Thursday, November 21, 2013

ኢትዮጵያ፣ በህዳርና በ… ሁልጊዜ አስታውሳለሁ!! (ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም)

November 21, 2013
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የህዳር ወር በኢትዮጵያውያን በአሰቃቂነቱ ሁልጊዜ ሲታወስ ይኖራል፡፡
እ.ኤ.አ ኖቬምበር 2013 ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በቃላት ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ ሰቆቃ የተፈጸመበት ወር ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ፣ በሚሰሩና የፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠየቅ ጥረት በማድረግ ላይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ ስልታዊ የሆነ ጥቃት ሲሰነዘር ቆይቷል፡፡ እንዲያውም በግል በሚኖሩበት ቤት እምነታቸውን በማራመዳቸው ብቻ ኢትዮጵያውያኑ/ቱ ዜጎች ላይ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል፣ እንዲጋዙም ተደርጓል፡፡Ethiopia November Victims never again, Alemayehu G. Mariam
እ.ኤ.አ 2011 የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ (Human Rights Watch) ዘገባ የሳውዲ አረቢያ ፖሊስ “ህገወጥ ስብሰባ በሚል ሰበብ 35 የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያወያንን/ትን“ “በአንድ ኢትዮጵያዊ የክርስትና እምነት ተከታይ የግል መኖሪያ ቤት በእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ዋዜማ ተሰባስበው ጸሎት በማድረግ ላይ እንዳሉ” በፖሊስ ቀጥጥር ስር ውለዋል” ይላል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ አረቢያ ጥገኝነት በሚፈልጉ እና ሌሎች ስደተኛ ኢትዮጵያውያት የቤት ሰራተኖች ላይ በሚደረገው ሰብአዊ መብት ረገጣ ምክንያት ምንጊዜም የማያቋርጥ ትችት እየተደረገ መሆኑን መግለጽ ማጋነን አይሆንም፡፡ በዚህ ወር በዕየለቱ በሚባል መልኩ የሳውዲ አረቢያ ፖሊሶች፣ የደህንነት ኃላፊዎችና ተራ የሳውዲ ዜጎች በየመንገዱ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን ያድናሉ፣ ይደበድባሉ፣ ያሰቃያሉ፣ አንዳንድ ጊዜም ይገድላሉ፡፡ የሳውዲ ፖሊሶች ኢትዮጵያውያንን ሲያሰቃዩ የሚያሳየው የቪዲዮ ቅርፅ ለህሊና የሚሰቀጥጥ ነው፡፡ የሳውዲዎች ኢትዮጵያውያንን በየመንገዱ የማባረር ሁከት፣ ጥቃት የመሰንዘርና የመግደል ድርጊት ምንም ዓይነት ማብራሪያ አያስፈልገውም፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ረገጣ የሚያሳየው የፎቶግራፍ ምስል አስደንጋጭና ከሰለጠነ የሰው ልጅ አስተሳሰብ በእጅጉ የዘለለ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አስተዳደር 200 ሺ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑትን በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን/ት ለማገዝ ምን እያደረገ ነው? ምንም!!! እራሱ አምኖ በተቀበለው መሰረት ገዥው አስተዳደር ምን ያህል ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ እንደሚኖሩ እንኩዋን አያውቅም፣ ሆኖም ግን ተጨባጭነት በሌለው መልኩ ኢትዮጵያውያንን/ትን ከሳውዲ አረቢያ ሙሉ በሙሉ በተቻለ መጠን ወደ ኢትዮጵያ እመልሳለለሁ የሚል ቃል ገብቷል፡፡
የወባ ተመራማሪው “የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር”፣ ቴዎድሮስ አድሃኖም የሳውዲ መንግስት በግዛቱ በሚገኙት ስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ሰራተኞች ላይ የፈጸመውን አረመኒያዊ የኃይል እርምጃ “መንግስቱ አውግዘዋል፡፡ ይኸ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፡፡ ይህን ጉዳዩ የሳውዲ መንግስት እንዲያጣራ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ እዚያ በነበሩበት ጊዜ በክብር መያዝ የነበረባቸውን ዜጎቻችንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስም ደስተኞች ነን፡፡ ተቀባይነት የለውም” የሚለውን አባባል ገዥው አስተዳደር እንደ አስፈሪ የጭካኔ ድርጊቶች፣ ያለመሰልጠንነትና ዘግናኝ ጨካኝነትና ወንጀለኛነት የሚሉትን ቃላት ለመግለጽ የሚጠቀምበት የውግዘት ቃል ነው፡፡ አልጄዚራ እንደዘገበው ከሆነ በተፈጸመው ድርጊት ተበሳጭተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን/ት አዲስ አበባ በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ሰላማዊ ተቃውሟቸውን ለማሰማት በሄዱበት ጊዜ የገዥው አስተዳደር ፖሊስ በቁጥጥር በማዋል  ድብደባ ፍጽሞባቸዋል፡፡ “ፖሊሶች ከመጡ በኋላ ደብድበውናል፣ እና በአሁኑ ጊዜ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በእስር ቤት ይገኛሉ” በማለት የተቃዋሚው የሰማያዊ ፓርቲ ነባር አባል ጌትነት ባልቻ ገልጿል፡፡ ጌትነት በመቀጠልም “የፓርቲው ሊቀ መንበርና ምክትል ሊቀመንበር ከታሰሩት ውስጥ ይገኙበታል” በማለት ሀሳቡን አጠቃሏል፡፡
ሆኖም ግን ኢትዮጵያውያን/ በሀዳር ወር መጎዳትና መጎሳቀል ለምን ይደንቀን? እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 ያለው የገዢ አስተዳደር ለመናገር በሚዘገንን መልኩ የጭካኔ ድርጊት በአትዮጵያኖች ላይ ፈፅሞአል:: በዚያው ዓመት የፓርላማውን ምርጫ ተከትሎ በግንቦት ወር በጠራራ ፀሐይ የተዘረፈውን የህዝብ ድምጽ በመቀወም ድምጻቸውን ባሰሙ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች እራሱ መለስ ዜናዊ ያቋቋመው አጣሪ ኮሚሽን 193 ያልታጠቁ ወንዶች፣ ሴቶች እና ልጆች በአዲስ አበባ መንገዶች በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን በመግለጻቸውና እና ሌሎች በከፍተኛ ደህንነት በእስር ቤት የሚገኙ እስረኞችን ሆን ተብሎ በጥይት ደብድበዋል፣ ሌሎች 763 የሚሆኑት በጽኑ ቆስለዋል፡፡
እ.ኤ.አ ከ2007 ጀምሮ በየጊዜው በህዳር ወር እ.ኤ.አ የ2005 ምርጫን ተከትሎ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጨዋና ያልታጠቁ ሰልፈኞች ተኩስ በመክፈት ገደሏቸው፣ አካለ ጎደሎ አደረጓቸው፡፡ እኔም ያንን ጊዜ ለማስታወሰ ስል መጻፌን ቀጥየ ነበር፡፡
በመጀመሪያው የማሰታወስ ጽሁፌ እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 እና በጁን 2005 የተከፈለው መስዕዋትነት ለዘላለም ይታወሳል! ለአንባቢ ዎቼም ሳስታዉስ በህይወት ላሉትና ለሞቱት ምስክርነት መስጠት እንዳለባችሁ የሞራል ግዴታ ተጥሎባችኋል ብዬ ነበር፡፡ ኤሊ ዌይሰል የዕልቂቱ ተራፊና የኖቬል ተሸላሚ በክብር እንዳስቀመጠው “ማስታዋስ አለብን ምክንያቱም የጋራ ትውስታችን የሆኑትን ያለፉ ድርጊቶች የወደፊቱን ትውልድ መብት መከልከል ስለማንችል ነው መርሳት መጥፎ ነገር ብቻ አይደለም ነገር ግን ስድብም ነው፡፡ የሞቱትን መርሳት ሁለተኛ ከመግደል እኩል ነው፡፡”
በ2005 ያለቁትን መርሳት ማለት በእነርሱ ላይ የተፈጸሙትን ግፎች መርሳት እንዲህም ያሉትን አረመኔአዊ ወንጀል መርሳትማለት ነው፡፡ እልቂቱን መርሳት ማለት ወንጀለኞች ተጠያቂ እንዳይሆኑ የልብ ልብ መስጠት ማለት ነው፣ ምክንያቱም ወንጀሎቹ ተረስተዋል፡፡ በመጨረሻም መርሳት ማለት በስልጣን ላይ ያሉ ወንጀለኞች እንደገና እና እንደገና የወንጀል ደረጃውን ከፍ በማድረግና ተጠያቂነት የሌለበትን ሁኔታ በመፍጠር ወንጀል እንዲሰሩ ማበረታታት ማለት ነው፡፡
አስታውሳለሁ! በምንም አይነት አልረሳምም፣ በፍጹም!!!
አስታውሳለሁ ምክንያቱም እኔ ካላስታወስኩ ማን ያስታዉሳል? አስታውሳለሁ ምክንያቱም የምረሳ ከሆነ ወንጀሎችና ወንጀለኞች ይረሳሉ፡፡ የምረሳ ከሆነ ታሪክ እንዴት ሊያስታውስ ይችላል? ታሪክ ሊያስታውስ የሚችለው ሌላ ሊያስታውስ የሚችል ሰው ሲኖር ነው:: በህዳር፣ በታህሳስ፣ በጥር፣ በየካቲት፣ መጋቢት፣ ሚያዝያ… ዛሬ ለኢትዮጵያ ወጣቶችና ነገ ለሚወለዱ ህጻናት አስታውሳለሁ፡፡
የእኔን ስራ በማድነቅና ለበርካታ ዓመታት ሲደግፉ ሲቆዩ ሌሎች ደግሞ ሲተቹ ሲቃወሙ የሚኖሩ አሉ። እኔ በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ ነው ይሉኛል:: በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ መሆን ለኔ ታላቅ ክበር ነው::
የ2005 ዕልቂትን አስታውሳሁ፡፡ እያንዳንዱን በግፍ የተገደሉትን አስታዉሳለሁ፡፡ አስታውሳለሁ ወጣት ሴቶች ወደፊት እናት ላይሆኑ፣ ወጣት ወንዶችን የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም  ወደፊት አባት ላይሆኑ፣ ወላጅ የሌላቸውን ወላጆቻቸው የተገደሉባቸውን አስታውሳለሁ፡፡ ልጆቻቸው የተገደሉባቸውን እናቶችንና አባቶችን አስታውሳለሁ::
ወንጀለኞችን አልረሳም፣ ተንኮል የሰሩትን 237ቱን የፖሊስ አባላት አስታውሳለሁ፣ የወንጀለኞችን ቁንጮና መሪ የነበረዉን አራዊትን  አልረሳም:: የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም::
አስታውሳሁ፣ መቼ ረሳለሁ: ሁልጊዜ  ህዳርን፣ ታህሳስን፣ ጥርን፣ የካቲትን፣ መጋቢትን፣ ሚያዝያን….አልረሳም፡፡
.
ስም
ጾታ
እድሜ
ስራ

መግለጫ
1
ሬቡማ ኢርጋታ
34
ግንበኛ
2
መለሳቸው አለምነው
16
ተማሪ
3
ሀድራ ኦስማን
22
አይታወቅም
4
ጃፋር ኢብራሂመ
28
ቢዝነስ
5
መኮንን
17
አይታወቅም
6
ወልደሰማያት
17
7
ባህሩ ደምለው
አይታወቅም
8
ፈቀደ ነጋሽ
25
መካኒክ
9
አብርሀምይልማ
17
ታከሲ ነጂ
10
ያሬድ እሸቴ
23
ቢዝነስ
11
ከበደ ገ/ህይወት
17
ተማሪ
12
ማቴዎስ ፍልፍሉ
14
ተማሪ
13
ጌትንት ወዳጆ
48
ቢዝነስ
14
ቃሰም ራሽድ
21
መካኒክ
15
ሸውሞሊ
22
ቢዝነስ
16
አሊየ ኢሳ
20
የቀን ስራ
17
ሣምሶን ያዕቆብ
23
የህዝብ ማመላ
18
አለባለው አበበ
18
ተማሪ
19
በልዩ ዛ
18
ትራንስ. ረዳት
20
ዩሱፍ ጀማል
23
ተማሪ
21
አብርሃም አገኘሁ
23
ትራንስ.ረዳት
22
መሀመድ በቃ
45
አርሶ አደር
23
ረዴላ አወል
19
የታክሲ ረዳት
24
ሀብታሙ ኡርጋ
30
ቢዝነስ
25
ዳዊት ፀጋዬ
19
መካኒክ
26
ገዛኸኝ ገረመው
15
ተማሪ
27
ዮናስ አበራ
24
አይታወቅም
28
ግርማ ወልዴ
38
ሾፌር
29
ደስታ ብሩ
37
ቢዝነስ
30
ለገሰ ፈይሳ
60
ቢዝነስ
31
ተስፋዬ ቡሽራ
19
ጫማ ጠጋኝ
32
ቢንያም ደገፋ
18
ስራ አጥ
33
ሚሊዮን ሮቢ
32
ትራንስ.ረዳት
34
ደረጀ ደኔ
24
ተማሪ
35
ነብዩ ሃይሌ
16
ተማሪ
36
ምትኩ ምዋለንዳ
24
ዶመስቲክ ሰራተኛ
37
አንዋር ሱሩር
22
ቢዝነስ
38
ንጉሴ ዋብግነ
36
ዶመስቲክ ሰራተኛ
39
ዙልፋ ሀሰን
50
የቤት እመቤት
40
ዋስይሁን ከበደ
16
ተማሪ
41
ኤርሚያስ ከበደ
20
ተማሪ
42
00428
25
አይታወቅም
43
00429
26
አይታወቅም
44
00430
30
አይታወቅም
45
አዲሱ በላቸው
25
አይታወቅም
46
ደመቀ አበበ
አይታወቅም
47
00432
22
አይታወቅም
48
00450
20
አይታወቅም
49
13903
25
አይታወቅም
50
00435
30
አይታወቅም
51
13906
25
አይታወቅም
52
ተማም ሙክታር
25
53
በየነ በዛ
25
አይታወቅም
54
ወሰን አሰፋ
25
አይታወቅም
55
አበበ አንተነህ
30
አይታወቅም
56
ፈቃዱ ኃይሌ
25
አይታወቅም
57
ኤሊያስ ጎልቴ
አይታወቅም
58
ብርሃኑ ዋርካ
59
አሸብር መኩሪያ
አይታወቅም
60
ዳዊት ሰማ
አይታወቅም
61
መርሀጽድቅ ሲራክ
አይታወቅም
62
በለጠ ጋሻውጠና
አይታወቅም
63
ብኃይሉ ተስፋዬ
20
አይታወቅም
64
21760
18
አይታወቅም
65
21523
25
አይታወቅም
66
11657
24
አይታወቅም
67
21520
21
አይታወቅም
68
21781
60
አይታወቅም
69
ጌታቸው አዘዘ
45
አይታወቅም
70
21762
75
አይታወቅም
71
11662
45
አይታወቅም
72
21763
25
አይታወቅም
73
13087
30
አይታወቅም
74
21571
25
አይታወቅም
75
21761
21
አይታወቅም
76
21569
25
አይታወቅም
77
13088
30
አይታወቅም
78
እንዳልካቸው ገብርኤል
27
አይታወቅም
79
ኃይለማርያም አምባዬ
20
አይታወቅም
80
መብራቱ ዘውዱ
27
አይታወቅም
81
ስንታየሁ በየነ
14
አይታወቅም
82
ታምሩ ኃይለሚካኤል
አይታወቅም
83
አድማሱ አበበ
45
አይታወቅም
84
እቴነሽ ይማም
50
አይታወቅም
85
ወርቄ አበበ
19
አይታወቅም
86
ፈቃዱ ደግፌ
27
አይታወቅም
87
ሸምሱ ካሊድ
25
አይታወቅም
88
አብዱዋሂደ አህመዲን
30
አይታወቅም
89
ታከለ ደበሌ
20
አይታወቅም
90
ታደሰ ፌይሳ
38
አይታወቅም
91
ሶሎሞን ተስፋዬ
25
አይታወቅም
92
ቅጣው ወርቁ
25
አይታወቅም
93
ደስታ ነጋሽ
30
አይታወቅም
94
ይለፍ ነጋ
15
አይታወቅም
95
ዮሀንስ ኃይሌ
20
አይታወቅም
96
በኃይሉ ብርሀኑ
30
አይታወቅም
97
ሙሉ ሶሬሳ
50
አይታወቅም
98
የቤት እመቤት
አይታወቅም
99
ቴዎድሮስ
23
አይታወቅም
100
ጫማ ሰሪ
ጫማ ሰሪ
101
በኃይሉ ብርሃኔ
30
አይታወቅም
102
ሙሉ ሶሬሳ
50
የቤት እመቤት
103
ቴዎድሮስ ኃይሌ
23
ጫማ ሻጭ
104
ደጄኔ ይልማ
18
መጋዝን ጠባቂ
105
ኡጋሁን ወልደገብርኤል
18
ተማሪ
106
ደረጀ ማሞ
27
አናጺ
107
ረጋሳ ፈይሳ
55
ላውንድሪ ሰራተኛ
108
ቴዎድሮስ ገብረዎልድ
28
የግል ንግድ
109
መኮንን ገ/እግዚአብሄር
20
መካኒክ
110
ኤሊያስ ገ/ጊዮርጊስ
23
ተማሪ
110
አብርሀም መኮንን
21
የቀን ሰራተኛ
111
ጥሩወርቅ ገ/ጻድቅ
41
የቤት እመቤት
112
ሄኖክ መኮንን
28
አይታወቅም
113
ጌቱ ምሀትተ
24
አይታወቅም
114
ክብነሽ ታደሰ
52
አይታወቅም
115
መሳይ ስጦታው
29
የግል ንግድ
116
ሙሉአለም ወይሳ
15
አይታወቅም
117
አያልሰው ማሞ
23
አይታወቅም
118
ስንታየሁ መለሰ
24
የቀን ሰራተኛ
119
ጸዳለ ቢራ
50
የቤት እመቤት
120
አባይነህ ሰራሴድ
35
ልብስ ሰፊ
121
ፍቅረማርያም ተሊላ
18
ሾፌር
122
አለማየሁ ገርባ
26
አይታወቅም
124
ጆርጅ አበበ
36
የግል ትራንስፖርት
125
ሀብታሙ ዘገየ
16
ተማሪ
126
ምትኩ ገ/ስላሴ
24
ተማሪ
127
ትዕዛዙ መኩሪያ
24
የግል ንግድ
128
ፈቃዱ ዳልጌ
36
ልብስ ሰፊ
129
ሸዋጋ ወ/ጊዮርጊስ
38
የቀን ሰራተኛ
130
አለማየሁ ዘውዴ
32
የቴክስታይል ሰራተኛ
131
ዘላለም ገ/ጻድቅ
31
የታክሲ ሾፌር
132
መቆያ ታደሰ
19
ተማሪ
133
ሀይልየ ሁሴን
19
ተማሪ
134
ፍስሀ ገ/ጻድቅ
23
የፖሊስ ተቀጣሪ
135
ወጋየሁ አርጋው
26
ስራ ፈላጊ
136
መላኩ ከበደ
19
አይታወቅም
137
አባይነህ ኦራ
25
ልብስ ሰፊ
138
አበበች ሆለቱ
50
የቤት እመቤት
139
ደመቀ ጀንበሬ
30
አርሶ አደር
140
ክንዴ ወረሱ
22
ስራ ፈላጊ 141
141
እንዳለ ገ/መድህን
23
የግል ንግድ
142
አለማየሁ ወልዴ
24
መምህር
143
ብስራት ደምሴ
24
መኪና አስመጭ
144
መስፍን ጊዮርጊስ
23
የግል ንግድ
145
ወሎ ዳሪ
18
የግል ንግድ
146
በሀይሉ ገ/መድህን
20
የግል ንግድ
147
ሲራጂ ኑሩ ሰይድ
18
ተማሪ
148
እዮብ ገ/መድህን
25
ተማሪ
149
ዳንኤል ሙሉጌታ
25
የቀን ሰራተኛ
150
ቴዎድሮስ ደገፋ
25
የጫማ ፋብሪካ ሰራተኛ
151
ጋሻው ሙሉጌታ
24
ተማሪ
152
ከበደ ኦርቄ
22
ተማሪ
153
ለሊሳ ፋጤሳ
21
ተማሪ
154
ጃገማ ባሻ
20
ተማሪ
155
ደበላ ጉታ
15
ተማሪ
156
መላኩ ፈይሳ
16
ተማሪ
157
እልፍነሽ ተክሌ
45
አይታወቅም
158
ሀሰን ዱላ
64
አይታወቅም
159
ሁሴን ሀሰን ዱላ
25
አይታወቅም
160
ደጀኔ ደምሴ
15
አይታወቅም
161
ዘመድኩን አግደው
18
አይታወቅም
162
ጌታቸው ተረፈ
16
አይታወቅም
163
ደለለኝ አለሙ
20
አይታወቅም
164
ዩሱፍ ኡመር
20
አይታወቅም
165
መኩሪያ ተበጀ
22
አይታወቅም
166
ባድሜ ተሻማሁ
20
አይታወቅም
167
አምባው ጌታሁን
38
አይታወቅም
168
ተሾመ ኪዳኔ
65
የጤና ባለሙያ
169
ዮሴፍ ረጋሳ
አይታወቅም
170
አብዩ ንጉሴ
አይታወቅም
171
ታደለ በሀጋ
አይታወቅም
172
ኤፍሬም ሻፊ
አይታወቅም
173
አበበ ሀማ
አይታወቅም
174
ገብሬ ሞላ
አይታወቅም
175
ሰይዴ ኑረዲን
አይታወቅም
176
እንየው ጸጋዬ
32
እረዳት ትራንስፖርት
177
አብዱራህማን ፈረጅ
32
የእንጨት ስራ ባለሙያ
178
አምባው ብጡል
60
የቆዳ ፋብሪካ ሰራተኛ
179
አብዱልመናን ሁሴን
28
የግል ንግድ
180
ጅግሳ ሰጠኝ
18
ተማሪ
181
አሰፋ ነጋሳ
33
አናጺ
182
ከተማ ኡንኮ
23
ልብስ ሰፊ
183
ክብረት እልፍነህ
48
የጥበቃ ሰራተኛ
184
እዮብ ዘመድኩን
24
የግል ንግድ
185
ተስፋዬ መንገሻ
15
የግል ንግድ
186
ካፒቴን ደበሳ ቶሎሳ
58
የግል ንግድ
187
ትንሳኤ ዘገየ
14
ልብስ ሰፊ
188
ኪዳና ሹክሩ
25
የቀን ሰራተኛ
189
አንዷለም ሺበለው
16
ተማሪ
190
አዲሱ ተስፋሁን
19
የግል ንግድ
191
ካሳ በየነ
28
ልብስ ሽያጭ
192
ይታገሱ ሲሳይ
22
አይታወቅም

የጸጥታ ኃይሎች እርስ በእርስ ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ በጥይት የተገደሉ ሰዎች፣

193
ነጋ ገብሬ
194
ጀበና ደሳለኝ
195
ሙሊታ ኢርኮ
196
የሃንስ ሶሎሞን
197አሸናፊ ደሳለኝ
198
ፈይሳ ገ/መንፈስ
በመቶዎቹ የሚቆጠሩትን የግድያ ሰለባዎች፣ አካለ ጎደሎዎች፣ ቁስለኞች፣ በኃይል የተመቱትንና ሰውነታቸው በጥይት የተበሳሱትን ሁሉ አስታውሳለሁ፡፡
..ኖቬምበር 2/2005ከቃሊቲእስርቤትለማምለጥሲሞክሩበታጣቂዎችበተከፈተተኩስበጥይትተደብድበውያለቁሰዎችስምዝርዝር፣
.
ስም
ጾታ
የተከሰሱበት ጥፋት፣
1
ጠይብ ሸምሱ መሀመድ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
2
ሳሊ ከበደ
ምንም ዓይነት ክስ አልተጠቀሰም
3
ሰፊው እንድሪስ ታፈሰ
በአስገድዶ መድፈር
4
ዘገዬ ተንኮሉ በላይ
በዝርፊያ ወንጀል
5
ቢያድግልኝ ታመነ
የተወነጀሉበት ያልታወቀ
6
ገብሬ መስፍን ዳኘ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
7
በቀለ አብርሃም ታዬ
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
8
ጉታ ሞላ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
9
ኩርፋ መልካ ተሊላ
በማስፈራራት ወንጀል
10
በጋሻው ተረፈ ጉደታ
የህዝብን ሰላም በማደፍረስ ወንጀል
12
አብደልወሃብ አህመዲን
በዘርፊያ ወንጀል
13
ተስፋዬ አብይ ሙሉጌታ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
14
አዳነ ቢረዳ
በነፍስ ማጥፋት ወንጀል
15
ይርዳው ከርሴማ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
16
ባልቻ አለሙ ረጋሳ
በዝርፊያ ወንጀል
17
አቡሽ በለው ወዳጆ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
18
ዋለልኝ ታምሬ በላይ
በአስገድዶ መድፈር
19
ቸርነት ኃይሌ ቶላ
በዝርፊያ ወንጀል
20
ተማም ሸምሱ ጎሌ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
21
ገብየሁ በቀለ አለነ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
22
ዳንኤል ታዬ ለኩ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
23
መሀመድ ቱጂ ቀኔ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
24
አብዱ ነጂብ ኑር
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
25
የማታው ሰርቤሎ
በአስገድዶ መድፈር
26
ፍቅሩ ናትናኤል ሰውነህ
በማስፈራራት ወንጀል
27
ሙኒር ከሊል አደም
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
28
ኃይማኖት በድሉ ተሸመ
ጽንፈኝትን በማራመድ
29
ተስፋዬ ክብሮም ተኬ
በዥርፊያ ወንጀል
30
ወርቅነህ ተፈራ ሁንዴ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
31
ሲሳይ ምትኩ ሁነኛ
በማጭበርበር ወንጀል
32
ሙሉነህ አይናለም ማሞ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
33
ታደሰ ሩፌ የኔነህ
በማስፈራራት ወንጀል
34
አንተነህ በየቻ ቁበታ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
35
ዘሪሁን መርሳ
በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ ወንወጀል
36
ወጋየሁ ዘሪሁን አስፋው
በዝርፊያ ወንጀል
37
በከልካይ ታምሩ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
38
የራስወርቅ አንተነህ
በማጭበርበር ወንጀል
39
ባዝዘው ብርሀኑ
ግብረሰዶም በመፈጸም ድርጊት
40
ሶሎሞን እዮብ ጉታ
በአስገድዶ መድፈር ወንጀል
41
አሳዩ ምትኩ አራጌ
በማስፈራራት ወንወጀል
42
ጋሜ ኃይሉ ዘገዬ
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
43
ማሩ እናውጋው ድንበሬ
በአስገድዶ መድፈር ወንጀል
44
እጂጉ ምናለ
በግድያ ሙከራ ወንጀል
45
ኃይሉ ቦስኔ ሀቢብ
የተቀደሰን ቦታ በማራከስ
46
ጥላሁን መሰረት
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
47
ንጉሴ በላይነህ
በዝርፊያ ወንጀል
48
አሸናፊ አበባው
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
49
ፈለቀ ድንቄ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
50
ጀንበሬ ድንቅነህ ቢለው
በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር
51
ቶሎሳ ወርቁ ደበበ
የዝርፊያ ወንጀል
52
መካሻ በላይነህ ታምሩ
የህዝብን ሰላም በማደፍረስ
53
ይፍሩ አደራው
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
54
ፋንታሁን ዳኘ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
55
ጥበቤ ዋቀኔ ቱፋ
ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት
56
ሶሎሞን ገብረአምላክ
የህዝብን ሰላም በማደፍረስ
57
ባንጃው ቹቹ ካሳሁን
በዝርፊያ ወንጀል
58
ደመቀ አበጀ
በግድያ ሙከራ ወንጀል
59
እንዳለ እውነቴ መንግስቴ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
60
አለማየሁ ጋርባ
እ.ኤ.አ በ2004 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመጽ ጋር በተያያዘ መልኩ በቁጥጥር የዋሉ
61
ሞርቆታ ኢዶሳ
የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ
ለምዘገባ፣ በዚህ እልቂት ላይ ተዋንያን የነበሩ 237 የተረጋገጠ የፖሊስ እና የደህንነት አባላት ዝርዝርን የያዘ ሰነድ ተቀምጧል፡፡
የኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ!
Yenesew Gebre from Dawro-Waka Ethiopia
የኔሰው ገብሬ
እ.ኤ.አ በ11/11/11 የኔሰው ገብሬ የተባለ የ29 ዓመት መምህር እና የሰብአዊ መብት ተሟጋች በደቡብ ኢትዮጵያ በዳውሮ ዞን በተርጫ ከተማ ከህዝብ መሰብሰቢያ ዳራሽ ፊት ለፊት እሳት በመለኮስ እራሱን በእሳት አያይዟል፡፡ ለሶስት ቀናት ቆስሎ ከቆየ በኋላ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡ እራሱን በእሳት ከማያያዙ በፊት የኔሰው ከህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውጭ ለተሰበሰበ ህዝብ እንዲህ የሚል ንግግር አሰምቶ ነበር፣ “በእኩልነት ላይ ባልተመሰረተ አስተዳደር እና ፍትህ በሌለበት እንዲሁም የሰብአዊ መብት በማይከበርበት አገር ውስጥ እራሴን ለመስዋዕትነት አቀርባለሁ፣ ይህንንም በማድረጌ ወጣቱ ትውልድ ነጻ ይወጣል፡፡” የአትዮጵያ ጀግናዉ የእኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ
“ገዳዮችን አስታውሳለሁ፣ የግድያ ሰለባዎችንም አስታውሳለሁ፣ ለትግሌ የሚያግዙ አንድ ሺ እና ከዚያ በላይ ያሉ አሳማኝ ምክንያቶች እና ተስፋ ቢኖረኝም፡፡ ባስታወስኩ ቁጥር ተስፋየ ይሟጠጣል፣ ያንን ድርጊት ባስታውስኩ ቁጥር ደግሞ ተስፋቢስነቴን የማስወገድ ኃላፊነት እንዳለብኝ እገነዘበላሁ፣ ተስፋ ከተስፋቢስነት በላይ ነው፡፡“ ይላል ኤሊ ዊሴል!
**ለጥቃቱ ሰለባዎች ተጨማሪ መረጃ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆኑት ያሬድ ኃ/ማርያም እ.ኤ.አ ሜይ 15/2006 በሰው ልጆች ላይ የተፈጸመ  ወንጀል በኢትዮጵያ፣ የጁንና ኖቬምበር 2005የአዲስ አበባው ዕልቂት በሚል ርዕስ ለአውሮፓ ህብረት ፓርላሜንት ለልማትና ውጭ ጉዳዮች እና ለሰብአዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ አስቸኳይ ጥምር ጉባኤ የቃረቡትን ምስክርነት ይመለከቷል፡፡
***የመርማሪ ኮሚሽኑ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ የጥቃቱ ሰለባዎችን ነጻ ሲያወጣ አጠቃላይ ኃላፊነቱን ግን በፖሊስና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ደፍድፎታል፡፡ መርማሪ ኮሚሽኑ አስተያየቱን በመቀጠል እንደሚከተለው አጠቃሎታል፣ “በተቃዋሚዎቹ የተጎዳ ንብረት የለም፣ በመንግስት በሞኖፖል በተያዘው መገናኛ ብዙሀን እንደተለፈፈው ጥቂት ተቃዋሚዎች የእጅ ቦንቦችንና ጠመንጃዎችን ታጥቀዋል እንደሚለው ሳይሆን በተቃራኒው የእጅ ቦንብ እና ጠብመንጃ የታጠቀ አንድም የተቀዋሚ አባል የለም፣ በመንግስት ታጣቂ ኃይሎች የተከፈተው ተኩስ ሰላማዊ ሰልፈኞችን ለመበተን ሳይሆን በተቃራኒው የሰልፈኞችን ጭንቅላትና ደረት ለመበርቀስ ዒላማ ያደረገ ነበር፡፡” የመርማሪ ኮሚሽኑ የ193 የእልቂቱ ሰለባዎችን ስም ዝርዝር የያዘ ሰነድ የሚያካትተው እ.ኤ.አ ከጁን 6 – 8 እና ከኖቬምበር 1- 4/2005 በዚህ ጊዜ ብቻ ያለውን ድርጊት እንዲያጣራ ለአጣሪ ኮሚሽኑ የተሰጠው ስልጣን ነበር፡፡ አጣሪ ኮሚሽኑ ግን በፓርላማው ከተሰጠው የጊዜ ገደብ ውጭ ከህግ ውጭ በመንግስት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች የተፈጸሙ ግድያዎችን ስም ዝዝዝር ያገኘ ቢሆንም እነዚህ ግድያዎች ኮሚሽኑ እንዲያጣራ ተለይቶ ከተሰጠው ጊዜ ውጭ በመሆናቸ ለህዝብ ይፋ ሳያደርገው ቀርቷል፡፡

‘The blood of Ethiopians cries out for justice’

November 21, 2013
by Chris Matthews


Ethiopians gathered outside the Saudi Arabian Embassy
© Chris Matthews
Cries of ‘shame on you’ rang around Curzon Street in London on 18 November as more than 300 Ethiopians gathered outside the Saudi Arabian Embassy to protest against the treatment of migrant workers in the country.
Waving flags, singing in unison and holding placards adorned with slogans demanding action – ‘The blood of Ethiopians cries out for justice’, ‘Stop the torture’ and ‘Being poor is not a crime’ – hundreds of London’s Ethiopian diaspora crowded the usually busy west London street.
The protest, in response to Saudi authorities clampdown on migrant workers, came after several migrants, including at least two Ethiopian nationals, were killed during violent clashes with security forces in the oil-rich Gulf State last week.
Sunday 3 November saw an end to a seven-month amnesty demanding that all migrant workers without legal status in the country be deported, resulting in the mass demonstrations and riots seen across the country and in the capital Riyadh.
Saudi Arabia is home to an estimated nine million migrants workers, many from Ethiopia and neighbouring East African nations, and authorities argue that the clampdown will reduce growing unemployment levels among Saudi nationals.
However, there are widespread accusations of abuse towards migrant workers in the Kingdom, with numerous reports of murder, rape and torture against members of the foreign population.
Zelealam Tesdema, one of the organizers of the London protest, urged the Saudi Arabian government to take action and called for those responsible for such acts to be brought to justice.
‘This protest is part of a global movement to stop the brutality, the rape and the murder of migrant workers. The government needs to stop the violence and bring the security forces and authorities to justice,’ Zelealam Tesdema said.
As numbers swelled and voices became louder and more fervent, a police cordon formed in front of the protesters, barring any advances to the gates of the Saudi Arabian embassy.
Zelealam Tesdema said it was vital people had the opportunity to ‘voice their concerns’. A petition calling on the ‘Saudi government to stop the brutal and inhumane treatment’ of Ethiopians was delivered to the embassy.
More than 23,000 Ethiopians, who were living illegally in Saudi Arabia, have now surrendered to officials there, and the Ethiopian government has already started repatriating those ordered to leave the country.
The UN Refugee Agency said that in excess of 51,000 Ethiopians have made the journey across the Gulf of Aden this year alone.
Another of the protest’s organizers, Bekele Woyecha, who has lived in London for six years, fears that many of those on return flights to the capital Addis Ababa will now be left with nothing.
‘A lot of people who left Ethiopia in the first place were doing so because of economic or political problems and so for them returning it will be difficult. These people have nothing now – the authorities in Saudi Arabia have taken everything that they have.’
In a country where labour laws are routinely abandoned and workers’ rights systematically ignored – highlighted by images of maltreatment against migrants circulating online in recent days – an environment of abuse has festered and Adam Coogle, Middle-East Researcher for Human Rights Watch, believes such malpractice is likely to continue.
‘Many migrant workers are unaware of the official rights available to them. Saudi Arabia will still be dependent on migrant workers for many years to come – the labour laws provide conditions in which abuses can take place.’
The large number of undocumented workers in the country has created a vast under-the-table economy and Coogle says that many employers have ‘complete power’ over migrant workers, often confiscating travel documents and preventing workers from changing jobs once they begin working for an employer.
And although such treatment of migrants is a problem not unique to the Arabian Peninsula, the tragic events of recent weeks have a shone an alarming light on the darkness that pervades in the country. The protest on the streets of London has helped bring awareness to the human rights violations and ongoing plight of migrant workers within the Saudi state a little more into focus

በ1997ቱ የኢትዮጵያ ምርጫ ታዛቢ የነበሩት አና ጐሜዝ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው

November 21, 2013

Photo: © Europen Parliament/P.Naj-Olearipietro.naj-oleari@europarl.europa.eu 


በ1997 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫና ምርጫውን ተከትሎ ተከስቶ በነበረው የፖለቲካ ውዝግብ አካል የነበሩት የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ አና ጐሜዝ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው፡፡
በኢትዮጵያ በ1997 ዓ.ም. ተካሂዶ የነበረውን ምርጫ በአውሮፓ ኅብረት ተወክለው ምርጫውን በዋና ታዛቢነት የመሩትና የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ አባል የሆኑት አና ጐሜዝ፣ ምርጫውን አስመልክቶ ባወጡት ሪፖርት ኢሕአዴግ ከሚመራው መንግሥት ጋር ጥልቅ የሆነ ግጭት ውስጥ ገብተው ነበር፡፡
አና ጐሜዝ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በምርጫው ሳቢያ ውዝግብ ከገቡበት ጊዜ አንስቶ የኢሕአዴግን ፖለቲካ በተለይም የሰብዓዊ መብት አያያዙን ከመተቸት ተቆጥበው አያውቁም፡፡ ይሁን እንጂ ከምርጫው በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አያውቁም፡፡
በሚቀጥለው ሳምንት በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የአፍሪካ፣ የካረቢያንና የአውሮፓ ኅብረት አገሮች የጋራ የፓርላማ አባላት ጉባዔ ላይ ለመገኘት በአገሮቹ ከተወከሉ ግለሰቦች መካከል አና ጐሜዝ እንዳሉበት በኢትዮጵያ በኩል የጉባዔው አስተባባሪ ከሆነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምንጮቻችን ለመረዳት ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለፖርቹጋላዊቷ የፓርላማ ተወካይ አና ጐሜዝ ቪዛ ሰጥቶ ይሁን ከልክሎ ለማወቅ ያደግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ ይሁን እንጂ ግለሰቧ በቲዊተር ገጻቸው ላይ በአዲስ አበባው ጉባዔ ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል፡፡ አና ጐሜዝ በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ምርጫ ትዝብት ሪፖርታቸው፣ ምርጫው ነፃና ፍትኃዊ እንዳልነበር ሪፖርት በማድረጋቸው ሪፖርቱ የውዝግቡ ምንጭ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሪፖርቱን ከማጣጣል አልፈው ግለሰቧን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ መዝለፋቸው ይታወሳል፡፡
አና ጐሜዝ በበኩላቸው እስከቅርብ ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የዕርዳታ ማዕቀብ እንዲጣልበት እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ ‹‹ዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ በተለይም የእንግሊዝና የአሜሪካ መንግሥታት በኢትዮጵያ ዜጎች ላይ መንግሥት የሚፈጽመውን በደል እያዩ እንዳላዩ፤ እየሰሙ እንዳልሰሙ ችላ ብለዋል፤›› በማለት ከዓመት በፊት የሰላ ትችት በመሰንዘር የአውሮፓ ኅብረት ለኢትዮጵያ የሚደረገውን ዕርዳታ እንዲያቆም ተከራክረዋል፡፡ 

ፕሬዝደንት ኢሳያስ ከዕይታ መሰወራቸው


November 20/2013

የአሜሪካ መንግስት ለዜጎቹ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል
-    በአስመራ ጀኔራሎች መካከል የስልጣን ሽኩቻ ይጠበቃል

በጥቅምት ወር 2006 ዓ.ም አጋማሽ በኤርትራ ጎዳና መታየታቸው የተነገረላቸው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከአደባባይ እና ከኤርትራ ቴሌቪዥን ዕይታ ውጪ መሆናቸው በአስመራ ከተማ ነዋሪዎች ከፍተኛ የሆነ መነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኗል።

የሰንደቅ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደገለፁት “ከዚህ በፊት ፕሬዝደንቱ ከሚሰቃዩበት የጉበት በሽታ ጋር በተያያዘ ለከፍተኛ ሕመም ተዳርገዋል። በአሁን ሰዓት በኳታር ሆስፒታል ሕክምና እየወሰዱ ይገኛሉ” ብለዋል።

በአስመራ ከተማ ውስጥ እየተናፈሰ ያለው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከበሽታቸው አገግመው ሀገር ሊያስተዳድሩ ይችላሉ የሚሉ በአንድ ወገን በሌላ ወገን ያሉት ከዚህ በኋላ ፕሬዝደንቱ ሀገር በሚያስተዳድሩበት ቁመና ውስጥ ሊገኙ አይችሉም የሚሉት ይገኙበታል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የአሜሪካ መንግስት እ.ኤ.አ. በግንቦት 10 ቀን 2013 ወደ ኤርትራ የሚጓዙ የአሜሪካ ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያርጉ የሚያሳስብና ከተቻለ ወደ ኤርትራ ጉዞ እንዳያደርጉ የሚመክር የማሳሰቢያ መልዕክት በዚሁ ሳምንት በድጋሚ ለዜጎቹ አስተላልፏል።
“የኤርትራና የአሜሪካ ጥምር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ያስራቸዋል። ስለታሰሩ ዜጎች ከአሜሪካ መንግስት ማብራሪያ ሲጠየቅም ምላሽ አይሰጥም። አስመራ የሚገኘውም የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጎቹ መታሰራቸውን ሰምቶ ማብራሪያ ለአስመራ መንግስት ቢያቀርብም ምላሽ አይሠጥም” ሲል መግለጫው ተቃውሞውን አሰምቷል።

በተለይ እ.ኤ.አ. ከ2012 ጀምሮ የኤርትራ መንግስት በግለሰብ ደረጃ ዜጎቹን አውቶማቲክ መሳሪያ በማስታጠቁ በቀላሉ የአሜሪካ ዜጎች ለአደጋ ተጋላጭ ይሆናሉ ከሚል ስጋት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ታጣቂዎች በአስመራ ከተማ ሚሊሽያ በሚል ስለሚታወቁ ማንኛውንም ሰው በፈለጉት ቦታና ሰዓት መፈተሽ ይችላሉ። በዚህም የተነሳ በአስመራ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻና የሃይማኖት ቦታዎች ለመጎብኘት የሚመጡ የአሜሪካ ዜጎች በእነዚህ ታጣቂዎች ላይ ሊደርስባቸው ከሚችለው ስጋት ለመዳን ከአሜሪካ መንግስት ዕውቅና ውጪ እንዳይንቀሳቀሱ መግለጫው አሳስቧል።
በኦክቶበር 3 ቀን 2013 በላምባዱሳ ለተሰውት 350 ኤርትራዊያን ማስታወሻ በተደረገ ስነ-ስርዓት በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር አካባቢ ኤርትራዊያን በመንግስታቸው ላይ ባሰሙት ቅሬታ ከፍተኛ ተቃውሞ መቀስቀሱ የሚታወቅ ነው።፡

የኢሳያስ አፈወርቂ ጤና መሻሻል ካላመጣ በአስመራ ወታደራዊ ባለስልጣናት መካከል የስልጣን ሹኩቻ መነሳቱ አይቀርም ሲሉ የዲፕሎማቲክ ምንጮቻችን ለሰንደቅ ጋዜጣ አስተያየታቸውን ገልፀዋል። አያይዘውም፤ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላምም የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ብለዋል።
የተባበሩት መንግስታት እ.ኤ.አ. 2009 የአስመራ መንግስት በሚከተለው የትርምስ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ መነሻነት በኤርትራ መንግስት ላይ ባስተላለፈው ማዕቀብ የተነሳ እስከ ዛሬ ድረስ የአስመራ መገናኛ ብዙሃን በአሜሪካ መንግስት ላይ ከፍተኛ የስም የማጥፋት ፕሮፖጋንዳ እየፈጸመ መሆኑ ይታወቃል።

Wednesday, November 20, 2013

Henok Semaegzer, Missing from Action and Misinforming the Public

November 20, 2013

The job of journalist is to Report what he or she sees. Ethiopians in Saudi Arabia have been under attack for almost two weeks now.The Arab media is calling them “rioters”. The lynching, the chopping of victims and badly beaten can be seen on social medias. Women were gang raped and the families of victims were heard crying and ask for help. They were all in Saudi Arabia not from another planet.Henok Semagzer yesterday on VOA was quoting the Saudi's
Henok Semaegzer yesterday on VOA was quoting the Saudi’s and tell the VOA listeners that “the killers are not Saudis and the crime is not in Saudi Arabia”. What a shame ??? The job of journalist is to have courage and report from the crime area than looking for an expert of “Middle East and Africa” from Columbia University in New York. If he reports from distance to do his research diligently.
I am ashamed of VOA that has enough resource for not sending its journalists to Saudi to visit the victims in jails, “concentration camp” and those who are hiding in their homes in Saudi Arabia.
Henok Semaegzer failed to research the video footage before airing the alleged claim by Saudi official. I have not heard anything like that from those who are reporting from Saudi Arabia, foreigners or Ethiopians.
Henok needs professional help to understand the crime area from distance if he has no courage to travel to Saudi Kingdom of Shame. Stop being a propaganda machine of Al Amoudi.
BeMakber,
Tedla Asfaw

በግጭት መካከል የሚሰራ ጋዜጠኛና ለመረጃ ፍቅር ያለው ዜጋ ህይወት

November 20/2013

 ዛሬ ሳውዲ አረቢያ በተለይም በመንፉሃ ሪያድ የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ መረጃዎችን ስንለዋዎጥ ባጅተናል ። አሰቃቂውን የወገን ጉዳት አብረን አውግዘን ፣ ወገኖቻችን ደራሽ ያገኙ ዘንድ ኢትዮጵያውያን ከአጽናፍ እስከ አጽናፍ በመላ አለም ያሰማነው ድምጽ ፍሬ አፍርቷል ! ደስ ሲል …  በሁከቱ የተፈጠረውን ችግር ፣ የፈሰሰውን እንባና ደም የአይን ምስክሮችን በአካል ላነጋገረና ህመሙን ሲታመም ለከረመ የእኔ ቢጤ ዛሬ የተገፊው ወገን ችግሮች ተቀርፈው ማየትና መስማት ቢችል ከምንም በላይ እንደሚያስደስት ቃላት የሚገልጹት አይሆንም!  ከሁከቱ ዋዜማ ጀምሮ በሁከቱና ከሁከቱ በኋላ ባሉት ቀጣይ ቀናት የእለቱን ክንዋኔ በቅርብ  ተከታትየዋለሁ ። ሁከቱ ሲግም “ጋመ !”  በማለትና ወገን ግፍ ሲበዛበት የዋይታ ድረሱልኝ ድምጹን የማሰማቴን ያህል ሃገር ሰላም ሲሆን መረጃ አጣቅሸ ” ሃገሩ አማን ነው! ጸጥ ረጭ ብሎ ረግቷል ” አላለሁ  … ይህን ሳደርግ ተቃውሞና ድጋፉ በሁሉም አቅጣጫ እንደ ጎርፍ ይወርድኛል  !  ይህን መሰሉን ኑሮ ከወጣትነት እስከ ጎልማሳነት የጋዜጠኝነት እድሜየ የገጠመኝ መሰናክል፣ የኖርኩበትና የማውቀው በመሆኑ አልደነቀኝም!


      ይህን ሁለት ሶስት ቀን በሳውዲ አረቢያ ዋና ከተማ ሪያድ ውስጥ በምትገኘውንና ብዙ ኢትዮጵያውያን የሚኖሩባት የነበረችውን የመንፉሃን መንደር ጨምሮ በመላ ሪያድ የሚገኙትን ከስልሳ በላይ መጠለያዎች ሁኔታ በቅር እከታተላለሁ ። በጅዳ መካና በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍ  ስላለው እንቅስቃሴ  ከተለያዩ የማህበረሰቡ አካላትና በተለይም በጊዜያዊ እስር ቤት ያለውን ጭብጥ መረጃዎችን አገኛለሁ ።  ነባራዊ የዜጎቻችን አያያዝና እየሆነ ያለውን ከክስተቶች ጋር ገምግሜ ተደጋጋሚ መረጃዎች ማቅረቤ ያልተመቻቸው ” ይህን ሶስት ወን የምታቀርበው ተረጋግቷል የሚል መረጃ አይመችም  ፣  ይህም  ከታች ያሉት እንዳይረዱ አንቅስቃሴውን አበረድከውሳ? ! ” በሚል የሰላ ወቀሳ አቅርበውልኛል ። የመንግስት ደጋፊዎች ደግሞ በአንጻሩ  በአንጻሩ “መንግስት እየወሰደው ያለውን እንቅስቃሴ አትዘግብም !” በማለት ይቃወሙኛል። አንዳንዴማ ሙግታቸውን ያወርዱታል። በሳውዲ ሪያድ መንፉሃ የቤት ለቤት አሰሳ ዝርፊያ ፣ማሳደድ ፣ድብደባ፣ ሴቶችን የመድፈር እና የግድያው ጥቃት በእኛ ላይ ህግና መመሪያ ተጥሶ መሆኑ ግንዛቤ ሳይኖራቸው ቀርቶ ይሁን አውቀው ” በሳውዲ በእኛ ላይ የተለየ የተወሰደ እርምጃ የለም! ” ብለው ቅር ያሰኙኝን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ብቻ “አወድስ !” ለማለት ይከጅላቸዋል። በትዊተር ጠቃሚ መረጃን የሚሰጡን ዶር ቴዎድሮስ አደሃኖም  ድምጻቸውን እስካሁን ካልሰማነው ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለ ማርያም ደሳለኝ የተሻለ እንቅስቃሴ አድርገዋል ብልም ለአሁኑ ችግር መንስኤ መስሪያ ቤታቸው ድርሻ አለው ለምለው እማኝ ሚኒስትሩ ጥሩ ሰሩ እንኳ ቢባል ብቻቸውን ስራውን እየሰሩት እንዳለ ተደርጎ አድሃኖምን በመለስ ቦታ ለማስቀመጥና ” ለማምለክ !” እየተኬደ ያለው ፕሮፖጋንዳ በስራየ ላይ ተጽዕኖ እንዲያደርግ ይሞክራሉ።  ከሁሉም የሚደንቀው በስልጡኑ ሚኒስትር ዶር ቴዎድሮስ የሚመሩት የሳውዲ አረቢያ ዲፕሎማቶች መረጃን አልቀበል አልሰጥ እያሉ ፍዳችን እያሳዩን ነው!
አዎ !  ዛሬም ነገም በግጭት መካከል የሚሰራ ጋዜጠኛ ኑሮ ከዚህ ያለፈ አይደለም !   … ትናንት ምሽት ካንድ ብርቱ ወዳጀ ለስለስ ብሎም ቢሆን የተሰነዘረብኝ ወቀሳ ግን ከዚህ በፊት ሞነጫጭሬያት የነበረችን የማለዳ ወጋወግ ሳብ አድርጌ ይህን መግቢያ ሰርቸ ወደ እናንተ እንዳደርሰው ምክንያት ሆነኝ  …  በግጭት መካከል የሚሰራ ጋዜጠኝነት ህይወት እንዲህ ነው!
መረጃ ስላለው ጠቀሜታ ያለኝ እምነት ጽኑ ነው፡፡ ይህ በመሆኑም የግል ፍላጎቴ ሆኖ በአረቡ አለም በሀገሬንና በዜጎቻችን ዙሪያ  የሚለቀቁ መረጃዎችን በቅርበት እከታተላለሁ ! የማገኘው መረጃ ትክክለኛ ለመሆኑ አስቀድሜ እጠነቀቃለሁ ፡፡ ተገቢ መረጃዎችን አሰባስባለሁ ፡፡ የዜናውን ክብደትና አስፈላጊነት አውጥቸ አወርዳለሁ ! ከዚያም እውነታው እንዲህ ነው ብየ መረጃን በትክክል ማግኘት ላለበት ወገኔ አቀርባለሁ፡፡ ዋናው ቁምነገር የያዝኩት መረጃ  እስከሆነ ድረስ የሚያሳስበኝ ነገር የለም ! ሁሉንም መረጃዎች ማቅረብ ባልችልም ይጠቅማሉ የምላቸውን መረጃዎች ለማካፈል ጥረት አደርጋለሁ፡፡  በአረብ ሃገር እንደ ሌላው ሃገር መረጃን ለማድረግ ቀላል አይደለም፡፡ ብዙ ድካም አለው ፡፡ ያም ሆኖ አስቸጋሪ የሆነው ውስብስብና አደገኛ የመረጃ ስብሰባ እኔን አያደክመኝም ! አይታክተኝምም  !
     መረጃውን ከወዲያ ወዲህ ቧጥጨና ፈልፍየ “እውነቱ ይህ ነው !” ስል የሚሰማኝ የደስታ ስሜት ከምንም በላይ ነው !  አዎ መረጃዎችን ሳቀርብ ከፊትና ከኋላ የሚሰነዘርበኝ በጎና በጎ ያልሆኑ አስተያየቶች መጠነ ሰፊ ናቸው፡፡  ባንድ ወቅት የማቀርበውን የሚወዱት በሌላ ጊዜ ይቃዎሙታል ! እኔኑ እንደ ግለሰብም ይጠሉኛል ብቻ ሳይሆን ድምጥማጤን ለማጥፋት ምለው ይገዘታሉ ! አንዳንዴ ደግሞ ይቃወሙኝ የነበሩት ያቀረብኩት መረጃ እንዳስደሰታቸው መጠን ይደግፉኛል ! ያሞካሹኛልም ! ይህ ሁሉ መረጃውን በአየር ላይ ባቀረብኩ ቅጽበት የሚስተዋል እውነታ ነው፡፡  ይህ ሁሉ ሲሆን እኔ የማንም ድርጂት አባልና ተቀጽላ ሆኘ ከማንም እንቅስቃሴ ላይ ቀዝቃዛ ውሃ  ለመቸለስና የማንንም ትግል ለማኮሸት አይደለም፡፡ የሚሰማኝ እንደ ዜጋና እንደ ባለሙያ መረጃ ማቀበሌ ብቻ ነው የማውቀው ! ብዙዎች የሚደሰቱበትን መረጃ አቀብየ ሁሉንም ደስ ላሰኝ አልልም ፣ ብዙዎች ሲደሰቱ በእርኩስ መንፈስ ደስታቸውን ለማደፍረስና አንገታቸውን እንዲደፉ አስደናጋጭ መረጃ ማቀበሉንም ነፍሴ ፍጹም አይፈቅደውም  !
      በመረጃ ቅበላው ዙሪያ አንዱን ወገን በማደሰትና ሌላውን በማስከፋት የመረጃ ፍሰቱን ላዛባው ህሊናየ አይፈቅድም ! የምወደው ሙያ ነውና ላረክሰውም አልሻም ! ይህ እስከሆነ ድረስ የማቀርበው መረጃ እውነተኛ ድርጊቱን እስከ ሆነ ድረስ ሁሉንም የሁሉንም ስሜት በአንድነት መግዛት አይቻለውምና የተቃውሞም ሆነ የድጋፍ አስተያየቶች ማስተናገድ ግድ ይላል ፡፡ ሁሉም በአግባቡና በጨዋ መንፈስ በየፈርጁ ሲቀርቡ ያስደስቱኛል !  ግርታን ይፈጥራሉ ለምላቸውና መልስ ለሚያስፈልጋቸው መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ ! እንዲህ እየሆነ የጎልማሳነት እድሜየን ገፍቻለሁና ለምጀዋለሁ ! በግጭት መካከል የሚሰራ ነጻ ጋዜጠኛና ለመረጃ ፍቅር ያለው ዜጋ ህይዎት ደግሞ ከዚህ ያለፍ ሊሆን አይጠበቅም ! አይችልምም !
እስኪ ቸር ያሰማን !

በነቢዩ ሲራክ



Tuesday, November 19, 2013

በቺካጎ እና አካባቢዋ የሳኡዲ አረቢያን ግድያ አስመልክቶ ከፍተኛ የሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ተከናወነ !

November19/2013

በዛሬው እለት በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያኖች የተካሄደው ይሄው ተቃውሞ ከቶምሰን ህንጻ (ከከተማው ከንቲባ ራሃም ኢማኑኤል ቢሮ )ጀምሮ የጎዳና ላይ ሰላማዊ ሰልፍ እና የዜጎቻችን መብት እና ክብር ይጠበቅ በሚል የተጀመረው የተቃውሞ ሰልፍ በደማቅ ሁኔታ ተጀምሮ በደማቅ ሁኔታ እንዳለቀ እንዲሁም የቺካጎ እና አካባቢዋንም ህብረተሰብ ያስደነቀ ልዩ ትእይንት እንደነበር ለማወቅ ተችልአል ። እንደ ማለዳ ታይምስ ዘጋቢ መረጃ ከሆነ በወቅቱ የተካሄደው ይሄው ሰላማዊ ሰልፍ ከመንግስት እና ከተቃዋሚ አባላቶች መካከል ጥቂቶቹ እንደተገኙ እና በሰልፉ ላይ ድምጻቸው እንዳሰሙ ተገልጾአል ።በወቅቱ የተካሄደው ይሄው ሰላማዊ ሰልፍ ከመንግስት እና ከተቃዋሚ አባላቶች መካከል ጥቂቶቹ እንደተገኙ እና በሰልፉ ላይ ድምጻቸው እንዳሰሙ ተገልጾአል ።

በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የቺካጎ እና አካባቢዋ የሚገኙ ወጣቶች በመሰባሰብ ድምጻቸውን ለስቴት ዲፓርትመንቱ ለማሰማት ከፍተኛ ጥረት ከማድረጋቸውም በላይ በተለያዩ የአሜሪካ ሚዲያዎች ላይ የአየር ሰአት አግኝቶ የሳኡዲውን ንጉስ አብደላን ለመውቀስ ያስችል ዘንድ ለመገናኛ ብዙሃኖች ጥሪ ቢደረግም በትላንትናው እና በዛሬው እለት በተካሄደው የተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ሪፖርተሮቻችን የተን ወደ ኢንዲያና እና ሌሎች ከተሞች ለሪፖርታዥ ስራ ሄደዋል ይህንን ጉዳይ ማንም ትተከታትሎ ሊሰራላችሁ አይችልም ሲሉ ተሰምተዋል ። ሆኖም ግን እንደተረዳነው ከሆነ ከሳኡዲ አረቢያ ጋር ያለቸውን የወዳጅነት ግንኙነት እና ጥቅም ላለማጣት የሚያደርጉት ትልቅ ጥረት መሆኑን ለመረዳት በቅተናል ።

በመላው አለም ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥትቶት የዜና ሪፖርት ሽፋን ሲያገኝ እና የኢትዮጵያኖች ድምጽ ሲሰማ በአሜሪካ ምድር ብቻ ይህንን ዜና ለመስራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው እስካሁን ድረስ የሳኡዲ ህዝብ በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ከፈጸሙ ጀምሮ አንዳችም ነገር ሪፖርታዥ ሊሰሩ እንዳልቻሉ በተግባርም አሳይተውናል ።ይህ በእነድዚህ እንዳለ በዚሁ በሰላማዊ ሰልፍ ላይ የሳኡዲ አረቢያ ተወላች የሆነ ወጣት በሰላማዊ ሰልፉ ላይ በመገኘት ሲገልጽ የህዝቡ ጉዳይ ሳይሆን ይህንን ነገር ያደረገው የመንግስቱ አስተዳደር ነው ብሎ ሳይጨርስ ህዝቡ በንዴት ወደ ድብደባ በማምራቱ በችሂካጎ ፖሊስ ዲፓርትመንት የእለቱ የሰልፉ አስከባሪዎች በቁጥጥር ስር ውሎ ህይወቱን ሊያተርፉት ችለዋል ። ይህ ወጣት ቀድሞ እንደገለጸው ከሆነ እኛም መንግስቱን እንቃወመዋለን ለተደረገው ነገር ሁሉ እናወግዛለን ሆኖም በኢትዮጵያኖች ላይ የተደረገውን ነገር ሁሉ አብረን እንድንቃወም በቅርቡ በጠራነው ሰልፍ ላይ ብትገኙልን ደስ ይለናል ብሎ ያቀረበውን ጥያቄ መሰረት በማድረግ  የድምጽ ማጉያው ቢሰጠውም ህዝቡ ፋታ ሳይሰጠው ወደ ድብደባ ማምራታቸው ተገቢ አልነበረም ሲሉ አንዳንድ ነዋሪዎች ተቃዎሞአቸውን አሰምተዋል ።


በዛሬው እለት ከዋሽንግተን ዲሲ ጀምሮ እንግሊዝ ፣ቺካጎ እና ሌሎችም አለማት ላይ የተደረጉት የተቃውሞ ሰልፎች ከፍተኛውን ድምጽ ያገኛል ተብሎ የሚታሰብ መሆኑ ይህ በሃገራችን ላይ የሚደረገውን ጥቃት  ለመከላከል የሚያሳይ ትልቅ እመርታ እንደሆነ በግልጽ ኢትዮጵያዊነታቸውን አሳይተዋል ። 




Monday, November 18, 2013

ጉዞ በኢሕአዴግ ዴሞክራሲ ባቡር

November 18/2013

መድረክ ህዳር 8 ቀን 2006 ዓ . ም በአረብ ሃገር የሚገኙ ወገኖቹን ድምፅ ለማሰማት በአ / አበባ ሳውዲ ኤምባሲ ቅዋሜ ለማቅረብ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ መከልከሉን ሰማሁ . ምን መስማት ብቻ የአ / አበባ መስተዳድርን የክልከላ ደብዳቤ አነበብኩት . የክልከላ ደብዳቤው በከፊል እንዲህ የሚል ነው , -

" ሆኖም ግን በዕለቱ በከተማዋ ተደራራቢ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎች በማካሄድ ላይ ያሉ እና በቅርቡም ለማካሄድ ዝግጅት ያጠናቀቁ ስለ አሉ እውቅና የተጠየቀበትን የሰላማዊ ሰልፍ ተገቢውን የፖሊስ ጥበቃ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመኾኑ የተጠየቀውን የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መኾኑን እንገልጻለን . "

ገርሞኝ የክልከላ ደብዳቤውን ደጋግሜ አነበብኩት . ደጋግሜ ባነበብኩት ቁጥር የ " ዲሞክራሲያችን ባቡር " ጉዞ ታሰበኝ . " ዲሞክራሲ " እና " ባቡር " የሚባሉት ቃሎች ደግሞ የአሜሪካንን ተረት አስታወሱኝ . ምነው ቢሉ ? በዲሞክራሲ መንገድ ከ 200 ዓመት በላይ የተጓዘች አሜሪካ ነቻ - እንደነገሩን . ታዲያ ከእነሱ ተረት ካላጣቀስን ከማን ልናጣቅስ ነው ? ሆሆሆ .... !

የሆኖ ሆኖ እንደተረታቸው እንተርት .

አሜሪካኖቹ በባቡር እየተጓዙ ነው አሉ . ጉዞው 24 ሰዓት ሙሉ ካለዕረፍት የሚደረግ ነው ; እረፍት ቅብርጥሴ ; አቁሙልኝ .... ምናምን ብሎ ነገር የለም . በዚህ የተነሳ ሁሉም የራሱን ስንቅ ይዟል . አናም ባቡሩ ጉዞውን ቀጥሏል .... ጠዋት የተነሳው ባቡር እኩለ ቀን አጋመሰ . የምሳ ሰዓት ደረሰ . ሁሉም ሰው ምሳውን አውጥቶ መብላት ጀመረ . የአጋጣሚ ነገር ሆኖ ከአንድ ሰው በቀር ሁሉም አንድ ዓይነት ምግብ ነው የሚመገበው . ያ ብቸኛ ሰው ግን ምሳውን አሳ ነው የያዘው . ደግሞም አበላሉ ቄንጠኛ ነው . አሳውን ያወጣና ጭንቅላቱን ቅንጥስ አድርጎ ለብቻ ያስቀምጥና ሌላውን ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል . እንደገና ሌላ አሳ ያወጣና ጭንቅላቱን ቆርጦ ያስቀምጥና የተቀረውን የአሳ ክፍል ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል .

በዚህ አበላሉ የተገረመው አጠገቡ የተቀመጠው ሰውዬ አሳ በሊታውን እንዲህ አለው -

" የአሳው ጭንቅላት ይበላል እኮ "

" አውቃለሁ " አለ አሳ በሊታው . " የአሳ ጭንቅላት ከአፉ ጀምሮ ኩርሽምሽም እየተደረገ እንደሚበላ አውቃለሁ "

" ታዲያ ለምን አትበላውም ? "

" ጭንቅላቱን የማልበላው ; ልሸጠው ስለፈለግኩ ነው " አለ - በኩራት .

" ለማን ነው የምትሸጠው ? "

" ጭንቅላታቸው ለማይሰራ ! "

ይኼኔ ጠያቂው ሰውዬ አሰበ . አሰበ አሰበና እንዲህ አለው -

" ታዲያ ለምን እኔ አልገዛህም "

" ይቻላል ! "

" ስንት ስንት ነው የምትሸጠው ? "

" ሁለት ሁለት ዶላር "

በዚሁ ተስማሙ . እናም ተገበያዩ . ገዢው አንዱን የአሳ ጭንቅላት አነሳና ከአፉ ጀምሮ መኮርሸም ጀመረ . አንዱን የአሳ ጭንቅላት እየበላ ግማሹ ላይ ሲደርስ አንዳች ነገር ታወሰውና ወደ ሻጩ ዞር አለና እንዲህ ሲል ጠየቀው -

" ግን አንተ ሙሉውን አሳ ስንት ነው የገዛኸው ? "

" አንድ ; አንድ ዶላር ..... "

ይኼኔ ገዢው ተናደደ . በንዴት " እንዴት ታታልለኛለህ " እያለ ተንጨረጨረ .

ገዢው እየደጋገመ " እንዴት ታታልለኛለህ ? " እያለ ሲንጨረጨር ሻጩ የሰጠው መልስ ነው የተረቱ መቋጠሪያው .

" ምን አታልልሃለሁ ! ይኸው ጭንቅላትህ ሰራ ! " የሚል ምላሽ ነበር የሻጩ ምላሽ .

እና እኔ ይህን ተረት ለምን መጥቀስ ፈለግኩ ?

ኢህአዴግ ባለፉት በርካታ ዓመታት ስለዲሞክራሲ ምሉዕነት ሲጠየቅ , " የዲሞክራሲ ጉዞ ረዥም ነው " የሚል መልስ ነበር የሚሰጠው . በሌላ አገላለፅ " በዲሞክራሲ ሥርዓት ባቡር ውስጥ ነን ; ጉዞውን ለመፈፀም ረዠም ርቀት መጓዝ ያስፈልጋል ," ሲለን ነበር .

የሆኖ ሆኖ የዲሞክራሲው ባቡር በተባለው ጉዞ ውስጥ ተሳፈርን . ተጓዝን . ተጓዝን . ተጓዝን . የኢህአዴግ ዲሞክራሲ መቁረስ ላይ ታደምን .

ከዚያስ ?

እኛ አሳ ይዘን ተገኘን .

ኢህአዴግ " ልግዛችሁ " አለን .

እኛም " ግዛን " አልነው .

ከ " ገዛን " በኋላ " ምን ታታልኙላችሁ " እያለ የሚንጨረጨር ይመስላል - ኢህአዴግ .

ከላይ በተረቱ ውስጥ የአሳ ጭንቅላት የገዛው ሰውዬ ስህተቱ አንድ እና አንድ ነው . የሙሉውን አሳ ዋጋ አስቀድሞ አለመጠየቁ ነው ስህተቱ . የኢህአዲግም ስህተት ተመሳሳይ ነው . የሙሉውን ዲሞክራሲ ዋጋ በውል ለይቶ አለማወቁ ነው . ስለዚህ ነው ሰባራ ሰንጣራ ሰበብ እየፈለገ የዲሞክራሲውን ጉዞ በክልከላ የሚያጅበው .

ስለዚህ ኢህአዴግና ኢሕአዴጋውን ከሁሉ አስቀድሞ ይህ የክልከላ ዲሞክራሲ ባቡር ጉዞ መጨረሻው የት ነው ? ብለው ራሳቸውን ቢጠይቁ ነው የሚሻለው .

እንደው ለማለት ያህል እንጂ ; ............ ?
================= ጉዞ በኢሕአዴግ ዴሞክራሲ ባቡር ============

መድረክ ህዳር 8 ቀን 2006 ዓ . ም በአረብ ሃገር የሚገኙ ወገኖቹን ድምፅ ለማሰማት በአ / አበባ ሳውዲ ኤምባሲ ቅዋሜ ለማቅረብ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ መከልከሉን ሰማሁ . ምን መስማት ብቻ የአ / አበባ መስተዳድርን የክልከላ ደብዳቤ አነበብኩት . የክልከላ ደብዳቤው በከፊል እንዲህ የሚል ነው , -

" ሆኖም ግን በዕለቱ በከተማዋ ተደራራቢ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎች በማካሄድ ላይ ያሉ እና በቅርቡም ለማካሄድ ዝግጅት ያጠናቀቁ ስለ አሉ እውቅና የተጠየቀበትን የሰላማዊ ሰልፍ ተገቢውን የፖሊስ ጥበቃ ለማካሄድ አስቸጋሪ በመኾኑ የተጠየቀውን የሰላማዊ ሰልፍ ጥያቄ ተቀባይነት ያላገኘ መኾኑን እንገልጻለን . "

ገርሞኝ የክልከላ ደብዳቤውን ደጋግሜ አነበብኩት . ደጋግሜ ባነበብኩት ቁጥር የ " ዲሞክራሲያችን ባቡር " ጉዞ ታሰበኝ . " ዲሞክራሲ " እና " ባቡር " የሚባሉት ቃሎች ደግሞ የአሜሪካንን ተረት አስታወሱኝ . ምነው ቢሉ ? በዲሞክራሲ መንገድ ከ 200 ዓመት በላይ የተጓዘች አሜሪካ ነቻ - እንደነገሩን . ታዲያ ከእነሱ ተረት ካላጣቀስን ከማን ልናጣቅስ ነው ? ሆሆሆ .... !

የሆኖ ሆኖ እንደተረታቸው እንተርት .

አሜሪካኖቹ በባቡር እየተጓዙ ነው አሉ . ጉዞው 24 ሰዓት ሙሉ ካለዕረፍት የሚደረግ ነው ; እረፍት ቅብርጥሴ ; አቁሙልኝ .... ምናምን ብሎ ነገር የለም . በዚህ የተነሳ ሁሉም የራሱን ስንቅ ይዟል . አናም ባቡሩ ጉዞውን ቀጥሏል .... ጠዋት የተነሳው ባቡር እኩለ ቀን አጋመሰ . የምሳ ሰዓት ደረሰ . ሁሉም ሰው ምሳውን አውጥቶ መብላት ጀመረ . የአጋጣሚ ነገር ሆኖ ከአንድ ሰው በቀር ሁሉም አንድ ዓይነት ምግብ ነው የሚመገበው . ያ ብቸኛ ሰው ግን ምሳውን አሳ ነው የያዘው . ደግሞም አበላሉ ቄንጠኛ ነው . አሳውን ያወጣና ጭንቅላቱን ቅንጥስ አድርጎ ለብቻ ያስቀምጥና ሌላውን ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል . እንደገና ሌላ አሳ ያወጣና ጭንቅላቱን ቆርጦ ያስቀምጥና የተቀረውን የአሳ ክፍል ቅርጥፍጥፍ አድርጎ ይበላል .

በዚህ አበላሉ የተገረመው አጠገቡ የተቀመጠው ሰውዬ አሳ በሊታውን እንዲህ አለው -

" የአሳው ጭንቅላት ይበላል እኮ "

" አውቃለሁ " አለ አሳ በሊታው . " የአሳ ጭንቅላት ከአፉ ጀምሮ ኩርሽምሽም እየተደረገ እንደሚበላ አውቃለሁ "

" ታዲያ ለምን አትበላውም ? "

" ጭንቅላቱን የማልበላው ; ልሸጠው ስለፈለግኩ ነው " አለ - በኩራት .

" ለማን ነው የምትሸጠው ? "

" ጭንቅላታቸው ለማይሰራ ! "

ይኼኔ ጠያቂው ሰውዬ አሰበ . አሰበ አሰበና እንዲህ አለው -

" ታዲያ ለምን እኔ አልገዛህም "

" ይቻላል ! "

" ስንት ስንት ነው የምትሸጠው ? "

" ሁለት ሁለት ዶላር "

በዚሁ ተስማሙ . እናም ተገበያዩ . ገዢው አንዱን የአሳ ጭንቅላት አነሳና ከአፉ ጀምሮ መኮርሸም ጀመረ . አንዱን የአሳ ጭንቅላት እየበላ ግማሹ ላይ ሲደርስ አንዳች ነገር ታወሰውና ወደ ሻጩ ዞር አለና እንዲህ ሲል ጠየቀው -

" ግን አንተ ሙሉውን አሳ ስንት ነው የገዛኸው ? "

" አንድ ; አንድ ዶላር ..... "

ይኼኔ ገዢው ተናደደ . በንዴት " እንዴት ታታልለኛለህ " እያለ ተንጨረጨረ .

ገዢው እየደጋገመ " እንዴት ታታልለኛለህ ? " እያለ ሲንጨረጨር ሻጩ የሰጠው መልስ ነው የተረቱ መቋጠሪያው .

" ምን አታልልሃለሁ ! ይኸው ጭንቅላትህ ሰራ ! " የሚል ምላሽ ነበር የሻጩ ምላሽ .

እና እኔ ይህን ተረት ለምን መጥቀስ ፈለግኩ ?

ኢህአዴግ ባለፉት በርካታ ዓመታት ስለዲሞክራሲ ምሉዕነት ሲጠየቅ , " የዲሞክራሲ ጉዞ ረዥም ነው " የሚል መልስ ነበር የሚሰጠው . በሌላ አገላለፅ " በዲሞክራሲ ሥርዓት ባቡር ውስጥ ነን ; ጉዞውን ለመፈፀም ረዠም ርቀት መጓዝ ያስፈልጋል ," ሲለን ነበር .

የሆኖ ሆኖ የዲሞክራሲው ባቡር በተባለው ጉዞ ውስጥ ተሳፈርን . ተጓዝን . ተጓዝን . ተጓዝን . የኢህአዴግ ዲሞክራሲ መቁረስ ላይ ታደምን .

ከዚያስ ?

እኛ አሳ ይዘን ተገኘን .

ኢህአዴግ " ልግዛችሁ " አለን .

እኛም " ግዛን " አልነው .

ከ " ገዛን " በኋላ " ምን ታታልኙላችሁ " እያለ የሚንጨረጨር ይመስላል - ኢህአዴግ .

ከላይ በተረቱ ውስጥ የአሳ ጭንቅላት የገዛው ሰውዬ ስህተቱ አንድ እና አንድ ነው . የሙሉውን አሳ ዋጋ አስቀድሞ አለመጠየቁ ነው ስህተቱ . የኢህአዲግም ስህተት ተመሳሳይ ነው . የሙሉውን ዲሞክራሲ ዋጋ በውል ለይቶ አለማወቁ ነው . ስለዚህ ነው ሰባራ ሰንጣራ ሰበብ እየፈለገ የዲሞክራሲውን ጉዞ በክልከላ የሚያጅበው .

ስለዚህ ኢህአዴግና ኢሕአዴጋውን ከሁሉ አስቀድሞ ይህ የክልከላ ዲሞክራሲ ባቡር ጉዞ መጨረሻው የት ነው ? ብለው ራሳቸውን ቢጠይቁ ነው የሚሻለው .

እንደው ለማለት ያህል እንጂ ; ............ ?

የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስደተኛ እንጂ ህገወጥ/ወንጀለኛ ዜጋ የለንም:

November 18/2013

- ይህ በአለም ላይ የማይካድ እውነት ነው :: ምንም ከሃገሩ ካለምክንያት አይሰደድም የአንድን ሃገር ድንበርም ጥሶ ካለምክንያት አይዘልቅም :: ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንገዶች ወደ አረብ አገራት ገብተዋል :: የይልፍ ወረቀት ገዝተው በአየር የወጡትን ጉዳይ ለጊዜው ተወት እናድርገው እና ​​በዛሬው ወቅት ህገወጥ እየተባሉ በአረቦቹ እና በስርኣቱ መሪዎች ስለሚወነጀሉት ኢትዮጵያውያን አጠር ያለ ነገር እናንብብ ::

ወደ አረብ አገራት የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን በሁለት ይከፈላሉ እነዚህ ስደተኞች አብዛኛዎቹ በባህር አቋርጠው እና አስቸጋሪ ፈተናዎችን አልፈው በሰላም ወደ ፈለጉበት የደረሱ የሸሹ የተደበቁ እጅግ አሳዛኝ ዜጎች ናቸው :: በሁለት ከፍለን ስናያቸው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስደተኞች ብለን እናስቀምጣቸዋለን : ; እነዚህ የሁለት ፈርቅ ስደተኞች በጅቡቲ እና በሱማሌላንድ ወደቦች በጀልባዎች ተጭነው የተረፈ ተርፎ የገባ ገብቶ አሁን ላሉበት ሁኔታ ደርሰዋል :: እስኪ ከፍለን እንመልከታቸው

የፖለቲካ ስደተኞች
እንዚ የፖለቲካ ስደተኞች በብዛት የተሰደዱት ከኦሮሚያ ክልል ሲሆን እነዚህ ኢትዮጵያዊ ስደተኞች በተለያየ ጊዜ የእነግ አባላት ናችሁ የኦነግ ጦር ረዳቶች ናችሁ ኦነግን ትደግፋላችሁ በሚል የተለያዩ ችግሮች እና መከራዎች ሲደርሱባቸው ድብደባ እና እስር ሲፈጸምባቸው ይህንን በመሸሽ እንዲሁም የቤተሰቦቻቸውን እና የራሳቸውን የእርሻ መሬት ሲነጠቁ የስራ እድላቸው በፖለቲካ እምነታቸው ሲጋረድባቸው ስርኣቱ በፈጠረው የፖለቲካ ጫና ቤተሰብ ማስተዳደር ሲሳናቸው ወደ የመን ሳኡድ አረቢያ ደቡብ አፍሪካ እና የተለያዩ አገሮች በምድር ጉዞ ይሰደዳሉ : ; እንዲሁም ሴት ልጆች በቤተሰባቸው ላይ ፖለቲካው የፈጠረን ጫና ለማሸነፍ ሲሉ እንዲሁ ይሰደዳል :: እንዚህ የፖለቲካ ስደተኞች ራሳቸውን ለማሸነፍ ሲፍጨረጨሩ ህገወጥ ወይንም ወንጀለኛ አድርጎ ማየት ሃላፊነት የጎደለው አስተሳሰብ ነው ::

የኢኮኖሚ ስደተኞች
በሃገሪቱ የተንሰራፋው የዘረኝነት ጁንታ አብዛኛው ህብረተሰብ እንዳይሰራ ግሬጣ ከመሆኑም በላይ የፖለቲካው አናት የንግድ ድርጅቶቹን በማስፋፋት በሃገሪቱ አንጡረ ሃብት እየተጫወታ ዜጎችን ለድህነት አገሪቱንም ለድቀት ዳርጓል :: የሃገሪቱ የትምህርት ጥራት ትውልድ እንዳያፈራ ተደርጎ አመድ ከተለወሰ በኋላ የስራ አጥ ቁጥሩ በእጥፍ ጨምሯል :: የምእራባውያኑ የገንዘብ ተቋማት የአፍሪካን እድገት ስለማይፈልጉ አምባገነንነትን በማበረታታት የሃሰት ፕሮፓጋንዳ ይነዛሉ :: እንዲሁም እንደ ቻይና የመሳሰሉት አገራት ከቀን ሰራተኛ ጀምሮ በተለያዩ ለውጪ ዜጎች በማይፈቀድ የስራ ዘርፍ ተሰማርተው የአገሪቱን ወጣት በስራ አጥነት እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ አድርገውታል :: ይህ አይነቱ መንግስት ባለስልጣናት ነጋዴነት ሙሰኝነት የውጪ ዜጎች ካለደረጃቸው ዝቅ ብለው የሚበጠብጡት የስራ እድል አሻሚነት ተደማምሮ በአመት ከ 800,000 በላይ ስራ አጥ ስለሚፈጠር የስደት መንስኤ ሊሆን ችሏል :: ወደ አረብ አገራትም የሚሰደዱ ዜጎች የዚህ እና የተያያዥ የኢኮኖሚ ችግሮች ሰለባ ከመሆናቸውም በላይ ይህ ደግሞ የስርኣቱ ለዜጎች የኑሮ እድገት ግዴለሽነት ያመለክታል ::

ይህ በእንዲህ እንዳለ የብሄራዊ እፍረት መንስኤ የሆነው ስርኣት በሚከተለው የፖለቲካ እና የእኮኖሚ ፖሊሲ ምክንያት ዜጎች አገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ እና ለሞት ለእስር ለስቃይ እና ለመንገላታት እንዲዳረጉ ሚናውን ተጫውቷል :: ይህንን መፍትሄ ለማምጣት የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ስር ነቀል ለውጥ ያስፈልገናል በጋራ አገር ላይ በጋር እንድንሰራ እኛ እናውቅላቹዋለን የሚል ስርኣት ከነአካቴው ሊቆም እና ሃይ ሊባል ይገባዋል : ኢትዮጵያውያን በአረብ አገራት እየደረሰ ያለው መከራ የምን ውጤት ነው መፍትሄውስ ምንድነው ብለን ቆም ብለን የምናስብበት ጊዜ ነው :: ማወቅ ያለብን ነገር ቢኖር ስርኣቱ አሁንም ካለው እኩይ አድራጎቱ ሊቆጠብ ስለማይችል ነገ በሌላም አገር የምንኖር ኢትዮጵያውያን ችግሮች ቢደርሱብን የገዛ ዜጎቼ ሳይሆን የሚለው አብሮ ህገወጥ እና ወንጀለኛ ብሎ በመፈረጅ ለሞት እና ለስቃይ ከመዳለግ ወደኋላ ስለማይል የትግል አድማሳችንን በማስፋት ወንጀለኛው ህገወጡ በሃገሪቱ የተንሰራፋው ስርኣት መሆኑን የማጋለጥ ግዴታ አለብን ; ጎን ለጎንም የመፍትሄ ሰዎች እየሆንን ባለው ስርኣት ላይ ጫና በማሳደር መትጋት ድርሻችን ነው ::
ምንሊክ ሳልሳዊ 






Sunday, November 17, 2013

“እንግዲህ ብታስሩንም እሰሩን እንጂ የታሰሩብንን አባላት ወህኒቤት ሄደን መጠየቃችን አይቀርም” Girma seifu

November 17/2013

 
ባለፈው ሰሞን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት በሽብርተኝነት ዙርያ ያደረጉትን ውይይት —- ኢቴቪ ነፍሴ ስንቴ እንደደጋገመው አልነግራችሁም። (ውይይት በድጋሚ ይካሄዳል እንዴ?) እኔ የምለው ግን —- ኢቴቪ “የ24 ሰዓት ሥርጭት የጀመርኩት ቢቢሲ ኢንስፓየርድ አድርጎኝ ነው” እያለ ያስወራል የሚባለው ከምር ነው እንዴ? ቢቢሲ ይሄን ቢሰማ እኮ ኢቴቪን አይለቀውም፡፡ ያለአንዳች ምህረት ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ነበር የሚገትረው – እንደ አምባገነኖቹ የአፍሪካ መሪዎች። አሃ— ከ“ግድያ” የማይተናነስ የስም ማጥፋት እኮ ነው፡፡ እስቲ አስቡት— ሰው “በቢቢሲ ተነሽጬ ነው” ብሎ የ24 ሰዓት “የፕሮፓጋንዳ ጣቢያ” ይከፍታል እንዴ? ኢቴቪ ዶክመንተሪ ፊልሞችም የሚሰራው ቢቢሲን ሞዴል አድርጎ ነው ሲባል ሰምቼ አፌን ይዣለሁ፡፡ (እነ“ሃረካት” እና “አኬልዳማ” እኮ ናቸው ዶክመንተሪ የተባሉት!) አያችሁልኝ የእኔን ነገር — የጀመርኩትን ወግ አንጠልጥዬ ኢቴቪን መተግተግ ያዝኩ፡፡ ደግሞ እኮ የሚሰማ ቢሆን ግዴለም ቀስ እያለ ከስህተቱ ይማራል እንል ነበር፡፡ እሱ ግን “የነቀፈኝ ሁሉ ጠላቴ” ብሎ ሳይደመድም የቀረ አይመስለኝም፡፡ በሉ ወደ ዋናው ጉዳይ ሸርተት እንበል፡፡
እናላችሁ — በሽብርተኝነት ዙሪያ በተደረገው ውይይት ላይ በፓርላማ ብቸኛው የተቃዋሚ ተወካይ የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፤ እንደተለመደው ኢህአዴግ “ከእንግሊዝ ከእነኮማው ቀድቼዋለሁ” የሚለውን የፀረ-ሽብርተኝነት ህግ ሞገቱ ሞገቱና ሲያቅታቸው “እንግዲህ ብታስሩንም እሰሩን እንጂ የታሰሩብንን አባላት ወህኒቤት ሄደን መጠየቃችን አይቀርም” አሉ፤ በተስፋ መቁረጥ። ለነገሩ ይህቺን እግረመንገዴን አነሳኋት እንጂ ዋና ጉዳዬስ ሌላ ነበር፡፡ ይኸውላችሁ —- በዚሁ ውይይት ላይ ከኢህአዴግም ከተቃዋሚም ጎራ የማይመስሉ አንድ “ሃኪም ነኝ” ያሉ ተሰብሳቢ፤ አስገራሚ አስተያየት ሰነዘሩ፡፡ (ምናለ የጦቢያን ፖለቲከኞች ቢያክሙልን?!) “ሃኪም ብዙ ባይናገርም እኔ ግን እድሉን ካገኘሁ እናገራለሁ” ያሉት ተሰብሳቢው፤ “የሚኒስትርነት ሹመት የሚሰጠው የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙር በመዘመር ቢሆን ኖሮ አብዛኞቹ ሚኒስትሮቻችን ፈተናውን ይወድቁ ነበር” ሲሉ የኢህአዴግ ሚኒስትሮችን ሸነቆጡ፡፡ ሽንቆጣውን ተከትሎ በአዳራሹ ውስጥ ከዳር እስከዳር የተስተጋባው ሳቅ ግን ግራ አጋባኝ፡፡ (የራሳቸው የሚኒስትሮቹ ሳይሆን አይቀርም!) ሃኪሙ ሳቁ ገታ እስኪል ጠበቁና፤“ይሄ ሳቅ የተናገርኩት ነገር እውነት መሆኑን ያረጋግጥልኛል” አሉ፡፡
አሁንም ያው ሳቅ ተስተጋባ፡፡ ይኼኔ ጆሮዬን ተጠራጠርኩት። “የኢትዮጵያን ብሔራዊ መዝሙር ችላችሁ አትዘምሩትም ማለት ያስቃል እንዴ?” ስል ጠየቅሁ – ሚኒስትሮቹን ሳይሆን ራሴን፡፡ ትንሽ ቆይቼ ግን “ግዴለም– ይሳቁ!” አልኩኝ፡፡ (ባለሥልጣናት ሲስቁ አይቼ አላውቅማ!) አንድ ጥያቄ አለኝ፡፡ “ልማታዊ መንግስት” ሳቅ ላይ ያለው አቋም እንዴት ነው? እኔ የምለው ግን— ከሚኒስትሮቻችንና ከሌሎች የመንግሥት ሹመኞች መካከል ምን ያህሉ ብሄራዊ መዝሙራችንን በትክክል ጀምረው ይጨርሱታል? (ዶክተሩ ጉድ አፈሉ እኮ!) አይዟችሁ — መዝሙሯ የሹመት መስፈርት እንድትሆን “ሎቢ” የማድረግ ወይም “ፒቲሽን” የማሰባሰብ እቅድ የለኝም፡፡ አንዲት ከፓርላማ የማትጠፋ የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኛ (ይቅርታ “ነፃ ፕሬስ” የለም፤ “የግል ፕሬስ” እንጂ ተብሏል ለካ!) ምን አለችኝ መሰላችሁ? “አብዛኞቹ የፓርላማ አባላትም መዝሙሩን የሚችሉት አይመስለኝም” ስትል ጥርጣሬዋን ሹክ አለችኝ፡፡
“እንዴት አወቅሽ?” አልኳት በጥርጣሬ እያየኋት። “ መዝሙር ሲዘመር አፋቸውን እየው እስቲ–አይነቃነቅም እኮ!” (“የኢትዮጵያን መዝሙር ሳያውቁ ኢትዮጵያን መምራት???”) በነገራችሁ ላይ — ከብሔራዊ መዝሙራችን ጋር በተገናኘ ሰሞኑን አንዲት ድንቅ የሆነች ኦሪጂናል የቢዝነስ አይዲያ ብልጭ ብላልኛለች፡፡ ምን መሰላችሁ? የሚኒስትሮቻችን ሞባይል ላይ ብሔራዊ መዝሙር መጫን ነው፡፡ ከዚያማ በቃ በፈለጉ ሰዓት ከሞባይላቸው ላይ እየከፈቱ Rehearse ያደርጋሉ – ይለማመዳሉ፡፡ ዝም ብሎ ቱባ ቱባ ሹማምንትን “ብሔራዊ መዝሙር አይችሉም” እያሉ ከማማት— እንዲህ እንደኔ ከእነ መፍትሄው ማቅረብ ብልህነትም ቅንነትም ይመሥለኛል፡፡ እንግዲህ—የብሔራዊ መዝሙራችንን ነገር በዚሁ እንግታና ወደ ሌላ ትኩስ የፖለቲካ አጀንዳ ደግሞ እንለፍ፡፡ እኔ የምላችሁ… ኢህአዴግ እንዴት “አውራ ፓርቲ” ሊሆን እንደቻለ በቅርቡ የተሰጠውን “ሳይንሳዊ” (ይቅርታ አብዮታዊ ማለቴ ነው!) ትንታኔ ሰምታችሁልኛል? የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አፈ ጉባኤ የተከበሩ አባ ዱላ፤ ስለኢህአዴግ “አውራ ፓርቲነት” ሲተነትኑ ፤ “የህዝቡና የፓርቲው ትክክለኛ መስተጋብር ውጤት ነው” ብለዋል፡፡
ይሄንን ብቻ አይደለም አፈጉባኤው ያሉት “ኢህአዴግ እያሸነፈ የሚቀጥልበትና ተቃዋሚ በተቃዋሚነት የሚቀጥልበት ሁኔታ ተፈጥሯል” ሲሉም የገዢውንና የተቃዋሚውን ጎራ የወደፊት እጣፈንታ በ“ግምታዊ ጥናት” ላይ ተመስርተው ተንብየዋል፡፡ አይገርማችሁም? እኔ እኮ ኢህአዴግ ድንገት ተነስቶ “አውራ ፓርቲ” ነኝ ያለ ነበር የመሰለኝ፡፡ ለካስ በጥናት ላይ ተመስርቶ ነው (በአብዮታዊ ጥናት ላይ ማለቴ ነው!) ባለፈው ዓመት ትዝ ይላችኋል አይደል —አቦይ ስብሃትን ጨምሮ በርካቶች “ፓርላማ አስደናቂ መነቃቃት አሳይቷል” ሲሉ፤ አፈጉባኤውን ጨምሮ በርካታ የምክር ቤቱ “ኢህአዴጎች” ሽምጥጥ አድርገው እንደካዱ? (ኢህአዴግ አንዳንዴ አድናቆትና ነቀፋ አይለይም ልበል?) በነገራችን ላይ — የኢህአዴግ “ወዶ-ገብ” የሆኑት በፓርላማ የግል ተመራጭ ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ሳይቀሩ “ዘንድሮ ፓርላማ ጥርስ አውጥቷል” በሚለው ሃሳብ እንደማይስማሙ ሽንጣቸውን ገትረው ተከራክረዋል፡፡ (ድሮም ጥርስ አለው ለማለት እኮ ነው!) የሚገርመው ግን ምን መሰላችሁ? ሰሞኑን አፈጉባኤ አባ ዱላ ከምክር ቤት አባላት ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ፓርላማው ጥርስ ብቻ ሳይሆን መንጋጋ ለማብቀል እየሞከረ እንደሆነ የሚጠቁሙ ፍንጮች አሳይተዋል፡፡ እንዴት አትሉኝም? በአፈ-ጉባኤው የተነቃቁ ንግግሮች በኩል ነው! እናማ ወዳጆቼ—ዘንድሮ ፓርላማው እሳት የላሰ ባይሆን ምን አለ በሉኝ! እንዴ — የተከበሩ አባ ዱላ እኮ ቀጥ በቀጥ ባይሆንም “እንደድሮው መፋዘዝ የለም” ብለዋል (አድናቂያቸው ነኝ!) ምናልባት እሳቸው ባሳቡት መንገድ ከሄደላቸው እኮ “Best African Parliament” የሚል አዋርድ ልናፍስ ሁሉ እንችላለን፡፡
እኔን ትንሽ ያልተመቸኝ ምን መሰላችሁ? ይሄ በኢህአዴግ አመራሮች ዘንድ የሰፈነው ተቃዋሚዎችን የመፍራት አባዜ (phobia) ነው፡፡ እኔ እኮ ጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም በቅርቡ ፓርላማ ውስጥ በሰጡት ማብራርያ “መንግስት አይፈራም፤ ባህሉም አይደለም–”ሲሉ ኢህአዴግንም ማለታቸው መስሎኝ ነበር፡፡ መሳሳቴ የገባኝ ዘግይቶ ነው፡፡ እውነቱን ልንገራችሁ አይደል —- ኢህአዴግ ተቃዋሚዎችን ወይ ይፈራቸዋል አሊያም ይጠላቸዋል፡፡ (ሁለቱም ደግሞ አክሳሪ ናቸው!) በቅርቡ አፈ-ጉባኤ አባ ዱላ፤ በአውራው ፓርቲ አባላት ከጥግ እስከ ጥግ ስለሞላው ም/ቤት ጥንካሬ ሲናገሩ፤ “ከየትኛውም ተቃዋሚ የበለጠ የኢህአዴግን (መንግሥትን) ጉድለቶች ነቅሶ የማውጣት ብቃት አለው” ብለዋል (ይሁንላቸው ባይመስልም!) አክለውም፤ እንደ ተቃዋሚ ግን ለማጋለጥ አይደለም የሚሰራው፤ ለማሻሻል እንጂ ብለዋል፡፡ (ወይ ማጋለጥ!) እኔ ደግሞ ምን እላለሁ መሰላችሁ — መልካም ሥራ በቅጡ መደነቅና መመስገን እንዳለበት ሁሉ መጥፎ ሥራ ደግሞ በደንብ መጋለጥ አለበት ባይ ነኝ፡፡ አሁን ለምሳሌ ሙሰኞችን ከማጋለጥ ውጭ ሌላ ምን አማራጭ አለ? (ምክርና ተግሳፅ ለ“ስኳር” አይሰራም!) እናም አውራ ፓርቲያችንን የምመክረው– የተባለውን ሁሉ አጨብጭበው ከሚቀበሉ “አባላት” ይልቅ ለጊዜው ቢኮሰኩስም ያለአንዳች ምህረት ስህተትንና ጉድለትን የሚያጋልጡ ተቃዋሚዎች ይሻላሉ፡፡

የጂዳ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት ባልታወቀ ሁኔታ ላልተወሰነ ጊዜ ተዘጋ

November 17/2013
የኢትዮጵያ ቆንጽላ ጽህፈት ቤት በጂዳ ስራውን ማቆሙን እና ላልተወሰነ ጊዜ መዘጋቱን መንግስት አሳወቀ ።የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፖብሊክ ቆንጽላ እንደገለጸው ከሆነ ምንም በማይያውቁት ሁኔታ በጂዳ የሚገኘውን መስሪያቤት መዝጋቱን ያሳወቀ ሲሆን በጂዳ የምትገኙት ኢትዮጵያኖች ፣ጉዳአችሁን እራሳችሁ ተወጡት እኔ ለእናንተ አገልግሎት ብቃት የመስጠቱ ብቃት የለኝም ሲል ማግለሉን እንድታውቁት የግርግዳ ላይ ወረቀት ለጥፎላችኋል ::
embassy letter
በሌላም በኩል አቶ ቴዎድሮስ አድሃኖም በሳኡዲ አረቢያ የሚገኙትን ዜጎቻችንን ለመርዳት ስንል የጂዳውን ቆንጽላ እንድንዘጋው ተገደናል ሲሉ በመገናኛ ብዙሃኖች ገልጸዋል ።ሆኖም ግን አጋዥ ሃይል ከተገኘ ከኢትዮጵያ ወደ ሳኡዲ አረቢያ ሊላኩ የሚገባ የኢምባሲ ሰራተኞች መላክ የሚቻል እና 24/7 አገልግሎት እየሰጡ ወገኖቻቸውን ለማዳን ፈጣን የሆነ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ መሆኑን ሳንገልጽ አናልፍም ።
ኤልሳቤጥ ተስፋዬ ከሜሪላንድ እንዲህ ብላናለች »»»"እሁዳችንን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ አስጀምረውናል! አሪፍ ቁርስ ናት ጎበዝ¡ ለነገሩ ክፍት ቢሆንስ ምን ይጠቅማል። በዱላ ከሚመልሱን በር ዘግተው ቢገላግሉን ይሻለል። ክፍት ሆኖም ዝግ ነበረ እኮ! ዝግ ጭንቅላት ተቀምጦበት በሩ ክፍት ቢሆን ከተዘጋ በር ምን ይለየዋል? እኔ የምለው ቆይ የትኛው ከሳውዲ ጋር ያላቸው ወዳጅነት ነው የወገኖቻችንን ደም እያስከፈለን ያለው? አቤት ወላድ ለጉድ ፈጥሮሽ በምን ቀን ነው ልጆችሽን ወደዛች ሀገር የሰደድሽው?
እባካችሁ ይሄን ያህል ብር ተመድቦ ይሄን ያህል ሰው በቀን እየገባ ነው ብላችሁ ኮመንት አድርጋችሁ ይባስ እንዳታሳምሙኝ። ትላንት ከአንድ ወዳጄ ጋር ስንጫወት "እየተደረገ ያለው ወደ ሀገር የመመለሱ ሂደት አባይን በጭልፋ እንደማለት ነው" ብሎኝ ነበር እውነቱን ነው። ጭልፋው እየጨለፈ,,,, እየጨለፈ,,,, ዝሎ ይወድቃል እንጂ ውሃውን ጨልፎ አይጨርሰውም፣ ዝሎ ባይወድቅ እንኳን ምን ያህል ጊዜና ምን ያህል አቅም ያስፈልገው ይሆን?! መንግስት ከብዛታቸው ጋር የሚመጣጠን አቅም ከሌለው ወይ በሰላም ወይ በተቃውሞ ለምን አይፈታውም? ወይም ሌላ መንግስት በመንግስትነቱ ለዜጎቹ ማድረግ ያለበትን ነገር ለምን አያደርግም? መንግስት ያለው ህዝብ እኮ በህይወት ነው ሀገሩ መግባት ያለበት። እየተደረገ ያለው እርዳታ እኮ እንኳን ለህይወታቸው ለአስከሬናቸውም መድረሱ ያጠራጥራል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የሳውዲው ቆንፅላ በሩን ዘገቶ ከጉዳዩ ራሱን ቢያገል ምን ይደንቃል የገዛ መንግስታችን በፌደራል አስጠብቆ አስከብሮት የልብ ልብ እንዲሰማው አድርጎታል። ወይ ጉድ ጭራሽ በር ዘግተው የእህት ወንድሞቻችንን አስከሬን በበሩ ቀዳዳ አጮልቀው ይቆጥሩ ጀመር አይ የኢትዮጵያ አምላክ ከመንበርህ የለህማ!" አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ደግሞ ይህንን አክሎአል "እነ ዶ/ር ቴድሮስ አድሐኖም የኢትዮዽያ ቆንስላ (በጅዳ) አገልግሎት እንዳይሰጥ የተዘጋው የቆንስላው ሰራተኞች ስደተኞቹን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እንዲያግዙ ስለተፈለገ ነው ይላሉ። ከሆነ ጥሩ ነው። ሰራተኞቹ ስደተኞቹን ሲተባበሩ ኢትዮዽያዊ ዜግነታቸው መሰረት አድርገው እንጂ በፖለቲካ አመለካከታቸው እንደማይመዝኗቸው ተስፋ አደርጋለሁ።
ግን.... ስደተኞችን ለመርዳት ቆንስላ መዝጋት??? እንዴት ነው ነገሩ? ስደተኞችን ለመርዳት ቆንስላው በሙሉ ዓቅሙ (እስከ ሃያ አራት ሰዓት ድረስ) ክፍት መሆን አለበት። የቆንስላው ሰራተኞች ስደተኞቹ ወደ ሚገኙበት ቦታ ተንቀሳቅሰው ዜጎችን እየረዱ ከሆነ ቆንስላው እየሰራ ነው ይባላል እንጂ ዝግ ነው አይባልም። በማስታወቅያውም ቢሆን ቆንስላው የተዘጋበት ምክንያት አይጠቅስም። የቆንስላው ሰራተኞች ስተደኞችን እየረዱ ከሆነ ስለ ቆንስላ መዘጋት ማስታወቅያ መለጠፍ አስፈላጊ አልነበረም ብዬ አስባለሁ። ለማኛውም ጥረት ከተደረገ መልካም ነው።
It is so!!!"

Saturday, November 16, 2013

የወያኔ መንግስት ያጓጓዛቸው ስደተኞች ብዛት 107 ነው 35,000 ስደተኞች በስቃይ ላይ ይገኛሉ

 November 16/2013

መንግስት እስካሁን ወደ ሃገር ቤት የመለሰው በ3 ቀን 107 ዜጎችን ብቻ ነው፤ 35,000 ሰው ለማመላለስ ስንት ቀን ይፈጃል?

 የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ኢትዮጵ ያውያንን የማስመለሱ ጥረት ተሳክቶ ዜጎችን እያስመለስን ነው ካሉ በኋላ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ወደ ሀገራቸው መመለስ እንደጀመሩ ቢናገሩም በሳዑዲ ያሉት ኢትዮጵያውያን ቁጥር እና እየተደረገ ያለው የማስመለስ ጥረት ግን በጣም ደካማና የችግሩን ዕድሜ በጣም የሚያራዝም ነው ተብሏል። ማስመለሱ የተጀመረ ዕለት 23፣ ከትናንት በሥቲያ ቀትር ላይ 34 ትናንት ማምሻውን ደግሞ 50 ኢትዮጵያውያን ብቻ የተመለሱ ሲሆን በድምሩ እስካሁን የተመለሱት ዜጎች 107 ብቻ ነው።
(የመንግስት ሚዲያዎች ወደ ሃገራቸው ተመለሱ ሲሉ ያሳዩዋቸው ኢትዮጵያውያን በአዲስ አበባ ኤርፖርት)
እንደ አምባሳደር ዲና ገለጻ፤ በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወደ አገራቸው የሚመለሱ ዜጎችን እየመዘገበ ነው ቢሉም ኢምባሲው ግን ስልኩ የማይነሳ ከመሆኑም በላይ ቦንድ የገዛ፣ የተመረጠ ብሄር አባል የሆኑትን እየመረጠ ቅድሚያ እንደሚሰጥ ኢትዮጵያውያኑ ከሳዑዲ አረቢያ ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል። የውጭ ሚዲያዎች ወደ ሃገራቸው ለመመለስ እጅ የሰጡ ዜጎችን ቁጥር 25 ሺህ የሚያደርሱት ሲሆን በሳዑዲ የሚገኙ ወገኖች ግን 35 ሺህ እንሆናለን ይላሉ። እነዚሁ ዜጎች ወደ ሃገራችሁ ትመለሳላችሁ በሚል የታጉሩበት ሥፍራ ላይ ካለመጸዳጃ፣ ካለ ውሃ፣ ባልተመቻቸ መኝታ እየተሰቃዩ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት በቀን ይህን ያህል ሰው ብቻ ማመላለሱ ችግሩን እንደሚያባብሰው ገልጸዋል።
    
“መንግስት በ3 ቀናት ውስጥ 107 ሰዎችን ብቻ ነው የመለሰው፤ ለኛ የተገለጸልን በቀን 400 ሰው እንልካለን የሚል ነበር” የሚሉት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን በቀን 400 ሰው የሚያመላልሱ ከሆነ በ87 ቀን ይፈጃል ብለን ነበር፤ አሁን ግን በመንግስት ሚድያዎች እንደሚገለጸው 20 እና 30 ሰው ብቻ በቀን ወደ ሃገሩ የሚመለስ ከሆነ በዚህ አስቸጋሪ ሁኔታ ይህ ሁሉ ሺህ ሕዝብ መቼ እንደሚመለስ ግራ ገብቶናል ሲሉ በስቃይ ላይ ያሉት ወገኖች ለዘ-ሐበሻ ብሶታቸውን ገልጸዋል።
“ወገኖቻችን ሊደርሱልን ይገባል፤ ኢትዮጵያውያን ለቀይ መስቀል እና ለአይ ኦ ኤም ችግራችንን ሊያስረዱልን ይገባል” የሚሉት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን ችግራችንን ስንገልጽ በኢትዮጵያ ኢምባሲ “ማን ኑ አላችሁ?” እየተባልን እንዋረዳለን፤ አያከብሩንም ሲሉ ያማርራሉ።
በሳዑዲ ኢትዮጵያውያን እየደረሰባቸውን ያለው ስቃይ የተረዱ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ዛሬ እዛው አዲስ አበባ የሚገኘው የሳዑዲ አረቢያ ኢምባሲ ደጃፍ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ተንቀሳቅሰው በመንግስት ወታደሮች መቀጥቀጣቸውና ብዙ ሰዎች መታሰራቸውም ዘ-ሐበሻ ዛሬ ጠዋት መዘገቧ ይታወሳል።
በሳዑዲ አረቢያ አሁንም ኢትዮጵያውያኑ በስቃይ ላይ እንዳሉ በስልክ የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
አሁንም ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እናቀርባለን።

Friday, November 15, 2013

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ጐን በመቆም ዋና ተባባሪ መሆኑን በዛሬው እለት አስመስክሯል!

November 15/2013

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡

እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡

በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ቢሆኑም እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራችን ድምፃችንን እንኳን እንዳናሰማ ታፍነናል፡፡ በዚህም እንቅስቃሴ ላይ የተሳተፉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡

የመንግሥት ፖሊሶች የራሳቸውን ዜጋ በመደብደብና በማሰቃየት ብሎም በማሰር በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን በደል ሀገር ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ወገኖቻቸው ላይ ደግመውታል፡፡

ይህ በውሸት ዲሞክራሲ ስም የተደበቀው አምባገነን መንግሥት ሕዝብን ለማሸማቀቅ የወሰደውን እርምጃ ወደ ጐን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅድም አያቶቹን በማስታወስ ያስረከቡትን ክብር ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ መሆናችንን እንገልፃለን፡፡

ፓርቲያችን እንዲህ አይነቱን የለየለት የመንግሥት ሕገ ወጥ ተግባር ትኩረት ሰጥቶ የሚመለከተው መሆኑን እየገለፅን፤ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጐናችን እንዲቆም በአፅንኦት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም