Thursday, November 6, 2014

ሰመጉ በቅርቡ በጋምቤላ ተከስቶ በነበረው ግጭት የሞቱ ሰዎችን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ

November 6,2014
ሰመጉ በግጭቱ መነሻ ዙሪያ የተናገረው ነገር ባይኖርም፣ በተለያዩ አካባቢዎች የብሄረሰቦች ግችት እየተስፋፋ ቢመጣም መንግስት ይህን አሳሳቢ ጉዳይ በዘላቂነት ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት ከችግሩ ክብደትና እየደረሰ ካለው ጉዳት አንጻር ሲታይ ጨርሶ የሚመጣጠን አይደለም ብሎአል። መንግስት ተመሳሳይ ግጭቶች እንዳይፈጠሩ ዘላቂ መፍትሄ ማበጀት ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ጉዳይ ነው የሚለው ሰመጉ፣ በመዠንገር ዞን ለተፈጠረው ሰብአዊ እልቂትና መንስኤ የሆኑ ምክንያቶችንና ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ግልሰቦችንና ቡድኖችን አጣርቶ አፋጣኝ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል። 

ሰመጉ ባወጣው መግለጫ ላይ መንግስት የሰጠው አስተያየት የለም። መኢአድ የተገደሉ ዜጎችን ቁጥር በመቶዎች የሚቆጠር መሆኑን ሲገልጽ፣ ኢሳት በበኩሉ ምንጮችን ዋቢ በማድረግ ከ50 በላይ ዜጎች መገደላቸውን ዘግቦ ነበር።

እሥሩ ተጧጡፏል፣ አንድነት ምርጫ እንዳይወዳደር አገዛዙ ይፈልጋል

November 6,2014
ግርማ ካሳ

ዜጎች መታሰራቸው እየቀጠለ ነው። በተለይም የአንድነት ፓርቲ አባላት (በጎንደር፣ በትግራይ፣ በመቱ፣ በአዲስ አበባ ፣ በወላይታ ….) ። ብዙዎች ከፍተኛ ደብደባ እየደረሰባቸው ነው። ሕወሃት ፣ በሕዝብ እንደተጠላ ስላወቀ የአንድነት ፓርቲ እንዲዳከም ወይም ከምርጫው ዉጭ እንዲወጣ እየሰራ ነው። አንድነት ሊያሸንፈው እንደሚችል ስላወቀ።
የድርጅቶች መተባበር አስፈላጊ በመሆኑ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር ተስማምቶ የቅድመ ዉህደት ስምምነት ፈርሞ ነበር። ሁሉም ነገር አልቆ ነበር። ሆኖም ምርጫ ቦርድ ወይንም አገዝዙ፣ ሕግ ወጥ በሆነ መንገድ ዉህደቱን አስቁሞታል። ይኸው እስከአሁን ድረስ በአቶ አበባው ለሚመራው መኢአድ እውቅና አልሰጠም ብሎ መኢአዶችን ምርጫ ቦርድ እያጉላላቸው ነው።
የአንድነት ፓርቲ በቅርቡ በድርጅቱ ሕገ ደንብ መሰረት፣ አዲስ አመራር መርጦ መንቀሳቀስ መጀመሩም ይታወቃል። ሆኖ ምርጫ ቦርድ/ ሕወሃት ፣ በንድነት ዉስጥ አስርጎ አስገብቷቸው ከነበሩን በአንድነት እንዲራገፉ ከተደረጉት 2፣ 3 ግለሰቦች ጋር በመመካከር፣ እንደገና ለአዲሱ የአንድነት አመራር እውቅና አልሰጠም እያለ ነው። (የዛሬዉን ሰንደቅ ያንብቡ) ምናልባትም መኢአድ እና አንድነት ከምርጫዉ ሊያግዳቸው፣ አሊያም የነርሱን ሰርተፊኬት፣ ቅንጅትን ለአየለ ጫሚሶ እንደሰጠው፣ ለነ ማሙሸትና እና ለነ ዘለቀ ረዲ ሊሰጣቸውም ይችልም ይሆናል።
አገዛዙ እያሰረ፣ ድርጅቶችን እያገደ፣ ሽብርተኞች እያለ ፣ አይኑን በጨው አጥቦ የፊታችን 2007 ምርጫ አሸነፍኩ ማለቱ አይቀርም። የዉጭው አለም ምንም አይለም። (99.9 በመቶ ሲያሸንፉም የዉጭ አለም ያደረገው ነገር የለም) ። ሆኖም ሕዝቡ ግን ወደ አመጽ መሄዱ አይቀሬ ነው። ሕዝቡ ቀንበር በዝቶበታል። ያሉት መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ የኑሮ ዉድነቱ፣ ዘረኝነቱ፣ የባለስልጣናት ጥጋብ ብዙዎችን በጣም እያማረረ ነው። ፖለቲካው በጣም እየከረረ ነው። እነዚህ ሰዎች ተመረጥን ብለው ቢያወጁም ፣ ያለ ምንም ጥርጥር በሕዝባዊ አመጽ መዉደቃቸው አይቀርም። በዚህ ሁኔታ ሕዝቡን ሊገዙ አይችሉም።
የምመርጠው በሰላማዊ ምርጫ ሕዝቡ ፍላጎቱን እንዲያንጸባርቅ ነው። ሕዝቡም ገዢዎችን ተጠያቂ የሚያደርገው በምርጫ ቢሆን ጥሩ ነው ያንን የምርጫ አማራጭ ገዢዎች ከወሰዱበት ህዝቡ ሌላ መንገድ መፈለጉ አይቀርም።
ለዚህ ነው ገዢዎች ልብ እንዲገዙ አሁንም የምመከረው። ምርጫው ፍትሃዊና ነጻ እንዲሆን ማድረግ አለባቸው። «በምርጫ 2007 ጥሩ ነገር አይተናል፣ ከዚያ በኋላ ያለዉን ደግሞ በ2012 ደግሞ እናስተካክለዋለን » የሚል ሐሳብ ዜጎች እንዲኖራቸው ማድረግ አለባቸው። አለበለዚያ 2012 የሚጠብቅ አይኖርም። ዜጎች አገዛዙን እንደ ግራዚያኒ አገዛዝ ቆጥረው ፣ አገዛዙን ለማስወገድ መንቀሳቀስ ይጀምራሉ።

Wednesday, November 5, 2014

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ተከሳሾች ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው

November 5,2014
• ‹‹እስላማዊ መንግስት ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም ተሳትፈዋል›› የተባሉ ሌሎች ተከሳሾ በሽብር ተከሰዋል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርት

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብር የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ዛሬ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት የዋስትና ጉዳያቸውን ለማየት ለህዳር 2/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ሀብታሙ አያሌው፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታና ዳንኤል ሺበሺን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ከቀናት በፊት መመስረቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የዋስትና ጉዳያቸውን አይቶ ብይን ይሰጣል ቢባልም የተከሳሽ ጠበቆች አጭር የጊዜ ቀጠሮ በጠየቁት መሰረት ለህዳር 2/2007 በአምስት ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ከ1-5ኛ እና የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ የተከሳሾች የዋስትና ጉዳይ ከመታየቱ በፊት በተከሳሾች ላይ የቀረበው ማስረጃ የገጽ ብዛት ተጠቅሶ ለጠበቃዎቹ እንዲደርሳቸውና የአቃቢ ህጎቹ ስም እንዲጠቀስ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡

ጠበቃው የዋስትና ጉዳዩን በተመለከተ በቃል ጥያቄውን ማድረስ እንደሚችሉ ገልጸው፣ ነገር ግን ጊዜ ተሰጥቷቸው በጽሑፍ ለዳኞቹም ለአቃቤ ህጎቹም ማቅረብ እንደሚችሉ ለችሎቱ በጠየቁት መሰረት ለቀጣይ ቀጠሮ በጽሑፍ አዘጋጅተው እንዲቀርቡ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ ያለውን የሰነድ ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ ማቅረቡን በመግለጽ የሰው ማስረጃዎችም እንዳሉት አስረድቷል፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አያሌው 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ሌሎች ተከሳሾች ደግሞ 1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ፣ 3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ፣ 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ፣ 5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ፣ 6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ፣ 7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን፣ 8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ፣ 9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ፣ እና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ 7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም በዋና ወንጀል አድራጊነት ተሳትፈዋል በሚል አቃቤ ህግ ዛሬ ክስ እንደመሰረተባቸው ታውቋል፡፡
ተከሳሾቹም፡-
1ኛ. ተከሳሽ ጃፋር መሀመድ
2ኛ. መሀመድ ኑሩ
3ኛ. መሐመድ ሰሊም
4ኛ. ኑረዲን ጀማል
5ኛ. መሀመድ አባብያ
6ኛ. አኑዋር ጃኒ
7ኛ. ጀማል አብዱ ናቸው፡፡
Photo: በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የሽብር ተከሳሾች ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠባቸው

• ‹‹እስላማዊ መንግስት ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም ተሳትፈዋል›› የተባሉ ሌሎች ተከሳሾ በሽብር ተከሰዋል

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርት

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብር የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ዛሬ በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት የዋስትና ጉዳያቸውን ለማየት ለህዳር 2/2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ሀብታሙ አያሌው፣ የሽዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታና ዳንኤል ሺበሺን ጨምሮ አስሩ ተከሳሾች ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ከቀናት በፊት መመስረቱ የሚታወስ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ ለዛሬ የዋስትና ጉዳያቸውን አይቶ ብይን ይሰጣል ቢባልም የተከሳሽ ጠበቆች አጭር የጊዜ ቀጠሮ በጠየቁት መሰረት ለህዳር 2/2007 በአምስት ሰዓት ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ከ1-5ኛ እና የ9ኛ ተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ተማም አባቡልጉ የተከሳሾች የዋስትና ጉዳይ ከመታየቱ በፊት በተከሳሾች ላይ የቀረበው ማስረጃ የገጽ ብዛት ተጠቅሶ ለጠበቃዎቹ እንዲደርሳቸውና የአቃቢ ህጎቹ ስም እንዲጠቀስ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ 

ጠበቃው የዋስትና ጉዳዩን በተመለከተ በቃል ጥያቄውን ማድረስ እንደሚችሉ ገልጸው፣ ነገር ግን ጊዜ ተሰጥቷቸው በጽሑፍ ለዳኞቹም ለአቃቤ ህጎቹም ማቅረብ እንደሚችሉ ለችሎቱ በጠየቁት መሰረት ለቀጣይ ቀጠሮ በጽሑፍ አዘጋጅተው እንዲቀርቡ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ አቃቤ ህግ በበኩሉ ያለውን የሰነድ ማስረጃ ከክሱ ጋር አያይዞ ማቅረቡን በመግለጽ የሰው ማስረጃዎችም እንዳሉት አስረድቷል፡፡

አቶ ሀብታሙ አያሌው ግራ እግሩ ላይ ጉዳት ስለደረሰበት ችሎቱን ተቀምጦ ለመከታተል መገደዱንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ አቶ ሀብታሙ አያሌው 2ኛ ተከሳሽ ሲሆን ሌሎች ተከሳሾች ደግሞ 1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ፣ 3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ፣ 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ፣ 5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ፣ 6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ፣ 7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን፣ 8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ፣ 9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ፣ እና 10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ 7 ሙስሊም ወንድሞች እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ ለመመስረት ተንቀሳቅሰዋል፣ በሽብር ወንጀልም በዋና ወንጀል አድራጊነት ተሳትፈዋል በሚል አቃቤ ህግ ዛሬ ክስ እንደመሰረተባቸው ታውቋል፡፡ 
ተከሳሾቹም፡- 
1ኛ. ተከሳሽ ጃፋር መሀመድ
2ኛ. መሀመድ ኑሩ
3ኛ. መሐመድ ሰሊም
4ኛ. ኑረዲን ጀማል
5ኛ. መሀመድ አባብያ
6ኛ. አኑዋር ጃኒ
7ኛ. ጀማል አብዱ ናቸው፡፡



የሰማያዊ ፓርቲ የጎንደር አስተባባሪ ታሰረ

November 5,2014
ነገረ ኢትዮጵያ
• ‹‹ጎንደር ውስጥ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ለማፈን የተደረገ ነው፡፡›› አቶ ዮናታን ተስፋዬ

• ‹‹የፀረ ሽብር ህጉ የገዥው ፓርቲን ስልጣን ለመጠበቅ እየዋለ ነው፡፡›› አቶ ይድነቃቸው ከበደ


የሰማያዊ ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል እና የሰሜን ጎንደር የዞን ሰብሰቢ አቶ አግባው ሰጠኝ ጎንደር ከተማ ውስጥ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በገዥው ፓርቲ ደህንነቶች መታሰሩን የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ፖሊስና የደህንነት ኃይሎች አቶ አግባው ሰጠኝን ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመውሰድ ከ1 ሰዓት ተኩል በላይ ፍተሻ እና ብርበራ በማካሄድ ስፍራው ወደልታወቅ ቦታ እንደወሰዷቸው ጎንደር ውስጥ የሚገኙ የፓርቲ አመራርና አባላት ገልጸዋል፡፡

አቶ አግባው ከተያዘ በኋላ ጎንደር ከተማ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እንዲሁም ዘመዶቹ ፖሊስ ጣቢያዎችን እየዞሩ ቢያጠያቁም ‹‹ነገ ጠዋት ጠይቁ!›› ከሚል ትዕዛዝ ውጭ የታሰረበትን ማወቅ እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡

አቶ አግባው ሰጠኝ ከመታሰሩ በፊት የማያውቃቸው ሰዎች ለእሱ ተቆርቋሪ መምሰል ‹‹አርፈህ ስራህ ስራ፣ ከሰማያዊ ጋር የምታደርገውን እንቅስቃሴ አቁም፣ አዲስ አበባ ያሉት የፓርቲው አመራሮች ግንኙነታቸው ከሌላ ሰው ጋር ነው፡፡ ስለማታውቅ ነው፡፡›› ይሉት እንደነበር እንዲሁም ከመታሰሩ በሁለት ቀናት በፊት ከደህንነት የተላኩ ነኝ የሚል ግለሰብ ‹‹ከዚህ የማትወጣ ከሆነ በህይወት ላይ እርምጃ እንወስዳለን፣ መጀመሪያም መክረንሃል›› ብለው ይዝቱበት እንደነበር የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

ፖሊሶች የያዙት የፍርድ ቤት ማዘዣ ‹‹በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ በመሆናቸው አስፈላጊውን ፍተሻ ማካሄድ እንዲችሉ›› እንደሚል መረጃው የደረሳቸው የህግ ጉዳይ ኃላፊው ‹‹በመጀመሪያ የፀረ ሽብር አዋጁም ተቀባይነት የሌለውና የተለየ ሀሳብ ያላቸውን ሰዎች ለማሰቃየትና ገዥውን ፓርቲ ለመጠበቅ የወጣ ህግ ነው፡፡ አሁንም የምናየው በሰላማዊ መንገድ የሚንቀሳቀሱ አባላት በመጠናከራቸው ለመገደብ እየተጠቀመበት ነው፡፡›› ሲል ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡

በተመሳሳይ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ‹‹ጎንደር አካባቢ በማህበራዊና ሌሎች ችግሮች ምክንያት በገዥው ፓርቲ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ አለ፡፡ አቶ አግባውን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮችና አባላት ህዝቡን ስለሚያስተባብሩ ነው የታሰሩት፡፡ ጎንደር ውስጥ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ለማፈን የተደረገ ነው፡፡ ከአሁን ቀደም አርባ ምንጭ ላይ ህዝቡ ተቀባይነት ያላቸውና ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አመራሮችና አባላት ላይ ተመሳሳይ እስር ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ሌሎች አባላትና አመራሮችም አሁንም ድረስ እያዋከቧቸው ነው፡፡›› ብሏል፡፡

ኃላፊው አክሎም ‹‹በተለይ በአሁኑ ወቅት ፓርቲዎች በጋራ እየሰሩ በመሆኑ ስጋት ውስጥ የወደቀው ገዥው ፓርቲ እንቅፋት ለመፍጠር ነው እስራቱን የሚፈጽመው፡፡›› ሲል ገዥው ፓርቲ ጠንካራ እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን የፓርቲ አመራሮችና አባላት በማሰር ፓርቲውን ለማዳከም የሚያደርገው የተለመደ ስልት መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡ በተመሳሳይ ሰሞኑን በመኢአድ፣ አንድነትና አረና አመራሮችና አባላት ላይም ተመሳሳይ እስር እንደተፈጸመ ተዘግቧል፡፡


የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የ24 ሰዓት የተቃውሞ ሰልፍ ጠራ

November 5,2014
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የመጀመሪያ ዙር ህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ
• የ24 ሰዓት (የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ ተጠርቷል
ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡
yilikal getenet
‹‹ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ›› እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡
‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል›› ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡ በህዳር ወር የሚያከናውናቸው ተግባራትም፡-
1. በቤተ እምነት ጸሎት እንዲደረግና ጥሪ ማቅረብና አማኞች እንደየ እምነታቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ማድረግ
2. የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማድረግ
3. የተቃውሞ ድምጽ ማሰማት (ሰላማዊ ሰልፍ)
4. ለመንግስት ተቋማት ደብዳቤ ማስገባት
5. በምርጫ ዙሪያ የፓናል ውይይቶችን ማድረግና
6. የህዝብን ተሳትፎ ማበረታታትና ድጋፍ ማሰባሰብ እንደሆኑ በመግለጫው አሳውቋል፡፡
ከእቅዶቹ መካከልም በሶስት ተከታታይ እሁዶች በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች 3 የአደባባይ ስብሰባዎች እንደሚኖሩ፣ በመጨረሻው መርሃ ግብርም ህዳር 27ና 28 በፕሮግራሙ ማጠቃለያነት የ24 ሰዓት (የውሎና የአዳር) የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡
በገዥው ፓርቲና በምርጫ ቦርድ ጥምረት ይፈጸማል ያለውን ህገ ወጥ ተግባር በመታገል ለሰላማዊ ትግሉ አወንታዊ አስተዋጽኦ ለማበርከት እስከመጨረሻው በፅናት ለመቆም መዘጋጀቱን የገለጸው ትብብሩ በአገር ቤትና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ በትብብሩ ሂደት ቆይተው እስካሁን ያልፈረሙና ሌሎች ፓርቲዎች እና የዓለም አቀፉ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ከጎኑ እንዲቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡
ነገረ ኢትዮጵያ

Monday, November 3, 2014

የወያኔ ግፍ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ

November 3,2014
ዘረኛዉ ወያኔና ባለሟሎቹ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በጋምቤላና በሸኮ መዠንገር አካባቢ የሚያካሄዱትን የማንአለብኝነት የመሬት ዝርፍያና ዜጎችን እርስ በርስ በማጋጨት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያደርጉት አራዊታዊ ሩጫ የተነሳ ከፍተኛ ቁጥር ያለዉ ህዝብ ይህ ነዉ ተብሎ ሊነገር የማይችል እልቂት እየተፈጸመበት ነዉ። የመዠንገር ህዝብ የሞትና የህይወትን ያክል የማይወጣዉ ምርጫ ስለቀረበለት ተወልዶ ያደገበትን የአባቶቹንና የአያቶቹን አካባቢ ለቅቆ በመዉጣት እራሱን ለመከላከል ባደረገዉ እንቅስቃሴ የብዙ ንጹሃን ዜጎችና ቁጥራቸዉ ቀላል የማይባል ምስኪን ወታደሮችም ህይወት ማለፉ በይፋ እየተሰማ ነዉ። ይህንን ተከትሎ ግፈኞቹ የወያኔ መሪዎች በአካባቢዉ ብዙ ዘመን በቆዩ ብሄሰቦች መካክል ሆን ብለዉ ግጭት እንዲነሳ እያደረጉ በህዝብ መካክል ግጭትትና ዕልቂት የተነሳ በማስመሰል በአካባቢዉ ከፍተኛ ሰቆቃ በመፈፀም ላይ ይገኛሉ።
በዚህ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች እየደረሰ ላለዉ መጠነ ሰፊ ግጭትና ዕልቂት ተጠያቂዉ በአካባቢዉ ለዘመናት አብሮ በመደጋገፍ የኖረዉ ህዝብ ሳይሆን የዚህ አሰቃቂ ዕልቂት ባለቤትና ጠንሳሽ ህወሓትና ዘረኛ መሪዎቹ መሆናቸዉን ለአንድም ደቂቃ ሊዘነጋ አይገባም። ይህ ግጭት ሊነሳ የቻለዉ ህወሓት የአካባቢዉን ደሃ ገበሬ ከትዉልድ መሬቱ ላይ እያፈናቀለ መሬቱን ለከፍተኛ የጦር መኮንኖቹና የኔ ለሚላቸዉ ባለሟሎቹ በማከፋፈሉ መሆኑን ይህንን ግፍ የሚሰማ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ልብ ሊለዉ ይገባል። ህወሃት የአማራን ተወላጆች አካባቢዉ የእናንተ አይደለምና ዉጡ እያለና እያፈናቀለ በሌላ በኩል ግን በየክልሉ የአካባቢዉን ነዋሪ እያፈናቀለ የራሱን ሰዎች የመሬት ባለቤት ማድረጉ አዲስ የጀመረዉ ክስተት ሳይሆን ቆየት ያለና ስር የሰደደ የወያኔ አሰራር ነዉ።
ይህ ዛሬ በጋምቤላና በአካባቢዋ እየደረሰ ያለዉ ግፍና መከራ ለአካባቢዉ ህዝብ ብቻ የሚተዉ ነጠላ ችግር ሳይሆን በአጠቃላይ ወያኔ በአገራችን ላይ ሆን ብሎ በማድረስ ላይ ያለዉ ችግርና መከራ አካል ነዉ። በጋምቤላ ዉስጥ የፈሰሰዉና እየፈሰሰ ያለዉ የሴቶች፤ የወጣቶች፤ የአረጋዉያንና የህጸናት ደም ለሁላችንም የነጻነት ጥሪ እያቀረበልን ነዉ። ይህ የነጻነት ጥሪ ሰምተን የምናልፈዉ ወይም ነገ እንደርሳለን በለን በቀጠሮ የምናልፈዉ ጥሪ አይደለም። ጥያቄዉ የአገርና የዜጎች ህልዉና ጥያቄ ነዉና ነገ ዛሬ ሳንል አሁኑኑ ይህንን የነጸነት ጥሪ ሰምተን ምላሽ ልንሰጠዉ ይገባል።
ይህ ወያኔ በደቡብ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በንጹሃን ዜጎቻችን ህይወት ላይ እየፈጸመ ያለዉ ግፍ በአገራችን ህዝብ ላይ ሲደርስ የመጀመሪያዉ አይደለም፤ ካላቆምነዉ በቀር የመጨረሻዉ እንደማይሆንም አካሄዱ በግልጽ እያሳየን ነዉ። ወያኔ ጋምቤላ ዉስጥ ለምለም መሬት እየፈለገና ነዋሪዉን እያፈናቀለ መሬቱን ለባለሟሎቹ ማደሉን ሳይታቀብ በማንለብኝነት እንደቀጠለበት ነዉ። መሬቱን የተቀማዉ ደሃዉ የጋምቤላ ገበሬም ጫካ እየገባ ከወያኔ ጋር መተናነቁን ቀጥሏል። ትናንት በኦሮሚያ፤ በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል አካባቢዎች በአማራ ተወላጆች ላይ የደረሰዉ ግፍና መከራ ዛሬ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዉስጥ በተለያዩ ብሄረሰቦች ላይ እየደረሰ ነዉ።
ግንቦት 7 የፍትህ፤ የነጻነትና የዲሞክራሲ እንቅስቃሴ ይህ ለከቱን የለቀቀ የህወሓት ዕብሪት እንዲተነፍስና በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰዉ ግፍና ሰቆቃ እንዲቆም እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ነግ በኔ እያለ የነጻነት ትግሉን እንደቀላቀል የትግል ጥሪ ያደርጋል። ወያኔ እያደረሰ ያለዉ እስራት፤ ድብደባ፤ ግድያና ስደት የሁላችንንም ቤት እያንኳኳ ነዉና ሁላችንም እንደ አንድ ሰዉ ቆመን ወያኔንና ወያኔ የፈጠረዉን ዘረኛ ስርዐት በትግላችን መደምሰስ አለብን። በጋምቤላና በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የፈሰሰዉ የንጹሃን ወገኖቻችን ደም ደመከልብ ሆኖ የማይቀረዉ ለመብታችንና ለነጻነታችን ቆመን ወያኔን ካስወገድን ብቻ ነዉ።
በህብረት እንነሳ!!!!

የአንድነት ፓርቲ አዲስ አመራር መግለ ጫሰጠ

November 3,2014
‹‹በእነሀብታሙ ላይ የተደረገው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እጅግ አሳፋሪ ነው››
‹‹ኢንጂነር ግዛቸው በአንድነት ቤት እንደጀግና መታየት አለባቸው››
‹‹ከመኢአድ እና ሰማያዊ ፓርቲዎች ጋር ተዋህደን መስራት አለብን››
አቶ በላይ ፍቃዱ /የአንድነት ሊቀመንበር/
—————-

‹የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁ አሸባሪ ነው››
‹‹ዘንድሮም አዋጁ ይሰረዝ ብለን መጠየቃችንን እንቀጥላለን››
አቶ ግርማ ሰይፉ /የፓርላማ ተወካይ የአንድነት ም/ፕሬዚዳንት/

——————————–
ባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጥቅምት 20 ቀን 2007 ዓ.ም፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ‹‹በፖለቲካ እስረኞች ላይ እየተፈጸመ ያለው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል!›› በሚል ርዕስ በጽ/ቤቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቶ ነበር፡፡ መግለጫውንም የሰጡት የወቅቱ የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ በላይ ፍቃዱ፣ ም/ ፕሬዚዳንት አቶ ግርማ ሰይፉ እና የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዘካሪያስ የማነ ብርሃን ናቸው፡፡


የኢህአዴግ አገዛዝ ከጊዜ ወደጊዜ ሰብዓዊ መብት በመጣስና ዜጎችን በማሰቃየት ወደር የሌለው መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው ‹‹ሥርዓቱ ለአገዛዜ ያሰጉኛል የሚላቸውን ንጹሃን የፖለቲካ አመራሮችን፣ ጦማሪያንና ጋዜጠኞችን ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ክስ በመመስረት ማሰሩ ሳያንስ እነዚህን ዜጎች ሰብዓዊ ክብራቸውን በመድፈርና ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እየፈጸመ በማሰቃየት ላይ ይገኛል፡፡›› ብሏል፡፡


ፓርቲው የሥርዓቱ ዱላ ሆኖ እያለገለ ያለው የጸረ-ሽብርተኝነት አወጁ እንዲሰረዝ በህዝባዊ ንቅናቄ መጠየቁን በማውሳት ገዥው ፓርቲ ግን አምባገነንነቱን አጠናክሮ በመቀጠል በዜጎች ስቃይ መደሰትን ለጥያቄው ምላሽ ማድረጉን አስረድቷል፡፡


አቶ አንዷለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን፣ አንዷለም አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ ሀብታሙ አያሌውና ሎሎችም በፖለቲካ እምነታቸው የተነሳ ወደማሰቃያ ስፍራ የተወሰዱ የአንድነት የቁርጥ ቀን ልጆች መሆናቸውን የጠቆመው መግለጫው፣፣ በሽብርተኝነት ወንጀል ተጠርጥረው በማዕከላዊ እስር ቤት በሚገኙት ዳንኤል ሺበሺ እና ሀብታሙ አያሌው ላይ የደረሰውን ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት ኮንኗል፡፡


ከመግለጫው በኋላ ከጋዜጠኞች የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው ምላሽ ተሰጥቶባቸው ነበር፡፡ ‹‹በእነ ሀብታሙ ላይ የተደረገው ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እጅግ አሳፋሪ ነው›› በማለት ለጥያቄዎች መልስ በመስጠት የጀመሩት አቶ በላይ ‹‹የቀድሞ የፓርቲው ሊቀ-መንበር ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው በሕገ ደንቡ መሰረት በፈቃዳቸው መልቀቂያ ካስገቡ በኋላ ብሐራዊ ምክር ቤቱ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ የስልጣን ሽግግሩን በሕግ አግባብ ፈጽሟል፡፡ ኢንጂነሩ ውሳኔያቸው ትክክል ነበር፡፡ እሳቸውም ደስተኛ ናቸው፡፡ ኢንጂነር ግዛቸው በአንድነት ቤት እንደጀግና መታየት አለባቸው፡፡ ብዙ ፈተናዎችን አልፈዋል፡፡ በአንድነት ቤት የተለየ ቦታ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡›› ብለዋል፡፡


ውህደትን በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄም የፓርቲው አዲሱ ሊቀመንበር ‹‹ከፓርቲዎች ጋር አብሮ የመስራት አቋም አለን፡፡ የአንድነት እና የመኢአድ የውህደት ጉዳይ ቢያልቅም በአሰራር ደረጃ ትንሽ የሚቀር ነገር አለ፡፡ በአንድነት ዕይታ የፖለቲካ ምህዳሩን ማስተካከል አለብን፡፡ ከመኢአድ እና ሰማያዊ ፓርቲዎች ጋር ተዋህደን መስራት አለብን፡፡ በድርጅቶቹ ባህል አኳያ እንጂ ሶስታችንም ከርዕዮተ ዓለም ጀምሮ ብዙ ልዩነት የለንም፡፡ አንድ ነን፡፡ ይህ ውህደት መቼ እንደሚሆን በእርግጠኝነት መናገር ባልችልም አንድ ቀን ግን እውን ይሆናል ብለን እናምናለን›› የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የፓርላማ ተወካዩ አቶ ግርማ ሰይፉ በበኩላቸው፣ የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ ፓርቲያቸው በ‹‹ሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት›› በሚለው ንቅናቄ ‹‹አዋጁ ይዘረዝ!›› በማለት መጠየቃቸውን አስታውሰው፣ ‹‹ዘንድሮም አዋጁ ይሰረዝ ብለን መጠየቃችንን እንቀጥላለን፡፡ የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁ አሸባሪ ነው›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡


በመጨረሻም ፓርቲው በመግለጫው፣ የበደልን ዘመን ለማሳጠር እንዲቻል ህዝቡ በቁጭት ለለውጥ እንዲነሳ ጥሪ አቅርቦ በደልን ለማስቆም መታገል ወሳኝና ብቸኛው መፍትሄ መሆኑን አስረድቷል፡፡

በተለያዩ ክልሎች ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቁ በሚል ከትምህርታቸው እየተፈናቀሉ ነው

November 3,2014
በአሶሳ እና በሽሬ እንደስላሴ ከተማ የሚኖሩ 1ኛ እና 2ኛ ደረጃ ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቁ በሚል ከትምህርት ገበታቸው እየተፈናቀሉ እንደሚገኙ ተገለፀ::

አቡ ዳውድ ኡስማን

በቤኒሻንጉል ጉምዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በአሶሳ ከተማ በሚገኙ የ1ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው መማር እንዳይችሉ እየተደረጉ መሆናቸውን ምንጮች አስታወቁ፡፡

በአሶሳ ከተማ በሚገኙ ት/ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው በትምህርት ገበታቸው ላይ መገኘት እንደማይችሉ የት/ቤቱ አስተዳደሮች እየከለከሏቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

በቤኒሻንጉል ጉምዝ በአሶሳ ከተማ በሚገኝ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት 35 የሚሆኑ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን ካላወለቃችሁ መማር አትችሉም በመባላቸው ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀላቸውን ምንጮች አስታውቀዋል፡:

የትምህርት ቤቱን ርዕሰ መምህርን በጉዳዩ ላይ ለማነጋገር በአሶሳ ከተማ በስፋት በህዝብ ዘንድ የሚታወቀው ሰለፊያ ተብሎ የሚጠራው መስጂድ ኮሚቴዎች ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ርዕሰ መምህሩ “እናንተ አሸባሪዎች እስካሁን አላቹ እንዴ” በማለት የተሳለቀባቸው ሲሆን ሴት ተማሪዎቹ ሂጃባቸውን እስካላወለቁ ድረስ በትምህርት ገበታቸው ላይ እንደማይቀጥሉ ምላሽ እንደሰጣቸው ታውቋል፡፡

በተመሳሳይም በትግራይ ክልል በሽሬ እንደስላላሴ ከተማ በሚገኙ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው መማር እየተከለከሉ መሆናቸውን ምንጮች ዘግበዋል፡፡

በበሽሬ እንደስላሴ ከተማ የሚኖሩ በርካታ ቁጥር ያላቸው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃባችሁን አውልቃችሁ ተማሩ በመባላቸው ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቅለው በቤት ውስጥ ተቀምጠው እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

የትምህርት ቤት አስተዳደሮች የተማሪዎችን ወላጆች በመሰብሰብ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገሩ ሲሆን ወላጆችን እና ተማሪዎችን ሲያስፈራሩ እንደነበር ተዘግቧል፡፡

በመላው ሃገሪቱ የሙስሊሞች ዋነኛ የእምነታቸው መገለጫ የሆነውን ሂጃብ እንዲያወልቁ ለማድረግ በመንግስት በኩል ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ይገኛል፡፡ የፌደራል ጉዳዬች ሚኒስተር ዶ/ር ሽፈራው በኢስላም ላይ ባላቸው የግል ጥላቻ በመነሳት ከመሰሎቻቸው ጋር በመቀናጀት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ለማፈናቀል በክፍተኛ ደረጃ እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ የሚታወቅ ሲሆን በመላው ሃገሪቱም በሴኩላሪዝም ሽፋን ሙስሊሞች ትምህርታቸውን አልያም ሃይማኖታቸውን እንዲመርጡ በማስገደድ ሙስሊሙን ከትምህርት ገበታ ለማራቅ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ሂጃብ የሙስሊም ሴት ህልውናዋ እንጂ ለድርድር የሚቀርብ የፖለቲካ አጀንዳ አይደለም።

1984 Great Ethiopian Famine: TPLF Still Licensed to Steal

November 3, 2014
by Alemayehu G. Mariam*
Remembering the Great Ethiopia Famine of 1984 (Part II)
In my commentary last week, (Remembering the Great Ethiopia Famine of 1984, Part I), I reviewed various commentaries I had written over the years challenging the fabricated and false claims of the Tigrean Peoples Liberation Front (TPLF) and its late leader Meles Zenawi that there has been no famine in Ethiopia since they took power in 1991.  I argued that Meles & Co., in a silent conspiracy of semantics and word games with the international donors and loaners, have managed to successfully conceal the existence of famine ravaging various parts of Ethiopia for over two decades. I concluded that famine in Ethiopia sugarcoated with fancy words and phrases is still famine!
Gebremedhin Araya (L), Max Perbedy (C), Tekleweyne Assefa (R)
Gebremedhin Araya (L), Max Perbedy (C), Tekleweyne Assefa (R)
In Part II of my memorial to the victims of the 1984 famine, I revisit the great TPLF swindle of humanitarian aid during the 1984-86 famine. I first wrote on the TPLF theft of humanitarian aid during this period in my May 2011 Huffington Post commentary entitled, “Licensed to Steal”. Using interview evidence from two former top TPLF leaders, I examined  the scope and magnitude of the of the criminal diversion of humanitarian aid by the TPLF for weapons purchases and other non-humanitarian purposes. The pattern and practice of international aid corruption by the TPLF which began in 1984 still persists in 2014 with today with finesse and sophistication.
“Ali Baba” Meles and the 40 TPLF/REST Aid Thieves in 1984-85
In 1984-85, at the height of the catastrophic famine in Northern Ethiopia, nearly a quarter of a billion dollars were raised internationally for famine relief. That famine was extreme and unprecedented in its severity. Michael Buerek of the BBC who visited the Tigrai region in 1984 described the situation as “a biblical famine in the 20th Century” and “the closest thing to hell on Earth”.
In 1984-85, normal delivery of emergency humanitarian aid to the Tigrai region and other famine-stricken areas in Northern Ethiopia was virtually impossible because of rebel activity and bombardment by the Derg military junta. The roads normally used to deliver aid supplies to the Tigrai region from the capital had become unusable because of intense rebel military activity. The various international famine relief non-governmental organizations (NGOs) had to find alternate routes to quickly deliver relief aid to famine victims in rebel-controlled areas.
As an alternative, many of the NGOs set up shop in Eastern Sudan close to the Tigrai border to expedite food delivery to famine victims. The large concentration of NGOs on the Sudanese border and the publicity surrounding the enormous fundraising efforts by various international celebrities for Ethiopian famine victims caught the attention of the TPLF leaders who saw a lucrative business opportunity for themselves and their rebel army. They proffered themselves to the NGOs as effective conduits for relief aid delivery in the areas they controlled.
According to Gebremedhin Araya, a former treasurer and TPLF co-founder Dr. Aregawi Berhe, top TPLF leaders including the late Meles Zenawi, implemented an elaborate scam to swindle millions of dollars from international famine relief organizations earmarked for famine relief. Gebremedhin and Aregawi stated Meles and his top cadres hatched out and successfully executed a fraudulent scheme to use a front “humanitarian relief” organization called “Relief Society of Tigrai” (REST) for aid delivery. The TPLF leaders managed to “convince” the various NGOs operating out of the Sudan that REST is a genuine charity organization completely separate from the TPLF, the military wing. In fact, REST was the other face of the TPLF coin.
… Sometimes we were using aid money to buy arms through secondary means. You come to the Middle East, you can buy arms if you have the money. So we were using some of the money to buy arms. You know this organization called REST, Relief Society of Tigrai. It was the humanitarian wing of the TPLF, and through REST aid money was coming to the TPLF. So when you get this aid money, you make a budget for relief, for the Front or to buy arms, medicine and so on. I would say we were relying on the aid money for sustaining the struggle.
We are talking about millions of dollars. I can cite you a concrete example. In 1985, when Tigrai was hit by a terrible famine, aid money was flowing through REST to the TPLF. So the MLLT (Marxist-Lennist League of Tigrai), and the TPLF leadership which is almost one and the same had to budget for $100 million U.S. dollars. I remember Meles Zenawi suggesting that 50 percent of that money should go to TPLF activities; 45 percent should go to MLLT organizing and 5 percent to support the victims… I know these two guys [Araya Gebremedhin and Tekleweyne Assefa]. They are TPLF fighters. One is pretending to be a merchant the other is pretending to be buying the sorghum from the merchant. Both of them are TPLF senior cadres and they are just doing a drama, pretending to be a merchant. All these things are dramas to get the money. [NGO representative Perbedy pictured above fanning a wad of cash] was fooled.”
Gebremedhin corroborated Aregawi’s statements. Gebremedhin (pictured above counting cash) said he personally handed cash payments in the hundreds of thousands of dollars to the late Meles Zenawi and the serpentine Godfather of the TPLF, Sebhat Nega. Meles and Nega, the two TPLF head honchos, controlled the cash flow of the TPLF. Although Gebremedhin was the chief TPLF treasurer, he said he was kept in the dark about the uses of the money obtained from the NGOs after he delivered it to Meles or Nega. Gebremedhin nevertheless had well founded suspicions about the uses and misuses of the money. However, the incriminatory evidence, (including  the candid photograph above depicting the two TPLF cadres and Max Perbedy, a representative of Christian Aid, one of the largest UK NGO, counting and recording stashes of cash in a large satchel on the floor), is shocking as it is damning and irrefutable.
To magnify the severity and dramatize the gravity of the famine situation for the NGOs, the TPLF leaders ordered the exodus of large numbers of victims from Tigrai into the Sudan creating a mushroom of refugee settlements overnight along the northern Sudanese-Ethiopian border. Using different techniques and methods, the TPLF leaders stage-managed an elaborate marketing “drama” for the NGOs to deliver aid to the large famine-stricken population inside Tigrai. This was done principally by organizing a small group of their most trusted and inner circle members to pose as “grain merchants” and solicit business from the NGOs.
The NGO deception games, or more accurately the Western NGO famine aid-sharking scheme, were varied. At the onset of the scam, the TPLF leaders used a three-staged process. In stage one, one group of TPLF/REST officials masquerading as legitimate grain merchants would approach the myriad NGOs and offer to sell them substantial quantities of grain for quick delivery to the famine victims. At the time, the TPLF had acquired hundreds of heavy trucks and stashed in secret underground warehouses grains from various sources, including NGOs, for use by its fighters. These secretly stashed grain stockpiles were in fact being offered for sale to the NGOs. The TPLF/REST “grain dealers” would make grain sales deals with the NGOs, complete the sale transaction and return back to their hideouts with the cash payment. Gebremedhin personally played a direct role in this drama as a “grain dealer”. He described his role with stunning simplicity:
I was given clothes to make me look like a Muslim merchant. The NGOs don’t know me because my name was Mohammed. It was a trick assigned (created) by the top leaders for the NGOs. I received a great amount of money from the NGOs and the money was automatically taken by (the TPLF) leaders. The money, much of it, the leaders put it in their accounts in Western Europe. Some of it was used to buy weapons. The people did not get half a kilogram of maize. Once the grain “purchase” was made another group of TPLF/REST operatives would take over the responsibility of “delivering” the relief aid inside Tigrai.
In the second stage, TPLF/REST officials would facilitate spot checks of grain stockpiles in their own secret warehouses. But the warehouses were tricked out. Gebremedhin said, “if you go there, half of the warehouse was stacked full of sacks of sand.” Gebremedhin said the NGO representatives would perform cursory visual inspections of the stockpiles in the warehouses, give their approval, make payments and cross back into the Sudan to make arrangements for additional grain purchases.
In the third stage, the same or different group of TPLF/REST operatives would go back to the NGOs and make a pitch for additional sales of grain for delivery in a different part of Tigrai. These offers did not actually involve any new or fresh supplies of grain. Instead, stockpiles of grain already in secret storage facilities in various locations throughout Tigrai were trucked around and shuttled to new locations, giving the appearance to the NGOs that fresh supplies of grain were being bought in for delivery. Since the aid workers had no means of independently verifying the grain that they are paying for is grain that is being shuttled from one location to another from TPLF stockpiles of fresh shipments, they would perform their usual cursory inspections and make payments. In that manner, TPLF/REST were able to sell and resell multiple times the same previously acquired stockpile of grain (and sand) to the NGOs generating millions of dollars in revenue.  
Martin Plaut, who as a BBC reported from the famine regions of northern Ethiopia in the 1970s’, in his March 2010 report identified a 1985 official CIA document which concluded, “Some funds that insurgent organizations are raising for relief operations, as a result of increased world publicity, are almost certainly being diverted for military purposes.”  Robert Houdek, a senior US diplomat in Ethiopia in the late 1980s, was quoted by the BBC saying that TPLF members at the time told him that some aid money was used to buy weapons. An aid worker named Max Peberdy stated that he had personally delivered to TPLF/REST officials $500,000 in Ethiopian currency to purchase  grain.
The evidence of TPLF aid theft and conversion is further corroborated by Prof. Seid Hassan in his meticulously researched and documented article, “The State Capture Onset in Ethiopia: Humanitarian Aid and Corruption” (recommended reading). Prof. Hassan concluded, “The documents I examined and the interviews and testimonials I gathered indicate that donors and aid agencies knew that the Relief Society of Tigray (REST) was the flip-side of the same coin- the TPLF and aid agency personnel knew a portion of the humanitarian aid that they were providing was being diverted for military purposes by the Fronts…”
Those accused of involvement in the wrongdoing have dismissed the evidence as “rubbish”;  they have not called for a full fact-finding inquiry to clear their names of such serious and grave charges. Until such inquiry takes place, the evidence of aid-sharking and theft stands unchallenged and unrefuted. Bob Geldof who organized Live Aid/Band Aid in 1984 collecting tens of millions of dollars in donations upon hearing of the claims of misuse of famine aid for arms purchases threatened, “If there is any money missing I will sue the Ethiopian government.”
One must grudgingly admire these TPLF con men for their sheer audacity, genius and creativity in ripping off tens of millions of dollars earmarked for famine relief from the NGOs in the mid-1980s (and also for the past twenty-three years from the Ethiopian people). Truth be told, Ali Baba and his 40 thieves could not have pulled off such a brilliant scheme to sell and re-sell to the NGOs the same sand as grain over and over again. Even Hermes, the Greek god of thieves, would not have been able to come up with such an exquisitely perfect plan to hoodwink and bamboozle gullible NGOs of hundreds of millions of dollars. The TPLF leaders truly deserves the title, “A New Breed of African Thieves”.
REST (Relief Society of Tigray) never rests
U.S. food assistance in Ethiopia is administered Ethiopia exclusively  through three foreign NGOs (Food for the Hungry (FH) (self-described as a “Christian organization serving the poor globally since 1971”), Save the Children (SC) (self-described as “the world’s top independent charity for children in need”), Catholic Relief Services (CRS) (the “official international humanitarian agency of the Catholic community in the United States”) and one domestic NGO, Relief Society of Tigray (REST). The very same REST that facilitated the swindling of hundreds of millions of aid dollars in 1984-86  is facilitating food aid delivery in Ethiopia in 2014.
Between 2010 and 2014 (and quite possibly prior to 2010 as well), REST was the ONLY  domestic NGO involved in the distribution of over USD$1.5 billion in food aid. According to an August 15, 2014 USAID report,  USAID through its Office of Food for Peace provided REST and other international NGOs USD$237 million in 2014; USD$236 million in 2013; USD$307 million in 2012; USD$313 million in 2011 and USD452 million in 2010.
REST still describes itself as the “humanitarian wing of the Tigray People’s Liberation Front”. REST in 2014 is in fact a behemoth domestic NGO monopoly and a conduit for the diversion and laundering of international aid funds to the TPLF just as it was in 1984. It has no domestic competition in the distribution of international food aid in Ethiopia. As a matter fact, the so-called “Proclamation on Charities and Society” which decimated virtually all NGOs in Ethiopia (in 2010 after enactment of that law the number of civil society organizations in Ethiopia was reduced from about 4600 to about 1400 in a period of three months) made REST the undisputed domestic NGO monopoly. According to one Ethiopian scholar, REST is a TPLF conduit. “The initial capital for TPLF’s business empire apparently came from several sources. A major conduit was the Relief Society of Tigray (REST), a famine-relief charity run by the Front. REST is widely credited for serving as an effective front organization for funneling aid money and materials from unsuspecting as well as willful foreign benefactors into TPLF coffers.”
The fact of the matter is that under the so-called Charities law, the only domestic NGOs allowed to operate in the country are those that are wholly owned subsidiaries of the TPLF or others who have established partnerships with individuals and organizations affiliated with the TPLF.  In 1984, the TPLF laundered international humanitarian aid through REST. In 2014, the TPLF still launders international humanitarian aid through REST. How ironic! The more things change, the more they remain the same!
In all of Africa, USAID has its largest aid program in Ethiopia. What has happened to the tens of billions of dollars in U.S aid given to the TPLF over the past 23 years? The answer to that question is a curiously mindboggling one! No one knows. Not even the USAID which has dumped billions of dollars into the coffers of the TPLF knows! That was the conclusion of the U.S. State Department Office of the Inspector (IG) in his “Audit of USAID/Ethiopia’s Agricultural Sector Productivity Activities  (Audit Report No. 4-6663-10-003-P (March 30, 2010)”.
…The [IG] audit found the [Agricultural Sector Productivity] program is contributing to the achievement of market-led economic growth and the improved resilience of farmers, pastoralists, and other beneficiaries in Ethiopia. However, it is not possible to determine the extent of that contribution because of weaknesses in the mission’s performance management and reporting system. Specifically, while the mission used performance indicators and targets to track progress in several areas…, the results reported for the majority of those indicators were not comparable with the targets. Moreover, the audit was unable to determine whether the results reported in USAID/Ethiopia’s Performance Plan and Report were valid because mission staff could neither explain how the results were derived nor provide support for those reported results. In fact, when the audit team attempted to validate the reported results, it was unable to do so at either the mission or its implementing partners (pages 6-12)…
 In October 2010, a few days after Human Right Watch released its report on the abuses of aid in Ethiopia, USAID and the Development Assistance Group (the 27 bilateral and multilateral development agencies providing “assistance to Ethiopia”, (sometimes collectively referred to as the “international poverty pimps”)  issued a statement denying the “widespread, systematic abuse of development aid in Ethiopia. Our study did not generate any evidence of systematic or widespread distortion.” Tweedle Dee testifying as a star witness on behalf of Tweedle Dum!
As Dambissa Moyo has convincingly argued, international aid has been a trap for Ethiopia and other African countries. The wages of international aid in Ethiopia have been a vicious cycle of dependency, endemic corruption,  market distortions, deepening poverty and terminal aid addiction.
Post Script:
There are two unsung heroes who have made significant contributions for decades in reporting on famines in Ethiopia. On the 30th anniversary of the Great Ethiopian Famine of 1984, I would like to personally thank Michael Duncan Buerk, the British journalist whose reporting of the 1984 Ethiopian famine not only inspired musician Bob Geldof  to launch the Live Aid concert but also brought great international awareness to the suffering of the Ethiopian people. I also wish to thank Martin Plaut, who as a BBC reporter and later as Africa Editor, exposed the siphoning off millions of dollars in Western aid to victims of the Ethiopian famine of 1984-85 for weapons purchases. Walter Lippmann, the famous American writer, reporter, and political commentator observed, “There can be no higher law in journalism than to tell the truth and to shame the devil.” I do not believe there are any journalists who told the naked truth and shamed the devil about the Great Ethiopian Famine of 1984-85 than Buerk and Plaut. All Ethiopians owe them a debt of gratitude.
International aid is a vicious poverty trap for Ethiopians, but a license to steal for the TPLF!
Professor Alemayehu G. Mariam teaches political science at California State University, San Bernardino and is a practicing defense lawyer.

Sunday, November 2, 2014

የወላይታ ዞን የአንድነት አመራሮች በመንግስት ሀይሎች ከባድ ድብደባ ተፈፀመባቸው

November 2,2014

(ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ) የወላይታ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ እና የዞኑ ድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ወኖ በዳሳ ትላንት ጥቅምት 22 ቀን 2007 ዓ.ም ከቀኑ በ 8 ሰዓት ከስብሰባ ወጥተው በወላይታ ሶዶ ከተማ በአንድ ሆቴል ውስጥ እያሉ በከተማው የፖሊስ አዛዥ መመሪያ በመንግስት ሀይሎች “እኛ ሀገር እመራን እናንተ ትቃወሙናላችሁ እናንተን እናጠፋቹሀለን” በማለት ከባድ ድብደባ እንደተፈፀመባቸው የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ለፍኖተ ነፃነት አስታወቀ፡፡ አመራሮቹ በድብደባው ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ታውቋል፡፡
UDJ
በድብደባው ከባድ ጉዳት የደረሰባቸው አቶ ወኖ በዳሳ ራሳቸውን ስተው በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ቢወሰዱም እስካሁን እንዳላገገሙ እና የዞኑ የአንድነት ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ ህክምና አግኝተው ከወጡ በኋላም በከተማው ደህንነቶች ክትትልና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝም ታውቋል፡፡
የወላይታ ዞን የአንድነት አመራሮች ላይ ድብደባ እንዲደርስ መመሪያ የሰጡት የከተማው የፖሊስ አዛዥ በአቶ ወኖ ላይ በደረሰው ከባድ ጉዳት ተደናግጠው በአምቡላንስ እንዲወሰዱ ካደረጉ በኋላ የዞኑ የአንድነት ሰብሳቢ አቶ ማሞ ገሞ “በአንድም ሚዲያ ስለሁኔታው እንዳይናገሩ” በሚል ክትትል እያስደረጉባቸው ያገኛል፡፡

የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር “የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ እራስህን ከወያኔ አሽከርነት(መጠቀሚያነት) ልታርቅ ይገባል” አለ

November 2,2014
በህዝብ ላይ የሚደርሰው ጭቆናና እርዛት እስከመቼ?

ከኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ የተሠጠ መግለጫ

የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት ዘወትር ስልጣናቸውን ለማራዘም ካላቸው ነቢራዊ ፍላጎት የተነሳ በህዝብ ላይ ግድያ እና እስር ከመፈፀም አልፈው ሐገራችን ኢትዮጵያን ከማትወጣበት ማጥ ውስጥ ለመክተት ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡ በቅርቡ እንኳን በአሶሳ ከተማ ንፁሀን የትግራይ ወጣቶች ማንነታቸው እስካሁን ባልታወቁ ታጣቂዎች ተገድለዋል ይኸውም መንግስትእየተከተለው ብልሹ የዘውግ አስተዳደር ዋጋ እያስከፈለ መሆኑ እየታየ ነው በሌላ በኩል ይህ ግድያ መንግስት እራሱ የትግራይ ህዝብን ከጎኑ ለማሠለፍ በማሠብ እንደገደላቸው ግምታቸውን አስቀምጠዋል እንደምክንያት የጠቀሱት ምርጫ 97ን ተከትሎ በተነሳው ተቃውሞ መንግስት ተቃውሞውን ለማባባስ ፈረንሳይ ለጋሲዮን ከቀድሞዋ የትምህርት ሚኒስቴር ወ/ሮ ገነት ዘውዴ ግቢ ወደውጭ ቦንብ በመወርወር 6 ፖሊሶችን በመግደል ፖሊሶችን ለማነሳሳት እና ህዝቡን ለማሳሳት ቢሞክርም በመጨረሻ ጉዳዩን የአሜሪካ ኤምባሲ ይፋ ሲያወጣው የመንግስት ሴራ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ የአሶሳው፣ የአምቦው፣ የጎንደሩ እና የወለጋው ግድያም ከዚህ የተለየ አይሆንም፡፡
የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴም ለመንግስት እና ለህዝቡ የሚከተለውን መልዕክት ማስተላለፍ ይወዳል፡፡
የመምህራኑ መልዕክት ለመንግስት

ማንኛውም መንግስት ህዝቡን ማዳመጥ ይኖርበታል መንግሥት ሕዝብን የሚያዳምጠው በሕገ መንግሥቱ ስለሚገደድ ብቻ መሆን የለበትም፡፡ የሕዝብ ወገን ነኝ የሚል ሥልጣን የያዘ ፓርቲና መንግሥት፣ ሕዝብን ምረጠኝ የሚል ፓርቲና መንግሥት፣ የሕዝብ ከበሬታና አመኔታ ሊያገኝና ዓላማውን በተግባር ላይ ሊያውል የሚችለው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ሥልጣን ላይ የሚቆየው ሕዝብን ሲያዳምጥ ብቻ ነው፡፡ ሕዝብን ማዳመጥ ለራስ ተብሎም መደረግ ያለበት ነው፡፡ የማያዳምጥ መንግሥት የማይደመጥ መንግሥት ይሆናልና፡፡

የመምህራኑ መልዕክት ለኢትዮጵያ ህዝብ

የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ለሐይማኖትህ፣ ለሐገርህ እና ለቀጣይ ትውልድ አስበህ እራስህን ከወያኔ አሽከርነት(መጠቀሚያነት) ልታርቅ ይገባል፡፡ መንግስት ህዝቡ ፊቱን ካዞረበት እና ካልተገዛለት ማንንም ሊገዛ እንደማይችል የቅርባችን የጋዳፊ አገዛዝ ምስክር ነው፡፡ ስለሆነም ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ከኢህአዴግ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት መመስረት የለብንም ከዚያም አልፎ ከወያኔ ጋር ተለጥፈው ህዝባቸውን የሚያስወጉ ጎረቤቶቻችንን ጭምር ከማንኛውም ማህበራዊ ህይወት በማግለል ትምህርት ልንሠጣቸው ይገባል፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!!!!!!!!!!!
የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

መንግስት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል

November 2,2014
• ‹‹መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዲቫሊዌት› ሊያደርግ ይችላል››

የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደገጠመው የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የብሄራዊ ባንክ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አጥኚ እጥረቱ መኖሩን አረጋግጠዋል፡፡

ከ20 ቀናት በፊት እያንዳንዱ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የውጭ ምንዛሬ ይሸጥ እንደነበር የተናገሩት ምንጮች፣ ከ20 ቀን ወዲህ ግን በሁሉም የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ማንኛውም አይነት የውጭ ምንዛሬ እንዳይሸጥ በደብዳቤ (cercular ዞሯል) ተከልክሏል፡፡

በመሆኑም አሁን ላይ ዜጎች በውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደተቸገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹በተለየ ሁኔታ የሚሸጥላቸው ሰዎች ከጉዞ ወኪላቸውና ከበላይ አካል ይዘውት በሚመጡት ደብዳቤ መሰረት ብቻ ነው ምንዛሬ ሊያገኙ የሚችሉት፡፡ ከዚህ ውጭ ግን እንደበፊቱ ማንም የውጭ ምንዛሬ ማግኘት አይችልም›› ሲል አንድ የንግድ ባንክ ሰራተኛ ገልጹዋል፡፡

የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ የተከሰተው በዶላር ምንዛሬ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የውጭ ምንዛሬዎች ላይ መሆኑንም ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ አሁን ላይ አንድ የአሜሪካ ዶላር በጥቁር ገበያ እስከ 22 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡

በሌላ በኩል ከብሄራዊ ባንክ አካባቢ የደረሱት የነገረ ኢትዮጵያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት መንግስት ቀደም ሲል በIMF የቀረበለትን የ‹ዲቫሊዌሽን› ጥያቄ መቀበሉ እንደማይቀር ታውቋል፡፡ ‹‹አሁን ያለው ሁኔታ እንደሚያሳየን መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዴቫሉዌት› ማድረጉ አይቀሬ መሆኑን ነው፡፡ አንዳንድ ‹አርቲፊሻል› የውጭ ምንዛሬ እጥረቶች ቢኖሩም ዋናው የችግሩ መነሻ ግን የ‹ዴቫሊዌሽኑ› ጉዳይ ነው›› ሲሉ የብሄራዊ ባንክ የኢኮኖሚ አጥኚው ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድተዋል፡፡

ሰሞኑን መንግስት ለወራት ተከልክሎ የነበረው የአረብ ሀገራት የስራ ጉዞ እንደገና እንዲጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም መናገራቸው አይዘነጋም፡፡ ይህም ወደ አረብ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎች ተጨማሪ ምንዛሬ እንዲያስገኙ ከማሰብ ሳይሆን እንደማይቀር ይገመታል፡፡
Photo: መንግስት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል

• ‹‹መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዲቫሊዌት› ሊያደርግ ይችላል›› 

የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደገጠመው የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የብሄራዊ ባንክ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አጥኚ እጥረቱ መኖሩን አረጋግጠዋል፡፡ 

ከ20 ቀናት በፊት እያንዳንዱ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የውጭ ምንዛሬ ይሸጥ እንደነበር የተናገሩት ምንጮች፣ ከ20 ቀን ወዲህ ግን በሁሉም የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ማንኛውም አይነት የውጭ ምንዛሬ እንዳይሸጥ በደብዳቤ (cercular ዞሯል) ተከልክሏል፡፡

በመሆኑም አሁን ላይ ዜጎች በውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደተቸገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹በተለየ ሁኔታ የሚሸጥላቸው ሰዎች ከጉዞ ወኪላቸውና ከበላይ አካል ይዘውት በሚመጡት ደብዳቤ መሰረት ብቻ ነው ምንዛሬ ሊያገኙ የሚችሉት፡፡ ከዚህ ውጭ ግን እንደበፊቱ ማንም የውጭ ምንዛሬ ማግኘት አይችልም›› ሲል አንድ የንግድ ባንክ ሰራተኛ ገልጹዋል፡፡ 

የውጭ ምንዛሬ እጥረቱ የተከሰተው በዶላር ምንዛሬ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የውጭ ምንዛሬዎች ላይ መሆኑንም ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ አሁን ላይ አንድ የአሜሪካ ዶላር በጥቁር ገበያ እስከ 22 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡   

በሌላ በኩል ከብሄራዊ ባንክ አካባቢ የደረሱት የነገረ ኢትዮጵያ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት መንግስት ቀደም ሲል በIMF የቀረበለትን የ‹ዲቫሊዌሽን› ጥያቄ መቀበሉ እንደማይቀር ታውቋል፡፡ ‹‹አሁን ያለው ሁኔታ እንደሚያሳየን መንግስት የብርን ዋጋ በቅርቡ ‹ዴቫሉዌት› ማድረጉ አይቀሬ መሆኑን ነው፡፡ አንዳንድ ‹አርቲፊሻል› የውጭ ምንዛሬ እጥረቶች ቢኖሩም ዋናው የችግሩ መነሻ ግን የ‹ዴቫሊዌሽኑ› ጉዳይ ነው›› ሲሉ የብሄራዊ ባንክ የኢኮኖሚ አጥኚው ለነገረ ኢትዮጵያ አስረድተዋል፡፡      

ሰሞኑን መንግስት ለወራት ተከልክሎ የነበረው የአረብ ሀገራት የስራ ጉዞ እንደገና እንዲጀመር ዝግጅት እያደረገ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም መናገራቸው አይዘነጋም፡፡ ይህም ወደ አረብ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎች ተጨማሪ ምንዛሬ እንዲያስገኙ ከማሰብ ሳይሆን እንደማይቀር ይገመታል፡፡

Saturday, November 1, 2014

Aid in the wrong hands – The Telegraph

October 31,2014

Hailemariam Desaleg
Hailemariam Desalegn, the Ethiopian prime minister, is untroubled by criticism in the local press or any public opposition, for the simple reason that both are effectively banned Photo: Getty Images
Is Ethiopia’s government, whose security forces are guilty of rape and torture, a worthy recipient of £329 million of British taxpayers’ money?
30 years ago, Band Aid mobilised a generation of British teenagers behind the campaign to help Ethiopia recover from famine. Today, Ethiopia is the second-biggest beneficiary of British aid, receiving no less than £329 million last year. And yet the same government that is favoured by this largesse has also carried out appalling atrocities. This week, Amnesty International detailed how Ethiopia’s security forces are guilty of rape and torture as they struggle against separatist rebels. Meanwhile, Hailemariam Desalegn, the prime minister, is untroubled by criticism in the local press or any public opposition, for the simple reason that both are effectively banned. The Department for International Development’s plan for Ethiopia shamelessly notes the country’s “progress toward establishing a functioning democracy”, but adds: “There is still a long way to go”. Indeed. A very long way to go.
The question is whether such a government is a worthy recipient of British taxpayers’ money. Our aid does not go to Ethiopia’s security forces, of course, nor to the secret police who create such fear. Yet British funding for schools and hospitals could release resources for Mr Hailemariam to spend on repression. Foreign aid will always give recipient governments more discretion over what to do with their own money. DfID would say that British aid is, for example, helping almost two million Ethiopian children to go to school – and that is a fair point. But DfID’s budget jumped by 32 per cent between 2012 and 2013 – the biggest percentage increase ever enjoyed by any Whitehall department in peacetime history. DfID has failed to allay the suspicion that its officials are more concerned with spending this money than guarding against possible unintended consequences. Sadly, that risk is greater in Ethiopia than 

አብርሃ ደስታ; ሀብታሙ አያሌው; የሽዋስ አሰፋ ; ዳንኤል ሺበሺ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው

October31,2014
Habtamu abrhayeshiwas daniel

• አብርሃ ደስታ የሁለት ድርጅቶች አባል ነው የሚል ክስ ተመስርቶበታል
• ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ታዟል
ነገረ ኢትዮጵያ 
በልደታ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ምድብ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በተሰየመው ችሎት 10 ተከሳሾች በፌደራል አቃቢ ህግ በይፋ ክስ ተመሰረተባቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ከ100 ገጽ በላይ የክስ ቻርጅ የተነበበላቸው ሲሆን ከክስ ቻርጁ ጋር ከ300 ገጽ በላይ የምርመራ ሰነድ ቀርቦባቸዋል፡፡
የክሱ መዝገብ የተከፈተው ዘላለም ወርቃገኘሁ በተባለውና ‹‹የግንቦት 7 አመራር ነው፡፡›› ተብሎ ክስ በተመሰረተበት ግለሰብ ሲሆን በዚህ የክስ መዝገብ የተካተቱትም፡-
1ኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ
2ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ አያሌው
3ኛ ተከሳሽ ዳንኤል ሺበሺ
4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታ
5ኛ ተከሳሽ የሽዋስ አሰፋ
6ኛ ተከሳሽ ዮናታን ወልዴ
7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን
8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ
9ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ደጉ
10ኛ ተከሳሽ ተስፋዬ ተፈሪ ናቸው
ለሁሉም ተከሳሾች ከዛሬ በፊት ክስ እንዳልደረሳቸውና ዛሬ ፍርድ ቤት ውስጥ እንደተሰጣቸው ታውቋል፡፡ በችሎቱ 6ኛ ተከሳሽ ከሆነው ዮናታን ወልዴ በስተቀር ሁሉም ያለ ጠበቃ የቀረቡ ሲሆን ጠበቃዎቹ ያልቀረቡበት ምክንያትም ጠበቆቹ ደምበኞቻቸው የሚቀርቡበት ቦታና ጊዜ ስላልተነገራቸው እንዲሁም ቀደም ብለው እንዳይገናኙ በመደረጋቸው መሆኑን አቶ ኃብታሙ አያሌው ችሎቱ ላይ ተናግሯል፡፡
ከሳሹ የፌደራል አቃቢ ህግ በ1996 የወጣው የወንጀል ህግ እና የጸረ ሽብር ህግ ጠቅሶ ክስ ያቀረበ ሲሆን ክሶቹ በሁለት ዋና ዋና ጭብጦች ቀርበዋል፡፡ የመጀመሪያው ጭብጥ ‹‹ከሽብርተኛ ቡድኖች ጋር በጋራ በመስራት›› የሚል ሲሆን ‹‹ህገ መንግስቱንና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል ለመናድ፣ የመንግስትን መሰረተ ልማት በማፈራረስ፣ ህዝብን ለአመጸ በማነሳሳት መንግስትን መለወጥ አላማው አድርጎ ከሚሰራውና ራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራው ቡድን ጋር አባል በመሆንና በወንጀል ድርጊቶች በመሳተፍ›› በሚል ቀርቧል፡፡
ሁለተኛው የክስ ጭብጥ ‹‹የሽብር ቡድን አመራር በመሆን›› የሚል ሲሆን በተለይም የአንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ‹‹የሽብር ቡድኑ አመራር በመሆንና አባል በመመልመል›› በሚል የክስ ጭብጥ ቀርቦበታልል፡፡
ከ2-5ኛ የክስ መዝገብ የሚገኙት ማለትም ሀብታሙ አያሌው፣ ዳንኤል ሺበሽ፣ አብርሃ ደስታና የሸዋስ አሰፋ ‹‹ህጋዊ የፖለቲካ ፓርቲን ከለላ በማድረግ ግንቦት 7 የተባለውን የሽብር ቡድን አላማ ለማሳካት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ፋሲል የኔ ዓለምና ሌሎች የሽብር ቡድኑ አባላት ጋር በስልክ በመነጋገርና በማህበራዊ ድህረ ገጸ የተለያዩ መልዕክቶችን ተለዋውጠዋል›› የሚል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ አብርሃ ደስታ ከግንቦት 7 በተጨማሪ ‹‹ደምኢት የተባለ ቡድን አባል ነው፡፡›› የሚል ክስ ቀርቦበታል፡፡
በስተመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ሁለት ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ አንደኛው ረቡዕ ጥቅምት 26/2007 ዓ.ም 3 ሰዓት ተከሳሾቹ ዋስትና ይሰጣቸው አይሰጣቸው በሚለው ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ከተከሳሾቹ ጠበቆች ጋር ተማክሮ ውሳኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ በሁለተኛነት ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት ቀደም ሲል ለአራት ወራት ወደቆዩበት ማዕከላዊ እስር ቤት እንዳይመለሱ ፍርድ ቤቱን ስለጠየቁ ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (3ኛ) እንዲቆዩ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
ተከሳሾቹ ትናንት ጥቅምት 20/2007 ዓ.ም አራዳ ምድብ ችሎት ይቀርባሉ ተብሎ የነበር ቢሆንም ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ጥቅምት 21/2007 ዓ.ም ጠዋት ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ተወስደው የነበረ ቢሆንም እንደገና ወደማዕከላዊ ተመልሰው ከሰዓት እንዲቀርቡ ተደርገዋል፡፡