Saturday, June 6, 2015

የህወሓት አምባገነናዊ ስርዓት በመላ አገሪቱ ያሰፈነውን ቅጥያጣ የገበያ ስርዓትና….

June 6, 2015
def-thumb ጭቆና በመቃወም ባለሀብቶችና በሰላማዊ መንገድ ሲታገሉ የቆዩ የተቀናቃኝ ፓርቲዎች አባላት በረሃ እየወረዱ ብረት ማንሳታቸውን ቀጥለዋል፡፡
ሰሞኑን በርካታ ቁጥር ያላቸው ባለሀብቶችና የአንድነት ፓርቲ አባላት በረሃ ወርደው አርበኞች ግንቦት ሰባትን ተቀላቅለዋል፡፡
ህወሓት-ኢህአዴግ የሚያራምደው በጎሰኝነት የተቃኘ የምጣኔ ሀብት ስርዓት አላላውስ ያላቸው ነጋዴዎችና ሰላማዊ ትግል ያበቃለት መሆኑን የተረዱት የአንድነት ፓርቲ አባላት ኢትዮጵያ ውስጥ የስርዓት ለውጥ መጥቶ እውነተኛ ነፃነት እንዲሰፍን ከልብ ከታመነ ብቸኛው መፍትሄ ጠብመንጃ ስለሆነ በአገር ቤት ያሉ ባለሀብቶችና የተቀናቃኝ ፓርቲ አባላት የእነሱን ፈለግ እንዲከተሉ ጠንከር አድርገው አሳስበዋል፡፡
ከሳምንት በፊት የአግአዚ ኮማንዶ ክፍለ ጦር አባላትን ጨምሮ በርካታ የመከላከያ ሰራዊት አባላትና ባለሀብቶች በረሃ ወርደው አርበኞች ግንቦት ሰባትን መቀላቀላቸውን መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

No comments: