Friday, August 4, 2017

(ሰበር ዜና ፓርላማ) ያለመከሰስ መብታቸው በፓርላማ የተነሳው የገንዘብ እና የኢኮኖሚ ትብብር ሚንስትር ዴኤታ በፖሊስ ቁጥጥር ዋሉ

Augest 4,2017
በሙስና ወንጀል ጠረጠርናቸው የሚሉአቸውን ባለስልጣናት እና ነጋዴ ማህበረሰብን ማደን ከተያዘ ሦስተኛ ሳምንቱን መያዙ የተገለፀ ነው ። በአሁን ሰአት የህወሀት መንግስት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ነው በተባለበት በዚህ ጊዜ ፣በስሩ የነበሩትን የከፈተኛ ባለሥልጣን አመራሮችን ከቦታቸው አንስቶአል ፣ የድርጅቱ ሚስጥር ጠባቂ ተብለው በሙስና ውስጥ የተዘፈቁትን በአምባሳደርነት ሹመት ወደ ተለያዩ ቦታዎች አሸጋሽጎአቸዋል።
ሆኖም ግን በመንግስት እና በውጭ አገራት የተመሰረቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን የሙስና መንሰራፋት መንግስት በይፋ እያወቀ  በሌሎች ትንንሽ ገዳዮ ላይ ትኩረቱን መጣሉ የሃገሪቱን ደህነንት የማይፈልግ መንግስት መሆኑን ያሳያል ሲሉ አንድ የመንግስቱ ባለስልጣን ለማለዳ ታይምስ የፃፉት ደብዳቤ ይገልጣል ።
በተለይም ይላሉ እኝሁ ባለስልጣን በዩኤስ አይድ እና በህወሃት መንግስት ባለስልጣን የተካሄደው ስምምነት የሀገሪቱን ውስጣዊ ደህንነት አሳልፎ የሚሰጥ በመሆኑ የተነሳ የሀገርና የአካባቢ ጥበቃ ተብሎ የተመደበውን ገንዘብ ቢመለስም ሆነ ይህነኑ ጉዳይ ለማስፈፀም ተብሎ ከውጭ ጉዳይ መስሪያቤት ዋና ሚንስትር ጀምሮ እስከ ጠቅላይ ምንስትር መስሪያ ቤቱ ድርስ የዩኤስ ኤይድ ድርጅት ለስራ ማስሌጃቸው ይሆን ዘንድ ለሚንስትሮቹ በግላቸው  የሰጠውን ገንዝብ እንዲመረምር እና ሚንስትሮችም ከፍተኛውን ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል ሲሉ ጠቁመዋል ።
ሀገሪቱን የውስጥ ችግሮቿን እያዩ ችግር ፈጣሪ አካላትን በበጎ አድራጎት በኩል መፍቀድ አሳፋሪ ቢሆንም ፣በአሁን ሰአት ሀገሪቱን ለማፍረስ እና የእር በእርስ ግጭት ለመቀስቀስ ቀላል እንደሆነ በደንብ አጥንተውበት ስር የሰደደ ሂደት ውስጥ መሆናቸውን እና በየክልሉ የአካባቢ ጥበቃ ተብሎ የተመሰረተው ይህንን አሜሪካ ድርጅት ጥናት በአስቸኳይ መንግስት ስራውን ማስቆም አለበት አለበለዚያ ግን ህዝቡን ለማጫረስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ያመላክታል በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።
ይሄው የአሜሪካ ድርጅት የኢትዮጵያ ችግሮች የቱ ጋር እንደሆነ የትኛው ቦታ ላይ የብሄሮች ግጭት እንዳለ ፣መንግስት ከየትኛው ማህበረሰብ ጋር አየተፋለመ እንዳለ ጠንቅቆ በጥናቱ ላይ ያወቀው ሲሆን ካለበት መንበረ ስልጣን ለማውረድም ይሁን ህዝቡን እርስ በእር ለማጫረስ ከፍተኛ የሆነ አማራጭ ያለው ስልት መሆኑን አውቆታል።
በመቀጠል ለዚህም ላካሄዱበት እያካሄዱበት ላለውም ጥናት ከሚንስትር መስሪያቤቶችም ሆነ ጠቅላይ ሚንስትሩ መስሪያቤት እስከ ታች ድረስ በሙስና ተጨማልቀው ሀገሪቱን ለውጭ ድርጅት ወስጣዊ ደህንነቷን አሳልፈው ሰጥተዋል ሲሉ ሀሳባቸውን ቋጭተዋል።
ፖሊስ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር ዛይድ ወልደገብርኤልንና ያለመከሰስ መብታቸው በዛሬው እለት በፓርላማ የተነሳው የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አለማየሁ ጎጆን በዛሬው እለት በቁጥጥር ስር አዋለ።
ዛይድ ወልደገብርኤል ከሁለት አመት በፊት ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተርነት ተነስተው ዋና ጽህፈት ቤቱን ሞንትሪያል ካናዳ ባደረገው አለም አቀፍ የስቪል አቬሽን ድርጅት; የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ይታወሳል።
ማለዳ ታይምስ

No comments: