝብ ተቀባይነት የለውም” ብሏል፡፡ በኢትዮጵያ የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች እስከሚከበሩ ድረስ የነፃነት ትግሉ በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥልም ሰማያዊ  አስታውቋል፡፡
በዘንድሮ ምርጫ የተሳተፈው ምርጫውን ሊያስፈፅሙ የሚችሉ ገለልተኛና ብቃት ያላቸው ተቋማት እንደሌሉ እያስገነዘበ መሆኑን የጠቆመው ፓርቲው፤ በምርጫው ምክንያት የተቃዋሚ ተወዳዳሪዎች፣ ታዛቢዎችና አባላት በገዥው ፓርቲ ካድሬዎች አፈናና እንግልት ደርሶባቸዋል ብሏል፡፡ “በህገ ወጥ አሰራሮች ታጅቦ የተከናወነ” ሲል የገለጸው የዘንድሮ ምርጫ፤ በምንም መመዘኛ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተአማኒ ሂደት ያልታየበት በመሆኑ ሂደቱንም ውጤቱንም አልቀበለውም ብሏል ሰማያዊ ፓርቲ፡፡
ከኢህአዴግና መድረክ ቀጥሎ በርካታ እጩዎችን ለምርጫው ያቀረበው የኢትዮጵያውያን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጫኔ ከበደ በበኩላቸው፤ በቅድመ ምርጫው ወቅት ኢዴፓ በሚዲያ የሚያስተላልፋቸው መልእክቶች ሳንሱር እየተደረጉበት መሆኑን በተደጋጋሚ መግለጻቸውን አስታውሰው፣ በምርጫው ላይ ችግር መታየት የጀመረው በሂደቱ ላይ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ በሂደቱ ወከባዎች በዝተውብን ነበር ያሉት ዶ/ር ጫኔ፤ በነዚህ ችግሮች ውስጥ ሆኖ ፓርቲያቸው በሂደቱ መሳተፍ መቀጠሉን ጠቁመው ሂደቱ ከህግ አፈፃፀም አንፃር ዲሞክራሲያዊ ነበር ማለት አይቻልም ብለዋል፡፡
የኢህአዴግ ፅ/ቤት የህዝብና ኮሚኒኬሽን ኃላፊው አቶ ደስታ ተስፋሁ በሰጡት አስተያየት፤ “ሂደቱ ጥሩ ነው ብለው ወደ ምርጫው ከገቡ በኋላ ውጤት አይቶ ሂደቱ ትክክል አልነበረም ማለት ተቀባይነት የለውም” ሲሉ የኢዴፓን ሃሳብ ተቃውመዋል፡፡ አንዳንድ ፓርቲዎች በሂደቱ አምነው ከገቡ በኋላ ህዝብ እንዳልመረጣቸው ሲያውቁ ምርጫው ተቀባይነት የለውም ማለታቸው እኛ ካላሸነፍን ከሚል አባዜ የሚመነጭ ነው ያሉት  አቶ ደስታ፤ በምርጫው ህዝቡ መብቱን በትክክል ተግባራዊ ስለማድረጉ የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች ታዛቢዎች ያረጋገጡት በመሆኑ የምርጫውን ውጤት አልቀበልም ማለት ለህዝቡ ውሳኔ ያለመገዛት ፀረ ዲሞክራሲያዊ አካሄድ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡ “ፓርቲዎች ህዝብ ለምን አልመረጠኝም ብለው ራሳቸውን መገምገም እንጂ ድክመታቸውን ወደ ሌላ አቅጣጫ ማዞር የለባቸውም” ብለዋል አቶ ደስታ፡፡
ከምርጫው በፊት የገዢው ፓርቲ አባላት ህግ በመጣስ ብዙ አፈናዎችና ወከባዎች ሲፈጽሙ ነበር ያሉት የኢዴፓ ፕሬዚዳንት፤ በምርጫው እለት የፓርቲያቸው ታዛቢዎች ከምርጫ ጣቢያዎች መባረራቸውን ጠቁመው፣ “ታዛቢዎች በሌሉበት የተካሄደው ምርጫ ተአማኒ ነው ብለን አናምንም” ብለዋል፡፡ “ምርጫው ሚስጢራዊ በሆነ ሁኔታ አይደለም የተከናወነው” የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፤ “መራጮች እየተገደዱ ሲመርጡ ታዝበናል፣ አሁንም ድረስ ታዛቢዎቻችን ለምን የተቃዋሚ ፓርቲ ታዛቢ ሆናችሁ በሚል እየተዋከቡብን ነው” ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል፡፡
ቅድመ ምርጫውም ሆነ የምርጫው እለት እንዲሁም ውጤት አገላለፁ የምርጫ ደንቦችንና ህጎችን ሙሉ በሙሉ የጣሰ ነው ያሉት ዶ/ር ጫኔ፤ ምርጫ ቦርድ ከአደረጃጀት አኳያ ራሱን ሊፈትሽ የሚያስገድደው ሂደት ተስተውሏል ብለዋል፡፡ የምርጫ ውጤቱ አገላለፅ ህዝቡ ትክክለኛ መረጃ እንዳያገኝ የሚያደርግ መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ ውጤቱን ሙሉ ለሙሉ ለምን መግለፅ እንዳልተቻለ ጠይቀዋል፡፡
“መንግስት ለመመስረት የሚያስችል ድምፅ ለማግኘት አስቸጋሪ የነበረ ቢሆንም የተወሰነ ወንበር በፓርላማ እንደምናገኘን  ጠብቀን ነበር፤ነገር ግን ምርጫው አሳታፊ ባለመሆኑ አልተሳካም” ብለዋል፡፡ ፓርቲያቸው የሚጠብቀው ዓይነት ምርጫ እንዳልተደረገ ጠቁመውም አሳታፊ ባልሆነ ሂደት ሰላማዊ ትግሉን የትም ማድረስ እንደማይቻል ገልፀዋል፡፡
ኢዴፓ ስትራቴጂውን እንደገና በመቀየር ለተሻለ ትግል እንደሚዘጋጅ በመጠቆምም ተመሳሳይ ርዕዮተ ዓለም ከሚከተሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር ግንባር ፈጥሮ ለመንቀሳቀስ ማቀዱን ተናግረዋል፡፡ ነገር ግን አሁንም ቢሆን ፓርቲው በምክንያታዊነት መንቀሳቀሱን ይቀጥላል ብለዋል፡፡
ፓርቲያቸው ከገዢው ፓርቲ ጋር ከፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት ባለፈ በተለየ ሁኔታ መነጋገር እንደሚፈልግም ዶ/ር ጫኔ አስታውቀዋል፡፡ ሌላው የምርጫ ተፎካካሪ የመላ ኢትዮጵያውያን አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሃሪ እንዲሁ፤ የምርጫውን ውጤት ለመቀበል እንደሚቸገሩ ተናግረዋል፡፡ “የተሰራው ስራ ለሀገር የሚበጅ አይመስለኝም” ያሉት ፕሬዚዳንቱ፤ “ምርጫው ትክክለኛ አይደለም፤ አንቀበልም” ብለዋል፡፡ በሃገሪቱ ትክክለኛ ዲሞክራሲ ለማምጣት ጥረት የሚያደርጉ አካላትን ተስፋ የሚያስቆርጥ የምርጫ ውጤት መሆኑን የጠቆሙት አቶ አበባው፤ በሰላማዊ ትግል ለውጥ ማምጣት የማይቻል ከሆነ የፓርቲዎች መኖር ጥቅም የለውም ብለዋል፡፡ ምርጫ የህዝብ ፍላጎት በትክክል የማይገለፅበት ከሆነ የትግሉ ጉዳይ አጠያያቂ ይሆናል ሲሉም አቶ አበባው አክለዋል፡፡
የምርጫ ውጤቱን ረቡዕ ማታ መስማታቸውን የተናገሩት የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፕሬዚዳንት አቶ ትዕግስቱ አወሉ፤ ስለ ምርጫው መረጃዎች እያሰባሰቡ እንደሆነና አቋማቸውን ለመግለጽ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ መወያየት ስላለበት ምላሽ ለመስጠት እንደማይችሉ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ግንባር (ኢፌድሃግ) በበኩሉ፤ ህዝብ ለመረጠው አካል እውቅና እንደሚሰጥ ጠቁሞ፣ ለቀጣይ ምርጫ  ድክመትና ጥንካሬውን ገምግሞ ዝግጅት እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፈው ረቡዕ 442 የምርጫ ክልሎችን ውጤት ይፋ ያደረገ ሲሆን በሁሉም ክልሎች ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግና አጋሮቹ ማሸነፋቸውን ገልጧል፡፡
ምርጫው በታሰበለት የጊዜ ሰሌዳ ያለምንም ችግር አሳታፊ፣ ፉክክር የታየበትና ዲሞክራሲያዊ ሆኖ ተጠናቋል ያሉት የቦርዱ አመራሮች፤ ከምርጫው ጋር የተገናኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ቅሬታዎችን መሰረተቢስ ናቸው በማለት ውድቅ አድርገዋቸዋል፡፡ “በምርጫው እለት ታዛቢዎችን ተባረውብናል፣ ኮሮጆዎች ሳይፈተሹ ድምፅ ተሰጥቷል፣ ኮሮጆዎች ተቀይረዋል፣ ምርጫው ተጭበርብሯል – የሚሉት መሰረተ ቢስ አሉባልታ ነው” ብለዋል – አመራሮቹ፡፡ 

Saturday, May 30, 2015

Ethiopia opposition says elections an ‘undemocratic disgrace’

May 29, 2015
Ethiopia opposition says elections an 'undemocratic disgrace'
(AFP) Ethiopia’s main opposition party on Friday condemned weekend elections, which saw the ruling party cruise back into office, as a “disgrace” and proof the country was a one-party state.
According to preliminary results from last Sunday’s elections, the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) of Prime Minister Hailemariam Desalegn secured all 442 parliamentary seats so far declared out of the 547 seats up for grabs.
The EPRDF, in power in Africa’s second-most populous nation for over two decades, were widely expected to secure a near clean sweep of parliament, and the outgoing chamber had just one opposition MP — but even this was taken by the ruling party.
“The Blue Party does not accept the process as free and fair and does not accept the outcome of unhealthy and undemocratic elections,” the main opposition party said.
“This 100 percent win by the regime is a message of disgrace” and shows that a “multi-party system is over in Ethiopia”.
Ahead of Sunday’s polls the opposition alleged the government had used authoritarian tactics to guarantee victory — such as intimidation, refusing to register candidates or arresting supporters.
The Blue Party’s spokesman, Yonatan Tesfaye, alleged that 200 party candidates were denied the right to stand for parliament and 52 party members were arrested in the run-up to the polls.
“We don’t think there is an independent justice system to deal with our complaints. We’ll continue our peaceful struggle,” he told reporters.
After the elections, the United States, which enjoys close security cooperation with Ethiopia, also said it remained “deeply concerned by continued restrictions on civil society, media, opposition parties, and independent voices and views.”
The European Union also said true democracy had yet to take root in Ethiopia, and voiced concern over “arrests of journalists and opposition politicians, closure of a number of media outlets and obstacles faced by the opposition in conducting its campaign.”
The African Union observer mission, however, described the polling as “credible” and “generally consistent with the AU guidelines on the conduct of elections in Africa.”
On Wednesday government spokesman Shimeles Kemal said the win came as the result of Ethiopia’s economic advances.
“Voters have credited the ruling party for the economic progress it introduced in the country,” he told AFP. “In view of the weak, fragmented opposition and the lack of a viable alternative, it was very likely that the ruling party would win in a landslide.”

Wednesday, May 27, 2015

ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙር!- የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

May 27, 2015
def-thumbግንቦት 18 2007 ዓ.ም
ምርጫ 2007 ተጠናቆ ተወዳዳሪም አወዳዳሪም የሆነው ህወሓት ይፋ ውጤት እስኪገልጽ እየተጠበቀ ነው። ሁሉ በእጁ ነውና ባለሥልጣኖቹ ምን ዓይነት ውጤት እንደሚስማማቸው እስከሚነግሩን ጥቂት ቀናት ይወስዱ ይሆናል። ከፈለጉ ሁሉን የፓርላማ ወንበሮች ሊወስዷቸው ይችላሉ፤ ካሻቸው ደግሞ ጥቂቱን ለተቃዋሚዎች ሊሰጡ ይችላሉ። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። በዚህ የፓርላማ ወንበሮች እደላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ አንዳችንም ሚና የለውም።
ምርጫ የሕዝብ የሥልጣን ባላቤትነት ማረጋገጫ ከሆኑ አቢይ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት አንዱ መሆኑ የታወቀ ነው። ሆኖም ግን ነፃ ተቋማት በሌሉበት፤ በአምባገነኖች አስፈፃሚነት የሚደረግ ምርጫ የመራጮች ነፃ ፍላጎት መግለጫ በመሆን ፋንታ የገዢዎች ሥልጣን ማረጋገጫ መሣሪያ ይሆናል፤ ከአገራችን እየሆነ ያለውም ይህ ነው።
የዘንድሮው ምርጫ 2007 ከዚህ በፊት ከነበሩ በባሰ ለአፈና የተጋለጠ የነበረ መሆኑ ከጅምሩ በግልጽ የታየ ጉዳይ ነበር። በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲዎች ላይ አገዛዙ የወሰደው የግፍ እርምጃ የዚሁ የምርጫ ዘረፋ ስትራቴጂ አካል ነበር። ከዚያ በተጨማሪም መራጮች እውነተኛ ፍላጎታቸውን በነፃነት መግለጽ እንይችሉ ዘርፈ ብዙ ጫናዎች ሲደረግባቸው ቆይቷል። የተወዳዳሪ ፓርቲዎች አባላት እንደተፎካካሪ ሳይሆን እንደጠላት ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡና ሲገደሉ ሰንብቷል። በምርጫው ሰሞንና በዕለቱ በተለይ ከተሞች በባዕድ ጦር የተወረሩ መስለው ነበር። ይህ ሁሉ ስነልቦናዊና አካላዊ ተጽዕኖ ታልፎ የተሰጠው ድምጽ ቆጣሪው ራሱ “ተወዳዳሪ ነኝ” ባዩ ህወሓት ነው።
በእንዲህ ዓይነት ምርጫ መሳተፍ ትርፉ “በሕዝብ ድምጽ ተመረጥኩ የማለትን እድል ለአምባገኑ ህወሓት መስጠት ነው”፤ “ለዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብም የተምታታ መልዕክት ማስተላለፍ ነው”፤ ”ለህወሓት ተጨማሪ ገንዘብ ማግኛና የኢትዮጵያን ሕዝብ መከራ ማራዘሚያ ነው“ በሚል በዚህ ምርጫ ላይ ማዕቀብ እንዲደረግ አርበኞች ግንቦት 7 ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። በርካታ ወገኖቻችን የምርጫ ካርድ ቢያወጡም የደረሰባቸውን ጫና ተቋቁመው በምርጫው ባለመሳተፍ ላሳዩት ጽናት አርበኞች ግንቦት 7 አድናቆቱን ይገልፃል።
ህወሓት በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ የምርጫ ጉዳይ እና የምርጫ ፓለቲካ ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የተጠናቀቀ ቢሆንም እንኳን ተጨማሪ ማስረጃ ለሚፈልጉ ግንቦት 16 ቀን 2007 መጥቶላቸዋል። አሁን ከፊታችን የተደቀነው ጥያቄ የሚከተለው ነው – አገራችን ከህወሓት አፈና ነፃ ለማውጣት ያለን አማራጭ መንገድ ምንድነው?
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ህወሓት ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ የሚወርደው ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽን ባቀናጀ ሁሉገብ ትግል ነው ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ለሁለቱም የትግል ዘርፎች ተስማሚ የሆኑ አደረጃጀቶችን አዘጋጅቷል።
ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ታጋዩ ከመኖርያ ወይም ከሥራ ቦታው ሳይለቅ በህቡዕ የሚከናወን ትግል ነው። ሕዝባዊ አመጽ ደግሞ ከመኖሪያና ሥራ ቦታ ለቆ መንቀሳቀስን ይጠይቃል። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች የህወሓትን ህጎች በመቃወም የሚደረጉ ናቸው። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች ድርጅት፣ ዲሲሊንና ጽናትን ይጠይቃሉ። ለድላችን ሁለቱም የትግል ዘርፎች እኩል ዋጋ አላቸው። እናም ከዛሬ ጀምሮ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደዝንባለውና አቅሙ በሚመቸው የትግል ዘርፍ ይሳተፍ። ሕዝባዊ ኃይልን መቀላቀል የቻለ ይቀላቀል፤ ያልቻለው በያለበት ተደራጅቶ በሕዝባዊ እምቢተኝነት ይታገል።
በየመኖሪያ ሠፈሩና በሥራ ቦታዎች የሚቋቋሙ የአርበኞች ግንቦት 7 ማኅበራት በርካታ ሥራዎች አሏቸው። ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅትን ማጠናከር የሁላችንም ድርሻ መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም፤ እናም ትኩረታችን እዚያ ላይ እናድርግ። እያንዳንዳችን ከሚመስሉንና ከምናምናቸው ጋር ተነጋግረን እንደራጅ፤ ወያኔ የሸረሸረብንን በራስ መተማመን እና የእርስ በርስ መተማመንን መልሰን እንገንባ። ውስጥ ውስጡን ጠንካራ አገራዊ ኅብረት እንፍጠር፤ የዕለት ተዕለት ተግባሮቻችን ደግሞ አካባቢያዊ ይሁኑ። ድርጅታችንን እያጠናከርን ወያኔን ከሁሉም አቅጣጫ እንሸርሽረው እንገዝግዘው። በዚህ መንገድ በሚደረግ ሕዝባዊ ትግል የሚገኝ ድል ፈጣን ከመሆኑን በላይ የድሉ ሕዝባዊነት ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ይሆናል።
ስለሆነም እያንዳንዱ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ታጥቆ እንዲነሳ፤ ወደ ተግባራዊ ትግል ፊቱን እንዲያዞር አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

Monday, May 25, 2015

Ethiopia: Onslaught on human rights ahead of elections – Amnesty

May 24, 2015
amnesty-internationalThe run-up to Ethiopia’s elections on Sunday has been marred by gross, systematic and wide-spread violations of ordinary Ethiopians’ human rights, says Amnesty International.
“The lead-up up to the elections has seen an onslaught on the rights to freedom of expression, association and assembly. This onslaught undermines the right to participation in public affairs freely and without fear as the government has clamped down on all forms of legitimate dissent,” said Muthoni Wanyeki, Amnesty International’s Regional Director for East Africa, the Horn and the Great Lakes.
The Ethiopian authorities have jailed large numbers of members of legally registered opposition political parties, journalists, bloggers and protesters. They have also used a combination of harassment and repressive legislation to repress independent media and civil society.
The lead-up up to the elections has seen an onslaught on the rights to freedom of expression, association and assembly. This onslaught undermines the right to participation in public affairs freely and without fear as the government has clamped down on all forms of legitimate dissent. Muthoni Wanyeki, Amnesty International’s Regional Director for East Africa, the Horn and the Great Lakes.
In the run-up to Sunday’s elections, opposition political party members report increased restrictions on their activities. The Semayawi (Blue) Party informed Amnesty International that more than half of their candidates had their registration cancelled by the National Electoral Board. Out of 400 candidates registered for the House of Peoples Representatives, only 139 will be able to stand in the elections.
On 19 May, Bekele Gerba and other members of the Oromo Federalist Congress (OFC)-Medrek were campaigning in Oromia Region when police and local security officers beat, arrested and detained them for a couple of hours.
On 12 May, security officers arrested two campaigners and three supporters of the Blue Party who were putting up campaign posters in the capital Addis Ababa. They were released on bail after four days in detention.
In March, three armed security officers in Tigray Region severely beat Koshi Hiluf Kahisay, a member of the Ethiopian Federal Democratic Unity Forum (EFDUD) Arena-Medrek. Koshi Hiluf Kahisay had previously received several verbal warnings from security officials to leave the party or face the consequences.
In January, the police violently dispersed peaceful protesters in Addis Ababa during an event organized by the Unity for Democracy and Justice Party (UDJ). Police beat demonstrators with batons, sticks and iron rods on the head, face, hands and legs, seriously injuring more than 20 of them.
At least 17 journalists, including Eskinder Nega, Reeyot Alemu and Wubishet Taye, have been arrested and charged under the Anti-Terrorism Proclamation (ATP), and sentenced to between three and 18 years in prison. Many journalists have fled to neighboring countries because they are afraid of intimidation, harassment and attracting politically motivated criminal charges.
Civil society’s ability to participate in election observation has been restricted under the Charities and Societies Proclamation (CSP) to only Ethiopian mass based organizations aligned with the ruling political party.
Amnesty International calls on the Africa Union Election Observation Mission (AU EOM) currently in Ethiopia to assess and speak to the broader human rights context around the elections in both their public and private reporting. It also calls on the AU EOM to provide concrete recommendations to address the gross, systematic and widespread nature of violations of the rights to freedom of expression, association and assembly which have undermined the right to participate in public affairs freely and without fear.
“The African Union’s election observers have a responsibility to pay attention to human rights violations specific to the elections as well as more broadly,” said Wanyeki. “The African Charter on Human and Peoples’ Rights protects the right of Ethiopians to freely participate in their government. This right has been seriously undermined by violations of other civil and political rights in the lead-up to the elections.”

Background
Amnesty International has been monitoring, documenting and reporting on the human rights situation in Ethiopia for more than four decades.
Since the country’s last elections in 2010, the organization has documented arbitrary and politically motivated arrests and detentions, torture and other ill-treatment, as well as gross, systematic and wide-spread violations of the rights to freedom of expression and association.
source: www.amnesty.org

Saturday, May 23, 2015

ኢህአዴግ ሆይ ነቄ ነን ተቀየስ! (ርዕዮት አለሙ – ከቃልቲ እስርቤት)

May 23, 2015
ርዕዮት አለሙ – ከቃሊቲ እስርቤት
አራት ሆነን ወደምንኖርበት የአሁኑ የማግለያ ክፍል ከመግባቴ በፊት በርካታ እስረኞች በተለምዶ የአራድኛ ቃላት የሚባሉትን በመጠቀም ሲነጋገሩ የመስማት እድል ነበረኝ፡፡ ለርዕሴ የመረጥኳቸው ቃላትንም ያገኘሁት ከነሱው መሆኑን መግለፅ ይኖርብኛል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፤Reeyot Alemu, the 31 year-2012 Courage in Journalism Award winner.
አንዳንድ እስረኞች የሚፈልጉትን አንዳች ነገር ለማግኘት በጉልበታቸው ወይም ጤፍ በሚቆላ ምላሳቸው ይጠቀማሉ፡፡ ሀይልን በመጠቀም ያስገድዳሉ ወይም ያታልላሉ ማለት ነው፡፡ እንዲህ አይነቶቹ እስረኞች እንደለመዱት ለማድረግ ሲሞክሩ አንዳንዴ ደፋርና የማይታለሉ እስረኞች ላይ ይወድቃሉ፡፡ እናም ለማታለል ወይ ለማስገደድ የሞከረች ባለጌ የሚጠብቃት መልስ “ነቄ ነን እባክሽ! ተቀየሽ! ንኪው!”የሚል ይሆናል፡፡ እኛን ማታለልም ሆነ ማስፈራራት ስለማትችይ ይቅርብሽ፡፡ ዞርበይልን እንደማለት ነው፡፡
ኢህአዴግም እያደረጋቸው ያለው የማታለል ሙከራዎችና ተገቢ ያልሆኑ የሀይል እርምጃዎች ተመሳሳይ ምላሽ ሊያሰጡት እንደሚገባ አምናለሁ፡፡ የዘንድሮውን ምርጫ ለማለፍ ከወትሮው በከፋ ሁኔታ እየሄደባቸው ያሉት እነዚህ ሁለት ጠማማ መንገዶች መጨረሻቸው አውዳሚ ነው፡፡ በመሆኑም “ኢህአዴግ ሆይ ነቄ ነን ተቀየስ!” በማለት እኛና ሀገራችንን ይዞ ወደጥፋት እያደረገ ያለውን ግስጋሴ መግታት ይገባል፡፡
ጠማማ መንገድ አንድ

የፈሪ ዱላውን የመዘዘው ኢህአዴግ

ኢህአዴግ የተቃዉሞ ድምፆችን በሰማበት አቅጣጫ ሁሉ ዱላውን ይዞ የሚሮጥና ያለሀሳብ የፈሪ ምቱን የሚያሳርፍ ደንባራ መሆኑን በተደጋጋሚ በተግባር አይተናል፡፡ በሰሜን አፍሪካ አመፅ ተቀሰቀሰ ሲባል ለአመፅ ምክንያት የሚሆኑ ድክመቶቹንና ጥፋቶቹን ከማስወገድ ይልቅ ነቅተው ሊያነቁብኝ ይችላሉ ብሎ የጠረጠረንን ጋዜጠኞችንና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን ለእስር መዳረጉ ከቅርብ ጊዜ ተዝታዎቻችን ውስጥ ይጠቀሳል፡፡ የሩቁን ብንተወው እንኳ ማለት ነው፡፡
በሀይማኖት ተቋማት ውስጥ እንኳ ሳይቀር ገብቶ ያለአግባብ ያሰራቸው የሙስሊም ሀይማኖት መሪዎችና አማኞች የማደናበሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ ካለፈው አመት ጀምሮ የምርጫውን ዝግጅት ማድረግ የጀመረው እንደለመደው ከሱ የተለየ ሀሳብ የሚያንፀባርቁ ጋዜጦችንና መፅሔቶችን በመዝጋትና፣ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን በማሰርና በመደብደብ ነበር፡፡ በምሳሌነት የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንና የሶስቱን ጋዜጠኞች ጉዳይ ማንሳት ይቻላል፡፡
ዘንድሮ ደግሞ ኢህአዴግን በድፍረት በመሄስ የሚታወቀውን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ ምርጫ ቦርድን በመጠቀም ያለአግባብ ከፓርቲያቸው እንዲገለሉ ያደረጋቸውን የአንድነት ፓርቲ አባላትን በግፍ ማሰሩን ተያይዞታል፡፡ በተመሰረቱ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለኢህአዴግ ፈተና የሆኑበት ደፋሮቹ የሰማያዊ ወጣቶችም የኢህአዴግ ሰለባ እየሆኑ ነው፡፡ የየትኛውም ፓርቲ አባላት ያልሆኑና ቅሬታቸውን በተለያዩ መድረኮች ያሰሙ በርካታ ግለሰቦችም ተመሳሳይ እጣ ገጥሟቸዋል፡፡
ኢህአዴግ ይሄን ሁሉ የፈሪ ዱላውን እያዘነበ የሚገኘው በሚወስዳቸው እርምጃዎች ከተቃዉሞ ድምፆችና እንቅስቃሴ የሚገላገል እየመሰለው ነው፡፡ እንደተሳሳተ ማን ቢነግረው ይሻል ይሆን? የራሱን ዜጎች ማክበር ስለማይሆንለት የአሜሪካ ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እንድትነግርልን ብናደርግ ሳይሻል አይቀርም፡፡ ለማንኛውም የሚኒስትሯን ጉዳይ ለጊዜው እንተወውና በሀገራችን ዴሞክራሲ ሰፍኖ ለማየት የቆረጥን እኛ ግን ከትግላችን ለሰከንድም ቢሆን እንደማናፈገፍግና በዚህም ምክንያት የሚደርስብንን ሁሉ ለመቀበል ፍቃደኞች እንደሆንን ልንነግረው ያስፈልጋል፡፡ “ኢህአዴግ ሆይ እየበዛኸው ያለኸው ግፍና በደል ይበልጥ ጠንካሮች ያደርገናል እንጂ አንተ እንደፈለከው አያንበረክከንም ነቄ ነን ተቀየስ” ልንለውና ጥንካሬያችንንም በተግባር ልናሳየው ይገባል ፡፡
ጠማማ መንገድ ሁለት

“አይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛቹ” ማለትን የሚወደው ኢህአዴግ

ኢህአዴግ እንደጠቀስኳቸው አይነቶችና ሌሎች የሀይል እርምጃዎችን በአብዛኛው የሚወስደው ሊያሞኛቸው እንደማይችል በተረዳው በነቁ ሰዎች ላይ ነው፡፡ እንዳልነቅ የገመታቸውን ደግሞ እንደጨለመባቸው እንዲቀሩ የሚያደርግ የሚመስለውን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ያዘጋጅላቸዋል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ታዲያ ይሄ ግምቱ ግቡን መምታቱ ይቀርና እንደሚያታልላቸው እርግጠኛ በሆነባቸው ዘንድ ሳይቀር መሳቂያ ሲያደርገው ይስተዋላል፡፡ ሌሎቹን ትቼ ለምርጫው ካዘጋጃቸው ማታለያዎቹ ውስጥ እጅግ በጣም ጥቂቶቹን ላንሳ፡፡

2.1 ተቃዋሚዎች አማራጭ የላቸውም፡፡

በተለይ በዘንድሮው ምርጫ ጆሮአችን እስኪያንገሸግሸው ድረስ ኢህአዴግ ሊግተን ከሞከራቸው ሀሳቦች ውስጥ “ተቃዋሚዎች አማራጭ የላቸውም” የሚለው ዋነኛው ነው፡፡ ገዢው ፓርቲ በእውነተኛና ጠንካራ ተቃዋሚዎች ላይ እየፈፀመ ያለውን ደባ የሚያውቅ ሁሉ ይሄ ሀሳብ በውስጡ በርካታ ሴራዎችን የያዘ መሆኑን ይረዳል፡፡ እንዴት ማለት ጥሩ! ኢህአዴግ ሰራኋቸው ብሎ የሚመፃደቅባቸውን ስራዎች በሙሉ ከነድክመቶቻቸውም ቢሆን መስራት የጀመረው ባለፉት አስርት አመታት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ዕድሜ ለ1997ዓ.ም የተቃዋሚዎች ድንቅ አማራጭና እንቅስቃሴ! ከዚያ በፊትማ ጥልቅ እንቅልፍ ውስጥ ነበር፡፡ በዚያ የምርጫ ወቅት ከተቃዋሚዎች ጋር ባደገረው ክርክሮች ባዶነቱ የታየበት ኢህአዴግ ራቁቱን ከመሸፈን ይልቅ ተቃዋሚዎችን መግፈፍ መፍትሔ አድርጎ ወሰደ፡፡ ያለፉትን አስር አመታት ሙሉ ጠንካራ አማራጭ ያላቸውንና በሀሳብ የተገዳደሩትን ፓርቲዎች በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ የማፍረስ፣መሪዎችን የማሰርና የማሳደድ እርምጃዉን ገፋበት፡፡ በዚህ ድርጊቱም በርካታ ጠንካራ ፖለቲከኞችን ከጫዋታ ዉጪ አደረጋቸው፡፡ ባደረሰባቸው ከባድ ኩርኩም ተቃዋሚዎችን ድንክ እንዳደረጋቸው እርግጠኝነት የተሰማው ገዢው ፓርቲ “ተቃዋሚዎች አማራጭ የላቸውም” ብሎ ለመፎከር በቃ፡፡ ድሮስ በራሱ የማይተማመን ሰው ሁሌም ትልቅ ለመምሰል የሚሞክረው ጠንካሮችን በማስወገድና በደካሞች ራሱን በመክበብ አይደል? የተቃዉሞው ሰፈር በየቀኑ ከኢህአዴግ በሚሰነዘርበት የሀይል ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት አያጠያይቅም፡፡ ሆኖም ዛሬም ቢሆን የኢህአዴግ ባለስልጣናት ጉንጫቸው እስኪቀላ ድረስ የሚገዳደሩና መልስ የሚያሳጡ ሰዎች አላጣንም፡፡ የሞኝ ለቅሶ መልሶ መላልሶ እንዲሉ ኢህአዴጎች ግን “ተቃዋሚዎች አማራጭ የላቸውም” የሚለዉን ነጠላ ዜማቸውን ለማቆም አልፈለጉም፡፡ ጠንካራ አማራጭ ያላቸውን ከጎዳናው ላይ በማስወገድ ብቸኛ ባለአማራጭ ሆነው ለመታየት በተግባር የሚያደርጉትን ሙከራ ማጀቢያ ሙዚቃ መሆኑ ነው፡፡ በመሆኑም “ኢህአዴጎች ሆይ ነቄ ነን ተቀነሱ!” ብለን ልናስቆማቸው ይገባል፡፡

2.2 በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ

ይሄ ምርጫ አልፎ ከመስማት ልገላገላቸው ከምፈልገው ሸፍጥ የተሞላባቸው የኢህአዴግ ፕሮፓጋንዳዎች አንዱ “የምርጫ ቅስቀሳውና ክርክሩ በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ ለማካሄድ እንደረዳቸው የእንትን ከተማ ነዋሪዎች ገለፁ” የሚለው ይገኝበታል፡፡ አስቀድሜ እንደገለፅኩት ገዢው ፓርቲ ተቃዋሚዎች አማራጭ እንደሌላቸው ደጋግሞ ነግሮናል፡፡ እንግዲህ በዚህ ስሌት መሰረት ከሄድን እየተፎካከሩ ያሉት ባለአማራጭ ኢህአዴግና አማራጭ የሌላቸው ተቃዋሚዎች ናቸው ማለት ነው፡፡ ከውድድሩ ሜዳ ላይ ሊገዳደሩት የሚችሉትን ሁሉ ለማስወገድ የሞከረው ኢህአዴግ በሱ ቤት ብቸኛና ምርጥ ቀስቃሽ የሆነ መስሎታል፡፡ “በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ” እያለ የሚያደረቁረንም ለዚህ ነው፡፡
አይ ኢህአዴግ! በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲካሄድ እንደማይፈልግ ተግባሩ እንደሚመሰከርበት እንኳ አይታየውም፡፡ አንድ ምሳሌ ልጥቀስ፡፡ በገዢው ፓርቲ የሚሽከረከሩ የሚዲያ ተቋማት የተቃዋሚ ፓርቲዎችን የምርጫ ቅስቀሳ ሳያስተናግዱ የቀሩባቸው ግዜያት ነበሩ፡፡ ህገመንግስቱ ገለልተኛ መሆናቸውን የገለፀውን ተቋማት ገለልተኝነት ጥያቄ ውስጥ ያስገባ ይዘት ያለው ቅስቀሳ ነው በሚል፡ አሳዛኝና አስቂኝ ምክንያት! እንደምርጫ ቦርድ፣ ፍርድቤትና የመሳሰሉት ያሉትን ገለልተኛ መሆን የሚገባቸውና በተግባር ግን ሆነው ያልተገኙ ተቋማትን መሞገት እንኳን የማይችል ተቃዋሚ መፈለግ ምን የሚሉት አምባገነንነት ነው? ሁሉም ነገር በአንድ በእርሱ የተበላሸ መስመር እንዲሄድ የሚፈልግና የተለዩ ሀሳቦችን ለማስተናገድ ያልፈቀደ ፓርቲ የሚያካሂደው ምን አይነት በዕውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንደሚሆን አይገባኝም፡፡
ፅድቁ ቀርቶ በወጉ በኮነነኝ እንዲሉ በመጀመሪያ ደረጃ ለውጥ የምንፈልግበት ምክንያት በዋናነት ያን ያህል ምሁራዊ ንድፈሀሳቦችን የሚጠይቅና የተወሳሰበም አይደለም፡፡ ኢህአዴግ ሆይ አይደለህም እንጂ ጎበዝ ተከራካሪ ብትሆን እንኳ እንደሰውና እንደዜጋ የመኖር መብታችንን የገፈፍክ አምባገነን ሆነህ ሳለ አፈጮሌ ስለሆንክ ብቻ እንድታስተዳድር የምንፈልግ ጅሎች መስለንህ ከሆነ ተሳስተሀል፡፡ ነቄ ነን አልንህ እኮ!

2.3 ከ “የህዝቡን ድምፅ መቀበል” እስከ “አስፈላጊው እርምጃ”

የምርጫውን መቅረብ ተከትሎ ኢህአዴግ እየነገረን ያለው ሌላው ጉዳይ የህዝቡን ድምፅ መቀበል እንደሚገባ ነው፡፡ ድምፄ ይከበርልኝ ብሎ አደባባይ የወጣን ህዝብ በመግደል ስልጣኑን በደም ያራዘመው ኢህአዴግ ይሄን ለማለት ምን የሞራል መሰረት አለው? ፈፅሞ ሊኖረው አይችልም፡፡ ነገሩ ወዲህ ነው፡፡ ኢህአዴግ አጭበርብሮም ሆነ በስልጣን ለመሰንበት ማንኛቸውንም ጉዳይ ፈፅሞ ካበቃ በኋላ በምርጫ ቦርድ “አሸናፊነቱ” ሲታወጅለት የህዝቡ ድምፅ እንደሆነ ተቆጥሮ እንዲወሰድለት ይፈልጋል፡፡ ስቴድየም “ድሉን” ምክንያት በማድረግ በሚያዘጋጀው ዝግጅት ላይም “መሾምና መሻር ለሚችለው የህዝቡ ሉአላዊ ስልጣን ” እጅ ለመንሳትም በእጅጉ ቋምጧል፡፡ የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትሪያችን እንደ ቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኮፍያቸውን አንስተውና ከወገባቸው ዝቅ ብለው ላልመረጣቸው ህዝብ “የእንኳን መረጥከን” ምስጋና ሲያቀርቡ እንደምናይ ለመገመት እደፍራለሁ፡፡ ይሄንን ድርጊት ለማሰናከል የሞከረ ሰው ደግሞ “አስፈላጊዉ እርምጃ” እንደሚወሰድበት አንዴ ኮሚሽነር፣ ሌላ ጊዜ ምክትል ኮሚሽነር ሲያሻው ደግሞ በርካታ ኮማንደሮችን ዋቢ እያደረገ ሰሞኑን ኢብኮ ሊያስጠነቅቀን ሞክሯል፡፡
ከፍተኛ መኮንኖቹም በቂ ትጥቅ እንዳሟሉና ከ2006ዓ.ም ጀምሮ ዝግጅት ሲያደርጉ እንደከረሙ በኩራት ሊነግሩን ሞክረዋል፡፡ ዝግጅታቸው ለእውነተኛ የሀገር ጠላትና አሸባሪ ቢሆን ኖሮ ኩራታቸው ኩራታችን ይሆን ነበር፡፡ ግን ዝግጅታቸው ለኢህአዴግ ተቀናቃኞች መሆኑን በሚገባ ስለምናውቅ ስሜታቸውን ልንጋራቸው አልቻልንም፡፡ ኢብኮ ከመኮንኖቹ ንግግር መሀል እያስገባ ሲያሳየን የነበረው የታጣቂና የትጥቅ ብዛትም የ “አርፋቹ ተቀመጡ” መልዕክትን ያዘለ ነው፡፡ በእኔ በኩል ለውጥ ያለፅናት ሊታሰብ እንደማይችልና ቦግ ድርግም በሚል አይነት ትግል ድል እንደማይገኝ ስለማምን ሁሌም በመስመሬ ላይ ነኝ፡፡ በትግሉ ውስጥ ያሉትን ሁሉ የምመክረውም ይሄንኑ ነው፡፡ ይሄ አቋማችን ህይወታችንን እስከመስጠት የሚያደርስ መስዕዋትነት ሊጠይቀን እንደሚችል አሳምሬ አውቃለሁ፡፡
ለሀገራችንና ለህዝቡ መልካም ለውጥ ለማምጣት እስከሆነ ድረስ ይሁን፡፡ ነገር ግን በትግሉ ውስጥ ያላችሁትን ሁሉ ትግሉን ወደፊት ሊያራምድ ከማይችልና ኢህአዴግን የበለጠ ስልጣን ላይ እንዲደላደል ከሚያደርግ አጉል መስዕዋትነት እንድትቆጠቡ አደራ እላለሁ፡፡ የምታደርጉት እንቅስቃሴ የተጠና፣ የለውጥ ሀይሎችን በሙሉ በአንድነት ያሰባሰበ፣ ቀጣይነት ያለውና በተቻለ መጠን አደጋን የሚቀንስ እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ ይሄንን በማድረግ ትግሉን ሊያስቆም ወይም ደግሞ የጅምላ እስርን ሊፈፅምና ሀገራችንን በደም አበላ ሊነክር የተዘጋጀውን ኢህአዴግ የትኛውም ፍላጎቱ ቢሆን እንዲሳካ ባለመፍቀድ “ነቄ ነን ተቀየስ! ” ልትሉት ይገባል፡፡

በመጨረሻም

ኢህአዴግን “ነቄ ነን ተቀየስ” ልንልባቸው የሚገቡንና ሌሎችንም እንዲነቁበት ማድረግ የሚገባን በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም ያለሁበት ሁኔታ ብዙ ለመፃፍም ሆነ እናንተጋ እንዲደርስ ለማድረግ ፈፅሞ አመቺ አይደለም፡፡ አሁን አሁንማ የምርጫውን መቃረብ አስመልክቶ የሚፈትሹኝ፣ የሚያጅቡኝ ሆነ ቤተሰብ የሚያገናኙኝ በሙሉ የህወሓት ሰዎች ብቻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ራሱን የብሔረሰቦች መብት አስከባሪ አድርጎ የሚያቀርበው ገዢው ፓርቲ ምነው እኔን ለመፈተሽና ለመጠበቅ እንኳ ሌሎቹን ብሔረሰቦች ማመን አቃተው?የፖለቲካ እስረኛ የሆኑ ወገኖችም ላይ ተመሳሳይ ሁኔታ እንደሚፈፀም ይገባኛል፡፡ ኢህአዴግ እንዲህ ከሚያደርግበት በርካታ ምክንያቶች አንዱ ሌላው የህብረተሰብ ክፍል የትግራይ ወገኖቹ ላይ ጥርጣሬና ጥላቻ እንዲያድርበት ለማድረግ እንደሆነ እገነዘባለሁ፡፡ የትግራይ ህዝብ ሌላው ብሔረሰብ በጥሩ አይን አያየኝም የሚል የተሳሳተ ግንዛቤ እንዲኖረውና ሳይወድ በግዱ የህወሓት ባርያ ሆኖ እንዲቀር መሆኑ ነው፡፡ አይ ኢህአዴግ! ፓርቲና ህዝብ መለየት የምንችል ነቄዎች መሆናችንን ረሳኸው እንዴ? የትግራይ ልጆችም ቢሆኑ ሴራህ ገብቷቸው አብረውን እየታገሉህ በመሆናቸውና ያልነቁትንም እያነቁ በመሆናቸው የሚሳካልህ አይመስለኝም፡፡
እንደው እንደው ግን እናንተዬ ከላይ የጠቀስኩት ከፋፋይ ባህርይው ብቻ እንኳን ኢህአዴግን ለመታገል ከበቂም በላይ ምክንያት አይሆንም? ይሆናል እንደምትሉኝ አውቃለሁ፡፡ በመሆኑም ይሄን በዜጎች መሀከል ጥላቻን ለመዝራት የሚሞክር መርዘኛ መንግስት ከትከሻችን ላይ አሽቀንጥሮ ለመጣልና ነፃነታችንን ለማወጅ በአንድ ላይ እንቆም ዘንድ ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስርቤት

Ethiopian Election: “The political space has been closed” Yilekal Getinet

May 22, 2015
Mr. Yilkal Getnet, chairperson of the rising Ethiopian opposition Semayawi Party
Yilekal Getinet, leader of Semayawi
Addis Ababa (AFP) – Ethiopia, Africa’s second-most populous country, holds general elections Sunday, the first since the death of long-time strongman Meles Zenawi whose successor Hailemariam Desalegn is seen as all but certain to stay in office.
Over 36.8 million Ethiopians have registered for the polls, considered by the international community as a key test of the state’s commitment to bring greater democracy to the Horn of Africa nation.
Rights groups routinely accuse Ethiopia of clamping down on opposition supporters and journalists and using anti-terrorism laws to silence dissent and jail critics.
The ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) has been in power for over two decades and is confident of a win, but insists the result will be decided on its economic record alone. Ethiopia is now one of Africa’s top performing economies and a magnet for foreign investment.
“There’s been improvement and people have seen that,” government spokesman Redwan Hussein told AFP.
“If they want to give us another chance they will vote for us. If they have a grudge, they will not give their vote to EPRDF. We will see the figures — but I don’t think we will lose many of the seats.”
Ethiopia, whose 1984 famine triggered a major global fundraising effort, has seen economic growth of more than 10 percent each year for the last five years, according to the World Bank.
Former Marxist rebel-turned-leader Meles, who died in 2012, was succeeded by Prime Minister Hailemariam, who has said he is committed to opening up the country’s political system to allow more space for opposition parties.
“It is an existential issue. If we do not have a proper multiparty democracy in this country, this country will end up like Somalia,” Hailemariam said late last year.
But the premier has also justified lawsuits taken against opposition leaders he accused of “links with terrorist organisations”.
‘Exceptional’ democracy?
The opposition accuses the government of using authoritarian tactics to ensure a poll victory.
“The political space has been closed,” said Yilekal Getinet, leader of Semayawi, the “Blue Party” in Ethiopia’s Amharic language and one of the main opposition parties.
“Many journalists, political activists, civil society leaders have been sent to jail or forced to leave the country,” he declared.
At Semayawi’s headquarters, activists claimed widespread intimidation by the ruling party.
“Our people are detained, harassed by EPRDF members and uniformed police. We asked the municipality frequently to make demonstrations, rallies, meetings and they denied us every time,” party activist Solomon Tessama said.
“The main problem is that the government and the party are not separate. The media, the security, the finances are under their control. On the ground, there are no free and fair elections.”
A official from the Agaw Democratic Party claimed that some of its activists in the northern towns of Bahir Dar and Gondar had been arrested or beaten.
Such complaints are dismissed as “baseless” by the National Election Board of Ethiopia (NEBE).
“The situation is better than previous years. The environment created for political parties this year is exceptional,” NEBE president Merga Bekana said.
The Election Commission will deploy some 40,000 observers at 45,795 polling stations.
The only foreign election observers are from the African Union, which has sent a team of 59. The European Union and the US-based Carter Center, which monitored 2005 and 2010 elections, were not invited back this time.
Candidates from 58 parties are running for office, but each must go through a system of drawing lots organized by the NEBE to limit to 12 the number of candidates per constituency.
Critics say the system is designed to hamper the main challengers — Semayawi, for example, had 456 applicants, but only 139 were allowed.
The 2010 election was won by the ruling EPRDF in a landslide. The party and its allies took all but one of the 547 seats in the House of People’s Representatives.
The main opposition parties rejected the results, claiming fraud, but their appeals were turned down by the electoral board and the supreme court.
Those polls were peaceful, unlike in 2005, when the opposition’s accusations of irregularities sparked violence that left 200 people dead. The opposition won 172 seats in that vote.