Sunday, February 17, 2013

አበበ ገላው ተጫማሪ የግድያ ዛቻ ደረሰው



abebe gelaw
(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛ አበበ ገላው ተጨማሪ የግድያ ሙከራ ዛቻ እንደደረሰው በጎግል ቮይስ በኩል በድምጽ ማስረጃ አቀረበ። “አበበ ደምህን እንጠጣዋለን፤ ከኛ የትም አታመልጥም” ሲል አስፈራሪው ሰው ይሰማል። ይህን ተከትሎ አበበ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው “የህወሃቶች ዛቻ እና የዘረኝነት ፉከራ ቀጥሏል። እስከ አሁን ያልተገለጠላቸው ሃቅ እንኳን ዛቻ ሞት ከትግላችንም ሆነ ከቁርጠኛ ጉዞአችን ፈጽሞ አይገታንም። ነጻነት ወይንም ሞት ብሎ የተነሳን ህዝብ ማንም አንባገነን አያስቆመውም። እኔ ብሞትም በዛ በታላቅ አደባባይ ላይ የተናገርኩት እውነት ግን ፈጽሞ አይሞትም፣ ምክንያቱም በያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ልብ ውስጥ የታመቀ ሃቅ ነውና። ሃቅ ሲታፈን ፈንድቶ መውጣቱ ያለ እና ወደፊትም የሚኖር ነው።”

No comments: