Thursday, November 2, 2017

የህውሃት የዘረኝነት ፓለቲካና መዘዙ ( ገዛኸኝ አበበ )

 November 2,2017


ወያኔ (ኢህአዲግ)የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ትልቁ የፖለቲካ አጀንዳ አድርጎ የተነሳው ሕዝብን ከሕዝብ ጎሳን ከጎሳ ሀይማኖትን ከሀይማኖት የፖለቲካ ድርጅትን ከፖለቲካ ድርጅት  በማጋጨትና በማጣላት ላይ ሲሆን ህሕዋት እያራመደ ባለው የዘርና የጎሳ ፖለቲካ የተነሳ በኢትዮጵያ ታሪክ ከመቸውም ጊዜ በላቀ እና ታይቶ በመይታወቅ ሁኔታ የወያኔ መንግስት አሁን የኢትዮጵያን ህዝብ በሁሉም የኢትዮጵያ ክልልና አካባቢ  ሕዝቡ ኢትዮጵያዊነቱን እንዳያይ በዘር እየከፋፈለው ነው:: የህውሃ/ኢህአዴግ ገና ወደ ስልጣን ብቅ ሲል በጦርነት ከደርግ የሚረከባቸውን ቦታዎች ፣ዳገትና ቀበሌዎች ሁሉ በቤተሰብ ሳይቀር እየከፋፈለ በተለያዩ ጥቅማጥቅሞች እያሰረ ልዩነታቸውን ብቻ እያሳየ ሌላ አማራጭ ያልነበረው ህዝብ ሲቀበለው ቆይቶ አሁን በክልል በዞን በወረዳ በቀበሌ እና ሰፈር ድረስ በዘርና በጎሳ ከፋፍሎ ይህ ወያኔ ከደደቤት በረሃ ይዞት የመጣው የዘረኝነት ፖለቲካ መዘዝ  ዘሬም በኢትዮጵያ ውስጥ ተንሰራፍቶ  በየሰፈሩ አሁን የእንትን ሰፈር ልጅ ከእንትን ሰፈር ልጅ ጋር በጩቤ በድንጋይ ሲፈነካከት ሲተራረድ ማየት ምንም አዲስ ነገር አይደለም፡፡

የአንዱን ወረዳ ነዋሪ ከሌላኛው ወረዳ ነዋሪ ጋር በሆነ ባልሆነው ሲኮራረፍ ሲገዳደል ሲቀጣቀጥ ማየት ምንም አዲስ አደለም፡፡ አንዱ ዞን ከሌላኛው ዞን ጋር በስራቸው በሚያስተዳድሩት ህዝብ ስም ጥቅም እየነገዱ አንዱን ከአንዱ አባትን ከልጁ እናትን ከልጇ ወንድምን ከወንድሙ ምን አለፋችሁ በቃ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ውስጥ እንደምታዩት ጠላቶች ሆነን ስንጨራራስ ስንተራረድ እንገኛለን፡፡ሰው ከሰው ጋር ለምን ይጋጫል ለምን ይገዳደላል የሚለው እውነተ ውስጥ አልገባሁም እርሱ ራሱን የቻለ ተፈጥሯዊ ክስተት ስለሆነ፡፡በዛም አለ በዚህ የመከፋፈላችን የመጨረሻ ውጤትና ምክንያት ፍጅት ነው፡፡ ሆኖም ፍጅት ሲባል ግን ኢትዮጵያ ውስጥ ሊነሳ የሚችለው ፍጅት እንደሁቱና ቱትሲ ይሆናል ብላችሁ ግን አታስቡት፡፡ መቸም ቢሆን ይህ ጉዳይ ሊከሰት አይችልም፡፡ በብሄር ግጭት ተነስቶ ኢትዮጵያ ሃገራችን ትጠፋለች አንድ ዘር ይጠፋል ማለት አይቻልም፡፡ ለዚህ ራሱን የቻሉ እውነተኛ ምክንያቶች አሉ፡፡ ሌላው ዓለም ላይ የሌሉ ሃገራችን ውስጥ ግን እንደ ዕድል ብቻ ሆኖ ያሉ ነገሮች ሕዝባችን ሳይማር ተፈጥሮ ብቻ አስተምራ ያኖረችው ትውልድና ትስስር በመሆኑ ብቻ አብረውን የሚኖሩ እውነቶች አሉ፡፡

ወያኔ ኢህአዴግ ግን ከዞን እና ቀበሌ ባለፈ የመጨረሻ ሴራውን በክልል በቋንቋ፣ ዘር ፣ቀለም ወዘተ እያለ በባህል፣ በእምነት እያለ የሚታዩና የማይታንን ልዩነቶች እየፈጠረ በመካከላችን ምንም አይነት ችግርና  ሳይኖር በፍቅር የኖረን ሆነን ሳለን ህህዋት ከጅምሩ ይዞ የተነሳውን  በቋንቋና በዘር ልዩነት ላይ የተመሰረተው የፌደራል ሥርአትና ኢትዮጵያን የመሰነጣጠቅ ሴራው  አሁን ላይ ስር እየሰደደ መጥቶ በኦህዴድ፣ ብአዴንና ደህዴድን የመሳሰሉ የመሳሰሉ የወያኔ አለቅላቂዎችና  አሽከሩች ተጨምረውበት በእነዚህ የኢትዮያን ሕዝብ ደም መጣጭ ድርጅቶች በኩል እየተገበረ ያለውን ኢትዮጵያን የመሰነጣጠቅ እና ለአስተዳደር ለማመቻቸት በመሰለ ሴራና ተንኮል ህዝባችን አንድነቱ ፍርሶ አሞቱ ፈሶ ኢትዮጵያዊው ወኔ እንዲደርቅ በማድረግ ለራሳቸውየሚጠቅማቸውን ለህዝባችን እና ሃገራችን ግን ትልቅ የአንድነት ነቀርሳን ተክለውብን ምኞታቸውን እያሳኩ ይገኛሉ፡:

ይህ የወያኔ የዘረኝነት ፖለቲካ መዘዝ ስር እየሰደደ በጣም በአሳሳቢ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ አስከፊና አሳዛኝ የሆኑ የተለያዩ ችግሮች እየወለደ፤ ጸብና ግጭቶችን እያበራከተ የዜጎችን ሕይወት በቀላሉ እየቀጠፈና የሕዝቦችን ሀብት በማውደም፣ቤቶችን በማቃጠል መጥፎ ክስተት  እየተከሰተ ይገኛል። ከዚህ በፊት እንደምናስታውሰው  በምሥራቅ ኢትዮጵያ ደገሃቡርና ጅጅጋ፤ በምሥራቅ ሀረርጌ ጋራሙለታ፤ በደኖ አንስቶ በባሌና በአርሲ በሚገኙ አካባቢዎች በዘር ላይ የተመሰረቱ ግጭቶችና የሰው ሕይወትና ንብረት የወደሙበት በምሳሌነት ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው። በምዕራብ ኢትዮጵያም ቢሆን በተለያዩ ወቅቶች በአሶሳ በባምባሲ፤ በሰሪ፤ በጋምቤላ በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ፤ ነቀምት፤ አምቦም ለዚሁ አስከፊ ሁናቴ የሚጠቀሱ ናቸው። በአርሲ ክፍለ ሀገር በአርባጉጉ አውራጃ ውስጥ በሚገኙ ጎሎልቻ፤ ጨሌ፤ ጃጁ፡ መርቂ በተሰኙ ወረዳዎችና አካባቢዎች በርካታ መኖሪያ ቤቶች የወደሙበት፤ ሕይወት የጠፋበት፤ የሰው ልጅ እንድ ከብት አንገትና ጡቶች የተቆረጡበት አሰቃቂና አሳዛኝ በድሎች ተካሂደዋል። በሌላ ቦታ ደግሞ ከነ ነፍሰሕይወታቸው ወደገደል ተውርውረው እንዲፈጠፈጡ የተደረጉም እንዳሉ የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ሲሆን ከሰሞኑ ደግሞ እንዳየነው ለሳምንታት በዘለቀው በኦሮሚያ እና በሱማሌ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት እንዲሁም በኢሊባቡር በአማራና በኦሮሞ ዜጎቻችን መካከል በተከሰተው ግጭት ለብዙ ሰዎችን መፈናቀልና ህይወት መጥፍት ምክንያት መሆኑ ይታወሳል በኢትዮጵያ እየተስፋፋ ያለው  የእርስ በእርስ ግጭት ሆነ ተብሎ በህውሃት የበላይነት የሚመራው መንግስት በስልጣን ለመቆየት የሚጠቀምባቸው ስልቶች እንደሆኑ ሁላችንም ጠንቅቀን ልናውቅ ይገባል

በምንም መንገድ ከታሪካዊ አመጣጡም ቢሆን እንደተረዳነው ወያኔ ኢህአዴግ ለኢትዮጵያ አንድነት ሳይሆን የታገለው አሁንም የሚሮጠው ለእነዚህ አላማዎች ብቻ ነው፡፡ አንድም ታላቋ ትግራይን መመስረትና የአማራውን  ተሰሚነት አኮላሽቶ መቅበር ነው፡፡ለዚህም አማራውን ዝም ካልነው አያስቀምጠንምየሚለው የመለስ መፈክር በቂ ምስክር ሲሆን ይህንን የሚያረጋግጡም በርካታ የምስልና የድምፅ ቅጅዎች በተለያዩ ነፃነት ናፋቂ የየትኛውም ብሄር ታጋዮች እጅ ይገኛል፡ከዚህ በፊት ኢትዮጵያን ሲመሩ የነበሩት መሪዎች ሁሉ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በማስከበረ ሕዝቡም አንድነቱን ጠብቆ እንዲኖር ብዙ መስዋትነትን  ከፍለዋል በወያኔ መንግስት እንደ አውሪ የሚቆጠረው ደርግ ሳይቀር ለኢትዮጵያ አንድነት ምሳሌ ናቸው ::ደርግ በርካታ አንቱ የሚያስብሉት ትግባራትን ፈፅሟል፡፡ በኋላም ለውድቀት የዳረገው በትክክል ደርግን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ጠልቶት ሳይሆን በመካከላቸው በነበረው ተራ የስልጣን ሽኩቻ ምክንያት በነበራቸው የሃሳብ  መለያየት፣ ውስጣዊ ሴራ እና አማራጭ በማጣት አንድን የደርግ ወታደር በሁለት ብር ሂሳብ ለወያኔ በሰጡ ባስጨረሱ ጀኔራሎች ሴራ እንጅ በወያኔ ጥንካሬ እንዳልሆነ እውን ነው፡፡

የሚገርመው ግን የኢትዮጵያን አንድነት ለማጥፋት አላማ ይዞ የመጣው ወያኔ ስልጣን እንደያዘ የጀመረው የደርግን ጅማሮዎችን በሙሉ ከምድረ ኢትዮጵያ ማጥፋት እና ማቃጠል አንድነቷና ዳር ድንበሯ ተከብሮ የቆየውን ሀገሪቷን መሸጥና መቆራራጥ ሀገሪቷን ወደብ አልባ በማድረግ ለታሪክ መጥፎ የሆነ ጠባሳ ማስቀመጥ ነበር ይህንንም  ከሻቢያ ጋር በመሰማማት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ አድርጎታል:: ወያኔ ኢህአዴግ አሁን የያዘው ስትራቴጅ ደግሞ የማያዋጣው ማጥ ውስጥ ስለከተተው የሚከተለው እንደ ትግሉ በግልፅ ራሱን በመገንጠል አላማ ማለትም የመሄድ ዓላማ ሳይሆን ተቃራኒውን ነው፡፡ ይህም ማለት አሁን በምኑም በምኑም ምንያት የከፋፈለውን ህዝብ የበለጠ በመከፋፈልና የመለያያ ታሪኮችን እንደመልካም አስተማሪ ታሪክ በመምዘዝ እና አደባባይ በማውጣት /ሆኑ አልሆኑ የሚለው ባይታወቅም ምንጭ ባይኖረውም/ አንዱን ከአንዱ በማፋጀት እራሱ መሄዱን ሳይጀምር ሌሎች በየአቅጣጫው እንዲሄዱ በማድረግ የተዳከመች ኢትዮጵያ የተፈረካከሰች ኢትዮጵያ ስትቀርበሉ እኔም የድርሻየን እናንተ ከሄዳችሁማብሎ ለመነሳት ነው ያሰበው፡፡ አንድ ልናውቀው የሚገባ  እውነት  ይህች ሃገር በፍጹም ልትበታተንና ልትጠፋ አትችልም:: ይህንም ውሃቶችና የወያኔ ተላላኪ፣ተለጣፊዎቹ ኦህዴድ፣ ብአዴንና ደህዴድ ያወቁት አይመስለኝም  ፡፡ ይህ ህዝብ አንድ ሆኗል በወያኔ ተንኳልና ሴራ አሁን ላይ በተለያዩ ነገሮች ቢጋጭም የተጋባ፣ የተዋለደ፣አብሮ የበላና ፣የጠጣ አብሮ ለኢትዮጵያ አንድነት ሲል የታዋጋ የደማና የቆሰለ ሕዝብ ነው :: ይህ እውነታና ሚስጥር ያልገባቸው አንዳንድ የወያኔ ኢህአዴግ ሴራ ማስፈጸሚያና መጠቀሚያ መሆናቸውን ያላወቁ በስሜት የሚነዱ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ናቸው፡፡ስለሆነም የኦሮሞው፣የአማራው፣የአፋሩ፣የትግራዩ፣የጋምቢላው ........ሕዝብ የወያኔ የዘር ፖለቲካ ማስፈጸሚያ እንዳይሆን ሊጠነቀቅ ይገባል እያልኩኝ እዚህ ላይ ላጠቃልል:: ውድቀት ለዘረኛው የወያኔ አገዛዝ !!

የኢትዮጵያ አንድነት ለዘላለም ተጠብቆ ይኖራል!!

gezapower@gmail.com

Monday, October 16, 2017

አቶ በረከት ስምኦን ሃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው ለመልቀቅ ጥያቄ አቀረቡ።


October 16,2017

በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ምርምር ማዕከል የኢንዱስትሪ ዘርፍ መሪ ሚኒስትር ሆነው ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ በረከት ስምኦን ሃላፊነታቸውን በፈቃዳቸው ለመልቀቅ ጥያቄ አቀረቡ።
ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ምንጮች ለቢቢሲ እንዳረጋገጡት አቶ በረከት የሥራ መልቀቂያ ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ አስገብተዋል።
አቶ በረከት ስምኦን ለበርካታ ዓመታት በቦርድ ሰብሳቢነት ሲመሩት ከነበረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክም ሊለቁ እንደሆነ ባለፈው ሳምንት ተነግሯል።
አቶ በረከት ባለፈው ሳምንት የሥራ መልቀቂያ ደብዳቤያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ማስገባታቸው የተነገረ ሲሆን፤ ለመጨረሻ ጊዜ በቢሮአቸው ተገኝተው የነበሩት ሀሙስ ዕለት ነበር።
አቶ በረከት በተመሳሳይ ጊዜ ከሁለት የሃላፊነት ቦታቸው የተነሱ ሲሆን ለሥራ መልቀቃቸው ግልፅ ያለ ምክንያት አልቀረበም።
ነገር ግን በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ምርምር ማዕከል ውስጥ በነበራቸው ቆይታ ብዙም ደስታኛ እንዳልነበሩ በቅርብ የሚያውቋቸው ሰዎች ይናገራሉ።
በተለይ ማዕከሉ በተለያዩ ጊዜያት የሚያቀርባቸው ሃገር አቀፍ የፖሊሲና የአስተዳደር ጥናቶች በጠቅላይ ሚኒስትሩና በመንግሥት ከፍተኛ ሃላፊዎች ዘንድ ብዙም ተቀባይነት አግኝተው ተግባራዊ አለመደረጋቸው ለቅሬታቸው ምክንያት እንደሆነ ይነገራል።
ቢሆንም ግን በኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ምርምር ማዕከል ያላቸውን ሃላፊነት ለመልቀቅ ሌላ ተጨማሪ ምክንያት እንዳላቸው ማረጋገጥ አልተቻለም።
የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ምርምር ማዕከል በአቶ አባይ ፀሐዬ ዋና ዳይሬክተርነት የሚመራ ተቋም ነው።
አቶ በረከት ስምኦን ከቀደምት የኢህአዴግ አመራሮች መካከል የሚመደቡ ሲሆን የገዢው ፓርቲ አንድ አካል የሆነው የብአዴን አመራር አባል ናቸው።
አቶ በረከት ባለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊነቶች ላይ የቆዩ ሲሆን፤ የማስታወቂያ ሚኒስትርና የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል

Friday, August 4, 2017

(ሰበር ዜና ፓርላማ) ያለመከሰስ መብታቸው በፓርላማ የተነሳው የገንዘብ እና የኢኮኖሚ ትብብር ሚንስትር ዴኤታ በፖሊስ ቁጥጥር ዋሉ

Augest 4,2017
በሙስና ወንጀል ጠረጠርናቸው የሚሉአቸውን ባለስልጣናት እና ነጋዴ ማህበረሰብን ማደን ከተያዘ ሦስተኛ ሳምንቱን መያዙ የተገለፀ ነው ። በአሁን ሰአት የህወሀት መንግስት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ነው በተባለበት በዚህ ጊዜ ፣በስሩ የነበሩትን የከፈተኛ ባለሥልጣን አመራሮችን ከቦታቸው አንስቶአል ፣ የድርጅቱ ሚስጥር ጠባቂ ተብለው በሙስና ውስጥ የተዘፈቁትን በአምባሳደርነት ሹመት ወደ ተለያዩ ቦታዎች አሸጋሽጎአቸዋል።
ሆኖም ግን በመንግስት እና በውጭ አገራት የተመሰረቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን የሙስና መንሰራፋት መንግስት በይፋ እያወቀ  በሌሎች ትንንሽ ገዳዮ ላይ ትኩረቱን መጣሉ የሃገሪቱን ደህነንት የማይፈልግ መንግስት መሆኑን ያሳያል ሲሉ አንድ የመንግስቱ ባለስልጣን ለማለዳ ታይምስ የፃፉት ደብዳቤ ይገልጣል ።
በተለይም ይላሉ እኝሁ ባለስልጣን በዩኤስ አይድ እና በህወሃት መንግስት ባለስልጣን የተካሄደው ስምምነት የሀገሪቱን ውስጣዊ ደህንነት አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ የተነሳ የሀገርና የአካባቢ ጥበቃ ተብሎ የተመደበውን ገንዘብ ቢመለስም ሆነ ይህነኑ ጉዳይ ለማስፈፀም ተብሎ ከውጭ ጉዳይ መስሪያቤት ዋና ሚንስትር ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ምንስትር መስሪያ ቤቱ ድርስ የዩኤስ ኤይድ ድርጅት ለስራ ማስሌጃቸው ይሆን ዘንድ ለሚንስትሮቹ በግላቸው  የሰጠውን ገንዝብ እንዲመረምር እና ሚንስትሮችም ከፍተኛውን ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል ።
ሀገሪቱን የውስጥ ችግሮቿን እያዩ ችግር ፈጣሪ አካላትን በበጎ አድራጎት በኩል መፍቀድ አሳፋሪ ቢሆንም ፣በአሁን ሰአት ሀገሪቱን ለማፍረስ እና የእር በእርስ ግጭት ለመቀስቀስ ቀላል እንደሆነ በደንብ አጥንተውበት ስር የሰደደ ሂደት ውስጥ መሆናቸውን እና በየክልሉ የአካባቢ ጥበቃ ተብሎ የተመሰረተው ይህንን አሜሪካ ድርጅት ጥናት በአስቸኳይ መንግስት ስራውን ማስቆም አለበት አለበለዚያ ግን ህዝቡን ለማጫረስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ያመላክታል በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።
ይሄው የአሜሪካ ድርጅት የኢትዮጵያ ችግሮች የቱ ጋር እንደሆነ የትኛው ቦታ ላይ የብሄሮች ግጭት እንዳለ ፣መንግስት ከየትኛው ማህበረሰብ ጋር አየተፋለመ እንዳለ ጠንቅቆ በጥናቱ ላይ ያወቀው ሲሆን ካለበት መንበረ ስልጣን ለማውረድም ይሁን ህዝቡን እርስ በእር ለማጫረስ ከፍተኛ የሆነ አማራጭ ያለው ስልት መሆኑን አውቆታል።
በመቀጠል ለዚህም ላካሄዱበት እያካሄዱበት ላለውም ጥናት ከሚንስትር መስሪያቤቶችም ሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ መስሪያቤት እስከ ታች ድረስ በሙስና ተጨማልቀው ሀገሪቱን ለውጭ ድርጅት ወስጣዊ ደህንነቷን አሳልፈው ሰጥተዋል ሲሉ ሀሳባቸውን ቋጭተዋል።
ፖሊስ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ዛይድ ወልደገብርኤልንና ያለመከሰስ መብታቸው በዛሬው እለት በፓርላማ የተነሳው የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አለማየሁ ጎጆን በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር አዋለ።
ዛይድ ወልደገብርኤል ከሁለት አመት በፊት ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርነት ተነስተው ዋና ጽህፈት ቤቱን ሞንትሪያል ካናዳ ባደረገው አለም አቀፍ የስቪል አቬሽን ድርጅት; የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ማለዳ ታይምስ

Thursday, August 3, 2017

የህወሓት “መከላከያ ሰራዊት” በበቃኝ ጥያቄ ተወጥሯል፤ ጄኔራሎች አሉበት!

July 3, 2017

ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ህወሓት የሚመካበትን የታጠቀ ሰራዊት የሚመሩ ከፍተኛ መኮንኖችና ጄኔራሎች በጡረታ ለመሰናበት ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። የአስቸኳይ አዋጁ ሲነሳ መልስ እንደሚያገኙ ቃል የተገባላቸው እንዳሉም ታውቋል።
የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ለደህንነት ሲባል መረጃውን ያገኘበትን ሳይገለጽ እንደጠቆመው “መከላከያ ሰራዊት” የሚባለውን የህወሓት ሥልጣን አስጠባቂ የታጠቀ ኃይል ከሚመሩት ጄኔራሎች መካከል “በቃኝ” ያሉት ጄኔራሎች ከሰባት በላይ ሲሆኑ፣ በከፍተኛ መኮንን ደረጃ ያሉት ግን ቁጥራቸው በርከት ያለ ነው።
ጄኔራሎቹ ሰራዊቱን ለመሰናበት ያቀረቡትን ዋና ምክንያት የመረጃ ሰዎቹ ቃል በቃል ይፋ ባያደርጉም፣ ከሰራዊቱ ጋር ላለመቀጠል ዕድሜ፣ ጤና፣ ጋብቻና ተያያዥነት ያላቸው ጥያቄዎችን እንደ ምክንያት አቅርበዋል። መልቀቂያ ያስገቡት ብቻ ሳይሆኑ በርካቶች ተመሳሳይ ፍላጎት እንዳላቸውም ጠቁመዋል። የዚህም ምክንያቱ ሥርዓቱ አያያዙና አሁን የደረሰበት ደረጃ ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው ሰላም አስጊ በመሆኑ ነው።
በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ ባለው የኃይል አሰላለፍ ስጋት ውስጥ የገቡና ችግሩ ሊወሳሰብ እንደሚችል በማሰብ አድፍጠው በመጠባበቅ ላይ ያሉ ከፍተኛ የሰራዊቱ አመራሮች ሲሰናበቱ አገር ውስጥ የመኖር ዕቅድ እንደሌላቸውና ለዚሁም አስቀድመው የጉዞ ዝግጅት ያደረጉ እንዳሉም ተጠቁሟል።
ጥያቄውን የተቀበለው ውሳኔ ሰጪ አካል ለጊዜው የሰጠው ቁርጥ ያለ መልስ የለም። በአስቸኳይ አዋጁ ምክንያት ሰራዊቱን የመልቀቅ ጥያቄ በመመሪያ በመታገዱ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መነሳት ተከትሎ ውሳኔ ሰጪዎች ምን እንደሚመለሱ ሊታወቅ እንደሚችል የመረጃው ሰዎች ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ነገረዋል።
በሰራዊቱ ውስጥ በሚታየው መረን የወጣ አድልዎ የተማረሩና የተሰላቹ ከፍተኛና መካከለኛ የመስመር መኮንኖችን ጨምሮ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት ስንብት እንደሚፈልጉ በመረጋገጡ በወታደራዊ ውሳኔ ሰጪዎችና ፖሊሲ አውጪዎች ዘንድ ስጋት ፈጥሯል
በዚህም የተነሳ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ጠቅሰው ስንብት የጠየቁ በከፍተኛ ደረጃ ክትትል እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል። “አገሪቱ አሁን ባለችበት ችግር ውስጥ፣ አስቸኳይ ጊዜ ላይ እያለን እንዴት ስንብት ለመጠየቅ አሰብህ” በሚል እንደሚገመገሙም ከመረጃው ሰዎች ለመረዳት ተችሏል።
በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን የ“በቃኝ” ህገ መንግስታዊ ጥያቄ በአስቸኳይ አዋጁ ስም አንቀው የያዙት ወሳኔ ሰጪዎች፣ ሰራዊቱን ፍልሰት እንዳያርደው ፍርሃቻ ስለገባቸው ከወዲሁ የአዳዲስ ሃይል ምልመላ ሲያካሂዱ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል። ከዚህም በላይ በየክልሉ ያለውን የልዩ ሃይል ከአስችኳይ ጊዜ መነሳት በኋላም በአንድ ዕዝ ውስጥ የማስገባት ስራ እንደሚሰራ ታውቋል።
እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሰራዊቱ አባላት የመሰናበት ፍላጎታቸውን አፍኖ መዝለቅ ስለማይቻል “ከጥልቅ ተሃድሶ በኋላ” በየክልሉ አዳዲስ ታጣቂ የማስፈለፈሉ ስራ እየተሰራ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። አሁን ባለው አሰራር ከመከላከያ መሰናበት የሚችለው በጋብቻ ወደ ውጪ አገር የሚሄድ ወይም ቀደም ሲል በማመልከት የትምህርት ዕድል ያገኘ ብቻ እንደሆነና ይህ መመሪያ መቼ እንደሚነሳ በግልጽ የተቀመጠ ነገር እንደሌለ የመረጃው ምንጮች ተናገረዋል።
የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምን አገዛዝ ወደ ፍጻሜው ለማምጣት እንዲረዳ “በመፈንቅለ መንግሥት” ሙከራ ሳቢያ በርካታ ጄኔራሎች ከሠራዊቱ ተወግደው ነበር። ይህ የተቀነባበረ ድርጊት ለህወሓት ወደ አዲስ አበባ መግባት ዕንቅፋት ይሆናሉ ተብለው የታሰቡን በቀላሉ “ከመንገድ የጠረገ” እንደነበር የሚታወስ ነው። አገር ውስጥ ባሉ የውስጥ አርበኞችና በውጭ አገራት የለውጥ ፈላጊ ሆነው በቀረቡ “ከሃዲዎች” ቅንብር ሳይካሄድ የከሸፈው መፈንቅለ መንግሥት የሚጠርገውን ጠራርጎ ካለፈ በኋላ ኮ/ሎ መንግሥቱ ከሥልጣን የመወገዳቸው ጉዳይ “የቀናት” ብቻ እንደሆነ “ያበሰረ” እንደነበር ብዙዎች የሚያስታውሱት ነው።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሰበብ አድርጎ የታፈነው የህወሓት ጄኔራሎች “የበቃኝ” ጥያቄ አስቀድሞ ከሥልጣናቸው የተለዩትን፣ በተለያዩ የሃብት መሰብሰብ ተግባራት የተሰማሩትንና ወደፊታቸውን የሰበሰቡትን ሃብት እየበሉ ለመኖር ባሰቡት ዘንድ እንዲሁም በሥልጣን ለመቆየት በሚያስቡት ጭምር የተደበላለቀ ስሜትን ፈጥሯል። ሆኖም የጄኔራሎቹ “የበቃኝ” ጥያቄ መነሻ ምክንያት ከላይ የተጠቀሱት ብቻ ይሁኑ ወይም ሌሎች ያልተጠቀሱ መነሾዎች ይኑራቸው ለጊዜው የታወቀ ነገር የለም። (ፎቶው “የበቃኝ” ጥያቄ ካቀረቡት ጋር ግንኙንት የለውም)
ከጎልጉል ድህረ ገጽ የተወሰደ

Thursday, July 27, 2017

በሙስና ከታሰሩ ባለስልጣናት መካከል የተወሰኑት ስም ዝርዝር ታወቀ | ይዘነዋል

July 27,2017

በአዲስ አበባ ታትሞ የሚወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበውና ዜና አቅራቢው ፋኑኤል ክንፉ እንዳጠናቀረው  በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ 34 ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ባለሀብቶችና ደላሎች፤ በትላንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት አስታወቀ::
የጽ/ቤቱ ኃላፊ ሚኒስትር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ ትላንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ 34 የሚሆኑ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶችና ደላሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታውቀዋል፡፡ ኃላፊዎቹ ተጠርጥረው የተያዙት “በፖሊስ፣ ዐቃቤ ህግና በፌደራልና አዲስ አበባ ዋና ኦዲተር መ/ቤቶች በተደረገ የማጣራት ስራ የሙስና ተግባር ውስጥ ተሳትፈው በመገኘታቸው መንግስት ሙስናን ለመከላከል በያዘው ቁርጠኛ አቋም ነው፤” ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል::
በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ  ኃላፊዎች ከተገኙባቸው የመንግስት  ተቋማት መካከል፤ የፌደራል መንገዶች ባለስልጣን፣ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን፣ ስኳር ኮርፖሬሽን እና የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር መስሪያቤቶች ጋር ይገኙበታል፡፡
የሰንደቅ ምንጮች እንደገለጽት፣ በስኳር ኮርፖሬሽ በኩል ተጠርጥረው ከተያዙ መካከል  የቀድሞው የተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አበበ ተስፋዬ እና የቀድሞው የተንዳሆ የፋይናንስ ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ድምፁ እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡ እንዲሁም፣ አቶ በኃይሉ ገበየሁ የኮርፖሬሽኑ ንብረት አስተዳደር ዳሬክተር እና አቶ ኤፍሬም አለማየሁ የቀድሞ የኮርፖሬሽኑ፣ ግዢና ንብረት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዳሬክተር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ግዢ ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳልካቸው ግርማ፤ እንዲሁም ወ/ሮ ሠናይት ወርቁ እና አቶ ኃየሎም ከበደ ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ማዋላቸው ታውቋል፡፡
አንድ የቀድሞ ሚኒስትር እና አንድ ሚኒስትር ዴኤታም ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ምንጮቻች የጠቆሙን ቢሆንም፣ ከሚመለከታቸው አካላት ለማረጋገጥ አልቻልንም፡

Sunday, July 23, 2017

የግብሩ አመጽ – የፍጻሜው ጦርነት

July 23,2017
ክንፉ አሰፋ
የአስቸኳይ (የአፈና) ግዜ  አዋጁ ገና አልተነሳም። በአዲሱ የግብር ትመና ሳብያ ከዳር እስከዳር የተነሳው ሕዝባዊ አድማ እና አመጽ ግን አዋጁን ውድቅ ያደረገው ይመስላል። አንድ ስርዓት ራሱ ያወጣው ህግ በህዝብ ሲሻርበት - ያኔ ነው ያበቃለት!
        ከቶውን "የአለምን  ኢኮኖሚ እየመራች ያለች ሃገር" የበጀት ሸክሟን ለምን በህዝብ ላይ መጣል እንዳለባት ግልጽ አልሆነም። እውነታው ከነዚህ ሁለት እይታዎች ውጭ አይሆንም።  ይነፋ የነበረው የእድገት ቀረርቶ እና ይነገር የነበር ሁለት ዲጅት እድገት ቁጥር ሁሉ ውሸት ነበር፣  ወይንም ደግሞ የሃገሪቱ ሃብት በጥቂቶች እየተዘረፈ ነው።
        ጆሮን ያሰለቸው የ"እድገት እና ትራንስፎርሜሽኑ" ዘፈን ቀዝቀዝ ማለት ሲጀምር የ "ደብል ድጅቱ" የፈጠራ ተረት እንደ በረዶ እየነጻ መሄዱ አልቀረም። እድገቱ የህዝቡን  ህይወት አልለወጠም። ተጀምሮ ከሚቋረጥ ህንጻ እና መንገድ ውጭ ትራንስፎርሜሽኑም በተግባር አልታየም።  ይልቁንም ተሸፍኖ የነበረው ችግር አሁን ፈጥጦ ወጥቶ በህዝብ ጫንቃ ላይ ጉብ ሊል ዳዳው፣ ገበሬውን መሬት በመንጠቅ፣ ነጋዴው ላይ ደግሞ ሚዛናዊ ባልሆነ የገቢ ግምት - ከፍተኛ ግብር በመጫን።   ምላሹንም እንደምናየው ነው።  አድማ፡ ህዝባዊ አመጽ፣... ተቃውሞ!
        በዘንድሮው የበጀት አመት የህወሃት መንግስት 320 ቢሊዮን ብር ማጽደቁን አብስሮን ነበር።  ይህ በጀት የ100 ቢሊዮን ብር  (1/3ኛ) የበጀት ጉድልት ነበረበት። ይህ የ100 ቢሊዮን ብር የበጀት ጉድለት ከብድር እና እርዳታ ይሸፈናል ተብሎ  ነበር የተጠበቀው። የ11 በመቶው እድገት ተረት - ተረት  ውስጥ የእርዳታው እና የብድሩ መጠን ተገልጾ አያውቅም። ሃገሪቱ በደፈናው እያደገች ነው አሉን። በፈጣን እድገት የአለምን ኢኮኖሚ የምትመራ ሃገር ተባለ።  ፈረንጆቹም አመኑ።
        እርዳታን  እንደ ስትራቴጂ የቀመሩት የህወሃት ጠበብቶች፣ ፈረንጆች ፊታቸውን ማዞር እንደማይሳናቸው እንኳን አላሰቡትም። በሶማሊያ ውስጥ የነሱን ቆሻሻ ጦርነት ስለተረከቡ ብቻ ጉዳዩን እንደ ይገባኛል መብት (for granted) አዩት። የሶማልያ ጉዳይ፣ የአልሻባብ ፖለቲካ ዲስኩር፣ የጸረ-ሽብር እንቶፈንቶ አሁን የለም። አሜሪካም ሆነች የአውሮፓ ህብረት ዜጎችን በአዋጅ እና በአስቸኳይ ግዜ አዋጅ አፍኖ የያዘው ስርዓት ጋር በረጅሙ እንደማይዘልቁ ግልጽ ነው። ታዲያ ከቻይናው የእድሜ-ልክ የእዳ ቁልል ውጭ የታሰበው የውጭ ገቢ ጠፋ። ማጠፍያው አጠረ። ለሰራዊቱና ለደህንነቱም ደሞዝ መከፈል አለበት።  ...ቀሪው ገንዘብ ከግብር እና ከሃገር ውስጥ የሚሰበሰብ ገንዘብ ብቻ ነው።
        እናም እዳው ሕዝብ  ላይ ተቆለለ። የቀን ገቢ በግምት እየታየ ተጫነ። በገቢና ወጪ ሳይሆን፣  በህዝብ ላይ በግምት ግብር ሲጫን በታሪክ የመጀመርያው ሳይሆን አይቀርም። አዲሱ የግብር ትመና በንግዱ ህብረተሰብድ ከባድ ቁጣ ቀስቅሷል። ከጫፍ እስከጫፍ የተነሳው የሥራ ማቆም አድማ የት ላይ እንደሚቆም አይታወቅም። በአስቸኳይ ግዜ በምትተዳደር ሃገር የተነሳው ይህ አድማ ቀድሞ የተጀመረው የመብት እና የነጻነት ትግል ቅጣይ ይመስላል። ቀድሞ የተነሳው የሕዝብ ጥያቄ ምላሽ አላገኘም።  የህወሃት የአፈና ሰንሰለትም እንደቀጠለ ነው። ዛሬ ነጋዴው ህብረተሰብ የሰለባው ባለሳምንት ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ሕዝብ መሰረታዊ ችግር ኢ-ፍትሃዊ የሆነ የግብር ፖሊሲ አይደለም። ችግሩ ስርዓቱ ራሱ ነው። ዛሬ የንግድ ቤቶች ቢዘጉ ሌላ የንግድ ቤቶችን የመክፈት አቅም ያላቸው የህወሃት ሰዎች በደስታ መፈንጠዛቸው አይቀርም። ...አሜካላው ሳይነሳ መፍትሄ አይታሰብም።
        ዋናው ነገር ወዲህ ነው። ግብር ለመክፈልም እኮ የህዝብ ውክልና ያለው ስርዓት መኖር ግድ ይላል። የሀዝቡን ይሁንታ ያላገኘ መንግስት፣ በሕዝብ ያልተመረጠ መንግሥት ግብር የማስከፈል መብት የለውም፣ ሕዝቡም ላልወከለው መንግስት ግብር ለመክፈል አይገደድም።    
        እ.ኤ.አ. በ1750ቹ እና 1760ቹ አስራ ሶስቱ የአሜሪካ ቅኝ ግዛቶች ይዘውት የተነሱት መፈክርን ያስተውሏል። "No Taxation Without Representation" ይላል። "ውክልና ከሌለ ግብር አይኖርም" እንደማለት ነው።  አሜሪካኖች በዚያ የነጻነት ትግላቸው ወቅት አቋማቸውን ለመግለጽ የተጠቀሙበት መሪ ቃል ነበር።  አመሪካውያኑ ይህንን መፈክር ይዘው በማመጽ የብሪትሽን ኤምፓየር እንዳናፈጡት የታሪክ ማህደር ያወሳናል።
         ህወሃት የህዝብ ይሁንታም የለው፣ መረጃም የለው። ሃይለማርያም ደሳለኝ በብሄራዊ ቴሌቭዥን ለይ ወጥተው እንዲህ አሉ። ስራችንን የምንሰራው፣ ውሳኔም የምንወስነው መረጃ ሳንይዝ እንዲሁ በግምት ነው። "መረጃ የሚጠናከርበት ስርዓት የለም።" አሉ።  እኚህ ሰው አንዳንዴ አውቀውም ይሁን ሳያውቁ  እውነትን ይለቁልናል። ንግግራቸው እኝህ ሰው ነጻ ያለመሆናቸውን ይጠቁመናል።   ሃገሪቱ ነጻ መውጣት ካለባት በመጀመርያ ነጻነትን ማወጅ ያለበቸው እሳቸው ናቸው። እውነት ነው።  ህወሃት እየመራ ያለው በግምት እና በጥይት ነው።
        የሃይለማርያም ንግግር አጉልቶ የሚያሳየን ነገር አለ። ስርዓቱ ችግር ፈጣሪ ብቻ ሳይሆን፣ ስርዓቱ ራሱ ችግር መሆኑን ግልጽ ያደርግልናል።
        ትግራይ "ክልል" ፕሬዝዳንት እና የመቐሌ ከንቲባ ላይ ከሰሞኑ የተፈጠረው ሕዝባዊ ተቃውሞ የሚሰብቀን ነገር ይኖራል። ከሰሞኑ በመቀሌ ስታድዮም የገባው ህዝብ በዝግጅቱላይ በተገኙ የህወሓት አመራሮችን "ሌባ ሌባ ሌባ .. ሃሳዊ (ውሸታም) መሲህ ሲሉ ተደምጠዋል። እንግዲህ የትግራይ ህዝብ ራሱ ተወክያለው ያለውን አመራር "ሌባ ሌባ " ካለ ምን ቀረ?... እንደኔ ግምት የቀረ የለም። ሃገር እየተመራች ያለችው መረጃ በሌላቸው፣ ራዕይ በሌላቸውና የህዝብ ይሁንታ ባላገኙ ሌቦች ነው።
        ከትግራይ ውጭ ያለውም ሕዝብ እንዲህ ነው የሚለው። "ወያኔ ሌባ ነው! ለሌባ ግብር አንከፍልም!"  
        "ኢትዮጵያንና ህዝቧን በጉልበት አፍኖ ለያዘ ዘራፊ ቡድን አንገብርም!!" ብለዋል ጊንጪዎች። ይህ የግብር አመጽ የፍጻሜው ጦርነት ይሆን? እድሜ ከሰጠን እናየዋለን።
        ለዛሬ በዚህ ላብቃ በመጪው ጽሁፌ ስለ "ኳስ እና ፖለቲካ" የምለው አለኝ።

Saturday, July 22, 2017

በአዲስ አበባ ሳሪስ፣ ኮልፌ፣ ቡራዩ፣ ደምቢዶሎ፣ ነጆ፣ ነቀምቴ በሥራ ማቆም አድማ ላይ ናቸው | ወደ ሰሜን ለሚሄዱ ተሽከርካሪዎች ማስጠንቀቂያ ተላለፈ!!

July 22,2017

( ዘ - ሐበሻ) ሕወሓት መራሹ መንግስት የጣለውን አግባብ ያልሆነ ግብር በመቃወም የተጀመረው የሥራ ማቆም አድማ በተለያዩ ቦታዎች እየተስፋፋ ነው:: በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ሳሪስ እና ኮልፌ አካባቢ ንግድ ሱቆች መዘጋጋታቸው ታውቋል::
ሳሪስ ሙሉ በሙሉ ዝግ ስትሆን በኮልፌ አካባቢ ግን አንዳንድ ነጋዴዎች የመንግስትን ማስፈራሪያ ተቀብለው መክፈታቸው ተሰምቷል:: ለነዚህ ሱቃቸውን በመክፈት መንግስትን ለተባበሩት ነጋዴዎች ከአካባቢው ነዋሪዎች ማስጠንቀቂያ እንደተላለፈላቸው ለማወቅ ተችሏል::
በደምቢዶሎ ከተማ ትንስፖርት ቆሞ ሱቆች ሙሉ በሙሉ በመዝጋት ተቃውሞው የቀጠለ ሲሆን ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ የሚታይባት ቡራዩ ከተማም ዛሬ ጭር ብላ መዋሏን የአካባቢው የህቡዕ ታጋዮች በፎቶ ግራፍና ቭድዮ አስታከው ከላኩት መረጃ ሌረዳት ተችሏል::
ነጆ ከተማም እንዲሁ ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን ዘጋግተው ቤት ቁጭ ያለ ሲሆን የመንግስት ኃይሎች ሱቆቻቸውን እንዲከፍቱ ከፍተኛ ግፊት እያደረጉባቸው እንደሆነ ከሥፍራው የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል::
በሌላ በኩል በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ በሰነበተችው ነቀምቴ ከተማ መንግስት የባጃጅ ሹፌሮችን ስራ አስፈትቶ ሥብሰባ እንዲቀመጡ ማድረጉ ታውቋል::
በሕዝባዊ እምቢተኝነቱ የቀጠለችው ነቀምቴ ከተማ የንግድ እንቅስቃሴዋ እጅጉን መዳከሙን የሚገልጹት የአካባቢው ነዋሪዎች መንግስት የባጃጅ ሹፌሮችን በስብሰባ ላይ የማትገኙ ከሆነ ታርጋችሁን እቀማለሁ በሚል አስፈራርቶ እንደሰበሰባቸውና በታክስ ስም ፕሮፓጋንዳውን እያስተማራቸው መሆኑን ከስፍራው የተገኘው ዜና ይገልጻል::
ይህ በ እንዲህ እንዳለ ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚጓጓዙ መኪኖች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ት ዕዛዝ ተላለፈ:: በሕቡዕ ጉዳዩን እያደራጁ የሚገኙት ወጣቶች (ቄሮዎች) ያሰራጩት ማስጠንቀቂያ እንደሚከተለው ቀርቧል::
“ማስጠንቀቂያ… ማስጠንቂያ… ዛሬ በሱልታ፣ በጫንጮ፣ በጎርፎ፣ በዱበር፣ በሙከ ጡሪ፣ በደብረ ፅጌ፣ በፊቼና በገርባ ጉራቸው ከተሞች ውስጥ ማንኛውም የንግድ እንቅስቃሴ ለ3 ተከታታይ ቀናት የማቆም አድማ ይደረጋል። ሱቆች፣ሆቴሎችና የሸቀጣሸቀጥ መደብሮች በሙሉ ተዘግተው ይውላሉ። በመሆኑም ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልልና ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ ማንኛውም የትራንስፖርት እንቅስቃሴዎች ሙሉ በሙሉ ይቋረጣሉ። ይህን ህዝባዊ ጥሪ አልፎ የሚንቀሳቀስ ተሽከርካሪ ወይም የንግድ እንቅስቃሴ የሚያደርግ አካል ካለ ለሚወሰድበት እርምጃ ተጠያቂ ራሱ ይሆናል።”
ወጣቶች (ቄሮዎች) ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ

Saturday, July 15, 2017

የአዲስ አበባ አስተዳደር መሬት አጥረው ባስቀመጡ ኤምባሲዎች ላይ እርምጃ ለመውሰድ መቸገሩ ተገለጸ

July 15,2017
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ አበባ መሬት አጥረው ባስቀመጡ የተለያዩ አካላት ላይ እርምጃ ለመውሰድ መቸገሩን መረጃዎች ጠቆሙ፡፡ በከተማዋ ለረዥም ጊዜ መሬት አጥረው ካስቀመጡ አካላት መካከል፣ የውጭ ሀገር ኤምባሲዎች፣ የሼህ ሁሰይን አሊ አላሙዲን ንብረት የሆነው ሚድሮክ ኢትዮጵያ፣ የመንግስት ተቋማት እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ እነዚህ አካላት የከተማዋን አንድ ሶስተኛ ሊያክል ምንም ያልቀረው መሬት በመውረር ያለ ምንም ስራ አጥረው አስቀምጠዋል፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ ተደጋጋሚ ቅሬታ ሲቀርብለት የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ አሁንም ምንም ዐይነት እርምጃ አለመውሰዱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በከንቲባ ድሪባ ኩማ የሚመራው የአዲስ አበባ አስተዳደር፣ መሬት አጥረው ከያዙ አካላት ጋር ለውይይት ተቀምጦ እንደነበር ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወቃል፡፡ ሆኖም መረጃዎች እንደጠቆሙት ከሆነ፣ በወቅቱ የተደረገው ውይይት ምንም ዓይነት ውጤት አላመጣም፡፡ በዚህም የተነሳ ስማቸው የተጠቀሱት አካላት እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ የከተማዋን መሬት እንደወረሩ ሊቀጥሉ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡ በዚህ ሳምንት ስብሰባውን ያካሔደው የከተማዋ አስተዳደር፣ በጉዳዩ ላይ ውይይት እንዳደረገ ቢገለጽም፣ መሬት አጥረው የያዙ አካላትን በተመለከተ የረባ ሪፖርት አላቀረበም፡፡
አስተዳደሩ ሰፋፊ መሬት አጥረው ከያዙ ኤምባሲዎች እና ሚድሮክ ኢትዮጵያ ይልቅ በትናንሽ ግለሰቦች ላይ እርምጃ መውሰዱን ነው የገለጸው፡፡ ለረዥም ጊዜ መሬት አጥረው ለያዙት ኤምባሰዎች እና ሚድሮክ ኢትዮጵያ ግን ወደ ስራ እንዲገቡ በድጋሚ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ብቻ ተሰጥቷቸው ታልፈዋል፡፡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው ሲባል ይህ ለበርካታ ጊዜ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ህጋዊ ባለ ይዞታ የሆኑ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ድንገት ተነስቶ በማፈናቀል እና ቤት በማፍረስ የሚታወቀው የከተማዋ አስተዳደር፣ ኤምባሲዎች እና ሚድሮክ ኢትዮጵያ ላይ ሲደርስ አቅም እንደሚያጥረው ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡ 

በከተማዋ 138 አካላት 150 ሄክታር መሬት አጥረው የያዙ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ ሰፊውን ድርሻ የሚወስዱት የውጭ ኤምባሲዎች፣ ሚድሮክ ኢትዮጵያ እና የመንግስት ተቋማት ናቸው፡፡ ሆኖ,ም አስተዳደሩ እርምጃ ወሰድኩኝ ያለው ግንባታ ባልጀመሩ ትናንሽ ባለሀብቶች ላይ ብቻ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በ13 ባለይዞታዎች ላይ ክሰ መሰረትኩኝ ያለው የድሪባ ኩማ አስተዳደር፣ ከ43 ባለሀብቶች ጋር ደግሞ ያለውን ውል በማቋረጥ መሬታቸውን መንጠቁን አስታውቋል፡፡

Source: BBN News July 13, 2017

Thursday, July 13, 2017

አምቦ ውጥረት ላይ ትገኛለች ነጋዴው ህብረተሰብ ጩኸቱን እያሰማ ነው

July 13, 2017
የአዲስ አበባ የግብር መክፈያ ቦታዎችም በአቤቱታ አቅራቢዎች እየተጨናነቁ ነው
የእለታዊ ገቢ ግብር አሰራርን በመቃወም በአምቦ ከተማ ዛሬ ተቃውሞ ሲካሄድ የዋለ ሲሆን፣ አንድ የፌደራል ፖሊስ መኪና ሲቃጠል ፣ አንድ አውቶቡስና ሌሎች የመስሪያ ቤት መኪኖችም ተሰባብረዋል። ይህን ዜና እስካጠናከርንበት በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር እስከ 11 ሰአት ድረስ በከተማዋ ተኩስ ይሰማ ነበር። ወደ ወለጋ የሚወስደው መንገድም በድንጋይ ተዘጋግቷል። በከተማዋ ያሉ አገልግሎት መስጫ ተቋማትና የንግድ ቤቶችም ተዘግተዋል። 
በአዲስ አበባ ደግሞ የግብር መክፈያ ቤቶች በአቤቱታ አቅራቢዎች ተጨናንቀው ታይተዋል። የወያኔ ህወሃት መንግስት በነጋዴው ህብረተሰብ ላይ የጣለው የግብር ጫና ነጋዴው ከሚሰራው ሁለት እጥፍ በላይ ከመሆኑ ባሻገር ምንም ጥናትን የያዘ እን የነጋዴ ማህበረሰቡን ገቢ ያላገናዘበ መሆኑን ነጋዴዎች ይገልጣሉ ። የተለያዩ የመረጃ ማእከሎችም ከስፍራው እንደገለጹ በአዲስ አበባም ሆነ አምቦ አለበለዚያም በሌላ ክልሎች ከፍተኛ ውጥረት መነሳቱ፣ የሃገሪቱን መንግስት ቢያስጨንቅም ጠንካራ እና ለሃገር እና ለህዝብ የሚያስብ አማራጭ የፖለቲካ ባለመኖሩ ህዝቡን ይበልጥ ከኪሳራ ውስጥ ጥⶀል ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
በየወረዳው የሚገኙ ጽ/ቤቶች በአቤቱታ አቅራቢዎች በመጨናነቃቸው ፣ ባለስልጣናቱ “የምትችሉትን ክፈሉና ሌላውን ቀስ ብላችሁ ትከፍላላችሁ” በማለት ለማረጋጋት ሙከራ ሲያደርጉ ታይተዋል። ነጋዴዎች ግን በባለስልጣኖች በኩል የሚሰጠውን መልስ የሚቀበሉት አልሆነም።
በዲላ ነጋዴዎች ግብር አንከፍልም በማለት በአንድ ድምጽ እየተናገሩ ሲሆን፣ ድምጻቸውን ለማሰማት የተቃውሞ ሰልፍ ለማዘጋጀት የሚያደርጉትን ሙከራ ከንቲባው ለማጨናገፍ እየተሯሯጠ መሆኑን ወኪላችን ገልጿል።

Friday, June 23, 2017

ሰራዊቱን ዝም ለማሰኘት የታቀደ የመጀመሪያ ዙር ስራ የተቃዋሚ ደጋፊ የተባሉ ወታደሮችን ለማጥቃት የታቀደ ግምገማ ሊደረግ መሆኑ ታውቋል

Juni 23,2017
ከጦር ሃይሎች የተገኘው መረጃ እንደተመለከተው በመከላከያ ሰራዊቱ ሁሉም እዞች በወታደሮች ላይ ግምገማ ሊደረግ መሆኑ ታውቋል::የግምገማው ዋናው ሂደት በሰራዊቱ ውስጥ የተገኘው የኢሕአዴግ ድምጽ አነስተኛ መሆኑ እና ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ከሚል አንጻር ተጠርጣሪ የተቃዋሚ ደጋፊ የተባሉ ወታደሮችን ለማጥቃት የታቀደ ግምገማ ሲሆን በግምገማው ላይ ሞባይሎች እንደሚፈተሹ እና ተቃዋሚዎችን በተመለከት ውስጥ ለውስጥ ፕሮፓጋንዳ ያራግባሉ እንዲሁም አለማቀፍ ጉዳዮችን በተመለከተ ከሚዲያ መረጃዎችን ይዘው መተው ያወራሉ የሚባሉ ወታደሮች የግምገማው ሰለባ እንደሚሆኑ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ተናግረዋል::የመከላከያ ሰራዊቱ ከሲቭል ደህንነት እና ከኢንሳ በተመደቡ እና የወታደሩን ካኪ ለብሰው በመመሳሰል በሚሰልሉ የሕወሓት አባላት አቅራቢነት ወንጀሎች ተቀነባብረው ግምገማውን እንደሚያጦዙት ይጠበቃል ሲሉ ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል::
የለውጥ ፈላጊ ሃይሎችን ደግፋችሁሃል በሚል ለጥቃት የተዘጋጀው ይህ ግምገማ አለመተማመን እና ጥርጣሬ በሞላው የመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ ልዩነቶችን በማስፋት በአንድ ብሄር የበላይነት የሚተዳደረውን አምባገነን ወታደራዊ አመራርን በማጠናከር ሌሎች ብሄሮች በፍርሃት እና በስጋት እንዲኖሩ ለማሸማቀቅ የሚያደርግ እንዲሁም ሰራዊቱን ለለውጥ ያነሳሳሉ የሚባሉ መኮንኖችን እና ወታደሮችን ሰብስቦ ለማሰር እና ደብዛቸውን ለማጥፋት የታቀደ እንደሆነ ታውቋል:ግምገማው የሚመራው በተለያዩ እና በጄነራልነት ማእረግ ባላቸው የሕወሓት መኮንኖች ሲሆን ሰራዊቱን ዝም ለማሰኘት የታቀደ የመጀመሪያ ዙር ስራ መሆኑን ምንጮቹ ገልጸዋል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ 450 የሕወሓት አባላት ተመልምለው ለወታደራዊ ስልጠኛ በሚል በተለያዩ የምስራቅ አውሮፓ አገሮች ለትምሕርት ሊላኩ መሆኑ ሲታወቅ ከአንድ ብሄር ብቻ ለምን/እንዴት ይህ ሆነ የሚል ጥያቄ መነሳቱን እና ምንም አይነት ምላሽ እንዳልተሰጠው ታውቋል::ምንጮቹ አያይዘው እንዳሉት ልሰላም አስከባሪ ሃይል ከፍተኛ አመራር እንዲሆኑ ለስልጠና የታጩት የሕወሃት አባላት ጉዟቸው እንደማይሰረዝ እና ጉዞውን ለተቃወሙት መኮንኖች ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል ይችላል ሲሉ ገልጸዋል::
ቆንጂት ስጦታውm

Saturday, April 29, 2017

ባሕር ዳር ኮንሠርት ላይ በፈነዳ ቦንብን ምክንያት በማድረግ በርካታ ወጣቶች ታሠሩ፤

April 29,2017
ባሕር ዳር ኮንሠርት ላይ በፈነዳ ቦንብን ምክንያት በማድረግ በርካታ ወጣቶች ታሠሩ፤
ባሕር ዳር ኮንሠርት ላይ በፈነዳ ቦንብን ምክንያት በማድረግ በርካታ ወጣቶች ታሠሩ፤
ሚያዚያ 21 ቀን 2009 ዓ.ም፤ በባሕር ዳር የመስቀል አደባባይ በነበረ የዘፈን ኮንሠርት ላይ ምሽት 1፡30 አካባቢ በፈነዳ ቦንብ ዝግጅቱ ተቋርጦ የመከላከያ ሠራዊትና የፌደራል ፖሊሶች ጥይት ይተኩሱ እንደነበር የመረጃ ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡
የዳሽን ቢራ ስሙን ወደ ባላገሩ መቀየሩን ተከተሎ በባሕር ዳር ከተማ የዘፈን ኮንሠርት በማዘጋጀት ለሕዝብ የማስተዋወቅ የመጀመሪያ ሙከራው ሲሆን ኩኩ ሰብሰቤና አረጋኸኝ ወራሽ ነበሩ፡፡ ወንድሞቻችን እየተገደሉና እየታሰሩ ምንም ዓይነት ዘፈንና ጭፈራ አንፈልግም በሚል የባሕር ዳር ከተማ ሕዝብ ወደ ኮንሠርቱ እንዳልሄደ ነው የነገሩን፡፡ የሥርዓቱ ደጋፊዎች የሆኑ ጥቂት ሰዎች በታደሙበት በዚህ ኮንሠርት ኩኩ ሰብስቤ ‹‹ቻልኩበት›› እያለች በመዝፈን ላይ ሳለች ድንገት ከፍተኛ የቦንብ ፍንዳታ ተሰማ፡፡ በዚህም አደባባዩ ውስጥ የነበሩ ቁጥራቸውና የጉዳት መጠኑ በውል ያልታወቁ ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል፡፡
ኩኩ ዘፈኗን አቋርጣ መጠጊያ ፍለጋ ለመሸሽ ተገዳለች፡፡ መድረኩ ላይ የነበሩ ሰዎች ሁሉ ዘፈኑን አቋርጠው የሸሹ ሲሆን ከፌደራል ፖሊስና ከመከላከያ ከፍተኛ ተኩስ ተከትሏል ብለውናል መረጃዎቻችን፡፡ አስተያየቱ የሠጡን ሰዎች ‹‹እኛ አገር አጥተን የምን ‹ባላገሩ› የሚል አተላ ሹፈት ነው›› ብለውናል፡፡ ይህን ተከትሎ ባለፉት ጥቂት ሰዐታት ብቻ ከመቶ ያላነሱ ወጣቶች በገፍ ታሥረዋል ብለውናል፡፡ በቀበሌ 15፣ 04፤03፣ 05፣ 06 አካባቢዎች የተገኘ ማንኛውም ሰው እየታሠረ እንደሆነ የመረጃ ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል ከአዲስ ዘመን እስከ አምባጊወርጊስና ትክል ድንጋይ ድረስ ከፍተኛ ውጥረት እንዳለ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ኦባንግ ሜቶ ከከፋ አደጋ ተረፉ!

April 29, 2017

  • “ዳግም የመኖር እድል ተሰጠኝ፤ ተማርኩበት፤ እናንተም ተማሩ”
“ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ሜቶ በሁሉም ስፍራ፣ በየትኛውም አጋጣሚ ለሚፈልጋቸው ሁሉ “አለሁ” የሚሉ ኢትዮጵያዊ ናቸው። ዘረኝነትን፥ ዘውገኝነትን፥ ጎሠኝነትን አጥብቀው ይዋጋሉ። ይጸየፉታል። ከዘር ቆጠራና ከቂም የጸዳች ኢትዮጵያን ማየት ህልማቸውና የመጨረሻ ግባቸው ነው።
ሰብዓዊነት ለአፍታም ከአንደበታቸው የማይለይ፣ በሚያውቋቸው ሰዎች ሁሉ የሚወደዱ፣ ግልጽ ተናጋሪነታቸው ልዩ የሚያደርጋቸው ኦባንግ በዚሁ ባህሪያቸው “አባ ነቅንቅ” የሚል ስም ተሰጥቷቸዋል። በስደት ለሚሰቃዩ የኢትዮጵያ ልጆች /እሳቸው ቤተሰቦቼ የሚሏቸው/ በጠሯቸው ቦታና ሁሉ በመገኘት ለሚያሳዩት ትጋት አቻ የላቸውም። ኢትዮጵያን በመወከል በከፍተኛ ቦታዎች የሚሟገቱ፣ ያዘነውን የሚጎበኙ፣ ለሴት እህቶቻችን ቀድመው የሚደርሱ እኚህ ውድ ሰው በድንገተኛ የመኪና አደጋ ተዓምር ሊባል በሚችል አጋጣሚ ከሞት የመትረፋቸው ዜና ስንሰማ ደንገጠናል። እርሳቸው ብቻ ሳይሆኑ አብሯቸው የነበረ ባልደረባቸውም ከዚህ ዘግናኝ አደጋ አምልጧል።
ባለፈው ሳምንት መገባደጃ ሚያዚያ 14 2009ዓም /22.04.2017 ከዋሽንግተን ዲሲ ወጣ ብሎ የደረሰባቸውን የመኪና አደጋ አስመልክቶ “ዳግም የመኖር ዕድል ተሰጠኝ፤ ተማርኩበት፤ እናንተም ተማሩበት። ዜናው የእኔ ከአደጋ መትረፍ ሳይሆን በቅጽበት የምትሰናበተውን ህይወታችንን በሚገባ ልንጠቀምበት እንደሚገባ መማሩ ላይ ነው” ሲሉ ነበር የገለጹት።
“አዎ” አሉ ጥቁሩ ሰው። “አዎ! ሞትን ለቅጽበት አየሁት። እንዳልወሰደኝ ስረዳ ሰዎች በቅጽበት ታሪክ እንደሚሆኑ በመረዳት በህይወት ዘመናቸው ደግ ለመስራት ለራሳቸው አለመማላቸው አሰብኩ” ሲሉ መልዕክታቸውን የጀመሩት ኦባንግ “እንኳን ነገ፣ በደቂቃዎች ምን እንደምንሆን ማስተማመኛ በሌለበት ሁኔታ ሰዎች ስለበቀልና ሌላውን ስለማጥፋት ስልት እየነደፉ ለመኖር መምረጣቸው አሳዘነኝ”።
ይህንን ሲናገሩ “የሚጸጽተዎ ነገር አለ እንዴ?” የሚል ጥያቄ ሰንዝረን ነበር። ኦባንግ ግን መልሳቸው ሌላ ነው። “እኔ ጸጸት ብሎ ነገር አላውቅም። የምጸጸትበት ነገርም ስለመፈጸሜ አስቤ አላውቅም። ነገር ግን ለወገኖቼ መሥራት የሚገባኝን እንዳልሰራሁ አስባለሁ። በተለያዩ ምክንያቶች ያስብኩትን ያህል አልተጓዝኩም። ይህ ከጸጸትም በላይ ነው። ምክንያቱም ዘረኝነትን ረግጠንና ቀብረን መጓዝ አለመቻላችን መድሃኒት የሌለው የቅዠት ተስቦ በሽተኛ አድርጎናል” ብለዋል። በውል የማይታወቅ ዘመን ወደኋላ በመሄድ ለአሁኑ ትውልድና ለአገራችን በማይጠቅም ጉዳይ ላይ ጉልበት፣ ሃብትና ጊዜ እየባከነ መሆኑንን የጠቆሙት ጥቁሩ ሰው “ከዚህ አዙሪት ሳንወጣ ሞት ይወስደናል፥ ለትውልድ የማይድን ቁስል ትተን፥ ትውልዱን መርዝ ወግተን እናልፋለን” ይላሉ።
ተፈጥሮ በጥድፊያ ወደ ሞት እየገፋችን ባለበት ሰዓት ሰው ሌላውን ስለመበቀልና ስለማጥፋት ዕቅድ ይዞ መስራቱ ከምንም ነገር በላይ ልብ የሚሰብር እንደሆነ ኦባንግ በሃዘኔታ ነው የገለጹት። “የማውቃቸውም ሆነ የማላውቃቸው በርካታ ወዳጅ ቤተሰቦች እንዳፈራሁ አውቃለሁ። ይህን ዜና ሲሰሙ እንደሚያዝኑ እረዳለሁ። ከዜናው በላይ ግን ለሚሰሙ ትምህርት እንዲሆን ይህንን መልዕክት ለማስተላለፍ ስል መናገርን መርጫለሁ። ዳግም የመኖር ዕድል ስለተሰጠኝ የዕድሉ ተጠቃሚ ለመሆን ስል ከሞት መልስ የተማርኩትን አካፍያለሁ። ለሚሰማ ትልቅ ጉዳይ ነው” ሲሉ ማሳሰቢያ አዘል መልክታቸውን ኦባንግ አስተላልፈዋል።
ከዘርና ከዘረኛነት ቋት ወጥተው “ከጎሳ በፊት ሰብዓዊነት” በሚል አዲሲቷ ኢትዮጵያ ልትተከልበት የሚገባውን መርህ የሚያቀነቅኑት ኦባንግ “መለስ ሲነገረው ቢሰማና ለአንድ ቀን ቀና ሰው ስለመሆን ቢያስብ፣ ብለን ብንመኝ ቢያንስ በቅርቡ ያለቁትን በሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችንን ነፍስ ማትረፍ፣ እየሰፋ የመጣውን የጎሳ በሽታ መቀነስ በቻልን ነበር። ግን ያሳዝናል በተቃራኒው ነው የሆነው። ያለመውንና ያሰበውን ሳያይ ህይወቱ በጥላቻና በዘረኝነት እንደመረረች ሄደ” ሲሉ የቀናነት እጥረት በሽታ ክፋት ያስረዳሉ።
የኮምፒውተር እቃ ለመግዛት አንድ መደብር ደረሰው ሲመለሱ የ18 ዓመት ወጣት ሴት በፍጥነት እያሽከረከች ሊያመለጡት በማይችሉበት ሁኔታ ተምዘግዝጋ ኦባንግ የሚያሽከረክሩትን መኪና በሳቸው በኩል ጎኑንን መታችው። ወጣቷ በከፍተኛ ፍጥነት ላይ ስለነበረች የኦባንግ መኪና ምቱ እንዳረፈባት ወደ ጎን ተገለበጠች። በመጨረሻም የአውራ ጎዳናው ጠርዝ መኪናዋን ያዛትና በቋፍ ተደግፋ እግሯን ሰቅላ ተገልብጣ ቆመች። የመውጫ በሮቹ በሙሉ ተቀርቅረውና ተጨረማምተው ስለነበር ዕርዳታ ሰጪዎች ባደረጉት ድጋፍ ኦባንግና ባልደረባቸው በኋለኛው በኩል ባለው የእቃ መጫኛ በር ሾልከው እንዲወጡ ተደረገ።
አደጋው ከደረሰ በኋላ አካባቢው ላይ የነበሩ ሰዎች እያነቡ ውስጥ የነበሩት እነ ኦባንግ ሲወጡ ሰላም መሆናቸውን ሲመለከቱ መገረማቸውን መስክረዋል። ፖሊስም ያለ አንዳች ጭረት፣ ደም፣ ስብራት፣ … ኦባንግና ባልደረባቸው መትረፋቸው “ድንቅ” ተብሎ ሊገለጽ እንደሚችል ሁኔታዎች ከተረጋጉ በኋላ ተናግሯል። እንደ ፖሊስ ገለጻ መኪናዋ ከተመታቸበት ቦታ ትንሽ ወደ አሽከርካሪው ተጠግቶ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ኦባንግ “ከሞት መልስ ተማርኩ” ለማለት እንደማይበቁ ይሆኑ ነበር። ይህንኑ አስመልክቶ ጥቁሩ ሰው “በፈጣሪ ኃይል ከሞት ተረፍኩ፣ ዳግም የመኖር ዕድል ተሰጠኝ ያልኩት ለዚህ ነው” ብለዋል።
አያይዘውም በቀናነት፣ በታማኝነት፣ በጸዳ ህሊና፣ በሃቅ፣ በመታመን፣ ለአገርና ለህዝብ ከመስራት የበለጠ የሚያኮራ ነገር እንደሌለ ተናገረዋል። በዘርና በጎሳ ተቧድነው፣ ጥላቻን መነሻ መሠረታቸው አድርገው፣ ሌላውን ለማጥፋትና ለመበቀል ዝግጅት እያደረጉ ላሉ፣ ዘመኑ በውል በማይታወቅ ጊዜ ወደኋላ ተመልሰው ቂምን የሚያራግቡና የክፋት ዘርን የሚረጩ ሁሉም ቆም ብለው በማሰብ ራሳቸውን ወደ መግዛት ብልኃትና ጥበብ እንዲመለሱ ጥሪ አስተላልፈዋል።
እሳቸው ከሞት አፋፍ መልስ የተማሩት ይህንን ነውና በግላቸው ከቀድሞው በላይ ራሳቸውን ለህዝብ እንደሚያስረክቡም ቃል ገብተዋል። ዜናውን አስቀድማ የነገረችን ምስክር “ኦባንግን ማጣት እንደ አገር ክስረት ነበር የሚሆነው። ኦባንግ ጀርባቸው የጸዳ፣ ለሚፈለገው ዓይነት ኃላፊነት የሚታመኑ፣ ታላቅ ራዕይ ያላቸው፣ ከነፈሰው ጋር የማይነፍሱ፣ ራሳቸውን ሆነው በነጻነት የሚኖሩ፣ የአንደበት ሳይሆን የተግባር ሰው የሆኑ … ኢትዮጵያዊ” ስትል ገልጻቸዋለች። አያይዛም “ከሚሠሩት ከፍተኛ ሥራ 10 በመቶውን ብቻ አደባባይ የሚያወጡ፣ ጊዜና ትውልድ በሰዓቱ ክብር የሚሰጣቸው ሰው እንደሆኑ አምናለሁ። የተረፉትም ለዚሁ ዓላማ ነው” ስትል ይህንን የተናገረችው የሚሰሩትን ሥራ ሁሉ በቅርብ ጠንቅቃ ስለምታውቅ መሆኑንንም አመልክታለች።
ኢትዮጵያን አስመልክቶ በከፍተኛ ቦታዎች በዝግ ስለሚሠሩት ሥራ ለምን በአደባባይ እንደማይገልጹ በተደጋጋሚ ኦባንግ ተጠይቀው “ገና ምን ሰራን፣ ሥራው ራሱ ሲገልጸው ማየት ይሻላል” የሚል መልስ በዚሁ ገጽ ላይ መመለሳቸው አይዘነጋም።
የመኪናውን አደጋ ያደረሰችው የ18 ዓመት ወጣት ምንም ጉዳት እንዳልደረሰባት ለመረዳት ተችሏል። የመኪና አደጋ ሲደርስ ሰዎች በአብዛኛው እርስበርስ ሲካሰሱና ሲሰዳደቡ በተደጋጋሚ የታየ ቢሆንም በዚህ አደጋ ወቅት ኦባንግ ልጅቷን በማረጋጋትና በማጽናናት የፈጸሙት ተግባር የልጅቷን ቤተሰቦችና ባካባቢው የነበሩትን ሁሉ ያስደመመ እንደነበር በቦታው የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግረዋል፡፡
የዝግጅት ክፍላችን ለአቶ ኦባንግ፣ ለባልደረባቸውና ለልጅቷ፣ እንዲሁም ለወዳጆቻቸው ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ ይላል።
ከጎልጉል የድረ ገጵ ጋዜጣ የተወሰደ

Thursday, April 20, 2017

የአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እንዳስታወቀው በክልሉ 66 ሽህ 102 ዜጎች በፍርድ እና ያለፍርድ እስር ቤት ውስጥ ይገኛሉ።

Aptil 20,2017

ሚያዝያ ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የክልሉ ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እንዳስታወቀው በክልሉ 66 ሽህ 102 ዜጎች በፍርድ እና ያለፍርድ እስር ቤት ውስጥ ይገኛሉ።

በክልሉ የእስረኛው ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያሻቀበ በመሄዱ የክልሉ ባለስልጣናት መፍትሄ እንዲሰጡበት ጠይቋል። እስረኞቹን ለማስተናገድ የተበጀተው በጀት ማለቁንም ኮሚሽኑ አስታውቋል። እስረኞቹ በአማካኝ ከ5 እስከ 10 ዓመታት በፍርድ ወይም ያለፍርድ በእስር እንደሚማቅቁ የገለጸው ኮሚሽኑ፣ ክልሉ ለ 22 ሺ 26 እስረኞች በቀን 9 ብር በድምሩ 203 ሺ 139 ብር፣ በአመት ደግሞ 73 ሚሊዮን 130 ሺ 40 ብር ወጪ ቢያደርግም፣ አሁን የእስረኞች ቁጥር በ3 እጥፍ በመጨመሩ ለማስተናገድ አለመቻሉን የክልሉ የማረሚያ ቤት ኮሚሽን ገልጿል፡፡

 የክልሉ ማረሚያ ቤት ለእስረኞች ህክምና ያወጣውን 2 ሚሊዮን 246 ሺ ብር ለመክፈል አልቻለም። የሁለት አመት ውዝፍ የህክምና ወጪ ለመክፈል ባለመቻሉም የጤና ተቋማት ለማስተናገድ ፈቃደኛ አንሆንም እያሉት መሆኑንም ገልጿል። እያንዳንዱ እስረኛ በአማካኝ 5 ዓመት በእስር ቤት ቢቆይ በጠቅላላው 1 ቢሊዮን 365 ሚሊዮን ፣ 200 ሺ ብር ምንም እሴት በማይጨምር ነገር ላይ ወጪ የደረጋል በማለት የችግሩን አሳሳቢነት ገልጿል።

የእስረኞች ቁጥር በአንዴ ያሻቀበው በ2008 ዓም የታየውን ህዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴ ተከትሎ ያለምንም የፍርድ ውሳኔ የታሰሩ ወጣቶች መበራከታቸውን ተከትሎ ነው። ይህ አሃዝ በማረሚያ ቤት አስተዳደር ስር የሚገኙ እስረኞችን እንጅ በየወረዳው እና በየቀበሌው ታስረው የሚገኙትን ዜጎች ቁጥር አያካትትም። በክልሉ በሚገኙ ወረዳዎችና ቀበሌዎች ለአመት፣ ለወራት ወይም ለሳምንታት የሚታሰሩት እስረኞች ቁጥር ቢደመር በክልሉ የሚገኘው እስረኛ ቁጥር ከተጠቀሰው በብዙ እጅ ይልቃል። በአማራ ክልል ያለውን የእስረኞች ቁጥር ግምት ውስጥ በማስገባት በመላ አገሪቱ በሚገኙ ህጋዊ በሚባሉ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ እስረኞች እንደሚኖሩ ዘጋቢያችን አስተያየቱን አሰፍሯል።

ህዝብ ተፈናቅሎ እያለቀሰ ባለበት ሰአት የመሰረት ድንጋይ አላስቀምጥም

April 20,2017
ሚያዝያ ፲፪ (አሥራ ሁለት) ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 9 የሚገኝ 10 ሺህ ካሬ/አንድ ሄክታር/ ለሆቴል ግንባታ በካሬ 650 ሺህ ብር ሊዝ የገዙት የኳታሩ ባለሃብት ፣ አገዛዙ ቦታው ላይ የሰፈሩትን ነዋሪዎች በሙሉ አንስቶ ቦታውን አጽድቶ መጨረሱን በመግለጽ የመሰረት ድንጋይ እንዲያስቀምጡ ቢጋብዝም፣ ባለሃብቱ ግን ‹‹ህዝብ ተፈናቅሎ እያለቀሰ ባለበት ሰአት የመሰረት ድንጋይ አላስቀምጥም›› ማለታቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት ባለሃብቱን ለማግባባት ተደጋጋሚ ሙከራ ያደረጉ ሲሆን፣ የኳታሩ መሪን የኢትዮጵያ ጉብኝት አስታኮ የመሰረት ድንጋይ ለማስቀመጥ ቀይ አሸዋ አፍስሰው የተጠረበ ድንጋይና ስሚንቶ አዘጋጅተው ቢጠብቁም፣ ባለሀብቱ ባለመቀበላቸው ድንጋይ የማስቀመጥ ስነስርዓቱ አልተከናወነም። የአካባቢው ነዋሪዎች መረጃውን ከክፍለ-ከተማውና የወረዳው መስተዳድር አካላት ማግኘታቸውን ተናግረዋል። የኳታሩ ባለሃብት ያነሱትን ጥያቄ ተከትሎ የአዲስ አበባ መስተዳድር “ከዚህ በፊት የቤት ግምቱ ይሻሻላል፣ የመኖሪያ ቤት መስሪያ ምትክ ቦታ በስምምነታችሁ መሰረት ይሰጣችኋል ፣ ይህ እስኪፈጸም በግዳጅ መፈናቀል አይኖርም” በማለት ለህዝቡ በአደባባይ የገባውን ቃል አጥፎ፣ ህዝብን በመከፋፈል፣ የተሳሳተ መረጃ በመስጠትና አፍራሽ ወጣቶችን አሰማርቶ በግዳጅ ለማፍረስ ከጀመረው ድርጊት አለመቆጠቡን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። መስተዳድሩ ለተፈናቃዮች የተሰጠው ቤት ይህ ነው በማለት ለባለሃብቱ የልደታ ኮንዶሚንየምን ማሳየቱን የሚገልጹት ነዋሪዎች፣ “ከእኛ መንግስት ይልቅ የኳታሩ ባለሃብት ያሳዩት ‹ሰብዓዊነት› በልጦ መገኘቱ፣ ይህ መንግስት እንደ ዜጋው እየተመለከተን ነው ብለን ለመቀበል አስቸግሮናል ›› በማለት ያሉበትን አሰቃቂ ሁኔታ ገልጸዋል። ተከራይ የቀበሌ ቤት ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ፣ ባለይዞታዎች ደግሞ በአብዛኛው ቤታቸውን በላያቸው ላይ አፍርሰው የግንባታ እቃዎችን በነጻ እንዲወስዱ በተፈቀደላቸው ‹አፍራሽ ወጣቶች› ፈርሶ ከአካባቢው እንዲለቁ የተደረጉ ሲሆን፣ በተለያየ ምክንያት ያለቀቁ ባለይዞታዎች የትንሣኤ በዓልን ‹‹ሌባ ሲጠብቁ ›› ማሰለፋቸውን በምሬት ገልጸዋል፡፡ እነዚሁ ባለይዞታ ነዋሪዎች — ያሉበትን አደገኛ ሁኔታ ቀኑን በሙሉ እዚያው ለሚውሉ የፖሊስ አባላት ቢያስረዱም ‹‹ እኛ ከዋናው መንገድ ወደ ውስጥ ለመግባት አንችልም፣ እኛም ለራሳችን እንፈራለን፣ አልታዘዝንም ›› በማለት መልስ መስጠታቸውን፣ ‹‹አፍራሽ ወጣቶችም ፖሊሶችን አፍርሰው ከሚያገኙት የጥቅም ተጋሪዎች እንዳደረጓቸውና ምንም እንደማይደረጉ በድፍረት የሚናገሩ መሆኑን፣ በሌላ በኩል አንዳንድ ፖሊሶች ‹‹ ይህ ወጣት የተወለደበትንና ያደገበትን ሠፈር ከማፍረስ መከላከል ሲገባው፣ ይህን ዓይነት ድርጊት ሲፈጽም እያያችሁ እኛን ምን አድርጉ ትላላችሁ›› ሲሉ በወጣቶቹ ሁኔታ ማዘናቸውን እንደገለጹላቸው አስረድተዋል፡፡