Thursday, July 13, 2017

አምቦ ውጥረት ላይ ትገኛለች ነጋዴው ህብረተሰብ ጩኸቱን እያሰማ ነው

July 13, 2017
የአዲስ አበባ የግብር መክፈያ ቦታዎችም በአቤቱታ አቅራቢዎች እየተጨናነቁ ነው
የእለታዊ ገቢ ግብር አሰራርን በመቃወም በአምቦ ከተማ ዛሬ ተቃውሞ ሲካሄድ የዋለ ሲሆን፣ አንድ የፌደራል ፖሊስ መኪና ሲቃጠል ፣ አንድ አውቶቡስና ሌሎች የመስሪያ ቤት መኪኖችም ተሰባብረዋል። ይህን ዜና እስካጠናከርንበት በኢትዮጵያ ሰአት አቆጣጠር እስከ 11 ሰአት ድረስ በከተማዋ ተኩስ ይሰማ ነበር። ወደ ወለጋ የሚወስደው መንገድም በድንጋይ ተዘጋግቷል። በከተማዋ ያሉ አገልግሎት መስጫ ተቋማትና የንግድ ቤቶችም ተዘግተዋል። 
በአዲስ አበባ ደግሞ የግብር መክፈያ ቤቶች በአቤቱታ አቅራቢዎች ተጨናንቀው ታይተዋል። የወያኔ ህወሃት መንግስት በነጋዴው ህብረተሰብ ላይ የጣለው የግብር ጫና ነጋዴው ከሚሰራው ሁለት እጥፍ በላይ ከመሆኑ ባሻገር ምንም ጥናትን የያዘ እን የነጋዴ ማህበረሰቡን ገቢ ያላገናዘበ መሆኑን ነጋዴዎች ይገልጣሉ ። የተለያዩ የመረጃ ማእከሎችም ከስፍራው እንደገለጹ በአዲስ አበባም ሆነ አምቦ አለበለዚያም በሌላ ክልሎች ከፍተኛ ውጥረት መነሳቱ፣ የሃገሪቱን መንግስት ቢያስጨንቅም ጠንካራ እና ለሃገር እና ለህዝብ የሚያስብ አማራጭ የፖለቲካ ባለመኖሩ ህዝቡን ይበልጥ ከኪሳራ ውስጥ ጥⶀል ሲሉ አክለው ገልጸዋል።
በየወረዳው የሚገኙ ጽ/ቤቶች በአቤቱታ አቅራቢዎች በመጨናነቃቸው ፣ ባለስልጣናቱ “የምትችሉትን ክፈሉና ሌላውን ቀስ ብላችሁ ትከፍላላችሁ” በማለት ለማረጋጋት ሙከራ ሲያደርጉ ታይተዋል። ነጋዴዎች ግን በባለስልጣኖች በኩል የሚሰጠውን መልስ የሚቀበሉት አልሆነም።
በዲላ ነጋዴዎች ግብር አንከፍልም በማለት በአንድ ድምጽ እየተናገሩ ሲሆን፣ ድምጻቸውን ለማሰማት የተቃውሞ ሰልፍ ለማዘጋጀት የሚያደርጉትን ሙከራ ከንቲባው ለማጨናገፍ እየተሯሯጠ መሆኑን ወኪላችን ገልጿል።

No comments: