Tuesday, February 19, 2013

ወንጀለኛ የህወሃት ጀሌዎችን በህግ ለመፋረድ ድጋፍዎን ይስጡ

ወንጀለኛ የህወሃት ጀሌዎችን በህግ ለመፋረድ ድጋፍዎን ይስጡ




abebe gelaw
ኢትዮጵያዊያን በሀገራቸው ጭቆና፣ አድልኦ፣ ግፍና በደል አንገሽግሿቸው ተሰደው በሚኖሩበት ምድር ሁሉ ክብራቸውና ነጻነታቸው ተጠብቆ መኖር እንደሚገባቸው ፈጽሞ አጠያያቂ አይደለም። የህግ ልእልና በሰፈነባቸው አገሮችም ይህንን መሰረታው መብት ለማስጠበቅ ከህግ በላይ ምንም ሀይልና ጉልበት ያለው መሰሪያ የለም።
ህወሃት መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት “አሰረን አሳደደን” በማለት በአውሮፓና በአሜሪካ የፖለቲካ ጥገኝነት በመጠየቅ በስደተኛ ስም በተለያየ የማምታቻ ሽፋን ተደብቀው ኢትዮጵያዊያን ያለስጋት የነጻነት አየር እየተነፈሱ እንዳይኖሩ ለማድረግ የሚጥሩ ሰላዮችና የጨቋኙ ስርአት አቀንቃኞች መኖራቸው በተለያየ ጊዜ የተረጋገጠ ሃቅ ነው።
ምንም እንዃን በርካታ ኢትዮጵያዊያን በተደጋጋሚ የነዚህ ወንጀለኛና አሸባሪ ግለሰቦች ሰለባ ቢሆኑም እስካሁን ጠንካራ ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው በቂ ጥረት አልተደረገም።
ባለፈው ግንቦት 10 2004 (May 18, 2012) ጋዜጠኛ እና የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው አበበ ገላው የቀድሞው አንባገነን መለስ ዜናዊን ወንጀሎች በአለም መሪዎች ፊት ስላወገዘ እና ስላጋለጠ እንዲሁም የታፈነ የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት ጩኸት ስላሰማ በተለያዩ የህወሃት ጀሌዎች የሽብር ፈጠራ ወንጀል ሰለባ ሆኗል። በቅርቡ ከነዚህ በህገወጥ የወንጀልና የስለላ ተግባር ከተሰማሩ የህወሃት ጀሌዎች መሃል ጥቂቶቹን ያጋለጠው ጋዜጠኛ አበበ ገላው፣ ጠበቃ ይዞ በህግ ለመፋረድ እንቅስቃሴ ጀምሯል።
ይሄንኑ አላማ ለማሳካት እና ወያኔዎች የፈጠሩትን የጸጥታ ስጋት አቅም በፈቀደ መንገድ ለመቅረፍ ጥቂት የECAD የፓልቶክ መድረክ አባላት በራሳቸው አነሳሽነት ባዋጡት ገንዘብ ለዚሁ አላማ ማስፈጸሚያ የሚሆን ልዩ የባንክ ሂሳብ ተከፍቷል::
ነጻነትና የህግ ልእልና በሰፈነባቸው አገሮች ከህግ በላይ ወንጀለኞችን የመፋለሚያ መሳሪያ ባለመኖሩ፣ ጉዳዩ ይመለከተናል የሚሉ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ይህንን ጥረት አቅማቸው የፈቀደላቸውን ያህል እንዲያግዙ ወገናዊ ጥሪ ቀርቧል።
ህግን ተጠቅሞ ህገወጦችን መፋረድ አንድ የትግል ስልት በመሆኑ ለአንድ ሰው ብቻ የሚተው ጉዳይ አለመሆኑ ለማንም ግልጽ ነው። እርስዎም ለዚሁ እንቅስቃሴ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ አስፈላጊነቱን ካመኑበት ከታች ከተዘረዘሩት አማራጮች በአንዱ መንገድ አስተዋጽኦ ማድረግ ይችላሉ:::
1/ በማንኛውም አሜሪካ በሚገኝ የWells Fargo ቅርንጫፍ AG Legal Fund, Acc. No. 3525090746 በቀጥታ ገንዘብ ማስገባት ይቻላል።
2/ አሜሪካ በሚገኝ ማንኛው Bank of America ቅርንጫፍ በኩል በቀጥታ ገንዘብ ማስገባት ይቻላል:
AG Legal Fund, Acc. No. 485010192701
3/ ከሌሎች አሜሪካ የሚገኙ ማንኛውም ባንኮች ለማስተላለፍ (wire) ለማድረግ AG Legal Fund, Acc. No. 485010192701 , ABA 121000248 መጠቀም ይቻላል::
4/ ከአሜሪካ ውጭ ከሚገኙ ባንኮች ገንዘብ ወደ AG Legal Fund ለማስተላለፍ Acc. No. 3525090746 SWIFT- WFBIUS6S መጠቀም ይቻላል::
5/ በኢንተርኔት አማካኝነት በ Paypal አስትዋጾ ማድረግ ከፈለጉ ከታች ያለውን ድር (link) በመጫን አስተዋጾ ማድረግ ይችላሉ። https://www.paypal.com/cgi-bin/webscr?cmd=_s-xclick&hosted_button_id=UHPF5RPB2PBSN
6/ ከዚህም በተጨማሪ በWestern Union ከላይ በተጠቀሱት የባንክ ሂሳቦች በአንዱ አማካኝነት ገንዘብ ማስተላለፍ ይችላሉ።
ስለጉዳይ ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁ. (001) 5718829882 በመደወል ወይንም በ ethlegalfund@gmail.com ኢሜይል ማድረግ ይችላሉ። እናመሰግናለን!!http://

Monday, February 18, 2013

አዜብ መስፍን የአዲስ አበባ ከንቲባ?

አዜብ መስፍን የአዲስ አበባ ከንቲባ?
Azeb  Mesfin, wife of Ethiopian Prime Minister Meles Zenawi
(ዘ-ሐበሻ) የቀድሟ ቀዳማዊ እመቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከዚህ ቀደም በምርጫ ትወዳድርበት የነበረውን የትግራይ ክልል በመተው በአዲስ አበባ ከተማ ለምርጫ እንደምትቀርብ ከወደ አዲስ አበባ የመጡ ዜናዎች አመለከቱ። “የአቶ መለስ ዜናዊን ሌጋሲ እኔ አስፈጽመዋለሁ” በሚል በአቶ መለስ የቀብር መታሰቢያ ፕሮግራም ላይ በድፍረት የተናገረችው ወ/ሮ አዜብ በአሁኑ ወቅት የፌደራሉ ፓርላማ አባል ብትሆንም ኢሕአዴግን ወክላ በመጪው የቀበሌና የወረዳ ምርጫ ላይ ኢሕ አዴግን በመወከል በበቂርቆስ ክፍለከተማ እንደምትወዳደር የዘ-ሐበሻ የአዲስ አበባ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል። በተለይ “አፍቃሬ ኢሕአዴግ” በመባል የሚታወቀው የአቶ ልደቱ አያሌው ኤዲፓ በዚህ ምርጫ ላይ ሙሉ በሙሉ ሳይሆን በከፊል ብቻ እንደሚሳተፍ ባሳወቀበት በዘንድሮው ምርጫ ከወ/ሮ አዜብ ጋር ይወዳደራል ተብሎ የሚጠበቀው የኢዴፓው ወንድወሰን ተሾመ ነው። አቶ ወንደሰን ተሾመ ኢዴፓ ብቸኛው ያቀረበው እጩ ሲሆን ይህም እጩ ከወ/ሮ አዜብ በሚወዳደሩበት የምርጫ ጣቢያ እንዲወዳደር የተደረገው የፖለቲካ ትርፍ ኢሕአዴግ ለማግኘት አስቦ ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ትዝብታቸውን ለዘ-ሐበሻ ይገልጻሉ። ባልተለመደ መልኩ ከትግራይ ክልል ተነስታ በአዲስ አበባ ከተማ ለምርጫ የምትወዳደረው ወ/ሮ አዜብ ምርጫው የተበላ እቁብ በመሆኑ በቀጥታ አሸንፋ የአዲስ አበባ ካቢኔ ውስጥ በመግባት የኦሕዴዱን ኩማ ደመቅሳ ቦታ በመቀበል የከተማዋ ከንቲባ እርሷን ለማድረግ የታቀደ ነገር እንዳለ ያስታውቃል ያሉት ታዛቢዎች በተለይም ከሰሞኑ ከወ/ሮ አዜብ ጋር ቅርርብ አላቸው የተባሉ አንዳንድ የአዲስ አበባ መጽሔቶች “የሴት ጠ/ሚ/ር ማየት ናፈቀን” የሚል ጽሁፍ ሁሉ መጻፉን ከወ/ሮ አዜብ ወደ አዲስ አበባ ከንቲባ መምጣት ጋር አያይዘውታል – ታዛቢዎቹ። አቶ አርከበ እቁባይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ በነበሩበት ወቅት በአዲስ አበባ የታዩ ለውጦችን ቢያደርጉም የአዲስ አበባ ሕዝብ በምርጫ 97 ወቅት “አርከበ ለከተማዋ እድገት ብትጥርም፤ ኢሕአዴግን ወክለህ ብቻ ስለመጣህ አንመርጥህም” የሚል ምላሽ ከህዝቡ አግኝቶ ኢሕአዴግ በምርጫው በ0 በተሸነፈበት ወቅት ከወ/ሮ አዜብ ጋር እንደማይዋደዱ የሚነገርላቸው አቶ አርከበ በባልየው በአቶ መለስ ዜናዊ “በአዲስ አበባ ላይ ቀለም ከመቀባት በስተቀር ያመጣኸው ለውጥ የለም” በሚል በስብሰባ ላይ በግልጽ ተሰድበው ነበር። በአሁኑ ወቅት ሕወሃት በክፍፍል ላይ እንዳለ እየተዘገበ መሆኑ ይታወቃል። የአቶ ስብሃት እና የወ/ሮ አዜብ ግሩፕ በየፊናው ተፋጧል። አሁን ወ/ሮ አዜብን በአዲስ አበባ ከንቲባነት አማሎ ድርጅቱን የማዳን ሥራ እየተሰራ ነው የሚሉ የፖለቲካ ተንታኞች አሉ።
http://www.zehabesha.com/

Sunday, February 17, 2013

አበበ ገላው ተጫማሪ የግድያ ዛቻ ደረሰው



abebe gelaw
(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ አበበ ገላው ተጨማሪ የግድያ ሙከራ ዛቻ እንደደረሰው በጎግል ቮይስ በኩል በድምጽ ማስረጃ አቀረበ። “አበበ ደምህን እንጠጣዋለን፤ ከኛ የትም አታመልጥም” ሲል አስፈራሪው ሰው ይሰማል። ይህን ተከትሎ አበበ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው “የህወሃቶች ዛቻ እና የዘረኝነት ፉከራ ቀጥሏል። እስከ አሁን ያልተገለጠላቸው ሃቅ እንኳን ዛቻ ሞት ከትግላችንም ሆነ ከቁርጠኛ ጉዞአችን ፈጽሞ አይገታንም። ነጻነት ወይንም ሞት ብሎ የተነሳን ህዝብ ማንም አንባገነን አያስቆመውም። እኔ ብሞትም በዛ በታላቅ አደባባይ ላይ የተናገርኩት እውነት ግን ፈጽሞ አይሞትም፣ ምክንያቱም በያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ የታመቀ ሃቅ ነውና። ሃቅ ሲታፈን ፈንድቶ መውጣቱ ያለ እና ወደፊትም የሚኖር ነው።”

Saturday, February 16, 2013

 
 

“ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”

ዓለም ባንክ ርምጃ ለመውሰድ ጫፍ ደርሷል
inspection panel and world bank
/ዜና ጎልጉል/ ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት “የአስተዋይነት” ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል።
ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል።
በኢህአዴግ ላይ የቀረበው ሪፖርት የመፍትሄ ሃሳብም ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት የጎልጉል ምንጮች፣ የዓለም ባንክ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሪፖርቱን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀበለውና ይፋ እንደሚያደርገው አስረድተዋል። የምርመራ ዘገባውን ስላጠናውና ስላቀረበው የኢንስፔክሽን ተቋምና የስራ ተሞክሮ በቂ ግንዛቤ ያላቸው እነዚህ ክፍሎች እንደሚሉት የዓለም ባንክ ቦርድ ይህ ተቋም ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ያቀረባቸውን ሪፖርቶች ላለመቀበል አንገራግሮ እንደማያውቅ ያስረዳሉ።
በሚመሩት ህዝብ ላይ ግፍ የሚፈጽሙ መንግስታትና በልማት ስም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚያካሂዱ አገራት የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በስፍራው በመገኘትና መረጃዎችን ከመሠረታቸው ዘልቆ በመመርመር አጥንቶ ተጠያቂ የሚያደርገው ኢንክሉሲቭ ዴቨሎፕመንት ኢንተርናሽናል Inclusive Development International (IDI) የሚባለው ተቋም ከኢትዮጵያውያኑ ሰለባዎች ውክልና በመውሰድ ስራውን ለማከናወን እንቅስቃሴ መጀመሩን ጎልጉል ምንጮቹን በመጥቀስ መዘገቡ ይታወሳል። ተቋሙም በውክልናው መሰረት ለኢንስፔክሽን ፓናል በዝርዝር የሰለባዎቹን በደል በማተት አሳውቆ ነበር።
ኢህአዴግ በርዳታና በብድር የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ፣ ለአፈና፣ ለወታደራዊ አቅም ግንባታ፣ ለተለያዩ የአፈና ተቋም ሰራተኞቹ ደሞዝና ህዝብን በመርገጥ ስርዓቱን ለሚንከባከቡ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን በመክፈል ገንዘቡን ለመጠቀም ከታለመለት ዓላማ ውጪ እንደሚያውለው በበርካታ መረጃዎች ያረጋገጠው የኢንስፔክሽን ቡድን ለዚሁ ስራው ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳንና ኢትዮጵያ በቅርቡ አቅንቶ ነበር።
ምርመራው ያስደነገጠው ኢህአዴግ በተለያየ መልኩ ሰለባዎች በደላቸውን እንዳይናገሩ፣ በጥቅም የተደለሉ ሰዎችን በየቦታዎቹ በማዘጋጀትና በማስፈራራት አፈና ማካሄዱን የጎልጉል የመረጃ ምንጮች በወቅቱ ቢያስታውቁም ጎልጉል መረጃውን ለስራው መሳካት ሲባል ይፋ ከማድረግ ተቆጥቧል።
ከቀናት በፊት ሪፖርቱን አጠናቆ ለዓለም ባንክ ቦርድ ያቀረበው የኢንስፔክሽን ቡድን (ፓናል) በማያወላዳ መንገድ ተጽኖ ፈጣሪ ተቋም መሆኑንን ያስረዱት ለስራውና ለተቋሙ ቅርበት ያላቸው ክፍሎች፣ ሪፖርቱን ከቦርዱ አባላት አንዱ እንኳ አልቀበልም ቢሉ ምን ሊከሰት እንደሚችልም አብራርተዋል።
“አንድ ወይም ከአንድ በላይ የቦርድ አባላት የፓናሉን ሪፖርት ውይይት እንዲደረግበት እስካልጠየቁ ድረስ ፓናሉ ባቀረበው መሠረት እንዳለ ይጸድቃል። ከጸደቀም በኋላ ሪፖርቱ በዓለም ባንክ ስም ይፋ ይሆናል። ሪፖርቱ ታምኖበት ይፋ ከሆነ በሪፖርቱ የቀረቡት የመፍትሄ ጭብጦች ተግባራዊ ከማድረግ ውጪ ሌላ አማራጭ የለም። እስካሁን ባለው አሰራር የፓናሉ ሪፖርት ተቃውሞ አጋጥሞት አያውቅም” ሲሉ መልስ ሰጥተዋል።
“ይህ ታላቅ ውጤት የተገኘው በእቅድና አስተውሎ በመራመድ ነው። ወደፊትም በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራቶች አሉ። የአገዛዙን ትምክህትና ማን አለብኝነት የሚያረግቡ፣ ብሎም የሚያተኑ ስራዎች ለመስራት ለተጀመረው ስራ ይህ ውጤት ከፍተኛ መነቃቃት ይሆናል” ሲሉ ጉዳዩን በቅርበት በመከታተል እዚህ ያበቁት ክፍሎች አስረድተዋል።
ጉዳዩ እንዴት እዚህ ደረጃ ደረሰ? ለሚሉት ጥያቄዎችና ኢህአዴግ ስለተከሰሰባቸው ዝርዝር ጉዳዮች ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ October 12, 2012 አስቀድሞ የዘገበውን ማጣቀስ አግባብ ሆኖ በመገኘቱ ከዚህ በታች እንዳለ አቅርበነዋል።

ኢህአዴግ በ600 ሚሊዮን ዶላር አጣብቂኝ ውስጥ ገባ!!

ብያኔው ከጸና ኪሣራው በቢሊዮን ዶላር ሊደርስም ይችላል!

ኢህአዴግ ከዓለም ባንክ ያገኘውን 600 ሚሊዮን ዶላርና በተመሳሳይ ፕሮጀክት ወደፊት ሊያገኝ የሚችለውን ከፍተኛ ገንዘብ በተመለከተ አደጋ ውስጥ መውደቁ ተሰማ። ኢንስፔክሽን ፓናል (Inspection Panel – IP) የተሰኘ ተቋም ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው ኢህአዴግ የቀረበበት ውንጀላ ከተረጋገጠ የሚያጣው ገንዘብ በቢሊዮን ዶላር እንደሚደርስ ታውቋል። ይፋ የሆነውን መረጃ አስመልክቶ ከኢህአዴግ ወገን እስካሁን በይፋ የተሰጠ ምላሽ የለም።
ግፍ የሚፈጽሙ መንግስታትን፣ በልማት ስም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚፈጽሙ ወንጀሎችን መረጃዎችን በስፍራው በመገኘትና ከመሠረቱ ዘልቆ በመግባት አደራጅቶ ተጠያቂ የሚያደርገው ኢንክሉሲቭ ዴቨሎፕመንት ኢንተርናሽናል Inclusive Development International (IDI) ከሰለባዎቹ ውክልና ተሰጥቶታል። ተቋሙም በውክልናው መሰረት ለኢንስፔክሽን ፓናል በዝርዝር የሰለባዎቹን በደል በማተት አሳውቋል።
የኢህአዴግ መከላከያ ሠራዊት የሚያደርሰውን እስራት፣ ግርፋት፣ አስገድዶ መድፈር፣ ከመኖሪያ ቦታ ማፈናቀል፣ የግዳጅ ሰፈራ ወዘተ በማምለጥ ወደ ኬንያ የተሰደዱ የጋምቤላ ነዋሪዎች ይህ ሁሉ ግፍ የሚፈጽምባቸው የኢትዮጵያ መንግሥት በልማት ስም ከዓለም ባንክ በሚያገኘው የዕርዳታ ገንዘብ በመሆኑ ለባንኩ በላኩት የአቤቱታ ደብዳቤ አመልክተዋል።
አቤቱታውን መሠረት በማድረግ የሚደረገው ምርመራ ውጤት ይፋ ሲሆን፣ በሌሎች አገሮች እንደተደረገው በዕርዳታ ስም የሚገኝን ገንዘብ ኢህአዴግ ለፖለቲካ ተግባር መጠቀሙ ሲረጋገጥ፣ በመስከረም ወር መጀመሪያ አካባቢ ከዓለም ባንክ ተፈቅዶ የነበረው 600ሚሊዮን ዶላር ሊከለከል ይችላል፡፡
የዛሬ ዘጠኝ ዓመት አካባቢ በሟቹ ጠ/ሚ/ርና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ መለስ ዜናዊ ቀጥተኛ ትዕዛዝ በጋምቤላ ክልል በተለይ የተማሩ ወንዶች ላይ በማተኮር 424 ንጹሐን የአኙዋክ ተወላጆች በተገደሉበት ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩት ወደ ጎረቤት አገር ኬንያ መሰደዳቸው ይታወሳል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ክልሉ ሰላም የለም፡፡ በየጊዜውም የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ሲካሄዱበት ቆይቷል፡፡ በተለይም ለም የሆነውን እጅግ ሰፋፊ መሬት ለውጪ ባለሃብቶች በሳንቲም በመሸጥ ላይ የሚገኘው የኢህአዴግ አገዛዝ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቀድሞው የደርግ ዘመን ሲካሄድ ከነበረው ባለፈ መልኩ እጅግ በሚያሰቅቅ ሁኔታ በመንደር ምስረታና አስገድዶ የማስፈር ፖሊሲ ከመኖሪያ ቀዬ የማፈናቀል ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን የኦክላንድ ተቋም፣ ሂውማን ራይትስ ዎች፣ … የመሳሰሉ ድርጅቶች ያወጧቸው ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡
ከ1998ዓም ጀምሮ የመሠረታዊ አገልግሎት ጥበቃ ፕሮግራም (Protection of Basic Services “PBS Program”) በሚል በአራት ተከታታይና ሁለት ተጨማሪ የገንዘብ ድጎማ የሚደረግባቸውን ፕሮግራሞች የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ ይህ መሠረታዊ የሆኑ አገልግሎቶችን ለማሟላት ተወጥኖ የሚካሄድ ፕሮጀክት በትምህርት፣ በጤና፣ በእርሻ፣ በንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ በገጠር መንገድ ሥራ፣ ወዘተ መስኮች ላይ እንዲውል (PBS I, PBS I-AF (Additional Financing), PBS II, PBS 11-AF, PBS-Social Accountability Program and PBS III) በማለት በተለያዩ ደረጃዎች ለተከፋፈለው ኦፐሬሽን ማስፈጸሚያ የሚውለው ገንዘብ ከ13ቢሊዮን ዶላር የሚበልጥ ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ ከፍተኛው የዓለም ባንክ ድርሻ 2ቢሊዮን ዶላር ሲሆን የተቀረው በሌሎች ለጋሽ መንግሥታት እና ድርጅቶች የሚሸፈን ነው፡፡ PBS III የተሰኘውን በሦስት ንዑሳን ፕሮግራሞች የተከፋፈለውን ፕሮጀክት ለማስፈጸም በአጠቃላይ የሚፈጀው 6.3ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ የባንኩ ድርሻ የሆነውን 600ሚሊዮን ዶላር ቦርዱ መስከረም 5ቀን 2005ዓም አጽድቋል፡፡
በአስገድዶ ማስፈር፣ መንደር ምስረታና ሌሎች በርካታ የሰብዓዊ መብቶቻቸው የተጣሱባቸው በኬንያ የሚገኙ ሦስት የአኙዋክ ስደተኞች ተወካይ ድርጅቶች በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ ሌሎች የሰብዓዊ ድርጅቶች ጋር በመሆን ባንኩ ሊሰጥ የወሰነውን ገንዘብ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥቅም ከመዋል ይልቅ ለኢህአዴግ የፖለቲካ ዓላማ ማስፈጸሚያ እየዋለ መሆኑን በመጥቀስ ለባንኩ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጂም ዮንግ ኪም መስከረም 6፤ 2005ዓም ደብዳቤ ልከዋል፡፡ በጥያቄያቸውም መሠረት በዓለም ባንክ በኩል ወደ ኢትዮጵያ የሚፈሰው ገንዘብ “በልማት ስም የኢትዮጵያ መንግሥት በጋምቤላ ክልል ለሚያካሂደው የመንደር ምስረታ እየዋለ ነው” በማለት ይከሳል፡፡ ሲቀጥልም የአኙዋክ ሕዝብ ለዘመናት ከኖረበት መንደር በማፈናቀል “የተሻለ አገልግሎት ይሰጣችኋል” በማለት በግድ የማስፈር ተግባር እየተፈጸመ ሲሆን “የተባለው አገልግሎትም ሆነ ለእርሻ የሚሆን በቂ ቦታ እንዲሁም ለከብቶች የሚበቃ የግጦሽና የውሃ ቦታ የላቸውም” በማለት ሰፈራውን የተቃወሙ ሁሉ እጅግ ከፍተኛ የሆነ የሰብዓዊ መብት ረገጣ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ጠቁሟል፡፡ ይህንን ግፍ የሚፈጽሙት ደግሞ የዓለም ባንክ ለመሠረታዊ አገልግሎት ጥበቃ ፕሮግራም (Protection of Basic Services “PBS Program”) ስም ለልማት እንዲውል ከሚሰጠው የዕርዳታ ገንዘብ በመንግሥት ተቀጥረው ደመወዝ የሚከፈላቸው ሠራተኞች መሆናቸውን ገልጾዋል፡፡ ይህንን ጉዳይ ከዓለም ባንክ ጋር እንዲነጋገሩላቸው Inclusive Development International (IDI) የተባለውን ድርጅት መወከላቸውን አስታውቀዋል፡፡ (የደብዳቤው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል)
ተመሳሳይ ጉዳዮችን በዓለምአቀፍ ደረጃ በመከታተልና በማስፈጸም የታወቀው IDI በመስከረም ወር አጋማሽ ላይ ጉዳዩ በቀጥታ ለሚመለከተው የመልሶ ማቋቋምና ልማት ዓለምአቀፍ ባንክና (International Bank for Reconstruction and Development (IBRD)) የዓለምአቀፍ ልማት ማኅበር (International Development Association (IDA)) ሥር ለሚገኘው የኢንስፔክተር ፓናል ባለ 18ገጽ ደብዳቤ ጽፏል፡፡ (የደብዳቤው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል) ይህ የኢንስፔክተር ቡድን ከፍተኛ ሥልጣን ያለው መ/ቤት ሲሆን የዓለም ባንክ የሚሰጠውን ገንዘብ በትክክለኛ ቦታ ላይ አለመዋሉን በመጥቀስ ክስ የሚያቀርቡ ወገኖችን ጉዳይ በመከታተልና ቦታው ድረስ የራሱን ምርመራ በማካሄድ ውጤቱ ተግባራዊ እንዲሆን የባንኩን እጅ የማስጠምዘዝ ዓቅም ያለው እንደሆነ ከዚህ በፊት ያካሄዳቸው የምርመራ ውጤቶች ይጠቁማሉ፡፡
ይህ የመርማሪ ቡድን የቀረበለትን አቤቱታ መቀበሉንና በጉዳዩ ላይ የማንም ተጽዕኖ የማይደረግበትን የራሱን ምርመራ እንደሚያደርግ ከትላንት በስቲያ ባወጣው ባለ 8ገጽ መግለጫ ላይ አሳውቋል፡፡ ይህ የአቤቱታ ፋይል ቁጥር የተሰጠው ጉዳይ በግልባጭ ለባንኩ ፕሬዚዳንትና ለከሳሽ ተወካይ ድርጅት (IDI) እንዲደርስ ተደርጓል፡፡(የደብዳቤው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል)
ጎልጉል የሰሜን አሜሪካ ዘጋቢ ባጠናከረው መረጃ መሠረት ቡድኑ ከያዝነው ዓመት የጥቅምት አጋማሽ በኋላ ወደ ምስራቅ አፍሪካ ያቀናል። ቡድኑ ስደተኞቹ የሚገኙባቸውን፣ እንዲሁም ጉዳዩን በሚመለከት አስፈላጊ የሚላቸውን ቦታዎችና ግለሰቦች ሙሉ በሙሉ ያነጋግራል። ለስራው መሳካት የሚሆነውን ሁሉ በሚፈለግበት ቦታ በመገኘት በግንባር እንደሚያከናውን ለማወቅ ተችሏል።
በተለያየ ጊዜ ኢህአዴግ የሚፈጽመውን ግፍና በደል በማደራጀት ሥርዓቱ ላይ ከትጥቅ የጠነከረ ትግል ማካሄድ እንደሚቻል አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል:: አያይዘውም በመላው አገሪቱ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ረገጣና የመብት ጥሰት በማሰባሰብ የኢህአዴግን የገንዘብ ምንጭ የማድረቅ፣ ብሎም በእርዳታ ገንዘብ የሚገነባቸውን የአፈና ተቋማት ማስለል እንደሚቻል አስታውቀዋል። ይህንን ታላቅ ስራ የሰሩትን አካላት ልምዳቸውን ለሌሎች በማካፈል አስፈላጊውን ስራ ሊሰሩ እንደሚገባም አሳስበዋል።

Friday, February 15, 2013

የነ አንዱዓለም አራጌ እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ይግባኝ ክስ ፍርድ ሳይሰጥ ቀረ


በፌደራሉ አቃቤ ህግ በሸባሪነት ክስ ተመስርቶባቸው በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት የጥፋተኝነት ውሳኔ የተላለፈባቸው የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አቶ አንዱዓለም አራጌ እና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ናትናኤል መኮንን፣ አቶ አንዱዓለም አያሌው ፣ አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ የስር ፍርድ ቤቱን ውሳኔ በመቃወም 6 ኪሎ ለሚገኘው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኛ በጠየቁት መሰረት ለየካቲት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. ለውሳኔ ተቀጥሮ ነበር፡፡ ነገር ግን በዕለቱ የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የመሐል ዳኛው ሳይገኙ ቀርተዋል፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ውሳኔውን ለመስጠት ጉዳዩ ሰፋ ያለ ጊዜ ስለሚፈልግ አይተን አልጨረስንም ብሏል፡፡ በዚህም ምክንያት የይግባኙን የመጨረሻ ፍርድ ውሳኔ ለመስጠት ለ3ኛ ጊዜ ለመጋቢት 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ሰበር ዜና!!!
የመርካቶ ወጣቶች መማርያ እና ማረፌያ የነበረው ኢስላህ ትምህርና ልማት ማህበር ትላንት በመንግስት ተዘጋ!!!

በአዲስ አበባ መርካቶ በተለምዶ አደሬ ሠፈር እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው የባዩሽ መስጊድ ወጣቶች ጀምአ መስራችነት በካባቢው ህብረተሠብ ተሣትፎ 1997 ተመስርቶ የነበረው ኢስላህ ትምህርና ልማት ማህበር ትላንት ከቀኑ 10 ሠዓት ጀምሮ በፓሊሶች ታሽጓል፡፡ ውስጡ የነበሩ የቢሮ መገልገያ ኮምፒተሮች እና የተለያዩ እቃዋችም በፓሊስ ተወስደዋል፡፡

... ኢስላህ የትምህርት እና እውቀት ማህበር በፍትህ ሚኒስተር እውቅና ያለውና በሀገር በቀል እርዳታ ድርጅትነት የተመዘገበ ሲሆን በባዩሽ መስጊድ ውስጥ የቤተመፅሀፍ አገልግሎት አና በወቅቱ ከቀበሌው አስተዳደር ባገኘው ቤት ለአካባቢው ህዝብ አና አጎራባች ቀበሌ ነዎሪዋች ለሆኑ የቲሞች፤ ትምህርት ጨርሰው ቤት ለተቀመጡ ወጣቶች፤ እንዲሁም ስራ ለሌላቸው ወጣቶች የተለያየ የሞያ ስልጠና ሲሰጥ እና ሲረዳ የቆየ ሲሆን በዚህ ስራውም ብዙ ወጣቶችን ራሳቸውን እንዲችሉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል፡፡ ለዚህ ስራውም በክ/ከተማው አስተዳደር ዘውትር ሲመሠገን እና አንደ ሞዴል ሲታይ ቆይቷል፡፡

ትላንት ወደ ድርጅቱ የመጡት ፓሊሦች " ይህ ኢስላህ የትምህርት እና እውቀት ማህበር፡ የአሸባሪዋች እና የአክራሪዋች መፈልፈያ ነው፡፡ " በማለት ያሸጉት ሲሆን እስካሁንም በፓሊስ እየተጠበቀ ነው፡፡ በዚህ የመንግስት ፀረኢስላምና ፀረልማት ድርጊት የአካባቢው ህብረተሠብ በጣም አዝኗል::

ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በጀርመን ተካሄደ

Dawit Fanta
የኢትዮጵያውያን የፖለቲካና ሲቪክ ማህበር አባላት አንድነት ድርጅት በፌብሯሪ 09, 2013 ዓ.ም. ያዘጋጀው ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በታሪካዊቷ የኑረንበርግ ከተማ ተካሄደ።
ከመላው ጀርመን የተሰባሰቡ ቁጥራቸው ከ350 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በታደሙበት በዚህ የውይይት መድረክ ላይ ከተለያዩ ድርጅቶት ተወካዮች የተገኙ ሲሆን የውይይት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሲቪክ ማህበሩ መስራችና ሊቀ መንበር አቶ በላይነህ ወንዳፍራሽ ነበሩ።
clip_image002አቶ በላይነህ በመክፈቻ ንግግራቸው ሲገልፁ የዚህ አይነቱ መድረክ መዘጋጀት የፖለቲካ ድርጅቶች ከህዝባችን ጋር ገጽ ለገጽ በመገናኘት አላማና ፕሮግራማቸውን ለማስረዳት ከመጥቀሙም በላይ ከህዝብ ጋር በሚኖራቸው የቀጥታ ግንኙነት መሠረት ሀገራዊ ፋይዳ እና ራዕይ ያለው የትግል አጋር የሆነ ተረካቢ ወጣት ትውልድ ለማፍራት ይረዳል ብለዋል።
”በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ውስጥ አራት አይነት ዜጎች አሉ” በማለት ንግግራቸውን የጀመሩት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት ተወካይ ኢንጂነር ስለሺ በዚያች ሀገር በተጠቃሚነት ደረጃ የህወሃት አባላት የመጀመሪያ እና ትልቁ ሲሆኑ፤ሁለተኛ ዜጋ የሚባሉት የወያኔ ተለጣፊ ድርጅት አባላት ናቸው።እንዲሁም በሦስተኛ ዜግነት የሚፈረጁት በወያኔ 5ለ1 አደረጃጀት ለመኖር፣ለመስራትና ለመማር ሲሉ በኢህአዴግነት የታቀፉ ሲሆን ከነዚህ ውጪ የሚገኘው አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል በአራተኛ ደረጃ የዜግነት እርከን ላይ ይገኛል ብለዋል።
ኢንጂነር ስለሺ በመቀጠለም በኢትዮጵያ አምስት አይነት የሽግግር አማራጮች እንዳሉ ሲዘረዝሩ 1ኛ ሥርዓቱ ከውስጥ በሚነሳ መሰነጣጠቅና በመዳከም ይወድቃል ብሎ በተስፋ መጠበቅ ሲሆን ይህም የመሆን ዕድሉ የጠበበና ”የስንፍና” አስተሳሰብ ነው ብለዋል።2ኛ የወያኔን ህገ-መንግስት ተቀብሎ በምርጫ ማሸነፍ የሚል ሲሆን ይህም በምርጫ 97 ተሞክሮ እንደታየው ተግባራዊ ሊሆን አይችልም ብለዋል።3ኛ. አንድ ጠንካራ ፓርቲ በኃይል ጠንክሮ ወጥቶ ወያኔን በመጣል ሥልጣን መያዝ የሚለው ሲሆን ይህም በኢትዮጵያ እየታየ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ለሀገራችን ፖለቲካዊና ማህበራዊ ችግሮች ዘለቄታ ያለው መፍትሔን የማያመጣ ይልቁንም ልክ እንደወያኔ ሁሉ ለማሸነፍ ብዙ መስዋዕት የከፈልኩት እኔ ነኝ ከሚል ዕሳቤ በመነሳት አምባገነናዊ ስርዐት የሚገነባበት ዕድል የሰፋ ይሆናል ሲሉ ይህንንም አማራጭ አጣጥለውታል።4ኛ. ብሔራዊ እርቅ ማድረግና የሽግግር መንግስት መመስረት የሚለው ሲሆን ብሔራዊ እርቅ የሚለውን ሀሳብ የወያኔ መንግስት ለዘመናት በማጣጣል ወደጎን ሲገፋው የኖረ ሀሳብ በመሆኑ ይህንንም አማራጭ በተጨባጭ ወደ ተግባር ለመተርጎም የማይቻል ሲሉ ገልፀውታል።5ኛ ሁሉን አቀፍ በሆነ ትግል የወያኔን ሥርዓት ማስወገድ እና የሽግግር መንግስት ማቋቋም ሲሆን ይህን ሀሳብ ድርጅታቸው እንደሚያምንበት ገልፀው የዚህን አማራጭ አዋጭነትም ሲያስረዱ የወያኔ ስርዓት መወገድ አለበት የሚለው የአብዛኛው ህብረተሰብ ጥያቄ መሆኑ፣”ትግሉም የጋራ፥ድሉም የጋራ” ከሚል መንፈስ በመነሳት እንዲሁም በግብፅ የተከሰተው አይነት ሁኔታ እንዳይፈጠር ከለውጡ በኋላ የሚኖረውን ክፍተት ለመዝጋትና ሁሉም ዴሞክራሲዊ ኃይሎች ያለቅድመ ሁኔታ ለመስራት ስለሚረዳ ሲሉ ሃሳባቸውን ቋጭተዋል።
በሌላ በኩል የነፃውን ፕሬስ ወክለው ንግግር ያደረጉት የጥላ መጽሔትና ዌብ ሳይት ዋና አዘጋጅ አቶ ዳዊት ፋንታ ሲሆኑ ዛሬ የወያኔ መንግስት ከጦር መሣሪያ ይልቅ ብዕርን አጥብቆ እንደሚፈራ ገልፀው ሥርዓቱ በፈጠረው አፋኝና ዘረኛ አስተዳደር ምክንያት ብዕር የሚያነሱ እጆች አንድም ለስደት አልያም ለሰንሰለት ተዳርገዋል በማለት ተናግረዋል።
clip_image002

የወያኔ መንግስት የፕሬስ ነፃነትን በአዋጅ አፅድቄአለሁ እያለ ቢመፃደቅም በተግባር እንደሚታየው ግን ይህ አዋጅ ለፕሬስ ነፃነት መከበር ዋስትና የማይሰጥ ይልቁንም ወያኔን በውጪው አለም ዴሞክራሲያዊ መንግስት አስመስሎ ለማሳየት የተዘጋጀ የወረቀት ላይ ነብር ነው በማለት አክለው ተናግረዋል።እንደ አቶ ዳዊት ገለፃ የወያኔ አስተዳደር በየጊዜው የሚያወጣቸው ህጎች ማለትም እንደ አዋጅ ቁጥር 652/2009 የመሣሠሉ ጋዜጠኞችን በአሸባሪነት የሚፈርጁ አሻሚ የህግ አንቀፆች የነፃውን ፕሬስ እጅ ተወርች ጠፍንገውት ይገኛል ሲሉ ሃሳባቸውን አጠቃለዋለዋል።
በሌላ በኩል የአማራው ነገድ ራሱን ከጥፋት ለመከላከል የመደራጀት አስፈላጊነትና አስገዳጅነት ነጥቦችን በመዘርዘር ንግግራቸውን የጀመሩት የሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት ተወካይ ዶ/ር አፈወርቅ ተሾመ ሲሆኑ ለሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት መመስረት ምክንያት ነው ያሉትን ነጥብ እንደሚከተለው አቅርበዋል፦
  • ”የአማራው ነገድ ከመቼው ጊዜ በከፋ መልኩ ህልውናው በከፍተኛ አደጋ ላይ የወደቀ መሆኑን እንገነዘባለን።አማራው በሆደ ሰፊነት፣በትዕግስትና በአርቆ ተመልካችነት ወያኔ በአማራው ላይ የሰነቀውን የዘር ጥላቻ እያረገበ ወደ መቻቻልነትና ወደ አብሮነት ይመለሳል፤ሥልጣናቸውን ሲያረግጡና ሲረጋጉ ወደ እውነተኛ ኅሊናቸው ይመለሳሉ በማለት በከፍተኛ ተስፋ ቢጠብቅም የጠበቀው ተስፋ እውን ሊሆን ካለመቻሉም በላይ በአማራው ላይ የከፋና የከረረ የዘር ማፅዳት ዘመቻ ተጠናክሮ በመቀጠሉ አማራው ባለፉት 22 ዓመታት ያሳየው ትዕግስትና ሆደ ሰፊነት ተፈላጊውን ውጤት ያላስገኘ በመሆኑ ትውልዱ ፈፅሞ ከመጥፋቱ በፊት ሌላ አማራጭ መከተል ግድ ብሎታል።ይህም አማራጭ አማራው በዜግነት ሲቪክ ድርጅት ተደራጅቶ ራሱን ከፈፅሞ ጥፋት መታደግ ነው።” በማለት ሃሳባቸውን ቋጭተዋል።
እንዲሁም የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ፣የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ዘብ እና የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር በጀርመን የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተወካዮች የድርጅቶቻቸውን አላማና ፕሮግራም ለተሰብሳቢው ያቀረቡ ሲሆን በውይይቱ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ከድርጅት ተወካዮች ምላሽ ተሰጥቷል።
በሁለት ክፍለ ጊዜ ተከፍሎ በተዘጋጀው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የተለያዩ ወቅታዊ የሆኑ ግጥሞችና መጣጥፎች በየመሀሉ የቀረቡ ሲሆን መድረኩን በብቃት በመምራት የሴቶች ተሳትፎ ጎልቶ የወጣበት ሁኔታም ተስተውሏል።
በመጨረሻም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ባለ ሦስት ነጥብ የጋራ የአቋም መግለጫ በማውጣት ውይይቱ ተጠናቋል።
  1. የወያኔ መንግስት በሃይማኖት ውስጥ የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት እናወግዛለን፤በሃገራችንም የሃይማኖት ነፃነት እስኪረጋገጥ ትግላችንን አጠንክረን እንቀጥላለን።በቅርሶቻችን እና ጥንታዊ እና ታሪካዊ ገዳማት ላይ የሚደርሰውን ጥፋት አጥብቀን የምንቃወም ሲሆን በቅርቡ ”ጂሃዳዊ ሓረካት” በማለት በወያኔ የፕሮፖጋንዳ ማሽን የተላለፈው ድራማ የወያኔን ፖለቲካዊ ኪሣራ የሚያመላክት እንዲሁም የሙስሊም ወንድሞቻችንን የድምፃችን ይሰማ ጥያቄ አቅጣጫ ፖለቲካዊ መልክ ለማስያዝ የተደረገ ከንቱ እና ያልተሳካ ሩጫ ነው።
  2. ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ቃልኪዳናችን ነው፥በመሆኑም በዘር፣በሃይማኖትና በብሔር ሳንከፋፈል በህዝባችን ላይ በኃይል የተጫነውን ሥርዓት ለማስወገድ ብሎም ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ መምጣት በሚደረገው ትግል ያለመታከት በሙሉ አቅማችን እንሳተፋለን።ለለውጥ ያለንን ቁርጠኝነትም በተግባር ለማሳየት ቃል እንገባለን።
  3. በወያኔ ማጎሪያ ካምፖች ውስጥ ያሉ የነፃነት ታጋዮችን፣የኅሊና እስረኞችንና የፖለቲካ አመራሮችን ሁልጊዜም የምንዘክራቸው ሲሆን ከምናደርገው የፖለቲካ ትግል ጎን ለጎን በነዚህ ጀግኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ሰቆቃ ለዓለማቀፉ ማህበረሰብ በሰላማዊ ሰልፎች፣በዲፕሎማሲ ጥረት እና በግልጽ ደብዳቤዎች የምናጋልጥ ይሆናል።ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!

Thursday, February 14, 2013

አሳዛኝ ዜና ሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ቆንስላ በር ላይ 1 ወጣት ረዳት አጥቶ ህይወቱ አለፈች።



አሳዛኝ ዜና ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ የወያኔ ዲፕሎማቶች የመሸጉበት የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት በር ላይ ወድቆ የወገን ያለህ የሚል የሲቃ ድምጽ ሲያሰማ የነበረው ወጣት ረዳት አጥቶ ህይወቱ አለፈች።

በመካከለኛ የእድሜ ክልል ውስጥ እንደ ሆነ የሚገመተው ይህ ወጣት ወገን አለኝ ብሎ ጅዳ በሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስል ጽ/ቤት በር ላይ ትላንት ወድቆ ጣረሞት ሲያሰማ እንደነበር ከጅዳ በሳውዲ አረቢያ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ፕሮግራም ዘጋቢ አቶ ነብዩ ሲራክ በወቅቱ ጉዳዩን ሰምቶ እንደነበር ይግለጽ እንጂ አቶ ነብዩን ቦታው ላይ በካላል ያዩት አንዳንድ በጅዳ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ለማህበራችን በላኩት መለዕክት ገልጸውልናል።

አቶ ነብዩ በወቅቱ የዚህን ወጣት ህይወት ከሞት ለመታደግ ህክምና ማግኘት የሚችልበትን መላምት በመፍጠር ወገናዊ ነት እና ረህራሄ ያልፈጠረባቸውን የወያኔ ጀሌዎች አስተባብሮ የዚህን ኢትዮጵያዊ ወጣት ችግር ቀርቦ መረዳት ሲቻል ወጣቱ በዚህ ፎቶ ላይ እንደተገለጸው ወድቆ ብርድ እና ጸሃይ ሲፈራረቅበት አይቶ ማለፉ የሚያሰተዛዝብ ከመሆኑም በላይ እራሱን የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ጣቢያ ዘጋቢ ነኝ ብሎ የሚጠራውን የአቶ ነብዩ ሲራክ ልብ እንደ ወያኔዎቹ በኢትዮጵያውያን ላይ ምን ያህል እየደነደን መምጣቱን ያሳያል።

በአጠቃላይ ኢትዮጵያዊ ወጣት በንጋታው ሞቶ ማየቱን የገለጸው አቶ ነብዩ ሲራክ በወጣቱ ሞት የተሰማውን ሃዘን በፌስ ቡክ ገጽ ላይ ለማስነበብ የሞከረው ሙሾ ከተለመደው አስመሳይ የአዞ እንባው እንደ ማይለይ አያሌ የጅዳ ነዋሪዎች ያወጋሉ።
በሳውዲ አረቢያ የሪያድ እና አካባቢው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ማህበር

Wednesday, February 13, 2013

ኦባንግ “ነጻ ስለመሆን የማንንም ፈቃድ አንጠይቅም።
13Feb

“ትግል አርቆ ማሰብ ይጠይቃል፤ እቅድ ይፈልጋል። ትግል ህዝብን ማስተባበርና የረዥም ጊዜ ትልምና ራዕይ ሊኖረው ያስፈልጋል። ስለዚህ ምን እናድርግ? ከየት እንጀምር?” የሚል ጥያቄ የዩኒቨርስቲው ተማሪዎች አነሱ። አቶ ኦባንግም የሚመሩት ድርጅት ዕቅዱና ራዕዩ በሂደት እዚህ እንዳደረሰው አስረዱ። በቀጣይም ከህንድ ዜጎች ስለሚጠበቀው ዋንኛ ትግል አወሱ። ካሩቱሪ የሚባለው ኩባንያ በኢንቨስትመንት ስም እያከናወነ ያለውን ተግባር ህንዶች ካሳለፉት የቀደመው ችግራቸው ጋር በማያያዝ ተናገሩ። መሃትማ ጋንዲ ገድል ፈጽመው ያለፉበትን ትግል በማድመቅ ይህ ትውልድ የጋንዲን ዓላማ በማንሳት ለወገኖቹ ስቃይ የመድረስ ግዴታና የታሪክ ውርስ እንዳለበት አሳሰቡ። በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ በመረጃ ተንትነው አብራሩ።
መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው” የንግግሩ መግቢያ ነበር። “በጨለማ ውስጥ ነን። ከፍተኛ በደል እየተፈጸመብን ነው። ለመረጃ ሩቅ የሆኑ ሰዎች፣ የስልጣኔ ጮራ ያልበራላቸው ሰዎች፣ የመማር ዕድል ያላቸኙ ሰዎች፣ ግፍ እየተፈጸማባቸው ነው። መብታቸውና ሰብዓዊ ክብራቸው ተረግጧል። በጉልበት መሬታቸው እየተነጠቀ በልማት ስም እየተሸጠ ነው። ይህ ሁሉ የሚደረገው በህንድ ህዝብና መንግሥት ስም ነው። ይህ አሳዛኝ ተግባር በስማችሁ እየተከናወነ ነው። በናንተ ስም። ተቃወሙ። ታገሉ። አግዙን። ለዚህ ነው መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው የምለው” ይህ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ንግግርና የትግል ጥሪ የቀረበው ህንድ ታዋቂው በሆነው ጃዋሃርላል ኔህሩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፊትለፊት ነበር።
ኦባንግ “ጥቁሩ ሰው” ወደ ህንድ ያመሩት ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጋር ለመነጋገር አልነበረም። በመጀመሪያ የተገኙት የህንድ ዓለምአቀፍ ማዕከል “Understanding Land Investment in East Africa” በሚል ስያሜ ባዘጋጀው ምክከርና የትግል ልምድ መለዋወጫ መድረክ ላይ ንግግር እንዲያቀርቡ ተጋብዘው ነው። አስቀድሞ በተያዘው ዕቅድ መሠረት በዚህ ስብሰባ ላይ እንዲሳተፉ በጋራ ንቅናቄው የተመረጡ ኢትዮጵያውያንና ሌሎች ግለሰቦች የነበሩ ቢሆንም ከወጪ እና ስፖንሰር አድራጊ ድርጅቶቹ ካጋጠማቸው ሌሎች ተዛማች ችግሮች ምክንያት ሳይሳካ እንደቀረ ተጠቅሷል፡፡
በዚሁ ታላቅ መድረክ ላይ ኦባንግ “ነጻ ስለመሆን የማንንም ፈቃድ አንጠይቅም። ሰው በሰውነቱ የሚከበርበት አገር እስከምንመሰርት ድረስ እንታገላለን። የብሶታችንና የትግላችን መነሻ ለናንተ አዲስ ትግል አይደለም” በማለት የስብሰባውን ቀልብ አነሱት። በህንድ የነጻነት ትግል ውስጥ አብሪ ኮከብ ሆነው የሚኖሩትን መሃትማ ጋንዲን በማስታወስ አገራቸውን ተቀራምተው የነበሩትን የእንግሊዝ የመሬት ቀማኞች እንዴት ድል እንደመቱ አሞካሽተው አቀረቡ። ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጥያቄ መልስ የሰጡት አቶ ኦባንግ በዩኒቨርስቲው ንግግራቸው ጋንዲን ማጉላታቸው ብቻ ሳይሆን በዩኒቨርስቲ ውስጥ ሌሎች ጋንዲዎች ስለመኖራቸው መናገራቸው ታላቅ ትርጉም የሰጠ እንደነበር ገልጸዋል።
በምክክሩ ላይ የክብር ተናጋሪ የነበሩት የኦክላንድ ተቋም ዋና ዳይሬክተር አኑራድሃ ሚታል “በኢትዮጵያ እየሆነ ያለው ሁሉ በፍጹም ተቀባይነት የለውም” በማለት ምክንያታቸውን አስረዱ። በኢትዮጵያ በወልቃይት ጠገዴ፣ በዋልድባ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ ስለተካሄደው መሬት ንጥቂያና ግፍ የተሞላበት ተግባር በዝርዝር አቀረቡ። የአኑራድሃ ንግግር ህንዶቹን አስደነገጠ።
የህንድ ዓለምአቀፍ ማዕከል ባዘጋጀው በዚህ የምክክርና የትግል ስልት የልውውጥ መድረክ የህንድ ፖለቲከኞች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ ጋንዲያዊ የትግል መስመር አጥብቀው የሚከተሉ የተለያዩ ፖለቲከኞች፣ የህንድ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ የገዢው ፓርቲ ተወካዮች፣ የቀድሞ ፖለቲከኞች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ ተሟጋቾች፣ ተለያዩ ማህበራት ተወካዮችና የተለያዩ አካላት የተገኙ ሲሆን ታላላቅ የመገናኛ አውታሮችም ተገኝተዋል።
ዶላር ከዜጎቹ የበለጠበት ኢህአዴግ
“ህወሃት/ኢህአዴግ ዶላር ካገኘ ለሚገባበት ገደል የሚቀርበውን አፋፍ አይመርጥም” በማለት የሚተችበትን ነጥብ ማስታወስ አግባብ ይሆናል። ኢህአዴግ ከስልጣኔ፣ ከወገኖቻቸውና ከዓለም መገናኛ ጀርባ ያሉ፣ በመረጃ ጨለማ ውስጥ የሚኖሩ ምስኪን ዜጎችን በሚዘገንን የንዋይ ፍቅር መብታቸውን እየጨፈለቀ ለመናገር የሚታክት በደል ፈጽሞባቸዋል። አኑራድሃ እንዳሉት “መሬት የመንግስት ነው” በሚል ዜጎችን የግድግዳና ጣሪያ ባለቤት በማድረግ ከቅድመ አያት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣውን ሃብታቸውን ዘርፏቸዋል።
ይህ አገር እየመራ እንኳን ራሱን በነጻ አውጪ ስም የሚጠራ ድርጅት በር ዘግቶ በዜጎቹ ላይ የሚፈጽመውን ተግባር በማጋለጥ ቅድሚያ የያዘው የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ነበር። ይህንን አቢይ ተግባር ጊዜ በመውሰድ ያጠናውና በመረጃ በማስደገፍ ስርዓቱ የህዝቦችን ደም እንደሚጠጣ ያጋለጠው አቶ ኦባንግ የሚመሩት ድርጅት ለነዚህ ወገኖች አንደበት በመሆን በዝግ የሚፈጸመውን ርህራሄ የጎደለው ግፍ ይፋ እንዲሆን አደረገ። “እመራዋለሁ” የሚለውን ህዝብ በንዋይ፣ ለዚያውም በዓለም ላይ ታይቶ በማይታወቅ ሂሳብ ድንግል መሬት የሚቸበችበው ህወሓት/ኢህአዴግ በኦሮሚያ አንድ ሄክታር መሬት ከአንድ ዶላር በታች እንደ ጉሊት ጨው መቸርቸሩ ይፋ መሆኑንን ከሰሙ መካከል የኦክላንድ ተቋም ቀዳሚ ሆነ።
በቅርቡ የአማርኛው ትርጉም ይፋ የሚሆነውን “በኢንቨስትመንት ስም የሚፈጸም የመሬት ነጠቃ፤ በኢትዮጵያ” የተሰኘውን ጥናት ያካሄደው የኦክላንድ ተቋም አቶ ኦባንግ ከሚመሩት ድርጅት ጋር በጋራ እየሰራ የሚገኝ ነው፡፡ ይህንንም ጥናት ተግባራዊ ለማድረግና በዘገባ መልክ ለማውጣት ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ያደረገውን አስተዋጽዖ የተቋሙ ዳይሬክተር በአደባባይ የሚመሰክሩት ሲሆን ለጥናቱ የጀርባ አጥንት በመሆን ያሳየውን ዕገዛ ያደንቃሉ፡፡ ተቋማቸው ባደረገው በዚህ ጥናት ኢትዮጵያን አስተዳድራለሁ የሚለው ኢህአዴግ ዜጎቹን ሳያማክርና ፈቃድ ሳይጠይቅ እንደ አሮጌ እቃ በየስርቻው የሚጥል አገዛዝ መሆኑን በማስረጃና በተግባር አራግፈው በአደባባይ ሰቀሉት።
ህንድ እንዴት ተደረሰ?
“የወረቀት ትግል ውጤት የለውም” ሲሉ የሚከራከሩ ነበሩ። አሁንም አሉ። አቶ ኦባንግ ግን በተቃራኒው ይህንን አስተሳሰብ አይቀበሉም። ህንድ አገር ስለመድረሳቸው ዋና ምክንያትና አጋጣሚ ተጠይቀው “ህንድ አገር ባጋጣሚ አልሄድኩም” በማለት መልሳቸውን ይጀምራሉ። በኢትዮጵያ ያለውን ስርዓት የለቀቀ አገዛዝ የሰለቻቸውን ዜጎች ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት ድርጅታቸው በየደረጃው ያስቀመጣቸው አካሄዶች እንዳሉ ይናገራሉ። “ህንድ አገር በመሄድ የህዝብ ለህዝብ የተቀናጀ ትግል እንደምናደርግ ያቀድነው አስቀድመን ነው። በዚህ አያቆምም። በእቅዳችን መሰረት እንቀጥላለን” የሚሉት ኦባንግ ሜቶ በኢትዮጵያ የሚካሄደው የመሬት ዝርፊያ ማቆሚያ እንደሚበጅለት በርግጠኛነት ያስረዳሉ። ይህ ግን የድርጅታቸው የመጨረሻ ግብ አይደለም።
ምን ውጤት ተገኘ?
ካሩቱሪ የተባለው ድርጅት በኢትዮጵያ ድንግል መሬት በመውሰድ ቅድሚያ አለው። ይህ ድርጅት የሚጠራው በህንዶች ስም ነው። በህንድ መንግስት በተወሰነ መልኩ የሚደገፍም ነው። በርካታ የአክሲዮን ባለድርሻዎችን ያሰባሰበ ነው። መሰረታዊው የምክክሩ ዓለማ የህንድ ወንድምና እህት ህዝብ እያወቁ እነሱ ታግለው ድል የነሱት የመሬት ዝርፊያ በነሱ ስም በሃያ አንደኛው ክፍለዘመን በኢትዮጵያዊያን ላይ መካሄዱን ማሳወቅ ነበር።
በዚሁ መሰረት ዜጎች ከራሳቸው ምድር ላይ እየተፈናቀሉ፣ እየተገረፉ፣ እየተገደሉ፣ እየተሰደዱ ወዘተ መከራ ሲደርስባቸው እንደነበር የሰሙ አዘኑ። “ይህ በስማችን ስለመደረጉ አናውቅም ነበር” ሲሉ ሃዘናቸውን ገለጹ። አንድ አዛውንት የስብሰባው ተሳታፊ “በኢትዮጵያና በህንድ ህዝብ መካከል ልዩነት የለም። አንድ ነን። ተያይዘን እንታገላለን። ህብረት እንፈጥራለን። ተያይዘን የምንታገልበት አንድ ቀን አሁን ነው” ሲሉ አስተያየት ሰጡ።
“ትግል እቅድ ይጠይቃል። ትግል ህዝብን የማስተባበርና የረዥም ጊዜ ትልም ሊኖረው ይገባል። አሁን ምን እናድርግ? ከምን እንጀምር” የሚል ጥያቄና የትግል ዝግጁነት ተሰማ። ለተከታታይ ቀናት የተካሄደውን ምክክር የህንድ ብሄራዊ ሚዲያዎችና ታዋቂ የዓለም መገናኛዎች ለህብረተሰቡ ይመግቡ ስለነበር፣ በቀጥታ የቴሌቪዥን ውይይት በመደረጉ ካሩቱሪ ተሸበረ።
የህንድ ዜጎች ምን ያደርጋሉ?
“በስማችን ወንጀል ሊሰራ አይገባም። በመንግስት ስም የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲካሄድ ዝም ብለን አንመለከትም። መንግስት ለካሩቱሪ የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ እንዲያቆም፣ የካሩቱሪ ባለ አክሲዮኖች ለዚህ ክፉ ተግባር ተባባሪ ከመሆን ተቆጠቡ” የሚሉና በየደረጃው እየጠነከረ የሚሄድ ማስገደጃ ለማድረግ እንደሚሰሩ ተሳታፊዎቹ አረጋግጠዋል።
ይህ ውሳኔ ባለሃብቱንና ባለ አክሲዮኖቹን በማስጨነቁ የድርጅቱ የባለ አክሲዮኖች ስብሰባ ከመካሄዱ በፊት የሚጀመረው ዘመቻ በጎርፍና በከብት መንጋ ኪሳራ ደርሶበት የነበረውን ኩባንያ በኪሳራ እስከማዘጋት የሚደርስ ትግል እንደሚደረግ ቃል ከማስገባት በላይ ታላቅ ነገር እንደሌለ አቶ ኦባንግ ይናገራሉ። አይያዘውም “የሰከነ ትግል ውጤቱ አሁንም በሰከነ መንፈስ በመከታተል የሚታይ ይሆናል። በዚህ አይበቃም ይቀጥላል። በስሜትና ጊዜያዊ በሆኑ ጥቅሞች ሳንነዳ እቅዳችንና ግባችን በሚያዘን መሰረት እንጓዛለን” ሲሉ ለጎልጉል ተናግረዋል።
መንግስት ለምን ፈራ?
ኢህአዴግ ስብሰባውንና የስብሰባውን ውጤት የፈራው ጥቅሙን ስለሚያጣ ነው። ካሩቱሪ ለቅቆ ሲወጣ ሁሉም መሬት ለመንጠቅ የመጡ ባለሃብቶች በየተራ ይወጣሉ። ይህ ዶላር ፍለጋ የሚምልባቸውን ምስኪን ህዝቦች እየገፋ ያለ ስርዓት ለአፈናው ለሚያወጣው ከፍተኛ በጀት፣ ለተነከረበት ከፍተኛ ሙስናና ዝርፊያ የሚሆን ገቢ ሲያንሰው የራሱ “ሌቦች” ጭምር ስለሚከዱት የህንድ ወገኖች እያሳዩ ያሉት ተቃውሞ ሳይነድና ሳይጠነክር አስቀድሞ ለማስቆም ህወሃት/ኢህአዴግ ሩጫ ጀምሯል።
የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንዳሉት በህንድ አገር የተካሄደው ምክክር በተጠናቀቀበት እለት ከኢትዮጵያ መንግስት በኩል ለኦክላንድ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ደብዳቤ ተጽፎላቸዋል። ደብዳቤው ዋና ዳይሬክተሯን ለማነጋገር የሚጠይቅ ሲሆን፣ ጉዳዩም አሁን በተጀመረው ዘመቻ ዙሪያ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። አቶ ኦባንግ ጉዳዩን አስመልክቶ ለተጠየቁት ሲመልሱ “የመሬት ነጠቃን በተመለከተ ማንኛውም ዓይነት ውይይት አይታሰብም። የተላከው ደብዳቤ ምንም ይሁን ምን አኑራድሃ ስለ ኢትዮጵያ መንግስትና ስለ ቅጥፈቱ ከበቂ በላይ መረጃ ስላላቸው ሊያሳስቷቸው አይችሉም። እኛም በብዙ ፈርጁ ከምናካሂደው ትግል አንዱ በመሆኑ ነቅተን ጉዳዩን እንከታተለዋለን” የሚል መልስ ሰጥተዋል።
 





     
ድምፃችን ይሰማ
የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የአርቡ ሕዝባዊ ትዕይንት ላይ ሁከት ለመፍጠር ያደረገው ሙከራ ከሸፈ
ሁከት ፈጣሪዎቹ በራሪ ወረቀቶች እንዲበትኑ ተልእኮ ተሠጥቷቸው ነበር
የድርጊቱ ዋነኛ ተዋናይ ዶክተር ሺፈራው እና የፍትህ ቢሮ ሃላፊዎች ናቸው
ባለፈው ሳምንት መንግስት ሕገ መንግስቱንና የራሱን ፍ/ቤቱን ትዕዛዝ በመጣስ ያሰራጨው ‹‹ጂሀዳዊ ሃራካት›› ‹‹ፊልም››ን በመከተል ሙስሊሙ ህብረተሰብ ባለፈው ጁሙዓ በአንዋር መስጊድ ባካሄደው ከባድ ተቃውሞ ላይ መንግስት ሁከት ለማስነሳት ሙከራ አድርጎ እንደነበርና፤ ሙከራውም ሳይሳካ መክሸፉ ተሰማ፡፡ በእለቱ የመንግስት ባለስልጣናት ዶ/ር ሺፈራው፣ የአዲስ አበባ መጅሊስ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሕመድ እንዲሁም የፌዴራል መጅሊስ ሀላፊዎች በጋራ ለመጅሊስ ተመራጭና በአዲሱ የአሕባሽ ማህበር ስር ለተሰባሰቡ ሰዎች አበል በማዘጋጀት አንድ ተልእኮ ሰጥተው ነበር፡፡ ይኸውም ሙስሊሙ ማህበረሰብ ‹‹በጂሃዳዊ ሀረካት›› ፊልም ስለተቆጣ ዛሬ ትንሽ ነካ ብናደርገው ለብጥብጥ ወደኋላ አይልም የሚል ግምት በማዘል የተሰባሰቡት ሰዎች በራሪ ወረቀት በአርቡ የተቃውሞ ትዕይንት መሀል እንዲበትኑ ነበር፡፡ ይበተናል የተባለው ወረቀት ‹‹መስጂዶቻችን የጥቂት አክራሪዎች መፈንጫ አይሆኑም›› የሚል ፅሁፍ ሰፍሮበት የነበረ ሲሆን ይህን ይበትናሉ የተባሉትና ስለተሰጣቸው አደገኛ ተልእኮ በውል የማያውቁ የሚበዙበት ቡድን ስራውን ለማሳካት ወደ አንዋር ቢንቀሳቀስም አንዋር ቢንቀሳቀስም በአንዋር የገጠመው በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ሙስሊምን ሲመለከት ሀሳቡን እንዲቀይር አስገድዶታል፡፡ሰበር ዜና
ከኢዱ ተቃውሞ ቀጥሎ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር የነበረበትና ሰዎች በአደባባይ እንባቸውን እየዘሩ ጭምር ለመሪዎቻቸው ያላቸውን ታማኝነት እንዲሁም መንግስት በመሪዎቻችን ላይ የፈጸመውን አሰቃቂ ቶርች በምሬት የገለጹበት ትይንት ላይ የተገኙት የመንግስት ተልእኮ አስፈጻሚዎች የሚያዩትን ነገር ባለማመንና የሙስሊሙን ቁጣ በቅርበት ማየት በመቻላቸው የተሰጣቸውን ተልእኮ ሳይፈጽሙ ቀርተዋል፡፡ ብዙዎቹ የተልእኮው አስፈጻሚዎች መንግስት እኛን እርስ በእርስ ሊያስገድለንና የራሱን የፖለቲካ ትርፍ ሊያጋብስ በማሰብ የጎነጎነው ሴራ ነው በሚል ስሜት የተሰጣቸውን ወረቀት ሳይበትኑ ተመልሰዋል፡፡ የወረቀቱ መበተን አላማ ወረቀቱን በሚበተንበት ወቅት የሚከሰተውን ግርግር ተጠቅሞ ወደ ሌላ አቅጣጫ መቀየር እንደነበር ተሰምቷል፡፡ ይህ የከሸፈው የጁመዓ ሴራቸው ባለፈው አንድ አመት በመላው ሃገሪቱ ለተፈጠሩ ሁከቶችና ግድያዎች መነሾውና ጠንሳሹ መንግስት መሆኑን ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፡፡
የዚሁ ተልእኮ አስፈጻሚዎ በነጋታውና ከዚያም ቀን በኋላ ከመጅሊስና አቶ ኩማ ደመቅሳን ጨምሮ ከሌሎች የመንግስት ሀላፊዎች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ቁጣ በተሞላበት መለኩ መንግስት ሰጥቷቸው የነበረው ተልእኮ አደገኛ እንደነበርና መንግስት በመሰል ተግባሮች ለምን መሰማራት እንደፈለገም ጠይቀዋል፡፡ በሙስሊሙ መሀከል ግጭት እና አለመግባባት እንዲፈጠር መንግስት ለምን ይፈልጋል? የሚለው ዋነኛው ጥያቄ ነበር፡፡ በተጨማሪም ማክሰኞ ከ‹‹ፊልሙ›› በኃላ ሌሊት ላይ በስህተት ተለቀቀ በተባለው ፊልም ለምን እንደተለቀቀ ተሳታፊዎቹ የጠየቁ ሲሆን አቡበከርን በዚህ አይነት ሁኔታ የሚያንገላታ ቪዲዮ ለሕዝብ መሰራጨቱ ፋይዳው ምንድን ነው? የሚል ሞጋች ጥያቄ ማንሳታቸው ተሰምቷል፡፡ ሆኖም ብዙዎቹ የመጅሊስና የፍ/ቢሮ ሃላፊዎችም በወቅቱ መልስ መስጥት ሳይችሉ ቀርተው እንደነበር ተሰምቷል፡፡ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ውስጥ በገንዘብና በስልጣን ተደልለውም ሆነ መንግስት በጎ የሰራ መስሏቸው በሌላው ህዝብ ላይ በተንኮል የሚሰለፉ ካለ ትልቅ ትምህርት የሰጠ ነው፡፡ ዛሬም ደግመን የምንናገረው የሚሊዮኖችን ጥያቄ በሃይል እርምጃና በተንኮል ለማክሸፍ መሞከር መንግሰታዊ ባህሪ አለመሆኑን ነው፡፡ ከመንግስት የሚጠበቀው ተግባር ህዝብን አስተባብሮ ለልማት ማሰለፍ እንጂ ህዝብን በህዝብ ላይ አነሳስቶ እልቂትን መጋበዝ አይደለም፡፡
አላሁ አክበር!

Monday, February 4, 2013

በደብረብርሃን ነዋሪዎች በፖሊሶች የተፈፀመን የመብት ጥሰት አጋለጡ

  • digg

በአማራ ክልላዊ መንግስት ሰሜን ሸዋ ዞን ዋና ከተማ በሆነው ደብረብርሃን ከተማ ፖሊስ በነዋሪዎች ላይ የመብት ጥሰት እየፈፀመ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች ዝግጅት ክፍላችን ድረስ በመምጣት በሰጡት መረጃ ፖሊስ በፀጥታ ማስከበር ስም በወንጀል ድርጊት ላይ መሰማራቱን አጋልጠዋል፡፡
ነዋሪዎቹ እንደሚሉት ፖሊስ ራሱን ከህግ በላይ አድርጐ ስለሚቆጥር የዜጐችን ህገመንግስታዊ መብት በሚጥስ አሰራር ላይ ተሰማርቷል፡፡ ነዋሪዎቹ ጨምረው እንደሚያስረዱት “ፖሊሶች ከካድሬና ከደህንነት በሚሰጣቸው ትዕዛዝ ንፁሐን ዜጐችን በፖለቲካ አመለካከታቸው እያስጠሩ ያሸማቅቃሉ፣ ያስፈራራሉ፣ ይደበድባሉ፣ ያስራሉ፡፡” ነዋሪዎቹ በምሳሌነት ሲገልፁም “የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም ከቀበሌው ኮሚኒቲ ፖሊስ፣ ከወረዳው ፖሊስ፣ ከክልሉ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ እና ከፌዴራል ፖሊስ የተውጣጣ ቡድን ከለሊቱ 8 ሰዓት ቀበሌ 06 ቀጠና 4 ውስጥ የጌታ ወ/ሚካኤል የተባሉን ግለሰብን ግቢ ከበቡ፡፡ የግቢው ነዋሪዎች ለአካባቢው ነዋሪ በስልክ በማሳወቃቸው የአካባቢው ህዝብ ወጥቶ ምንድነው? ብሎ ጠየቀ፡፡ እዚህ ግቢ የሚኖር አቶ አበበ በቀለ የተባለ ግለሰብ አካባቢውን በጥብጧል የሚል መረጃ ደርሶን ነው ብለው መለሱ፡፡ የመላው አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ የሰሜን ሸዋ ተጠሪ የሆኑት አቶ አበበ ከነጐረቤቶቹ በሠላም ተኝቷል፡፡ በአካባቢው የተፈጠረም የፀጥታ መጓደል የለም፡፡ ማነው እንዲህ ብሎ የነገራችሁ በዚህን ሰዓት ከተለያየ ቦታ የተውጣጣ ፀጥታ አስከባሪዎችስ እንዴት ተቀናጅታችሁ ልትመጡ ቻላችሁ ብለን ብንጠይቃቸው መልስ ሳይሰጡ አቶ አበበንና ለፖሊሶቹ ጥያቄ ያቀረቡትን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ወሰዱ፡፡ የፍ/ቤት ትዕዛዝን ብንጠይቅ ምን አገባችሁ፡፡ የመጠየቅ መብት የላችሁም አሉን፡፡ ለሊቱኑ ለተለያየ ሚዲያ ደውለን በማሳወቃችን ንጋት ላይ በ12 ሰዓት ስትጠሩ ትመጣላችሁ ብለው ታሳሪዎቹ ለቀዋቸዋል” ብለዋል፡፡ ታሳሪዎቹ “የታሠርንበት ወንጀል ይነገረን፤ የከሰሰን ሰው ማነው” ብለው ቢጠይቁም መልስ እናዳለገኙ መረጃ ሰጪዎቻችን ጠቁመውናል፡፡ ያለ አንድ ምክንያት ዜጐችን በአመለካከታቸው ለማዋከብና በሐሰት ለመወንጀል ሲባል የአካባቢው ህዝብ ሠላም ማጣቱም እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል፡፡
በጉዳዩ ላይ የቀበሌው ኮሚኒቲ ፖሊስ አስተያየት እንዲሰጥበት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ ይሁን እንጂ የወረዳውን ፖሊስ አዛዥ ኢ/ር ምንውዬለትን በስልክ አግኝተን ጠይቀናቸው ጉዳዩን አጣርተው እንደሚደውሉ ቢነግሩንም ዜናው እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ምላሽ አልሰጡንም፡፡


Saturday, February 2, 2013

ሕዝቡ በምርጫ እንዳይሳተፍ ጥሪ ቀረበ




ጥር ፳፬ (ሀያ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ኢህአዴግ ሊያካሂደው ባሰበው የአካባቢ ምርጫ እንዳይሳተፍ 39ኙ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ።
ፓርቲዎቹ ህዝባዊ ጥሪውን ያቀረቡት ”ኢህአዴግ ስለ አካባቢ ምርጫ የሰጠው መግለጫ የጥያቄዎቻችንን ትክክለኛነትና አግላይ አቋሙን ያረጋገጠበት ነው” በሚል ርዕስ ባወጡት መግለጫ ነው።
የ ኢህአዴግ ምክር ቤት ጸሀፊ አቶ ሬድዋን ሁሴን ፓርቲዎቹ በምርጫ ላለመሳተፍ መወሰናቸውን አስመልክቶ በቅርቡ በሰጡት መግለጫ ፦<<እነሱ ተሳተፉ አልተሳተፉ የሚጨምሩትም፤የሚቀንሱትም ነገር የለም>> ማለታቸው ይታወሳል።
የ አቶ ሬድዋን መግለጫ ኢህአዴግ ዛሬም በ አገራዊና ህዝባዊ ጉዳዮች ላይ ለሚነሱ ጥያቄዎች በሙሉ ወሳኝም፣ ባለመፍትሔም እኔ ብቻ ነኝ ከሚል የ እብሪት ስሜት አለመላቀቁንና ሀላፊነት በጎደለው ጭፍን ጥላቻ እየተነዳ መሆኑን ያመለክታል ብለዋል።
ባሻገር አህአዴግ በዋና ጸሀፊው አማካይነት የሰጠው መግለጫ በውሸት የታጀለ እና እርስ በርሱ የሚጣረስ እንደሆነ ፓርቲዎቹ በርካታ አብነቶችን በመጥቀስ አመላክተዋል።
አክለውም “ይህ አካሄድ ለማንም የማይጠቅም ከመሆኑም በላይ ብዙ ርቀት ሊያስኬደው እንደማይችል በድጋሚ ሊገለጽ ብቻ ሳይሆን በህዝባዊ ሀይል ሊገታ የሚገባው መሆኑን እንረዳለን” ሲሉም አስጠንቅቀዋል።
ደጋግመን እንደገለጽነው ጥያቄዎቻችን ቀላሎች ናቸው ያሉት ፓርቲዎቹ እነሱም፦መንግስትና ኢህአዴግ ይለያዩ፣የመገናኛ ብዙሀን ፍትሀዊ አጠቃቀም ይኑር!፣የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃነት የመንቀሳቀስ መብት ይከበር!፣ምርጫ ቦርድ ከገዥው ፓርቲ ተጽዕኖ ተላቅቆ በነፃነት ይደራጅ!የህግ የበላይነት ይረጋገጥ!፣በገዥው ፓርቲ አማካይነት ለ አፈና የወጡ ህጎች ይሻሩ! በድምሩ የዜጎች ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ተከብረው የህዝብ የሥልጣን ባለቤትነት ይረጋገጥ ዘንድ የምርጫ ሜዳው ይስተካከል የሚሉ ናቸው ሲሉም መሰረታዊ ጥያቄዎቻቸውን አስፍረዋል።
ነገር ግን ከ ኢህአዴግ መግለጫ ለመረዳት የቻልነው ገዥው ፓርቲ ባለፉት 21 ዓመታት በሄደበት የማናለብኝነትና የሀይል መንገድ ለመቀጠል መወሰኑን እና ችግሮችን ለማስተካከል ፈቃደኛ አለመሆኑን ነው ያሉት ፓርቲዎቹ፤በመሆኑም በምርጫው መሳተፍ የወንጀል አጃቢ ከመሆንና ለገዥው ፓርቲ ይሁኝታ ከመስጠት በዘለለ ፋይዳ እንደሌለው ተገንዝበናል ብለዋል።
መላው የ አገራችን ህዝብም የምርጫው አካል በመሆን ኢዲሞክራሲያዊና ኢህገ-መንግስታዊ ለሆነ አካሄድ ይሁኝታ እንዳይሰጥ ጥሪ እናቀርባለን በማለትም ህዝቡ በምርጫው እንዳይሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።
<<ፓርቲዎቹ መግለጫቸውን ሲቋጩም፦በተባበረና በተቀናጀ ህዝባዊና ሰላማዊ ትግል ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት፤እንዲሁም ከድርጅታችን ይልቅ ለ አገራዊ የህዝብ ጉዳዮች ቅድሚያ በመስጠት በትብብር ለመሥራት ቃላችንን እናድሳለን>>ብለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢህአዴግ ለምርጫ ቀስቃሾች የሚያወጣው ገንዘብ አስደንጋጭ ሆኗል
ኢህአዴግ በመጪው ሚያዚያ ወር ለሚካሄደው የአዲስ አበባ፣ የድሬዳዋ ከተሞች እና የክልል ምክር ቤቶች እና የወረዳዎች ምርጫ በርካታ ሰዎች የምርጫ ካርድ እንዲያወጡ ቤት ለቤት ለሚቀሰቅሱለት ካድሬዎቹ የቀን ውሎ አበል እና የስብሰባዎችና ድግሶች በሚሊዮኖች የመንግሥት ገንዘብ እያወጣ መሆኑን ምንጮች አስታወቁ፡፡
በርካታ ሰዎች ካርድ እንዲያወጡ ቤት ለቤት እንዲቀሰቅሱ መልምሎ የላካቸው በዝቅተኛ ገቢ ላይ የሚገኙ እናቶችን፣ ሴቶችን እና ወጣቶችን ከሴቶች ሊግ፣ ከወጣቶች ሊጎች እና ፎረምና ወጣት ማህበራት እና ዝቅተኛ የየአካባቢው ካድሬዎቹን መልምሎ ሲሆን በቀን ከሃምሳ ብር እስከ 250 እንደ ቀኑ ውጤታቸውና ደረጃቸው እየከፈለ ነው ፡፡
ለአንዳንዶቹም በድርጅቱ ደብዳቤ ለሚመለከታቸው የሥራ መስኮች- የአንበሳ አቡቶቡስ ቴኬት ቆራጭነት፣ በየሴክተርና የመንግሥት መስሪያ ቤቶች በተላላኪነት፣ በአትክልተኝነት፣ በጥበቃ ሠራተኝነት ለመቅጠር ቃል በመግባትና የድጋፍ ደብዳቤ በመስጠት እና ነቃ ያሉ ወጣቶችን ደግሞ ተደራጅተው በሚፈልጉት የሥራ መስክ እንዲሰማሩ የገንዘብ ብድርና የመሥሪያ ቦታ ለማመቻቸት ቃል እንደገባላቸው ታውቋል፡፡ ያስቀመጠው የምርጫ ኮታ ባለመሙላቱም በልዩ ልዩ ምክንያት ላልተመዘገቡ ሰዎች በሚል ምርጫ ቦርድ ለተወሰኑ ተጨማሪ ቀናት ምዝገባውን እንዲቀጥል በውስጥ ደብዳቤ አዞአል ፡፡
የኢህአዴግ ካድሬዎችና በየማህበራቱ ያደራጃቸው ወጣቶች ቤት ለቤት በሚያደርጉት የማስመዝገብ ዘመቻ የቤቱ አባወራ እና እማወራ በማያውቁበት ሁኔታ በቤት ውስጥ ለእንግድነት የመጡ ሰዎችን፣ የቤት ውስጥ ሠራተኞችን ሳይቀር ጊዜያዊ የቀበሌ መታወቂያ ወረቀት በቀበሌዎችና ወረዳዎች በማሰጠት ድርጅቱ ያሰበውን ኮታ ለማሟላት ሌት ተቀን ሲሰራ ቆይቷል።
የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ጽ/ቤት የዜና ምንጮቻችን እንደገለጹልን ኢህአዴግ በርካታ ሰዎችን በአንድ ለአምስት የጥርነፋ ዘዬው (ስትራቴጂ) የምርጫ ካርድ እንዲያወጡለት የፈለገው፣ በምርጫው ወቅት የምርጫ ካርድ ያወጡ ሰዎችን እንዴት አድርጎ የምርጫ ካርዳቸውን ወደ እራሱ የድምጽ ኮሮጆ የሚያስገባበትን የተጠና ዘዬ ለመተግበር ዝግጅቱን በማጠናቀቁ ነው ብለውናል፡፡
33 የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢህአዴግ አጃቢ አንሆንም በማለት ከምርጫው ራሳቸውን ማግለላቸው ይታወሳል።

Tuesday, January 29, 2013

ሕወሐት ለሁለት ተሰነጠቀ፤ ወረቀት ለአባለት ተበተነ
ከኢየሩሳሌም አርአያ
ዛሬ በመቀሌ ለአባላ ትና አልፎም ለህዝቡ በተበተነ የትግርኛ ፅሁፍ እነ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሐዬ፣ ፀጋዬ በርሔ ከነባለቤታቸው እንዲሁም ሌሎች ከድርጅቱ እንዲባረሩTigray People Liberation Front Split በተበተነው መግለጫ ተጠቁሞዋል። በመግለጫው፥ ከጀርባ አሉ የተባሉትና « የዚህ መኅንዲስ» ተብለው የተፈረጁት ስብሃት ነጋ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተባሉት መካከል በዋነኛነት ተፈርጀዋል። እነ ቴውድሮስ ሃጎስ፣አዜብ መስፍንና በረከት እጃቸው እንዳለበት የተነገረለት ይኸው መግለጫ ተከታዩን ይመስላል፤
«ተቆርቋሪ ለሆናችሁ የትግራይ ተወላጆ በሙሉ፤
«ድርጅትህ ሕወሐት እስከ ዛሬ ታግላ እዚህ ደረጃ አድርሰሃለች። በተለይም የሁሉም ነገር አድራጊና ፈጣሪ የነበረው ባለ ራዕይው መሪህ በቅርብ ጊዜ አጥተኽል።
ዛሬ እነዚህን ደካማ ጐኖች ተጠቅመው ለጠላት አሳልፈው ሊሰጡህ የሚፈልጉ ያውም ደግሞ የእኔ የምትላቸው ጅቦች ተነስተውብህ ይገኛሉ። ይህንን ግልፅ ለማቅድረግ አሁን በቅርብ ጊዜ በመቀሌ የድርጅቱ ማ/ኰሚቴ ስብሰባ አካሄደን ነበር። በዚህ ስብሰባ ላይ ነው እንግዲህ ተከታዩ ነገር የተነሳው። ይኽውም፥ እነ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሐዬ፣ ፀጋዬ ከሚስቱ ጋርና ሌሎችም ያሉበት ይህን አሉ፤
«ድርጅታችን ጨርሶ ተዳክሞዋል። እኛ የኢትዮጲያ ሕዝብ ትግል መስራች ሆነን ሳለ ወደኋላ ተገፍትረን በአንፃሩ ሌሎች ከእኛ ኋላ የተፈጠሩና ራሳችን ያሳደግናቸው ሲጠናከሩ ድርጅታችን ግን እየተዳከመ በመሄድ ላይ ነው። ባዛው መጠን ሕዝባችን እየተጎዳ ነው። ስለዚህ አሁን ካጋጠመን አደጋ መውጣት ካለብን ከድርጅቱ -የተወገዱትን ግን በመጥፎ ጎዳና ያልተሰማሩትን መልሰን ወደ ፓርቲው ማስገባት አለብን። ይህ ካልሆነ ግን የሕዝብ ትግል አውላላ ሜዳ ላይ ጅብ በልቶት ሊቀር ነው።» በማለት ከጠላቶቻችን ጋር እንታረቅ እያሉን ነው።
“ሕዝባችን አስተውል። በዚህ አይነት ዳግመኛ በድርጅታችን ተኃድሶ እንደሚያስፈልገን ነው የተገነዘብነው። በሚቀጥለው የካቲት ወር በሚካሄደው ጉባኤያችን ይህንን ጉዳይ ትኩረት ሰጥቶና አጥርቶ (ውሳኔ አሳልፎ) እንደሚወጣና እነዚህንና መሰሎቻቸው ከሚያራምዱት አቋም ጋር ጠራርጐ እንደሚያስወግድልን ተስፋ እናደርጋለን። በዚህም እያንዳንዱ እንደከዚህ ቀደሙ የተለመደ አስተዋፅኦ (ሚና) እንደሚያበረክት አንጠራጠርም።
በተጨማሪ ከጀርባ ሆኖ የዚህ አፍራሽ ዋና ቀያሽ መሃንዲስ ስብሃት ነጋ መሆኑን ደርሰንበታል።”

Monday, January 28, 2013

ኢትዮጵያ በወታደራዊ እንቅስቃሴዎች እየታመሰች ነዉ::
ኢትዮጵያ ዉስጥ ዳር አገርም ሆነ መሀል አገር በየቦታዉ የሚታየዉ ወታደራዊ እንቀስቃሴ ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ መምጣቱን አዲስ አበባና በየክልሉ የሚገኙ ወታደራዊ ምንጮቻችን ገለጹ። በተለይ የመለስ ዜናዊ ሞት ለህዝብ ይፋ ከሆነበት ግዜ ጀምሮ ኢትዮጵያ ከደርግ ዘመን ወዲህ ታይቶ በማይታወቅ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ እየታመሰች መሆኗን በየክልሉ የሚገኙ ዘጋቢዎቻችን የመከላከያ ምንጮችን ዋቢ በማድረግ የላኩልን ዜና ያስረዳል።
ከሁለት ሳምንት በፊት ከ35 በላይ ታንኮችን የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ምስራቅ የአገሪቱ ክፍል የተጓዙ ሲሆን፣ ከአራት ቀን በፊት ደግሞ ከ30 ያላነሱ ታንኮች በከባድ ተሽከርካሪዎች ተጭነዉ ወደ ሰሜናዊዉ የአገራችን ክፍል ተጉዘዋል። ጠብ አጫሪዉ የወያኔ አገዛዝ የጦር መሳሪያዎችን ለምን በዚህ አይነት ፍጥነትና ብዛት እንደሚያንቀሳቅስ በትክክል ለማወቅ ባይቻልም በብዙ ምዕራባዉያንና የአገር ዉስጥ ወታደራዊ ጠበብቶች ግምት አገሪቱ ውስጥ በየክልሉ በሁሉም መስክ የሚታየው ህዝባዊ አመጽና አለመረጋጋት ወያኔን ክፉኛ ስላስደነገጠዉ ህዝባዊ እንቅስቃሴዉን በወታደራዊ ሀይል ለመቆጣጠር የታለመ ሊሆን ይችላል ተብሎ ይታናል። በሌላ በኩል ደግሞ የተለያዩ ስርዐቱን በትጥቅ ትግል የሚፋለሙ ሀይሎች በተለይ በቅርቡ የተቋቋመዉ እራሱን “የግንቦት ሰባት ሀይል” ብሎ የሚጠራዉ የተለያዩ ሀይሎች ስብስብ ወያኔን ክፉኛ እንዳስደነገጠዉ ብዙ ለአገዛዙ ቅርበት ያለቸዉ ምንጮች በመናገር ላይ ናቸዉ።

Friday, January 18, 2013

ሰበር ዜና መንግስት በምስክር እጦት ጭንቅ ውስጥ ገብቷል፡፡ የብዙዎች ምላሽ ‹‹በሐሰት አንመሰክርም›› የሚል ሆኗል፡፡     
በእስር ላይ የሚገኙ መሪዎቻችን እና ሌሎች ወንድሞቻችንን በአሸባሪነት ከስሶ ሲያንገላታ የቆየው መንግስት በምስክር እጦት ችግር ውስጥ መግባቱ ታወቀ፡፡ መንግስት ኮሚቴዎቻችን ላይ በመሰረተው ክስ በሐሰት ሊያስመሰክራቸው ያዘጋጃቸው 197 (አንድ መቶ ዘጠና ሰባት) ሰዎች መኖራቸውን ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም የተገለጸውን ቁጥር ያህል ምስክሮች ማግኘት አልቻለም፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው ለምስክርነት የታሰቡት ብዙዎቹ ግለሰቦች ምስክር ለመሆን ፈጽሞ ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተከትሎ ነው፡፡ መሪዎቻችን ባልዋሉበት እና በማያውቁት ወንጀል የከሰሳቸው መንግስት በየአካባቢው ‹‹ድጋፍ ይሰጡኛል፤ እተማመንባቸዋለሁ›› የሚላቸውን ግለሰቦች ለምስክርነት ተደጋጋሚ ጥሪ ቢያደርግላቸውም በሐሰት አንመሰክርም የሚል ቆራጥ አቋም ማሳየታቸው ተሰምቷል፡፡
ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳቸውን የመብት ጥያቄዎች ለመንግስት እንዲያደርሱለት በአስር ጣቱ አምኖባቸው የመረጣቸው ኮሚቴዎቻችን እና ሌሎች ዳኢዎች መንግስት እውቅና ሰጥቷቸውና ስለ ሰላማዊነታቸውም በመንግስት ብዙሀን መገናኛዎች መስክሮላቸው፤ ከአገሪቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ድርድር ሲያደርጉ እንደቆዩ ይታወሳል፡፡ ሆኖም መንግስት የቀረቡትን የመብት ጥያቄዎች ለመመለስ አለመፈለጉና እነሱም ጥያቄዎቹ እንዲመለሱ ተደጋጋሚ ጥያቄ በማቅረባቸው ‹‹አሸባሪ›› የሚል ታፔላ ተለጥፎባቸው ከሐምሌ 2004 ጀምሮ በእስር እና ስቃይ ላይ የሚገኙት መሪዎቻችን ንጹህ መሆናቸውን የተረዱ ብዙዎች በሀሰት እነሱ ላይ ለመመስከር ፈቃደኛ አለመሆናቸውን በቀጥታ መግለጽ ችለዋል፡፡
መንግስት ይህን የመስካሪዎች እምቢታ ተከትሎ አዳዲስ ምስክሮችን ለመመልመል ቀን ከሌት እየሰራ እንደሚገኝ ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ የመንግስት ደህንነቶች ቁጣና ንዴት በተሞላበት መልኩ ሰዎችን ምስክር እንዲሆኑ በአካልም ጨምር እየሄዱ በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተጨማሪም ደህንነቶቹ በአዲስ አበባ አንድ አንድ መስጊዶች በመገኘት ግለሰቦችን በግድ በመያዝ ምስክር እንዲሆኑ እየጠየቁ ሲሆን፤ ፈቃደኛ አልሆንም ያሉ ሰዎችንም ‹‹የማትመሰክር ከሆነ አንተን ነው የምንከስህ›› በማለት በማስፈራራት ላይ ይገኛሉ፡፡ የሀሰት ምስክርነትን (ሸሀደተ ዙር) አስከፊ ወንጀልነት የተረዱ በርካታ ሙስሊሞች አሁንም በእምቢታቸው የዘለቁ ሲሆን፤ አሁንም ግን ጥቂት የማይባሉ ‹‹ተገደን ነው የምንመሰክረው›› የሚል ምላሽ እየሰጡ ያሉ ግለሰቦች በመኖራቸው ከዚህ ከድርጊታቸው እንዲታቀቡና ከአስከፊው የሀሰት ምስክርነት መዘዝ እራሳቸውንና ቤተሰባቸውን እንዲጠብቁ አደራ እንላለን፡፡
አቡበከር ሲዲቅ (ረ.ዓ) የአላህ መልዕክተኛ (ሶ.ዐ.ወ) እንዲህ ማለታቸውን ዘግበዋል፡- ‹‹የከባዶች ከባድ የሆነውን ሀጢአት አልነግራችሁንም›› እኛም ‹‹አዎ! የአላህ መልዕክተኛ እንዴታ!›› አልን፡፡ እሳቸውም ‹‹በአላህ ማጋራት (ሽርክ) እና ወላጅን ያለመታተዝ ናቸው›› አሉና ተደላድለው ከተቀመጡበት ድንገት ተነስተው እንዲህ አሉ ‹‹አዋጅ! ውሸት መናገር እና በሐሰት መመስከ›› እያሉ የሚያቆሙት አልመስልህ እስኪለኝ ድረስ ደጋገሙት ፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል

Thursday, January 17, 2013

‹‹አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም››
ሁለት ወቅታዊ ጉዳዮች
1. ከመለስ ሞት በኋላ መረጋጋት የተሳነው ኢህአዴግ ከበርካታ ችግሮች ጋር ፊት ለፊት ተፋጧል፡፡ ከችግሮቹ በከፊልም የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡ …በረከት ስምኦን የነበራው ተደማጭነት እየተሸረሸረ ነው፣ የበረከት ባለቤት የበረከትን መፅሃፍ ለመሸጥ (ገዥ ፍለጋ) በየተቋማቱ እየተንከራተቱ ነው፤ አዲሱ ለገሰ የተደማጭነት መስመሩን ‹‹ኢህአዴግን ለማጠናከር›› በሚል ምክንያት ይበልጥ እያደረጀ ነው፤ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከቀን ወደ ቀን በህወሓት ውስጥ ተሰሚነቱ እየጨመረ ነው፣ በእርግጥም ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች የአስጊ ህመም ችግር የሌለባቸው ተብለው የሚመደቡት ደብረፅዮን፣ አባይ ፀሀዬና ቴውድሮስ አድሃኖም ናቸው፣ አቦይ ስብሃት ነጋ ‹‹መፈንቅለ ፓርቲ›› በህወሓት ውስጥ ለማድረግ ቀን ከለሌት እያሴሩ ነው፣ ከሁለት ወርበኋላ የሚደረገው የኢህአዴግ ጠቀላላ ጉባኤ አዲስ ነገር ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል፤ ኦህዴድ በሹም ሽር ሊናጥ ነው፣ አለማየሁ አቱምሳ በሩቅ ምስራቅ ለሚከታተለው ህክምና እስከአሁን ያለውንም ሆነ በቀጣይ የሚያስፈልገውን ወጪውን እየሸፈነ ያለው ሼክ መሀመድ አላሙዲ ነው፤ ለምን? አለማየሁ የመንግስት ባለስልጣን ነው፣ በተጨማሪም ሆን ተብሎ በተሰጠው መርዝ ነው ታማሚ የሆነው የሚባለውን ወሬ ይዘን፣ ከዚህ ጀርባ ማን ነው ያለው? የሚል ጥያቄ መቀርቡ አይቀርም (የሰማሁት መረጃ ጆሮ ያቃጥላል) ግን ለምን? ኩማ ደመቅሳ መልካም አስተዳደር ባለማስፈንና ሙስናን መቆጣጠር ባለመቻል እየተወቀሰ ሲሆን፣ በተቃራኒው አባዱላ ገመዳ በኦህዴድ ውስጥ መረጋጋትን በማስፈንና ስራውን በብቃት በመወጣት በሚል ተመስግኗል፣ (የማኪያቬሊ ከፋፍለ ግዛ ማለት ይህ ይሆን?) በሚያዚያ ወር የሚደረገውን ምርጫ ተከትሎ የቱኒዝያንና የግብፅን መሰል ህዝባዊ አመፅ ይቀሰቀሳል በሚል አገዛዙ ፍርሃት አድሮበታል፣ 33ት ፓርቲዎች ነገ በምርጫው ላይ የሚኖራቸውን አቁም በሰማያዊ ፓርቲ ፅፈት ቤት ከጠዋቱ አራት ሰአት ላይ የፋ ያደርጋሉ (በእርግጥ የደረሱበት ውሳኔን ብግሌ ትክክል ነው ብዬ አምናለሁ፣ ከዚህ ውጪም ገዥው ፓርቲን ለድርድር የሚያስገድድ ዕድል የላቸውም)፣ በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ኦስትሪያዊውን አገር ጎብኚ ማን ገደለው? ለምን ተገደለ? የደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት ድራማስ በማን የተቀነባበረ ነው? ኃላፊነቱንስ ማን ነው የሚወስደው? የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ ¬¬‹‹ለሽብር ድርጊት ሊውል ሲል ደረስኩበት›› በማለት ከተቀበረበት እንዳወጣው የነገረንን የጦር መሳሪያ ማነው የቀበረው? ይህ መሳሪያስ በእነማን የክስ መዝገብ ላይ ማስረጃ ሆኖ ሊቀርብ ነው የታቀደው? በቀጣይስ የቦንብ ፍንዳታ በየትኛው ከተማ፣ መቼ፣ ስንት ሰዓት ላይና በምን ሁኔታ ይደርስ ይሆን? …ይህኛው መንገድስ የት ድረስ ያስኬዳል? ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄትን ማፈኑስ ለምን አስፈለገ?
2. በሽብርተኝነት የተከሰሱትን የህዝብ ሙስሊም መሪዎችን በይቅርታ ለመፍታት መንግስት የማጭበርበሪያ ስልቱን እየተጠቀመ ነው፡፡ በዕለት ሀሙስ ጥር 2 ቀን 2005 ዓ.ም በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሳቅ ይመሩ ከነበሩት ሽማግሌዎች ውስጥ የተዘጋጀ ሶስት ሰዎች ያሉት አንድ ቡድን በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተገኝቶ ነበር፡፡ ከቡድኑ አባላት ፓስተር ዳንኤል እና ፕሮፌሰር አህመድ ዘካርያስ ለታሳሪዎቹ እንዲህ የሚል የማጭበርበሪያ መደራደሪያ አቅርቦ ነበር፡- ‹‹ጉዳያችሁ በፍርድ ቤት እየታየ ነው፤ ስለዚህም ክሱ አሁን ባለበት ደረጃ ሊቋረጥ አይችልም፡፡ እናም ክርክራችሁን አቋርጡና ጥፋተኛ ነን በሉ፣ ከዛም ፍርድ ቤቱ ከፈረደባችሁበኋላ ‹ይቅርታ› ጠይቃችሁ እናስፈታችኋለን›› ሆኖም የሙስሊሙ መሪዎች ‹‹ይህንን በጭራሽ አንቀበለውም፣ ጥፋተኛ ነኝም አንልም፣ አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም›› ሲሉ በድፍረትና በቁርጠኝነት መልሰውላቸው ወደ እስር ክፍላቸው ተመልሰዋል፡፡ በእርግጥም የኮሚቴው አባላት ትክክለኛ ውሳኔ ነው የወሰኑት፡፡ ምክንያቱም ይህ የሽምግልና ቡድን ቀንደኛ የስርአቱ ደጋፊ ሲሆን፣ መደራደሪያ ብሎ የሚያቀርበው ሁሉም ነገር የአገዛዙን የፖለቲካ ጥቅም የሚያስከብር ነውና፡፡ በድህረ ምርጫ 97 የታሰሩትን የቅንጅት አመራርንም በዚህ አይነት መልኩ መሸወዱ ይታወሳል፡፡(በነገራችን ላይ ሽማግሌዎቹ በተጠቀሰው ዕለት አንዱአለም አራጌን ጠርተው አናግረውታል፤ እስክንድር ነጋን ግን ዘለውታል፡፡ ለምን? ሌላው አስገራሚ ጉዳይ ደግሞ የሽማግሌ ቡድኑ ለሙስሊሙ መሪዎች ‹‹የመጣነው አንዱአለምን ፈልገን ነው፣ እናንተን እግረ መንገዳችንን ሰላም እንበላችሁ ብለን ነው›› ሲሏቸው፣ ለአንዱአለም ደግሞ የዚህን ግልባጭ ምክንያት ሰጥተውታል፡፡
http://www.ecadforum.com

Thursday, January 3, 2013


Ethnic clash among AAU 4 Kilo students causes damages

Listen to this article. Powered by Odiogo.com


Addis Abeba
3/1/13

A violent ethnic based conflict among Addis Abeba University (AAU) College of Natural Sciences/4 Kilo Campus students that started yesterday afternoon (02-01-2013) 4PM resulted in the damage of properties and injuries of students.
According to De Birhan's sources the violent conflict had reportedly started after "unidentified students posted a poster containing a derogatory message on the College's main Library and two other places about Oromo ethnic students". The conflict continued until mid night when Oromo ethnic students non violently blocked and banned most students from entering or leaving their dormitories. The tension turned out violent when a student was severely attacked around mid night.

The violent clash that continued until early morning had restarted after it was contained several times by the Federal Police who surrounded the Campus and tried to quell the situation. Several students from the conflicting groups that form along ethnic lines were severely wounded and were taken to Zewditu and Yekatit 12 Hospitals. Windows, doors and other properities of the Univeristy and many students' dormitories were damaged in the clash that continued until 3AM this morning.

Students that have been suspected to have had direct involvement in the violence are now under Police custody. Although there is Police presence and calamity in the Campus, students are still barred from either leaving or entering the Campus.

Similarly, De Birhan has learnt that there was a fall out between students and the College's Administration for the past two weeks over grading issues.

The College had introduced a new Grading System/scale, which requires students to score more than 95 out of 100 to get an "A", however students protested the new scale and class representatives had to meet with the College Administration on the matter. Due to disagreement, some representatives had even walked out of the meeting. After tense meeting and talks, the Administration finally agreed to reduce the required score to get an 'A' to 85 points out of 100.

The College was founded on March 20, 1950 by Emperor Haile Silassie I who declared the foundation of the University College of Addis Ababa, including the faculties of Arts and Science. At the time there were only 33 students enrolled. At present, over 5000 undergraduate, 3000 extension, over 1000 MSc and 50 PhD students are enrolled in the College. The Faculty today comprises six departments: Biology, Chemistry, Physics, Earth Sciences,Mathematics and Statistics and four programs namely Biothechnology, Food Science, Computational Science, Matreials Science and Environmental Science.
Breaking News: Protest erupts at Addis Ababa University

Addis Ababa University main campus
Awramba Times (Addis Ababa) – Protest sparked at the College of Natural Sciences, Arat Kilo Campus of the Addis Ababa University. According to our sources in Addis Ababa, The main cause of the protest is due to an ethnic derogatory poster against Oromo-ethnic students placed at the College’s main Library and two other places.
So far, more than 20 students from the conflicting ethnic groups were wounded and were taken to government hospitals. On the other hand Police have accused several students of causing damage to university property, including broken windows and doors. More details to come…
http://www.awrambatimes.com